Telegram Web Link
#AddisAbaba

በጀኔቭ የመኪና አስመጭና በቤቶች ኮርፖሬሽን መካከል የተፈጠረው ነገር ምንድን ነው ?

በአዲስ አበባ ቂርቆስ ክ/ከተማ ደንበል አደባባይ አካባቢ " ጄኔቭ የመኪና አስመጪና ሻጭ ድርጅት " የተከራየው ህንፃ የኪራይ ውሉ እንዲቋረጥ ሊደረግ በመሆኑ ያለውን ቅሬታ እያቀረበ ይገኛል።

የጀኔቭ ዋና እና ምክትል ማናጀሮች ቅሬታቸው ፦
- ህንፃው ለMixed አገልግሎት ሆኖ ሳለ ለሆቴል ማስፋፊያ ይሰጥ መባሉ፣
- እኛ እራሳችን ከፍተኛ ግብር ከፋይ ሆነን ለሌላ ለሆነ አካል ይሰጥ መባሉ፣
- ቤቱ ለልማት ይሰጥ ተብሎ የካቢኔ ውሳኔ ባለማግኘታቸው፣
- ለልማት ይሰጥ የተባለው በ2013 ዓ/ም ሆኖ ሳለ አሁን ውሉ ይቋረጥ መባሉ፣
- ቤቶች ኮርፖሬሽን ሊሟገት ሰገባው የኪራይ ውሉ እንዲቋረጥ የድጋፍ ደብዳቤ በመፃፉ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ራሱ ኮርፖሬሽኑ ቢያለማው እኛ መልቀቅ እንችላለን የመንግስት ቦታ ስለሆነ ግን ለምንድነው ለሶስተኛ ወገን ተላልፎ የሚሰጠው ? ያውም ሆቴል ሳይሆን ሆቴል ተብሎ ሲሉ ጠይቀዋል።

የቤቶች ኮርፖሬሽን የፃፈው የድጋፍ ደብዳቤ ላይ፥ ምክንያቶቹን በዝርዝር ካብራራ በኋላ፣ የተከራይ ውል እንዲቋረጥ ያዛል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጥ ኮርፖሬሽኑን ጠይቋል።

የኮርፖሬሽኑ ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ አማኑኤል አያሌው፣ “ የመጀመሪያ ስህተቱ ሰዎቹ ልክ እንደ ግል ይዞታ አድርገው እያቀረቡ ነው። ይዞታው የቤቶች ኮርፖሬሽን ነው። ቅሬታ አቅራቢዎቹ ደግሞ የንግድ ቤት ተከራይ ናቸው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ ከተማ አስተዳደሩ ‘እዚያ አካባቢ የሆቴል ዲዛይን ነው’ አለ። እኛ ሆቴል አንገነባም። ስለዚህ እኛ ይዞታ አናስተላልፍም ለግለሰብ። እሳቸውም ለእኛ ቅሬታ ቢያቀርቡ መስጠት አንችልም ” ብለዋል።

አቶ አማኑኤል፣ “ ቅሬታ ካላቸው ለከተማ አስተዳደሩ ነው ማቅረብ ያለባቸው። ቦታው ለእኔ ይመደብ ብለው ማቅረብ ይችላሉ ” ነው ያሉት።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ ቦታው ለልማት እንዲነሳ በካቢኔ ስለመወሰኑ እንደማያውቁ ላነሱት ቅሬታ በሰጡት ምላሽ አቶ አማኑኤል፣ “ የካቢኔ ውሳኔ ተለጥፏል ያውቃሉ። በ2013 ዓ/ም የተለጠፈ የካቢኔ ውሳኔ ነው ” ብለዋል። (ይህን የሚገልጽ ዶክመትም አሳይተዋል)

ለቲክቫህ የላኩት ሰነድም ህንፃው ለልማት እንዲነሳ በከተማ አስተዳደሩ በ2013 ዓ/ም መወሰኑን ያትታል።

እንዲሁም፣ ቦታው ለMixed አገልግሎት ሆኖ ሳለ ለምን ለሆቴል ማስፋፊያ ይሰጥ በመባሉ ጀኔቭ ላነሳው ቅሬታ፣ “ ይህ ሰው ተከራይ ነው። ይህን ያህል ቅሬታ ማንሳት የለበትም፣ ተቀባይነት የለውም ” ብሏል ኮርፖሬሽኑ።

“ ተከራይ ነው፤ በንግድ ህጉ መሠረት ይህ ሰው ሲዋዋል መንግስት ወይም ኮርፓሬሽኑ ቤቱን ለልማት  ሲፈልገው ውል ያቋርጣል ይላል ” ነው ያለው።

ተወሰነ የተባለው በ2013 ዓ/ም ሆኖ ሳለ ለምን አዘግይቶ አሁን መጠየቅ አስፈለገ ? ሲል ጀኔቭ ላነሳው ጥያቄ አቶ አማኑኤል፣ “ አብዛኛውን ውሳኔ አንቀበልም። መሬቱን ማቆየትና ማልማት ስለምንፈልግ ” ሲሉ መልሰዋል።

አክለው፣ “ ግን አሁን የአዲስ አበባ ከተማ መልሶ ማልማት ላይ ያለው ‘ ከመንግሥት እንቅፋት እየሆነናችሁ ነው ’ የሚል ቅሬታም እየመጣ ስለሆነ ማልማት በምንችለው መንገድ እኛ እናለማን። ባለሃብቱ ማልማት ባለበት ደግሞ ባለሃብቱ ” ነው ያሉት።

የጄኔቭ ማናጀር አቶ አብርሃም ለማ በበኩላቸው፣ “ ራሳቸው ተጠይቀው የሰጡት መልስ አለ። ‘ ራሱን ችሎ የሚገነባ ቦታ ስለሆነ ራሳችን እንገነባለን። ካልሆነ ደግሞ ተከራዩ ማልማት የሚችል ከሆነ ቅድሚያ እንሰጣለን’ ” የሚል ምላሽ ከከተማ ከንቲባ ለቀረበላቸው ጥያቄ እንደሰጡ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#Amhara

የኤፍራታ ግድም ወረዳ አስተዳዳሪ ተገደሉ።

በወረዳው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች የወረዳውን አስተዳዳሪ አቶ አልብስ አደፍራሽን ትለንትና በምሽት በመግባት እንደገደሏቸው ተሰምቷል።

ወረዳው ባወጣው የሀዘን መግለጫው ፥ " አቶ አልብስ ለዓመታት በቀውስ ነጋዴዎች ለችግር ተጋልጦ የሴራ ፖለቲካ መሸቀጫ የተደረገውን የጀውሃና አካባቢው ማህበረሰብ ቀርቦ በማወያየት መተማመን ፈጥሮና አደራጅቶ ወደ ቀደመ አካባቢውና ኑሮው እንዲመለስ በማድረግ ላይ ነበሩ " ሲል ገልጿል።

አክሎ " የወደሙትን የጤናና ሌሎች ተቋማትንም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት በመስራት መልሶ እያቋቋመ የነበረ ደከመኝን የማያውቅ፣ ለእውነት የቆመ ንፁህ የሕዝብ ልጅና አገልጋይ፤ እውነተኛ የአማራ ጀግና ነበር " ብሏል።

አቶ አልብስ አደፍራሽ ትላንትና ምሽት ቤታቸው በገቡ ታጣቂዎች ተገድለዋል።

@tikvahethiopia
#Tigray

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በትግራይ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በያዝነው ሳምንት አገልግሎት መስጠት የጀመረው በመቐለ ከተማና አከባቢዋ ነው።

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በትግራይ አገልግሎት መስጠት ስለመጀመሩ አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ በ2 ምዕራፎች 16 የትግራይ ከተሞች የ4G እንዲሁም የ5G የሞባይል ዳታ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ ነው ብሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
" የሃይማኖት ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ ምን ይዟል ? በኢትዮጵያ አዲስ የተዘጋጀ " #የሃይማኖት_ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ አለ። ይህ ረቂቅ አዋጅ በርካታ ጉዳዮችን ይዟል። አንዱ የአምልኮና የመቃብር ቦታን የተመለከተ ሲሆን ፥ ረቂቅ አዋጁ ለሃይማኖት ተቋማት የመሬት አቅርቦት በመሬት አጠቃቀምና የሊዝ ሕጎች መሠረት ይወሰናል ይላል። ለአምልኮ ወይም ለመቃብር ቦታ በተጠየቀበት አካባቢ ለሃይማኖት ተቋሙ ለተመሳሳይ…
#Update

" በሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ " ላይ የመጨረሻ የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩም የሃይማኖት ተቋማት ቅሬታ ማቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

ተቋማቱ ረቂቅ አዋጁ ከመፅደቁ በፊት የሁሉንም የሃይማኖት ተቋማት መብትና ክብር የሚጠብቅ መሆኑ ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።

በአብዛኛው ተከብሮ የቆየው የሃይማኖቶች ነፃነት ላይ ገደቦችን እንዳይጥል ሥጋት እንዳላቸው ገልጸዋል።

የቀረቡ ቅሬታዎች ምንድናቸው ?

1ኛ. ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ተወካዮች የተነሳው ቅሬት፦

በረቂቁ አዋጁ ላይ የአደባባይ በዓላትን በሚመለከት " የአደባባይ ኩነት " ተብሎ መቀመጡን በማንሳት ይህ ትክክለኛ ትርጉም አይደለም ብለዋል፡፡

ለዚህ በማሳያ " የአደባባይ ኩነት በተፈቀደው ቦታ ብቻ መደረግ አለበት " በሚል በረቂቁ ላይ የተቀመጠውን ነው።

ለአብነት #የጥምቀት_በዓል የአደባባይ ሃይማኖታዊ በዓል ቢሆንም ፤" ከተፈቀደለት አደባባይ ውጪ መንገዶች ላይ መካሄድ አይፈቀድም " የሚል ትርጓሜ እንዳይሰጠው #ያሠጋል ብለዋል፡፡ 

ሌላው " የሃይማኖት ተቋም የሚይዘው ስያሜ፣ ዓርማ ወይም ምልክት ቀድሞ ከተቋቋመ ተቋም ስም፣ ዓርማ ወይም ምልክት ጋር ተመሳሳይ መሆን የለበትም " በሚል ረቂቁ ላይ የተቀመጠው ነው።

ይህ ፤ " #በከፊልም ሆነ #ሙሉ_በሙሉ ተመሳሳይ መሆን የለበትም " በሚል ሊስተካከል እንደሚገባው ገልጸዋል።

ለዚህ ምክንያቱ " የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሚለውን ስያሜ የኢትዮጵያ የሚለውን ብቻ በማውጣትና የራሳቸውን በመተካት አገልግሎት ላይ ሲያውሉ የሚታዩ አካላትን ስለተመለከትን ነው " በማለት አስረድተዋል፡፡

2ኛ. የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ ቤትን በመወከል የተገኙ ተሳታፊዎች ያቀረቡት ቅሬት ፦

ሃይማኖታዊ ተግባራትን በሚከለክለው የረቂቅ አዋጁ ክፍል " በአውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናሎች መፈጸም የተከለከለ ነው " በሚል የቀረበው ሊስተካከል ይገባል ብለዋል።

#ሶላት_የደረሰበት_ሙስሊም በአውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናሎች እንዳይሰግድ መከልከል እንደማይቻል ገልጸዋል፡፡

" በከተሞች ውስጥ ለአምልኮና መቃብር የሚሰጥ ቦታ የከተማውን የዕድገትና የልማት ዕቅድ ወይም ማስተር ፕላን የማይቃረን መሆን አለበት " በሚለው ረቂቁ ላይ ይህ ወደ ተግባራዊነቱ ሲገባ አስቸጋሪ እንደሚሆን ገልጸዋል።

መጀመሪያ የተገነባ ቤተ እምነት " ከከተማው ማስተር ፕላን ጋር የሚቃረን ነው " በሚል እንዳይፈርስ ዋስትና የማይሰጥ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

በመንግሥት ተቋማት የሚሠሩ ሠራተኞች ሁሉ እምነት እንዳላቸው፣ ለአብነትም አንድ ሙስሊም በመንግሥት ተቋም ተቀጥሮ ሲሠራ ሶላቱን በሚሰግድበት ወቅት፣ በተቋሙ ውስጥ ሃይማኖታዊ ክንውን አድርጓል ሊባል መሆኑንና ረቂቁ ይህን እንዴት ማስታረቅ እንደሚችል ጥያቄ አስነስቷል፡፡

3ኛ. የወንጌል አማኞች ካውንስል ተወካዮች ቅሬታ ፦

ረቂቅ አዋጁ በወንጌላውያን ሃይማኖት ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ገልጸዋል።

" በተለይ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ የሚከለክሉ የረቂቁ ክፍሎች፣ ወንጌል መስበክ መሠረታዊ አስተምሯችን ለሆነው ለወንጌላውያን ተቀባይነት ሊኖረው የማይችል ነው " በማለት ተናግረዋል፡፡

ይህ ' መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም ' በሚል የተቀመጠውን መርህ የጣሰ እንዳይሆን ሥጋታቸውን ገልጸዋል፡፡ 

Credit ➡️ Reporter Newspaper

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ በሀገሪቱ ውስጥ ያለ ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርቱን ለሰላም ሚኒስቴር ማቅረብ እንደሚኖርበት ፤ ከውጭ አገር የሚመጣ የገንዘብ ዕርዳታ በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል። " የሃይማኖት ጉዳዮች አዋጅ " የተሰኘው ረቂቅ አዋጁ የሃይማኖት ተቋማቱ ተቀባይነት ያለው የሒሳብ አያያዝና የኦዲት ሥርዓት…
#Update

" በሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ " ላይ የመጨረሻ የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ላይ ረቂቁ ከባለፈው መጠነኛ #ማሻሻያዎች ተደርጎበት መቅረቡን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

ምንድናቸው ?

በመጀመሪያው ረቂቅ አዋጅ ያልነበረና የመንግሥትንና የክልሎችን ግዴታና ኃላፊነት በመዘርዘር የተቀመጠው ክፍል አንዱ ነው።

በዚህ ክፍል ላይ መንግሥት በሃይማኖት አስተምህሮና የውስጥ ጉዳይ #ጣልቃ_መግባት_እንደማይችል ተደንግጓል፡፡

በተጨማሪ ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ከውጭ አገር የሚላክለትን የገንዘብ ዕርዳታ፣ ስጦታ ወይም ሌሎች የገንዘብ ድጋፎችን በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት ተደንግጎ የነበረው የረቂቅ አዋጁ ክፍል ከተሻሻለው ረቂቅ እንዲወጣ ተደርጓል፡፡

ነገር ግን ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ፦

° የሃይማኖት ተቋሙን ኦዲት ሪፖርት ለሰላም ሚኒስቴር እንዲያቀርብ፣

° የበጀት ዓመቱ በተጠናቀቀ #በ3_ወራት የፋይናንስ እንቅስቃሴውን በገለልተኛ ኦዲተር ማስመርመር እንደሚኖርበት የተቀመጠው የረቂቁ ክፍል በተሻሻለው ላይ #ተካቷል፡፡

ሌላኛው ተሻሽሎ የቀረበው የረቂቅ ክፍል #አለባበስን እና የተማሪዎች #አመጋገብን ጨምሮ በማንኛውም የትምህርት ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚደረግ ሃይማኖታዊ ተግባር የመንግሥትና ሃይማኖት መለያየት መርህንና የሃይማኖት ነፃነትንም በጠበቀ መንገድ መከናወን አለበት የሚለው ነው፡፡

የሰላም ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች ምን አሉ ?

የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረኩ #የመጨረሻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ከዚህ ቀደም #በመንግሥት እና #በሃይማኖት መካከል ያለው ልዩነት ምን ድረስ እንደሆነ ሳይታወቅ ቆይቷል ብለዋል።

አዋጁን ማዘጋጀትም ያስፈለገው ይህን ጉዳይ በግልጽ ለማስቀመጥ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

መንግሥት በሃይማኖት ተቋማት ነፃነት ውስጥ ጣልቃ የመግባት ፍላጎት እንደሌለው  ፤ ነገር ግን አብረው በሚሠሩባቸው ጉዳዮች በሕግ የተቀመጠ አሠራር ሊኖር እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

በመድረኩ ላይ የተነሱ ሐሳቦችን በግብዓትነት #ወስዶ ለሚመለከተው አካል የሚቀርበውን ረቂቅ አዋጅ እንደሚያዘጋጅ ተገልጿል፡፡

Credit - Reporter Newspaper

@tikvahethiopia
#Axum #Tigray

" በጦርነቱ ጊዜ እኮ #መከራው ከባድ ነበር !! "

ወ/ሮ በላይነሽ መኣሾ (የአክሱም ነዋሪ ለድምጺ ወያነ) ፦

" ሰላም በመሆኑ ጥሩ ነው ያለው።  ብርሃን አየን።

በሰላም እየተንቀሳቀስን ነው። #ሕጻናት እየተጫወቱ ነው።

ብዙ ለውጥ ነው ያለው።

በጦርነቱ ጊዜ እኮ #መከራው እጅግ ከባድ ነበር። አሁን በጣም በጣም ይሻላል ፤ ቢያንስ #እፎይ ብለን  መተኛት እንችላለን።

ቢሆንም ግን #የከፋው_ሰው_አለ ፤ ሰው የሚበላው የሚጠጣውን አጥቶ በጣም ከፍቶታል ፣ የመንግስት ሰራተኛውም ያለፉት ዓመታት ደመወዝ ባለመከፈሉ ለተለያዩ ችግሮች ተጋልጦ ነው ያለው ፣ የተፈናቃዮች ነገርማ #አይወራም ፣ ሕጻናት ልጆች የሚበሉትን አጥተው በየከተማው #በልመና ነው ተሰማርተው ያሉት። "

#Ethiopia #TigrayRegion #Peace

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት #AddisAbaba

በመንገድ ኮሪደር ልማትና በአስፓልት የማንጠፍ ስራ ምክንያት ከመስቀል አደባባይ ወደ ቦሌ አየር መንገድ የሚወስደው ዋናው መንገድ በከፊል ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

መዚህ መሰረት ፡-

- ከለገሐር በመስቀል አደባባይ ወደ ቦሌ አየር መንገድ

- ከእስጢፋኖስ በቀጥታ ወደ ቦሌ አየር መንገድ

- ከኡራኤል በመስቀል አደባባይ ወደ ቦሌ አየር መንገድ

እንዲሁም #በውስጥ_ለውስጥ ወደ ዋናው ቦሌ አየር መንገድ የሚወስዱ መንገዶች ከዛሬ ግንቦት 26 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ #በየዕለቱ ስራው እስኪጠናቀቅ ድረስ ከቀኑ 8:00 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12:30 ሰዓት ለተሽከርካሪ በከፊል ዝግ ይሆናሉ።

አሽከርካሪዎች የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥማቸው ሌሎች አማራጭ መንገዶችን መጠቀም እንዳለባቸው አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
#SouthAfrica

ከሰሞኑን በደቡብ አፍሪቃ " የ2024 ምርጫ " ተደርጎ ነበር።

በምርጫው ማንም አሸናፊ አልሆነም።

የዘንድሮ ምርጫ ገዢው ፓርቲ የአፍሪቃ ብሔራዊ ምክር ቤት / ANC / 40.18 በመቶ ድምጽ በማግኘት ቀዳሚ ቢሆንም መንግሥት መመስረት የሚያስችለውን ድምጽ ግን አላገኘም።

ፓርቲው በ30 ዓመታት የመሪነት ታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ አብዛኛውን የምክር ቤት መቀመጫ ተነጥቋል።

በዚህም መንግሥት ለመመስረት ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች መጣመር ግድ ይለዋል።

ፓርቲው ምክር ቤቱ ካለው 400 መቀመጫዎች 159 ብቻ ነው ያሸነፈው።

የወቅቱ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎዛ መንግሥት ለመመስረት #ከተቃዋሚዎች ጋር እንደሚነጋገሩ አመልክተዋል።

በምርጫው 87 መቀመጫዎችን ያሸነፈው የመሃል ቀኝ ዘመሙ ዴሞክራሲያዊ ጥምረት (DA) ነው።

ከገዢው ፓርቲ ጋር ጥምር መንግሥት ለመመስረት የሚያስችል ንግግር ለማድረግ መዘጋጀቱን አስታውቋል።

ሶስተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው የቀድሞ ፕ/ት ጃኮብ  ዙማ ፓርቲ MK ሲሆን ከገዢው ፓርቲ ጋር የመነጋገር ፍላጎት ቢኖረውም " ራማፎዛ ሥልጣን ላይ እያሉ ንግግር አላደርግም " ማለቱን ዶቼ ቨለ ዘግቧል።

በዘንድሮ ሀገር አቀፍ ምርጫ እጅግ በርካታ #ወጣቶች ድምፅ መስጠታቸው የተሰማ ሲሆን ገዢውን ፓርቲ የአፍሪቃ ብሔራዊ ምክር ቤት /ANC/ በድምጻቸው #ቀጥተውታል

ለዚህ ደግሞ  ፦
- የከፋ ሙስና
- የመልካም አስተዳደር ችግር
- ስራ አጥነት መፋፋት
- የወንጀል መባባስ ... ዋነኞቹ ምክንያቶች እንደሆኑ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
በየትኛውም ስፍራ፣ በማንኛውም ሰዓት!
ሕብር ሞባይል ባንኪንግን በማውረድ ሂሳብዎን በቅርበት እና በቀላሉ ይከታተሉ፡፡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ!
https://www.hibretbank.com.et/hibir-mobile-landing-page/

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡ አዳዲስ መረጃ እንዲርሶ የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጫኑ፡፡
    ቴሌግራም- https://www.tg-me.com/HibretBanket
    ሊንክዲን- https://www.linkedin.com/company/hibretbank/
    ዌብሳይት- https://www.hibretbank.com.et/
#Hibretbank
#WKU

" አሳይመንቱን ቤት ድረስ አምጥተሽ ስጪን " በማለት ተማሪውን ደፍሯል የተባለው የዩኒቨርሲቲ መምህር ጉዳዩ በፍርድ ቤት እየታየ ይገኛል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰሞኑን ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ #ሴት ተማሪዎች መልዕክቶችን ተቀብሏል።

ይህም " የሴቶች ጥቃት አሳስቦናል " የሚል ነው።

ተማሪዎቹ የመደፈር እና የጥቃት ወንጀል በመምህር ሳይቀር መፈጸሙን በመግለጽ ስጋታቸውን ገልጻዋል።

በየጊዜው እንዲህ ያለ ነገርም እንሰማለን ነው ያሉት።

ከጠቆሙት አንዱ ጉዳይ በመምህሯ የተደፈረችን ተማሪ የሚመለከት ነው።

በተማሪዎች ስለሚነሳው ጉዳይ ተቋሙ ምን ይላል ? በማለት ጥያቄ አቅርበናል።

ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የዩኒቨርሲቲው አመራር የመምህሩ ጉዳይ #ከ2_ወራት_በፊት መከሰቱን እና ከአስገድዶ መድፈር ጋር በተያያዘ በቅርብ የተፈጸመ ጥቃት አለመኖሩን ገልጸዋል።

" ወንጀሉን ከ2 ወራት በፊት እንደፈጸሙ የተጠረጠሩት መምህር በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ፍርዳቸውን እየተጠባበቁ ነው " ብለዋል።

ድርጊቱ እንዴት ተፈጸመ ?

በወቅቱ አንድ የሂሳብ መምህር በክፍል ውስጥ ሆነው ከተማሪዎቻቸው አሳይንመንት በመቀበል ላይ ነበሩ። የአንደኛዋን ተማሪያቸውን ወረቀት ግን ሳይቀበሉ ነበር የወጡት።

ይሁንና " #አልቀበልሽም " የተባለችው ተማሪም ምን አድርጌ / ምንስ አጥፍቼ ነው ? ብላ በምትጨነቅበት ሰአት ከክፍሉ ተጠሪ ያገኙትን ስልክ ተጠቅመው የደወሉላት መምህር  " አሳይመንትሽን ቤቴ መጥተሽ ማስረከብ ትችያለሽ " ይሏታል።

ተማሪዋም በተሰጣት አድራሻ ተመርታ ወደተባለችው ቦታ ትሄዳለች። የጠበቃት ግን አሳይመንቱን መቀበል ሳይሆን ሌላ ነበር።

ተማሪዋ እያነባች ጓደኛዋን ይዛ ወደሆስፒታል ካመራች በኃላ በሆስፒታል ህክምና አግኝታለች።

የሆስፒታል ማስረጃዋን ይዛም ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ሂዳ አመልክታቸለች።

በወቅቱ ዩኒቨርሲቲው በተማሪዋ አቤቱታና በቀረበዉ የህክምና ማስረጃ  መሰረት ጉዳዩን ወደ #ዲስፕሊን በመዉሰድ በፍጥነት መምህሩን ከስራ ሊያግድ ችሏል።

መምህሩ ድርጊቱን ከፈጸመ በኋላ #ራሱን_ደብቆ እና ስልኩን አጥፍቶ ቆይቷል ተብሏል።

የዩኒቨርስቲው አስተዳደር #የስራ_እግድ ማሳለፉንም ተከትሎ ከተደበቀበት በመዉጣት ሲመለስ ጉዳዩን ከዩኒቨርስቲው በመረከብ ይዞ መምህሩን ሲያፈላልግ የነበረው ፖሊስ #በቁጥጥር_ስር ሊያውለው ችሏል።

አሁን ላይ የምርመራ ሂደቱ አልቆ ፍርዱን እየተጠባበቀ ሲሆን ወደፊት የፍርድ ሂደቱ የሚገለጽ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

ከሰሞኑ በዚሁ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አንድ ሽጉጥ የታጠቀ ወጣት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ተኩስ በመክፈቱ አንዲት ተመራቂ ወጣት ተማሪና አንድ መምህር መጉዳቱን መረጃ መለዋወጣችን ይታወሳል👉 https://www.tg-me.com/tikvahethiopia/88025

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba ከአንድ ሳምንት በፊት በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ሚሊኒያም አዳራሽ አካባቢ ከፖሊስ ኃይል ጋር በነበረው የተኩስ ልውውጥ ወቅት ሁለት " የፋኖ አባላት (አንድ አመራር እና አንድ አባል) " ፦ - ናሁሰናይ አንዳርጌ - አቤነዘር ጋሻው መገደላቸው መነገሩ ይታወሳል። ከዛ በኃላ እናቶቻቸው በሀዘን ውስጥ ሆነው አስክሬን ለመውሰድ እንዳልቻሉና እላይ ታች እያሉ እንደሆነ ግን ምንም መፍትሄ እንዳላሀኙ…
ፎቶ ፦ በሚያዝያ ወር መጀመሪያ አዲስ አበባ ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ ከፖሊስ ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ የተገደሉት ሁለት የፋኖ አባላት ቤተሰቦች አስከሬናቸውን ሳያገኙ ፍትሃትና ባህላዊ የሽኝት ሥነ ሥርዓት ጎንደር ውስጥ ፈጽመዋል።

ሁለቱ ወጣቶች ማለትም ፦
- ናሁሰናይ አንዳርጌ
- አቤኔዘር ጋሻው በተኩስ ልውውጥ ከተገደሉ በኃላ ወላጆቻቸው ወደ አዲስ አበባ በመምጣት አስከሬናቸውን አግኝተው ቀብር ለመፈጸም ፌደራል ፖሊስ ፣ አዲስ አበባ ፖሊስ ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ድረስ ጥያቄ ቢያቀርቡም ምላሽ ሳያገኙ 2 ወር ለሚጠጋ ጊዜ መጠበቃቸውን እና በመጨረሻም ተስፋ መቁረጣቸውን ተናግረዋል።

ዛሬ ግንቦት 26 ቀን 2016 ዓ.ም. ጎንደር ውስጥ የናሁሰናይ አንዳርጌ አስከሬኑ በሌለበት በባህላዊ መንገድ በቤተሰብና በወዳጆች ፍትሃቱና የሽኝት ሥነ ሥርዓቱ በአባ ጃሌ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።

አንድ የቤተሰብ አባል ፤ ለቀስተኛው ካለ አስከሬን በተካሄደው የስንብት ሥነ ሥርዓት ላይ ለመታደም ወደ ቤተ-ክርስቲያን እያመራ ሳለ የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች የናሁሰናይ ፎቶ እና ስም ያለበትን 2 ባነር በኃይል ተቀብለዋል። ከዚህ ውጭ ምንም የተፈጠረ ነገር የለም " ብለዋል።

የአቤኔዘር ጋሻው የሽኝት በተመሳሳይ ቤተሰቡ አስከሬኑ ባላገኘበት ሁኔታ ቀደም ብሎ መከናወኑን የቤተሰቡ አባላት ገልጸዋል።

#Credit - BBC AMHARIC

@tikvahethiopia
🇪🇹 #NationalDialogue 🇪🇹

➡️ " በሃገራዊ ምክክሩ #ሁሉም አካላት ካልተሳተፉ ምክክሩ ውጤት ላያመጣ ይችላል " - የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት

➡️ " ያኮረፉ እና ጫካ የገቡ #ታጣቂዎች በምክከሩ እንዲሳተፉ ከሲቪል ማህበረስብ  እና ከተለያዩ ሀገራት #ኤምባሲዎች ጋር እየሰራን ነው " - ኮሚሽኑ

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት እየተደረጉ ያሉ ግጭቶች ቆመው ሁሉም አካላት ወደ ንግግር አንዲመጡ ጠይቋል

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጫካ የሚገኙት ታጠቂዎች በምክክሩ ላይ እንዲሳተፉ ከለላ እንዲደረግላቸው መንግስትን የመጠየቅ ፍላጎት እንዳለው ገልጿል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ሰብሳቢ ደስታ ዲንቃ " በሃገራዊ ምክክሩ ሁሉም አካላት ካልተሳተፉ ምክክሩ ውጤት ላያመጣ ይችላል " ብለዋል፡፡

በጫካ ያሉ ታጣቂዎች በምክክሩ አንዲሳተፉ ለዚህ ሁኔታዎች እንዲመቻቹ  ምክር ቤቱ የጠየቀ ሲሆን ፥ " ይህ ካልሆነ ግን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ስራ ውጤት ላያመጣ ይችላል " ሲል የጋራ ም/ቤቱ ስጋቱን ተናግሯል።

#ሌላው_ስጋት ብሎ ያነሳው ደግሞ የምክክር ኮሚሽኑ የተቋቋመበት አዋጅ  ግጭቶችን የማስቆም ሃላፊነት አልተሰጠውም ግጭት ሳይቆም በግጭት ውስጥ የሚደረግ ምክክር ደግሞ ውጤት ላያመጣ ይችላል ብሏል፡፡

የጋራ ም/ቤቱ ከጅምሩ ጀምሮ " በምክክሩ አንሳተፍም " ያሉ ፓርቲዎችን፣ በተለያየ ክልሎች ያሉ ታጣቂዎች በምክክሩ እንዲሳተፉ እንዲደርግ ኮሚሽኑን ጠይቋል፡፡

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት ዶክተር ዮናስ አዳዬ ምክክሩ አሳታፊ እንዲሆን፣ ያኮረፉ እና ጫካ የገቡ ታጣቂዎች በምክከሩ እንዲሳተፉ ከሲቪል ማህበረስብ  እና ከተለያዩ አለም ሀገራት ኤምባሲዎች ጋር እየሰራን ነው ሲሉ ተናግረዋል።

" ጫካ የገቡ አካላት በምክክሩ እንዲሳተፉ በመገናኛ ብዙሃን ተደጋጋሚ ጥሪዎችን እያደረግን ነው " ያሉት ዶ/ር ዮናስ " ሕጋዊ የሆነ መስሪያ ቤት ስለሌላቸው ጥሪ ለማድረግ ተቸግረናል፣ እዚህ ነን  አለን የሚሉ ከሆነ የተመካከሩ ጥሪ ወረቀት ይዘን ለመሄድ ዝግጁ ነን " ብለዋል፡፡

Credit - Sheger FM 102.1

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#እንድታውቁት #AddisAbaba በመንገድ ኮሪደር ልማትና በአስፓልት የማንጠፍ ስራ ምክንያት ከመስቀል አደባባይ ወደ ቦሌ አየር መንገድ የሚወስደው ዋናው መንገድ በከፊል ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ መዚህ መሰረት ፡- - ከለገሐር በመስቀል አደባባይ ወደ ቦሌ አየር መንገድ - ከእስጢፋኖስ በቀጥታ ወደ ቦሌ አየር መንገድ - ከኡራኤል በመስቀል አደባባይ ወደ…
#EthiopianAirlines

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለበረራ ኤርፖርት የሚመጡ ሁሉ የመንገድ መዘጋቱን ታሳቢ እንዲያደርጉ አሳሰበ።

የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ በመንገድ ኮሪደር ልማትና የአስፓልት ንጣፍ ስራ ምክንያት ወደ ቦሌ ዓለም-አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የሚወስዱ አንዳንድ መንገዶች በከፊል ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድም መንገደኞች ለበረራ ወደ ኤርፖርት በሚሄዱበት ወቅት ይህን ታሳቢ በማድረግ ሊከሰት ከሚችል መዘግየት ራሳቸው እንዲጠብቁ አሳስቧል።

የሚዘጉት መንገዶች #የትኞቹ_ናቸው ? በዚህ ሊንክ ይመልከቱ ፦ https://www.tg-me.com/tikvahethiopia/88048

#EthiopianAirlines

@tikvahethiopia
#OROMIA #PEACE

" የመንግሥት ወታደሮች ፣ ሌላም ፣ ንጹሃንም ዋጋ መክፈል የለባቸውም፤ ... ለሰላም ክፍት ነን ድርድሮችም እንዲቀጥሉ እንፈልጋለን " - የኦሮሚያ ክልል መንግሥት

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አሁንም ቢሆን ያሉ ችግሮች #በሰላም እንዲፈቱ መንግሥት #ለድርድር ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል።

የክልሉ መንግሥት አመራሮች ከኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጋር በአዲስ አበባ እንደመከሩ ተነግሯል።

በምክክሩ ላይ የተገኙት የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዜዳንት እና የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ታፈሰ ውይይቱ ልማትና ጸጥታ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ሲሉ ለቪኦኤ ተናግረዋል።

በውይይቱ ፦

- የልማት ስራ ያለ ሰላም ውጤት አልባ እንደሆነ / ሰላም ለሁሉም ነገር መሰረት እንደሆነ ፤

- ሰው ሰርቶ የሚበላው ፣ ወልዶ የሚስመው ሰላም ሲኖር እንደሆነ አጽንኦተ ተሰጥቶበታል ብለዋል።

" ሰላም ለመንግሥት ብቻ የተተወ ስላልሆነ እንዴት ነው አብሮ መስራት የሚቻለው ? " የሚለውም መነሳቱን አስረድተዋል።

" መንግሥት እና ሸኔ የጀመሩት ድርድር ፤ በተለያየ ምክንያት አኩርፈው ጫካ የገቡ ነፍጥ ያነገቡ ጓዶች አሉ ፤ መንግሥት በሆደ ሰፊነት ዛሬ ነገ ሳይል እነዚህን አካላት ጠርቶ በጠረጴዛ ዙሪያ መነጋገር አለበት ይህ ሲደረግ ደግሞ ለሰዎቹ እውቅና ተሰጥቶ የህግ ከለላ ተሰጥቶ ነው ውይይት መደረግ ያለበት " የሚለውም መነሳቱን ገልጸዋል።

" በመንግሥት በኩል ' ዛሬም ቢሆን ክፍት ነው እንነጋገራለን ፣ ችግሮችን በጋራ ተነጋግረን እንፈታለን ' የሚል ምላሽ ነው የተሰጠን " ሲሉ ተናግረዋል።

የኦሮሚያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ አሁንም ቢሆን የክልሉ መንግሥት በውይይት ያምናል ብለዋል።

" የመንግሥት ወታደሮች ፣ ሌላም ፣ ንጹሃንም ዋጋ መክፈል የለባቸውም፤ ሙሉ ትኩረታችን ወደ ሰላም ማምጣት ነው ያለብን። የፈለግነውን ነገር በአዳራሽ መወያይት ይቻላል። ጥረቶች ብዙ ነው ያደረግነው አሁንም ለሰላም ክፍት ነን እኛ 3ኛ ዙር ይሁን፣ 5ኛ ዙር ይሁን ፣ 10ኛ ዙር ድርድሮች እንዲቀጥሉ እንፈልጋለን " ብለዋል።

#Ethiopia
#Oromia #VOA

@tikvahethiopia
2024/09/27 23:27:57
Back to Top
HTML Embed Code: