Telegram Web Link
#አቢሲንያ_ባንክ

የጥያቄና መልስ ውድድር ቅዳሜ ሰኔ 22 ከረፋዱ 4:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ በየሳምንቱ አስር አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ቴሌግራም ፕሪምየምን ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ፡ https://www.tg-me.com/BoAEth


#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
TIKVAH-ETHIOPIA
#Hawassa በሀዋሳ ከተማ የስፓርት ውርርድ ( #ቤቲንግ ) ቤቶች እየታሸጉ / እየተዘጉ ይገኛሉ። ይህ ተከትሎ የስፖርት ውርርድ ቤት ባለቤቶች " እንዴት የንግድ ፈቃድ እያለን ይዘጋብናል ? " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል። እነዚህ የስፖርት ውርርድ ቤቶች ከወራት በፊት በተለያዩ ምክኒያቶች ተዘግተው የቆዩ ሲሆን በቅርቡ ተከፍተው ነበር። አሁን ላይ ተመልሰው መዘጋት/መታሸግ መጀመራቸው…
#Update

" የስፖርት ውርርድ ቤቶችን የመዝጋትና የመክፈት አሰራር አድሎአዊነት የተንጸባረቀበት ነው " - ቅሬታ አቅራቢዎች

" የተከፈቱ ቤቶች ከብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ህጋዊ ደብዳቤ ያመጡ ናቸው " - የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ

በቅርቡ በሀዋሳ ከተማ ያሉ የስፖርት ውርርድ ቤቶች  " ህጋዊ አይደሉም ፣ በብዛት  የተከፈቱበት አካባቢም የትምህርትና የመኖሪያ ሰፈር ነው " በሚል ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ቢዘጉም ከቀናት ቆይታ በኋላ ግን የተወሰኑት ተከፍተዉ ስራ ጀምረዋል።

ይህንን ተከትሎ ፥
- ለምን ሁሉም በህግና ስርአት እየሰራ እና ግብርም እየከፈለ እያለ በከፊል ተከፍቶ በከፊል ይዘጋል ?
- ቤቶቹን የመዝጋትና የመክፈት ስራን የሚሰራዉ የከተማው ፖሊስ አሰራሩ አድሏዊነት የታየበት ነው፤
- ገንዘብ ሰጥተው የሚያስከፍቱ ሰዎችም እንዳሉ እየተሰማን ነው ሲሉ የስፖርት ውርርድ ቤታቸው የተዘጋባቸዉ ግለሰቦች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸዉ የከተማዉ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር መልካሙ አየለ ፥ አሁን ላይ ተከፍተዉ ወደስራ የተመለሱት ከብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ህጋዊ ደብዳቤ ያቀረቡ መሆናቸዉን ገልጸዋል።

በተጨማሪም " ለሀገር ፈጽሞ ጥቅም የማይሰጠዉ የቨርቹዋል አሰራር አሁንም እንደተከለከለ ነው። ካሁን በፊት እንደህግ ያስቀመጥነዉ የመኖሪያ ቤትና የትምህርት ቤቶች ዙሪያ የተጣለዉ ክልከላ ዛሬም ቀጥሏል " ብለዋል።

ከዚህ ውጭ አከፋፈቱን በተመለከተ የሚነዛዉ ስም ማጥፋት አግባብ አለመሆኑን ገልጸዉ ማንኛዉም አካል ህጋዊ ሆኖ ከመጣ ድርጅቱን ማስከፈት እንደሚችል ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

በአዲስ አበባ ከኮሪደር ስራው ጋር በተያያዘ ከመገናኛ ወደ ቦሌ የሚወስደው መንገድ ከሃያት ሆስፒታል በኋላ ከነገ ሰኔ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰኑ ቀናት ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ሙሉ ቀንና ምሽትን ጨምሮ ለማንኛውም አይነት ተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረግ ተገልጿል።

አሽከርካሪዎች ሃያት ሆስፒታል ጋር ሳይደርሱ በፊት እና ከሆስፒታሉ አጠገብ ያሉትን የቀኝ መታጠፊያዎችን እንዲጠቀሙ የአ/አ ከተማ የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ጥሪ አቅርቧል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia
#Ethiopia

" በ7 ቀናት ማስረጃ አቅርቡ ካልሆነ ሕጋዊ እርምጃ እንወስዳለን " - የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 11 ፓርቲዎች በ7 ቀናት የሴትና የአካል ጉዳተኛ አባሎቻቸውን መረጃ እንዲያቀርቡ አሳሰበ።

የተባለውን የማይፈጽሙ ከሆነ ሕጋዊ የሆነ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አሳውቋል።

ቦርዱ ሀገሪቱ ውቅጥ በሕጋዊ መንገድ ተመዝግበው ለሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከመንግሥት የሚመደብ የ2014፤ 2015 እና 2016 በጀትን አከፋፍሏል።

ይሀንን የበጀት ድጋፍ ለማከፋፈል በሕጉ ከተቀመጡ መሥፈርቶች መካከል የፖለቲካ ፖርቲዎች ያሏቸውን ሴት እና አካል ጉዳተኛ አባላት ቁጥር በቃለ-መኃላ አስደግፈው ማቅረብ ነው፡፡

በዚህም መሠረት ፥ 21 ፖለቲካ ፖርቲዎች በ2016 ዓ/ም ለቦርዱ ያሰወቁት የሴት እና የአካል ጉዳተኛ አባሎቻቸው በ2014 እና 2015 ዓ.ም ካቀረቡት ቁጥር አንጻር የተጋነነ ሆኖ ተገኝቷል።

በዚህም ምክንያት ፖርቲዎቹ የአባሎቻቸውን ሙሉ መረጃ ለቦርዱ እንዲያቀርቡ መጋቢት 25/2016 ዓ/ም አሳውቆ ነበር።

10 የፖለቲካ ፖርቲዎች የተለያዩ ምላሾችን የሰጡና በእጃቸው የሚገኙ መረጃዎችን አቅርበዋል።

11 ፖርቲዎች ማለትም ፦

➡️ የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ህብረት
➡️ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ
➡️ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ
➡️ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር
➡️ ብልጽግና ፓርቲ (ገዢው ፓርቲ)
➡️ ራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
➡️ የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ
➡️ የጋምቤላ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ
➡️ ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ለሉዓላዊነት
➡️ ሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
➡️ የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ ግን በአንድ ዓመት ውስጥ ከ10,000 እስከ 900,000 የሴት አባላትና የአካል ጉዳተኛ አባላት ቁጥር ነው ያቀረቡት።

ፓርቲዎቹ ላቀረቡት ለዚህ ቁጥር ያላቸውን ማስረጃ እንዲያቀርቡ ቢጠየቁም እስካሁን ሳይሰጡ እንደቀሩ ተገልጿል።

በመሆኑም በ7 ቀን ውስጥ ማስረጃውን ካላቀረቡ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ቦርዱ አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia
#አሜሪካ

ባለፈው ሳምንት በአሜሪካ ፤ በሉዊዚያና ግዛት ከታች አንስቶ እስከ ዩኒቨርሲቲ ባሉ በሁሉም የመማሪያ ክፍሎች ውስጥ አስርቱ ትዕዛዛት እንዲለጥፉ ታዟል።

ትላንት ደግሞ የኦክላሆማ ግዛት በአስቸኳይ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት እንዲጀመር አዟል።

የግዛቱ ትምህርት ቢሮ በግዛቱ ያሉ የሕዝብ ትምህርት ቤቶች መጽሐፍ ቅዱስን በትምህርት ስርዓታቸው በአስቸኳይ እንዲያካትቱና እንዲያስተምሩ መመሪያ አስትላልፏል።

በግዛቱ የትምህርት የበላይ ተቆጣጣሪ ሪያን ዋልተርስ የተላከ መመሪያ " አፋጣኝ እና ጥብቅ ተፈጻሚነትን " የሚፈልግ አስገዳጅ ድንብ ነው ይላል።

ዋልተርስ " መጽሐፍ ቅዱስ ታሪካዊና ባህላዊ መሠረት ነው "  ብለዋል።

" ያለ መጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ እውቀት የኦክላሆማ ተማሪዎች የአገራችንን መሠረት በትክክል መረዳት አይችሉም " በማለት ነው በአስቸኳይ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት እንዲሰጥ መታዘዙን ያመለከቱት።

በግዛቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ከ5ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ይተገበራል።

ከ5ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ እያንዳንዱ ክፍል መጽሐፍ ቅዱስ ሊኖረው ይገባል ተብሏል። ሁሉም አስተማሪዎች በክፍሉ ውስጥ ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ማስተማር እንዳለባቸው ታዟል።

የሲቪል መብት ተሟጋች ድርጅቶች ግን ይህንን ውሳኔ ተቃውመዋል።

ሃይማኖት እና መንግሥት መለያየት አለባቸው ብለዋል።

አንድ መንግሥትን ከሃይማኖት መለያየት እንዳለበት የሚሰራ ተቋም ፥ " የሕዝብ ትምህርት ቤቶች ሰንበት ትምህርት ቤቶች አይደሉም " ብሏል።

" ሪያን ዋልተርስ የተሰጠውን የመንግሥት ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም ሃይማኖታዊ እምነቱን በሌሎች ላይ ለመጫን እየተጠቀመበት ነው። ይህ እኛ ባለንበት ሊሳካ አይገባም " ብሏል ተቋሙ።

በአሜሪካ የሃይማኖት ነፃነትን ለማስጠበቅ የሚሰራው ኢንተርፌይዝ አሊያንስ ፤ " መመሪያው ግልጽ በሆነ መልኩ ሃይማኖትን መጫን ነው " ሲል ገልጾታል።

" እውነተኛ የእምነት ነፃነት ማለት የትኛውም የሃይማኖት ቡድን አመለካከቱን በሁሉም አሜሪካውያን ላይ እንዳይጭን መከላከል ነው " ብሏል።

#BBC #CNN

@tikvahethiopia
ባሉበት ሆነው በኮንፈረንስ ጥሪ በጋራ ያውጉ !

የቦታ ርቀት ሳይገድብዎ እንደልብዎ የሚወያዩበት የኮንፈረንስ ጥሪ አገልግሎትን በመጠቀም እስከ አምስት ሆነው በአንድ ላይ ይወያዩ፤ ይጨዋወቱ!

የመጀመሪያውን ስልክ ደውለው ደንበኛው መስመር ላይ እንዲጠብቅዎ በማሳወቅ ተጨማሪ ጥሪ ማድረግ (Add call) እስከ አምስት ሰው የሚፈልጉትን ያህል ካስገቡ በኋላ ለማገናኘት ‘Merge’ ወይም ‘conference’ የሚለውን በመጫን የስልክ ጥሪዎቹን ወደ አንድ ማምጣት ይችላሉ፡፡

ለማንኛውም ጥያቄ ወይም አስተያየት በ https://www.tg-me.com/EthiotelecomChatBot 24/7 ያግኙን !

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE የ2016 ዓ/ም የመውጫ ፈተና እና የሪሚዲያል ማጠቃለያ ፈተና ውጤቶች መቼ ይፋ ይደረጋሉ ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ የ2016 ዓ/ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና እና የዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና መቼ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል። የትምህርት ሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራር ፥ የሪሚዲያል ተማሪዎቹ ውጤት ከሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና መጠናቀቅ በኋላ ባሉት ቀናት ይፋ እንደሚደረግ…
#Update

የ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ውጤት ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተልኳል።

የተማሪዎቹ ውጤት ዛሬ ለተቋማቱ መላኩን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአንድ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር አረጋግጧል።

በዚህም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የተማሪዎቻቸውን የመውጫ ፈተና ውጤት ከዛሬ ጀምሮ ይፋ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

የዘንድሮው የመውጫ ፈተና ለ57 የመንግሥት እና ለ124 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በ244 የቅድመ ምረቃ መርሐግብሮች መሰጠቱ ይታወቃል።

Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቴፒ #አሽከርካሪዎች ° “ ከቴፒ ቡና ጭነን ለመውጣት ተከልክለን ከቆምን ወር ሊሞላን ነው ” - አሽከርካሪዎች ° “ ክልል ኮሚቴ አቋቁቁሞ ነገሩን እያጣራ ነው ”- ቡናና ሻይ ባለስልጣን የጫኑትን ቡና ይዘው እንዳይንቀሳቀሱ በመከልላቸው ያለምንም መፍትሄ ከሦስት ሳምንታት በላይ ለመቆም እንደተገደዱ አሽከርካሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አማረዋል። “ ለሥራ የምንወጣው ቤተሰቦቻችንንም ለማስተዳደር…
#Update

“ አሁንም ድረስ ቡና ጭነው የቆሙ ተሽከርካሪዎች አሉ ” - አሽከርካሪዎች 

“ የቆሙት ተሽከርካሪዎች በወንጀል ተጠርጣሪዎች ናቸው ” - ቡናና ሻይ ባለስልጣን

ከቴፒ የጫኑትን ቡና ይዘው እንዳይወጡ ከዚህ ቀደም ተከልክለዋል ከተባሉት 24 ተሽከርካሪዎች መካከል 3ቱ አሁንም እንዳልተለቀቁ አሽከርካሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ የሰጡ አንድ አሽከርካሪ፣ “ አሁንም ቡና ጭነው የቆሙ ተሽከርካሪዎች አሉ። ደቡብ ምዕራብ ቦንጋ ከተማ በቡናና ሻይ ባለስልጣን ግቢ ውስጥ አቁመዋቸዋል ” ብለዋል።

ሌሎችም አሽከርካሪዎች፣ በበኩላቸው ይህንኑ ሀሳብ ተጋርተው፣ ተሽከርካሪዎቹ ቦንጋ የቆሙት ቴፒ ከወጡ በኋላ ቡናው ' Commercial ነው ’ ተብሎ መሆኑን አስረድተዋል።

የተለቀቁት ተሽከርካሪዎችም ቢሆኑ የተለቀቁት ከአንድ ወር መጉላላት በኋላ በመሆኑ በኑሮ ላይ ከባድ ጉዳት እንደገጠማቸው አስረድተው፣ “መጨረሻ ላይ ቡናው Local ነው ተብሎ ተለቀቅን፣ በዚህ ጉዳይ ሲጀመር መጠየቅ ያለበት ሹፌር አልነበረም” ብለዋል።

ከአሽከርካሪዎቹ በኩል ለተነሳው ለዚህ ቅሬታ ምላሽ እንዲሰጡ ቲክቫህ ጥያቄ ያቀረበላቸው የቡናና ሻይ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የግብይት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሻፊ ዑመር፣ “ ስንመረምር 3ቱ መኪና Local ብለው የጫኑት የExport ቡና ሆነ ” ብለዋል።

“ ስለዚህ የExport ቡና መሸጥ ህገ ወጥ ነው። አገርን ዶላር ማሳጣት ነው። 3ቱ መኪና እዛው ቆመው ነው ያሉት በፓሊስ እጅ ነው ” ሲሉ ተናግተዋል።

አቶ ሻፊ “ አሁን ላይ የቆሙት ተሽከርካሪዎች በወንጀል ተጠርጣሪዎች ናቸው ” ብለው “ እንደዚህ ያደረጉ አካላትም ለህግ እንዲቀርቡ ለደቡብ ምዕራብ ደብዳቤ ፅፈናል ” ሲሉ አክለዋል። 

ትክክለኛ የችግሩ ምንጭ ማነው ? በማለት ላቀረብነው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ አቶ ሻፊ፣ “በሁሉም Side አለ” ብለዋል።

“ ላኪዎቹ የ Local አስመስለው Exportable ቡና ሲገዙ በጥሩ ዋጋ ስለሚሸጡ። ለአገር አያስቡም። አቅራቢው ደግሞ ቡናን በአፈርና ውሃ እያሸ ወደ Local እንዲገባ ስለሚያደርግ ችግር አለበት” ሲሉ ተናግረዋል።

አክለው፣ “አሽከርካሪዎቹም ቢሆኑ እያወቁ ነው የተሻለ ዋጋ ስለሚከፈላቸው ቴፒ ሂደው የሚጭኑት። ሲጀመር የExports ቡና ማከማቻ፣ Localን ወደ Export የሚለየው አዲስ አበባ ነው። ቴፒ የሚያስሄዳቸው ነገር የለም” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ትግራይ

ግለሰቡ በአሰቃቂ የግድያ ወንጀል ተጠርጥሮ ይፈለጋል።

ግድያው መቼና ? የት ተፈፀመ ? 

አሰቃቂ የግድያ ተግባሩ ግንቦት 17/2016 ዓ.ም ነው የተፈጸመው።

የተፈፀመበት ደግሞ በትግራይ ደቡባዊ ዞን ራያ ዓዘቦ ወረዳ ሀወልቲ ቀበሌ ዓዲ መጥሓን በተባለ ልዩ ቦታ ነው።

በግድያ ተግባር ተጠርጥሮ የሚፈለገው ግለሰብ ኣባዲ መሓሪ ረዳ ይባላል።

ግለሰቡ የአምስት ልጆች እናት የሆነች ባለቤቱ ወ/ሮ ዕፃይ ከበደ ገድሎ ከተሰወረ ከአንድ ወር በላይ ሆኖታል። 

የወ/ሮ ዕፃይ ቤተሰቦችና የራያ ዓዘቦ ወረዳ ፓሊስ በጋራ በግድያ ወንጀል ተጠርጥሮ የተሰወረውን ኣባዲ መሓሪ ረዳ የተባለ ግለሰብ ያየውና ያለበት ቦታ የሚያውቅ 0996709824/0919548923 የሞባይል ቁጥሮች በመጠቀም መረጃ እንዲሰጣቸው ትብብር ጠይቀዋል።

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የተማሪ ደራርቱ ገዳይ የ18 ዓመት ጽኑ እስራት ተፈርዶበታል። የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ የነበረችውን ደራርቱ ለሜሳን አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ በጩቤ ሶስት ቦታ በጀርባዋ ላይ በመውጋት የግድያ ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በ18 አመት ፅኑ እስራት መቀጣቱን የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ አንድ ፖሊስ አስታውቋል። ረቡዕ ግንቦት 9 ቀን 2016 ዓ/ም በግምት ከጧቱ 2፡45 ሰዓት አከባቢ ተከሳሽ አቶ…
#Assosa

የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ የነበረችውን ደራርቱ ለሜሳን በመግደል ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ ዮሐንስ መርጋ በይግባኝ በእድሜ ልክ እስራት ተቀጣ።

ደራርቱን በጩቤ ሶስት ቦታ ጀርባዋን በመውጋት የግድያ ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት መቀጣቱ ይታወሳል።

በውሳኔው ቅር የተሰኘው የአሶሳ ከተማ አስተዳደር አቃቤ ህግ ይግባኝ ጠይቋል።

የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተከሳሹ በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን ከአሶሳ  ፖሊስ መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

Via @tikvahuniversity
#Chapa

እራስዎን በዲጂታል ክፍያ ከሚፈፀሙ ማጭበርበሮች ይጠበቁ!

እነዚህን ቀላል የጥንቃቄ መንገዶች በመጠቀም እራሶን በዲጂታል ክፍያ ከሚፈፀሙ ማጭበርበሮች ይጠበቁ!
የላኪዉን አጠቃላይ መረጃ ያረጋግጡ
ፒኖትን አያጋሩ
ለተጀመሩ ግብይቶች ብቻ ምላሽ ይስጡ
🚨አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎች ሲኖሩ ሪፖርት ያድርጉ
🔔ስለተለያዩ የማጭበርበር ዘዴዎች መረጃ ያግኙ

🚫አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎች ሲኖሩ ወደ 📞8911 በመደወል ሪፖርት ያድርጉ

🌐 ለበለጠ መረጃ ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ፡ https://chapa.co/
🌐Visit our website Chapa.co or use our shortcode 📞8911 for more information

#chapa #chapapayments #Fraudawareness #Digitalpayment

Website
|Telegram | Instagram | Facebook |LinkedIn |X
#መምህራን

" ለልማት በሚል ከደመወዛችን እየተቆረጠብን ነው " - መምህራን

" እውነት ነው። ከህግ አግባብ ውጪ የመምህራን ደመወዝ እየተቆረጠ ነው " - የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር

የደመወዝ በወቅቱ አመከፈል፣ የጥቅማጥቅም ክፍያ አለማግኘት ችግር ባልተቀረፈበት ሁኔታ፣ ያለፈቃዳቸው ከደመወዝ ለልማት በሚል እየተቆረጠባቸው መሆኑን መምህራን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አማረሩ።

መምህራኑ በሰጡት ቃል፣ " ለልማት በሚል እስከ 50 በመቶ ከደመወዛችን እየተቆረጠብን ነው። የወር አስቤዛን በቅጡ ከማይሸፍን ደመወዝ ላይ እየተቆረጠ እንዴት ቤተሰብ እናስተዳድር ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

ይህ የመንግስት ድርጊት ሰንበትበት እንዳለ ገልጸው፣ ጭራሽ ቤተሰብ ማስተዳደር አቅቷቸው በብድር እየማቀቁ በመሆኑ ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።

መምህራኑ ያቀረቡት ቅሬታ እውነት ነው ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበለት የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር፣ " እውነት ነው ችንሩን በደንብ ነው የምናውቀው "  ብሏል።

የማኀበሩ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ ሽመልስ አበበ በሰጡት ቃል፣ " በየክልሉ የተለያየ የመልካም አስተዳደር ችግር አለ። ያለመምህራን ፈቃድ የደመወዝ  ቆረጣም በጣም #ትክክል ያልሆነ፣ #ጉልበተኝነት የበዛበት፣ #ሰሚ ያጣ ነው " ብለዋል።

ታዲያ ለቅሬታው ማኀበሩ ምን እየሰራ ነው ? ለሚለው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ " ትክክል አይደለም ብለን እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አድርሰናል። ባለፈው ነሐሴ ወር በነበረን ውይይት " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

አሁንም በተለይ ዳውሮ ዞን የሚገኙ መምህራን እንደሚያለቅሱ፣ ማኀበሩም ለትምህርት ሚኒስቴር እንዳሳወቀ፣ ትምህርት ሚኒስቴርም ያለፈቃዳቸው ደመወዝ እንዳይቆረጥ ለክልሉ ትምህርት ቢሮ ደብዳቤ እንደጻፈ፣ ክልሉም ደመወዛቸው እንዳይቆረጥ ለሚመለከተው አካል እንዳሳወቀ አስረድተዋል።

" ዞኑ ላይ 'ለማዕከል ግንባታ' በሚል ለዛ ነው ደመወዛቸው እየተቆረጠ ያለው። መምህራኑም እዚህ ድረስ መጡ። እኛም ለእንባ ጠባቂ ተቋም ደብዳቤ ጻፍን። የተለያዩ አካላትን ለመድረስ ጥረት አደረጉ። ግን እንባ ጠባቂም ምን ያህል ኃላፊነቱን እንደተወጣ አላውቅም " ነው ያሉት።

" በእኛ በኩል ያላረግነው ነገር የለም " ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፣ " ግን አሁን ህግ የሌለ በሚስል ሁኔታ የመምህራን ደመወዝ እየተቆረጠ ነው " ብለዋል።

መምህራኑ ደመወዛቸውን ቀድመው ለተለያዩ ፕሮግራሞች ከፋፍለው የሚጠቀሙበት ብቸኛ ገቢያቸው እንደሆነ ገልጸው፣ " መካከል ላይ ደመወዝ ሲቆረጥ ምስቅልቅል ይወጣል " ሲሉ አስረድተዋል።

" ይህንን የማያይ ምን አይነት የዞን አመራር እንዳለ አይገባኝም በበኩሌ። እጅግ በጣም ጫፍ የወጣ ስልጣን መጠቀም እንደሆነ ነው የምረዳው። መምህራን እየተሰቃዩ ነው የሚያዳምጣቸው አጥተዋል " ሲሉ አክለዋል።

ምን ያህል መምህራን ናቸው ደመወዝ የተቆረጠባቸው ? ለሚለው ጥያቄ አቶ ሽመልስ፣ " ለምሳሌ ዳውሮ ላይ የዞኑ መምህራን በሙሉ ተቆርጦባቸዋል። ኦሮሚያ ላይ የ230 ሺህ መምህር ይቆረጣል ደመወዙ " ነው ያሉት።

የሚቆረጠው መጠን በሁሉም ቦታ እንደየሁኔታው እንደሚለያይ አስረድተው፣ የክልል መንግስታት በማናለብኝነት ደመወዝ መቁረጥ አግባብነት እንደሌለው ቆም ብለው እንዲያስቡ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የመምህራኑን ቅሬታ በተመለከተ ምን ሀሳብ እንዳለው በቀጣይ የመረጃ የምናደርሳችሀ ይሆናል።

#TikvahErhiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት #አዲስአበባ

ነገ ለስራ ይሁን ዘመድ ጥየቃ ወይም ደግሞ ለተለያየ ፕሮግራም ከቤት የምትወጡ ካላችሁ የሚዘጉ መንገዶች ይኖራሉ።

መንገዶች የሚዘጉት  80ኛውን የመቻል ስፖርት ቡድን ምስረታን ምክንያት በማድረግ በሚካሄድ የጎዳና ላይ ሩጫ ነው።

ሩጫው 10 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን መነሻ እና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ነው።

በዚህም ፦

- ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ

- ከካዛንቺስ ወደ ባምቢስ

- ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ

- ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት

- ከለገሃር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ

- ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ሩጫው እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ አንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
#Ethiopia

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች ከነገ ሰኔ 23 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ ያስመርቃሉ፡፡

🎓 ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 23/2016 ዓ.ም
🎓 አክሱም ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 23/2016 ዓ.ም
🎓 መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 23/2016 ዓ.ም
🎓 አሶሳ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 25/2016 ዓ.ም
🎓 ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 25/2016 ዓ.ም
🎓 ወለጋ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 25-26/2016 ዓ.ም
🎓 ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 25/2016 ዓ.ም
🎓 ጅማ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 25/2016 ዓ.ም
🎓 ሠመራ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 26/2016 ዓ.ም
🎓 ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 26 እና 27/2016 ዓ.ም
🎓 ቦረና ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 26/2016 ዓ.ም
🎓 አምቦ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
🎓 ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
🎓 ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
🎓 ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
🎓 ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
🎓 ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
🎓 አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
🎓 ወራቤ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
🎓 ዲላ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
🎓 ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
🎓 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 29/2016 ዓ.ም
🎓 ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 29/2016 ዓ.ም
🎓 ደምቢ ዶሎዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 29/2016 ዓ.ም
🎓 መቱ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 29/2016 ዓ.ም

Via @tikvahuniversity
#Chapa

የማያቁት ወይም በእርሶ ያልተነሳ የክፍያ መጠየቂያ (USSD) ሲላክልዎ የይለፍ ቃሎትን በፍጹም አያስገቡ።

🚫አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎች ሲኖሩ ወደ 📞8911 በመደወል ሪፖርት ያድርጉ

🌐 ለበለጠ መረጃ ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ፡ https://chapa.co/ ወይንም ዛሬውኑ በ 8911 ይደውሉልን ።

#chapa #chapapayments #Fraudawareness #Digitalpayment

Website |Telegram | Instagram | Facebook |LinkedIn |X
#Amhara

ከሰሞኑን በአማራ ክልል፣ በባህርዳር ከተማ የተለያዩ የመንግሥት አካላት ፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ከተካሄደ የሰላም ኮንፈረንስ በኃሏ ተቋቁሟል የተባለው ' አመቻች የሰላም ምክር ቤት ' በአማራ ክልል እየተደረገ ያለው የእርስ በእርስ ጦርነት ነው ብሏል።

ምክር ቤቱ በዚህ ጦርነት ፥ " ወንድም ከወንድሙ፣ ልጅም ከአባቱ ጋር ነው እየተገዳደለ ያለው " ሲል ገልጿል።

ለፌዴራል መንግሥት / ለአማራ ክልላዊ መንግሥት እና ለፋኖ ኃይሎች ሲል በስም ጠርቶ ባቀረበው የሰላም ጥሪ " የወገናችሁን ስቃይ ተረድታችሁ ምንም መሸናነፍ በማትችሉት ጦርነት ከመቆየት ሁለታችሁም ማሸነፍ ወደምትችሉት ንግግር እና ድርድር እንድትመጡ እንጠይቃለን " ብሏል።

ም/ ቤቱ መንግሥት እና የፋኖ ኃይሎች ወደ ሰላም መድረክ እንዲመጡ ለማመቻቸት እንደሚሰራ አመልክቷል።

" በአማራ ክልል ባለው ጦርነት ንጹሃን ይገደላሉ፣ በጠራራ ጸሃይ ያለ ከልካይ ይዘረፋሉ  " ያለው ምክር ቤቱ ከ12 እስከ 13 ቢሊዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን አመልክቷል።

መንግሥት ጦርነቱን በድርድር ለመቋጨት ፍቃደኛ እንደሆነ ገልጾ " ብዙ መሪ እና አደረጃጀት ያላቸው የፋኖ ታጣቂዎች ለመደራደር ወደ አንድ መምጣት አለባቸው በማለቱ ይህ የሰላምና ድርድር አመቻች ምክር ቤት መቋቋሙ ተነግሯል።

ምክር ቤቱ 15 አባላት ያሉት ነው።

በሌላ በኩል ፥ ከሰሞኑን በርካታ ሰዎች በክልሉ መገደላቸው ተሰምቷል።

በሰሜን ጎንደር ዞን ፤ በዳባት ወረዳ፣ በመንግስት የጸጥታ አካላት እና ፋኖ ኃይሎች መካከል በተደረገ የተኩስ ልውውጥ የፓሊስ አባላት መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ሁነቱን በቅርበት ሲከታተሉ የነበሩ ነዋሪ ፤ " ከተማው ውስጥ አሁንም ሀዘን/ልቅሶ አለ " ሲሉ ተናግረዋል።

" ሀዘኑ የተፈጠረው በአካባቢው ላይ ከ ‘ ፋኖ ’ ጋር በነበረ ውጊያ በርካታ የአካባቢው የጸጥታ አባላት ስለተገደሉ መሆኑን አረጋግጫለሁ " ብለዋል።

የሟቾች ቁጥር ምን ያህል ነው ? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ " የሟቾች ቁጥር ከ115 በላይ ነው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ሟቾቹን በተመለከተም አድማ ብተና ሚሊሻና ፖሊስ እንደሆኑ ገልጸዋል።

ቃላቸውን የሰጡ ሌሎች ነዋሪዎች የሟቾች ቁጥር እስከ 130 እንደሚደርስ ንጹሐን እንደቆሰሉ ገልጸው ሰሞኑን ከተማዋ ከባድ ሀዘን እንዳስተናገደች ተናግረዋል።

ስለግድያው ምላሽ የጠየቅነው የዳባት ወረዳ ከንቲባ ጽ/ቤት፣ ጉዳዩን በጽሞና ከሰማ በኋላ ማብራሪያ ለመስጠት ፍቃደኛ አልሆነም።

በዚሁ ባሳለፍነው ሳምንትም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን ባአዊ ዞን የቲሊሊ ወረዳ ነዋሪዎች ደግሞ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች 3 ሰዎችን ከቲሊሊ ሆቴል አውጥተው ገድለዋል ሲሉ ከሰዋል።

ሌሎች 2 ሰዎችም ተገድለዋል። በድምሩ 5 ንጹሐን በቲሊሊ ወረዳ መገደላቸውን ተናግተዋል።

በቦታው የተኩስ ልውውጥ ተደርጎ ነበር እንዴ ? በሚል ለነዋሪዎቹ ለቀረበው ጥያቄ ምንም ተኩስ እንዳልነበር፣ ግማሾቹን መንገድ ላይ በሚጓዙበት፣ ሌሎቹን ደግሞ ከሆቴል አስወጥተው እንደገሏቸው አስረድተዋል።

የመንግስት አካላት ስለሁኔታው እንዲያብራሩልን ብንጠይቅም ፍቃደኛ አልሆኑም።

ከዚህ ባለፈም ፥ በሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ከደብረ ሲና ከተማ ወጣ ብላ በምትገኝ  " ሾላ  ሜዳ " በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ ሰኔ 19 በመንግሥት ኃይሎች ደርሷል በተባለ ጥቃት ቢያንስ 15 ሰዎች መገደላቸውን እና 4 የሚሆኑ ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎችን ዋቢ በማድረግ ቢቢሲ አማርኛው ዘግቧል።

በጥቃቱት ከአያቶቹ ጋር የሚኖር የ14 ዓመት ታዳጊ መገደሉን ፥ አንድ የአይን እማኝ ደግሞ አንድ ሻይ ቤት 11 ሰዎች መገደላቸውን በ20ዎቹ እድሜ የሚገኝ ወንድማቸው ተገድሎ ሜዳ ላይ እንዳገኙት ተናግረዋል።

ሌላ የአይን እማኝ የ11ዱ ሟቾችን ስም ዝርዝር መሰብሰብ እንደቻሉ ሰኔ 20 ቀን/2016 ዓ/ም 4 ተጨማሪ አስከሬን እንደተገኘ ገልጸዋል።

የጸጥታ ኃይሎቹ በአካባቢው ለለቅሶ መጥተዋል የተባሉ 3 የፋኖ ታጣቂዎችን ተከትለው ሳይመጡ እንዳልቀረና ስለ ታጣቂዎቹ መረጃ በመፈለግ ግድያውን እንደተፈጸመ አክለዋል።

በተመሳሳይ በሰሜን ጎጃም ዞን ፤ በይልማና ዴንሳ ወረዳ አዴት ከተማ ሰኞ ሰኔ 17 ቀን 11 ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፥ በእለቱ የፋኖ ታጣቂዎች እና የመንግሥት ኃይሎች ለሰዓታት የዘለቀ ከባድ ውጊያ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።

ይህን ተከትሎ ጥቃቱ መፈጸሙን አንድ ሴትና 10 ወንዶች እንደተገደሉ ገልጸዋል።

ግድያው የ ' ፋኖ ታጣቂዎች ' ከተማይቱን ለቀው መውጣታቸውን ተከትሎ 02 ቀበሌ እርሻ ሰብል በተባለ ሰፈር መንገድ ላይ እና ቤት ለቤት መፈጸሙን ገልጸዋል።

" ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ " በሚል ግድያው ተፈጽሟል ሲሉ ከሰዋል።

ፋኖ በከተማው ተቆጣጥሮ ውሎ በወጣበት ሰዓት የመንግስት ጸጥታ ኃይል ተመቶ እንደነበር ነዋሪዎች ተናግረዋል።

በተፈጠረው ክስተት ከተማዋ በከባድ ሀዘን ውስጥ መውደቋን ገልጸዋል።

በአማራ ክልል ፤ ያለው ጦርነት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን በተለያየ ጊዜ በተለያየ ቦታ እየተፈጠረ ባለው ግጭት የሰዎች ህይወት እየጠፋ ነው።

ከሰሞኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ህዝቡ በሰላም እጦት የከፋ ችግር ላይ ወድቆ እንደሚገኝ ተናግረው ፥ መገዳደሉና ፣ በጠላትነት መፈላለጉ እንዲያበቃ ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ አገኘሁ ተሻገር፥ " በቃ! እስኪበቃን ተገዳድለናል ፣ እስኪበቃን ተዋጋን ስለዚህ አሁን ላይ ይብቃን ፣ መፍትሔው ንግግር ነው ፣ መነጋገር ነው ፣ መከባበር ነው " ሲሉ ነበር የተናገሩት።

#Ethiopia
#AmharaRegion

@tikvahethiopia
2024/09/29 20:17:50
Back to Top
HTML Embed Code: