Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
" የሃይማኖት ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ ምን ይዟል ? በኢትዮጵያ አዲስ የተዘጋጀ " #የሃይማኖት_ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ አለ። ይህ ረቂቅ አዋጅ በርካታ ጉዳዮችን ይዟል። አንዱ የአምልኮና የመቃብር ቦታን የተመለከተ ሲሆን ፥ ረቂቅ አዋጁ ለሃይማኖት ተቋማት የመሬት አቅርቦት በመሬት አጠቃቀምና የሊዝ ሕጎች መሠረት ይወሰናል ይላል። ለአምልኮ ወይም ለመቃብር ቦታ በተጠየቀበት አካባቢ ለሃይማኖት ተቋሙ ለተመሳሳይ…
#ኢትዮጵያ

በሀገሪቱ ውስጥ ያለ ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርቱን ለሰላም ሚኒስቴር ማቅረብ እንደሚኖርበት ፤ ከውጭ አገር የሚመጣ የገንዘብ ዕርዳታ በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

" የሃይማኖት ጉዳዮች አዋጅ " የተሰኘው ረቂቅ አዋጁ የሃይማኖት ተቋማቱ ተቀባይነት ያለው የሒሳብ አያያዝና የኦዲት ሥርዓት መዘርጋት እንደሚኖርባቸው፣ የኦዲት ሪፖርታቸውን ለሰላም ሚኒስቴር ማቀረብ እንዳለባቸው ይደነግጋል፡፡ 

ረቂቅ አዋጁ ምን ይዟል ?

- የሃይማኖት ተቋማት የሚጠቀሙት የሒሳብ አያያዝ ሥርዓት የገቢ፣ የወጪና አጠቃላይ የንብረት ዝርዝር የያዘ መሆን አለበት።

- የገቢ አሰባሰብና የወጪ አስተዳደር በሕጋዊ መንገድ ማከናወን አለባቸው።

- የሃይማኖት ተቋም በራሱ #የገቢ_ማስገኛ ሥራዎችን በሚያከናውንበት ጊዜ ለዚሁ ሥራ ሲባል የተለየ የባንክ ሒሳብ መክፈትና የተለየ መዝገብ መያዝ አለበት።

- ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ከውጭ የሚላክለትን የገንዘብ ዕርዳታ፣ ስጦታ ወይም ሌሎች የገንዘብ ድጋፎችን በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ አለበት። ሲያሳውቅም ፦
° የለጋሹን ድርጅት ወይም ግለሰብ ስም እና አድራሻ፣
° የተለገሰው የገንዘብ፣ ስጦታ ዓይነት እና መጠን ፣
° ስጦታው / ድጋፉ የተሰጠበት ልዩ ዓላማ መካተት አለበት።

- ማንኛውም  የሃይማኖት ተቋም  የበጀት ዓመቱ ባለቀ በ3 ወር ውስጥ የፋይናንስ እንቅስቃሴውን በገለልተኛ ኦዲተር ማስመርመር አለበት። የኦዲተሩን አቋም እና የውሳኔ ሐሳብም መያዝ ይኖርበታል።

- የሰላም ሚኒስቴር የደረሰውን የኦዲት ሪፖርት አመቺ በሆነ መንገድ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ ይኖርበታል።

#ሪፖርተርጋዜጣ

@tikvahethiopia
🇪🇹 #NationalDialogue 🇪🇹

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከግንቦት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ የምክክር ምዕራፉን ይጀምራል።

ለ7 ቀናት ያህል በሚቆየው የአዲስ አበባው ምክክር ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከ2 ሺህ በላይ ሰዎች እንደሚሳተፉ ኮሚሽኑ ገልጿል።

በምክክሩ የውይይት የአጀንዳ ሀሳቦችን የሚያመጡ ለምክክሩ የሚቀርቡ ተሳታፊዎች ሲሆኑ ፤ እነዚሁ ተሳታፊዎች በተስማሙባቸው የጋራ አጀንዳዎች ላይ የመፍትሔ ሀሳቦችን እንደሚያቀርቡ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አመልክቷል። #DW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ትግራይ

በትግራይ፣ መቐለ የሚገኘው ፍሬምናጦስ የአረጋውያን ፣ የአእምሮ ህሙማንና የህፃናት እንክብካቤ ማእከል ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ሚገመት የገንዘብ የቁሳቁስ ድጋፍ ቃል ተገባለት።

ይህን የገንዘብና የአይነት ድጋፍ ቃል የተገባለት ትላንት " #አለሁ_ለፍሬምናጦስ " በሚል በመቐለ ከተማ በተካሄደ ዓለም አቀፍ የሆነ የገቢ ማሳባሰብያ የቴሌቶን ፕሮግራም ላይ ነው።

መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጅነሪንግ የተባለ የትእምት ኩባንያ በምግባረ ሰናይ ደርጅቱ ላክ በባለፈው ሚያዝያ ወር በተነሳ የእሳት ቃጠሎ የወደመውን አዳራሽ ሙሉ ለሙሉ መልሶ እንደሚገነባው ቃል ገብቷል።

ከዚህ በተጨማሪም የ20 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው የጭነት መኪና፣ አምቡላንስ የምግባረ ሰናይ ድርጅቱ ለሚያሰገነባው ግዙፍ የእንክብካቤ ማእከል የሚውሉ ማሽነሪዎች በአገር ውስጥና በውጭ በጎ ለጋሾች ተበርክቷል።

የምግባረ ሰናይ ድርጅቱ መስራችና ስራ አስኪያጅ አባ ገብረ መድህን በርሀ ፥ " ጦርነት በፈጠረው ጉዳት ምክንያት #የአእምሮ_ህሙማን_ቁጥር በመጨመር ላይ በመሆኑ ድርጅቱ ለሚሰጠው የነፃ እንክብካቤ አገልግሎት የህዝቡ እገዛ ይሻል " ብለዋል።

ፍሬምናጦስ የአረጋውያን የአእምሮ ህሙማን የህፃናት እንክብካቤ ማእከል በአሁኑ ወቅት 29 አረጋውያን ፣ 206 የአእምሮ ህሙማን እና 40 አሳዳጊ የሌላቸውን ህፃናት ጨምሮ በአጠቃላይ #ከ275_በላይ ለሆኑ ወገኖች የተሟላ የመጠለያ አገልግሎት በመስጠትና በመንከባከብ ላይ ይገኛል። 

በትግራይ በነበረው አስከፊ የሆነ ጦርነት ምክንያት ግን ወደ ማዕከሉ መግባት የሚፈልጉ ወገኖች ቁጥር በእጅጉ ጨምሯል።

ለማሳያ ባለፉት ወራት ብቻ 1500 የእእምሮ ህሙማን ወደ ማእከሉ ለመግባት መመዝገባቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከምግባረ ሰናይ ድርጅቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። 

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
የሕብረት ባንክ ማህበራዊ ገፆቻችንን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!

ቴሌግራም: https://www.tg-me.com/HibretBanket
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/HibretBank
ሊንክዲን: https://www.linkedin.com/company/hibretbank/
ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/hibretbank/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@hibretbanket

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ወንጀል ችሎት እነ ቀሲስ በላይ መኮንን ፖሊስ ጣቢያ እንዲቆዩ አዟል። በዋስ ጥያቄያቸው ዛሬም ውድቅ ተደርጓል። ቀሲስ በላይ መኮንን በችሎቱ ፥ " ፖሊስ ይዞኝ ሳይሆን እራሴ ነው የሄድኩት " ብለዋል፡፡ " #ብዙ_የሀገር_ጉዳይ በእጄ ስላሉ ጥፋ ብባል እንኳ የምጠፋ ስላልሆንኩ ፤ በጤናዬ ላይ በደረሰው እክልና በቤተሰቦቼ ላይ በደረሰው…
#Update

ከ 'አፍሪካ ህብረት' የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ በ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር የምዝበራ ሙከራ የተከሰሱት እነ ቀሲስ በላይ የጠየቁት ዋስትና ውድቅ ተደርጓል።

ጥያቄውን ውድቅ ያደረገው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።

ከምዝበራ መኩራው ጋር በተያያዘ የተከሰሱት ፦

1ኛ. ቀሲስ በላይ መኮንን፣
2ኛ. በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው እያሱ እንዳለ ወ/መስቀል፣
3ኛ. በኮሚሽን ስራ ላይ የተሰማራው በረከት ሙላቱ ጃፋር፣
4ኛ. አለምገና ሳሙኤል ዲንሳ
5ኛ. የኒሞና ንግድ ስራ ኃላ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አበራ መርጋ ተስፋዬ ናቸው።

ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያሉ ተከሳሾች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር።

ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄም ውድቅ ተደርጎ በማረፊያ ቤት እንዲቆዩ ታይዟል።

ፍርድ ቤት ለግንቦት 29/2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

በዛሬ ችሎት ተጠርጣሪዎች የተከሰሱበት አዋጅ ከ10 ዓመት በላይ የሚያሳስርና ከባድ ፍርድ የሚያስከትል በመሆኑ ማረሚያ ወርደው ፍርዳቸውን ይከታተሉ ተብሏል።

ቀሲስ በላይ #የጤና_እክል እንዳለባቸው ጠቅሰዋል። በፌደራል ፖሊስ ጊዜያዊ ማቆያ ለመቆየት እንዲችሉ እንዲፈቀድላቸውም ጠይቀዋል።

ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የተወከለ መርማሪ የጊዜያዊ ማቆያው ቦታ ጥበት መኖሩን ጠቅሶ ወደ ማረሚያ ቤት እንዲወርዱ እንዲደረግ ጠይቋል።

ፍርድ ቤቱ እስከ ቀጣይ ቀጠሮ ግንቦት 29 ቀን ድረስ ባሉበት የፖሊስ ማረፊያ እንዲቆዩ ፈቅዷል።

4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት የፌደራል ፖሊስ ተገቢ ጥረት አድርጎ አፈላልጎ እንዲያቀርባቸው ታዟል።

መረጃው ከኤፍቢሲና ዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ የተወሰደ ነው።

https://telegra.ph/fbc-05-27-2

@tikvahethiopia
#ቦይንግ

ቦይንግ የአፍሪካ ዋና መሥሪያ ቤቱን በአዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ እንደሚከፍት ማስታወቁ ተዘግቧል።

ውሳኔው ግዙፉ የኤሮስፔስ ኩባንያ ቦይንግ፤ በአፍሪካ ላቀደው የማስፋፊያ ስራ ኢትዮጵያ ከኬንያ እና ደቡብ አፍሪካ እንድትቀድም አድርጓታል።

ይህም ደግሞ ኬንያ ወይም ደቡብ አፍሪካ የቦይንግ የማስፋፊያ ቦታዎች ይሆናሉ የሚለውን ግምት ውድቅ አድርጓል።

እ.ኤ.አ. በ2023 ላይ ኢትዮጵያ እና ቦይንግ አንዳንድ የአውሮፕላን ክፍሎችን በኢትዮጵያ ለማምረት የጋራ ስምምነት አድርገዋል።

ቦይንግ በድረ-ገፁ ላይ እንዳሰፈረው " የአፍሪካ ዕምቅ የተፈጥሮ ሀብት እና እያደገ የመጣው ወጣት የሰው ሃይል በሚቀጥሉት ሁለት አስርተ ዓመታት ውስጥ በአየር ትራፊክ እና በአውሮፕላን ፍላጎት ላይ ከፍተኛ እድገት ያመጣል " ብሏል።

ቦይንግ ኩባንያ ፥ የአፍሪካውያን የመጓጓዣ አገልግሎት በሚቀጥሉት 20 ዓመታት ከ1,000 በላይ አዳዲስ ጄት አውሮፕላኖችን እንደሚፈልጉ ገምቷል።

ከእነዚህ ውስጥ 80% ነባር አውሮፕላኖችን ለማስፋት ያለመ እንደሆነ DW Africa ዘግቧል።

@tikvahethiopia
የግንቦት 2016 ዓ.ም የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ #ረቡዕ ይከፈታል።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በዓመት ሁለት ጊዜያት ከሚካሔዱት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤያት አንዱ የግንቦት 2016 ዓ.ም የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ነው፡፡

ይህ ጉባኤ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ርእሰ መንበርነት ረቡዕ ግንቦት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ከጧቱ 2፡30 ሰዓት ጀምሮ በመንበረ ፓትርያርክ የቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ እንደሚከፈት ተገልጿል።

@tikvahethiopia
#ግንቦት20

ነገ የደርግ መንግሥት የወደቀበት የግንቦት 20 በዓል ይከበራል።

በዓሉ በተለይ ኢህአዴግ ስልጣን ላይ በነበረበት ዓመታት በሀገር ደረጃ ስራ እና ትምህርት ተዘግቶ በድምቀት ሲከበር ቆይቷል።

ካለፉት 6 ዓመታት ወዲህ ግን በዓሉ የነበረውን ድምቀት አጥቶ ተቀዛቅዟል። ያም ቢሆን ግን የተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በዕለቱ ዝግ ይሆናሉ።

የዘንድሮው የግንቦት 20 በዓልስ ?

በቅርቡ ይፋ የተደረገው እና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ገና ያልጸደቀው " የሕዝብ በዓላት እና የበዓላት አከባበር ረቂቅ አዋጅ " ተከብረው በሚውሉ ብሔራዊ ባላት ውስጥ ግንቦት 20ን አላካተተም።

በእርግጥ አሁን ላይ ባለውም አዋጅ ሳይካተት እንደ ብሔራዊ በዓል ሲከበር ነው የቆየው።

በዓሉ በሕግ በዓልነቱ ታውቆ አከባበሩም ተዘርዝሮ ያልወጣ ቢሆንም እንደ ብሔራዊ በዓል ሲከበር ቆይቷል ፤ በዕለቱም ሰራተኞች የእረፍት ጊዜ ያገኛሉ።

ከዚህ በተያያዘ በርካቶች " ስለ ነገው በዓል ግልጽ ይሁንልን " ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ጉዳዩ ይመለከታቸዋል ብሎ ያሰባቸውን አካላት " ነገ ግንቦት 20 ስራ ተዘግቶ ነው የሚውለው ? "  ሲል ጠይቋል።

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የመንግስት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " አዲሱ የበዓላት ሕግ ገና አልጸደቀም፤ ስለዚህ ዝግ ነው " ሲሉ አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

በተጨማሪም " ነገ በሚከበረው የግንቦት 20 በዓል መስሪያ ቤት ዝግ ነው ወይስ ክፍት ? " ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ከበደ ደሲሳ ጥያቄ አቅርቦላቸዋል።

እሳቸውም ፤ " በካላንደር ላይ የተለወጠ ነገር ስለመኖሩ እርግጠኛ አይደለሁም። ካላንደር ይዘጋዋል " ብለዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው፣ " ካላንደር እንደሚዘጋው ነው የምናውቀው ለምን እንዳወዛገበ አይገባኝም " ሲሉ አክለዋል።

አንዳንድ መስሪያ ቤቶች ሠራተኞች ሥራ እንዲገቡ ጠርተዋል መጥራት ይችላሉ ? ለሚለው ጥያቄ በሰጡት ምላሽም ፣ " መስሪያ ቤቶች በራሳቸው ውሳኔ ሥራዎችን ሊያቅዱ ይችላሉ። ከሠራተኞቻቸው ጋር ተስማምተው " ብለዋል።

አክለው " መጥራት ይችላሉ ማን ይከለክላቸዋል። አብዛኞቻችን ሥራ የምንውልበት ጊዜ ይኖራል። ያ ማለት ግን ያንን አፍርሰው ሳይሆን መስሪያ ቤቶች፣ ሠራተኞች በፈቃዳቸው ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

" እሁድም እኮ ሠራተኛ የምናስገባበት ወቅት አለ። እንጂ ከዚያ ያለፈ የተለዬ ነገር የለም " ነው ያሉት።

በሌላ በኩል ፥ የአሜሪካ ኤምባሲ ነገ የደርግ መንግሥት የወደቀበትን #የግንቦት_20 በዓል ምክንያት በማድረግ ሙሉ ቀን ስራ ዝግ ሆኖ እንደሚውል አሳውቋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
የሕዝብ_በዓላት_እና_የበዓላት_አከባበር_ረቂቅ_አዋጅ_.pdf
420.3 KB
" የሕዝብ በዓላትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን የተዘጋጀ ረቂቃ አዋጅ " ምን ይዟል ?

የሚከተሉት በዓላት በሀገርአቀፍ ደረጃ ተከብረው የሚውሉ ብሔራዊ በዓላት ናቸው ፡-

1. መስከረም አንድ ቀን የዘመን መለወጫ (እንቁጣጣሽ) በዓል
2. የካቲት ሃያ ሶስት ቀን የአድዋ ድል በዓል
3. ሚያዚያ ሃያ ሶስት ቀን የዓለም የሠራተኞች (የላብአደሮች) ቀን
4. ሚያዚያ ሃያ ሰባት ቀን የአርበኞች (የድል) ቀን በዓል

በተጠቀሱት ብሔራዊ በዓላት የመንግስት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ ይሆናሉ፡፡

የሚከተሉት በዓላት በሀገርአቀፍ ደረጃ ታስበው የሚውሉ ብሔራዊ በዓላት ናቸው ፡-

1. የካቲት አስራ ሁለት ቀን የሰማዕታት ቀን
2. ሕዳር ሃያ ዘጠኝ ቀን የኢትዮጵያ ህብረ-ብሄራዊነት (የብሔር ብሔረሰቦች) ቀን

በተጠቀሱት ብሔራዊ በዓላት የመንግስት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት ይሆናሉ፡፡

የሚከተሉት በዓላት በሀገርአቀፍ ደረጃ የሚከበሩ ኃይማኖታዊ በዓላት ናቸው ፡-

1. መስከረም አስራ ሰባት ቀን የመስቀል በዓል
2. በየአራት አመቱ የሚመጣው ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ ታህሳስ ሃያ ዘጠኝ ቀን የሚውለው የገና ወይም የልደት በዓል
3. ጥር አስራ አንድ ቀን የጥምቀት በዓል
4. የስቅለት በዓል
5. የትንሳኤ (ፋሲካ) በዓል
6. የኢድ-አልአድሃ (አረፋ) በዓል
7. የመውሊድ በዓል
8. የኢድ አልፈጥር በዓል

በተጠቀሱት ኃይማኖታዊ በዓላት የመንግስት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ ይሆናሉ።

⚠️ ይህ ገና ረቂቅ አዋጅ ሲሆን ገና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት #አልጸደቀም። ረቂቅ አዋጁ በም/ቤት ሲጸድቅና በነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከሚወጣበት ቀን ጀምሮ ነው የጸና የሚሆነው።

ከላይ በተያያዘው ፋይል ሙሉውን ያንብቡ።

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#መቐለ

ከሳምንት በፊት " በአፈልጉን ማስታወቅያ "  ስትፈለግ የሰነበተች ተማሪ በውሃ ጉድጓድ ውስጥ ሞታ ተገኘች።

ተማሪ ቤቴልሄም ገብረሚካኤል ነጋሽ ግንቦት 11 ቀን 2016 ዓ/ም ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ላይ ነው በመቐለ ከተማ ፤ ዓዲ ሓቂ ክፍለ ከተማ ዓዲ ሓውሲ ቀበሌ ከሚገኝ ቤትዋ እንደወጣች የቀረችው።

ዛሬ ግንቦት 19 ቀን 2016 ዓ/ም ግን አስክሬኗ ደብሪ ቀበሌ ጨለዓንቋ ተብሎ በሚታወቅ ኩሬ ተጥሎ መገኘቱ ተገልጿል።

የ17 ዓመትዋ ተማሪ ቤቴልሄም በመቐለ የቀላሚኖ ልዩ ትምህርት ቤት የ10ኛ ክፍል ተማሪ የነበረች ስትሆን ከአንድ ሳምንት የአፋልጉን ጥሪ በኋላ በውሃ ጉድጓድ አስክሬኗ ተጥሎ መገኘቱ ብዙዎችን አስደንግጧል፤ አሳስዝኗል።

የተማሪዋ አስክሬን በፓሊስ ትእዛዝ ወደ ዓይደር ሪፈራል ኮምፕሬሄንሲቭ ሆስፒታል ተወስዶ ከተመረመረ በኋላ አመሻሽ በመቐለ አቡነ አረጋዊ ቤተክርስትያን በክብር እንዲያርፍ ተደርጓል።

በቀብር ስነሰርዓቱ ላይ ቤተሰቦች፣ የቀላሚኖ ትምህርት ቤት ኮሙዩኒቲ ፣ ወዳጆች እና አብሮ አደጎችን ጨምሮ በርካታ ህዝብ በመገኘት የተሰማው ጥልቅ ሃዘን በእንባ በመታጀብ ገልጿል።

በቀብር ስርዓቱ ላይ የተገኘው ህዝብ ፍትህ ጠይቋል።

የአሟሟትዋ ጉዳይ እጅግ በጣም ያሳዘናቸው የተለያዩ የህብረተሰብ አካላት ወንጀሉ ተጣርቶ ወንጀለኞች ወደ ህግ እንደዲቀርቡ ጠይቀዋል።

ፖሊስ በጉዳዩ ላይ የሚሰጠው ዝርዝር ማብራሪያ ካለ ተከታትሎ እንደሚልክ የመቐለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
#Abyssinia_Bank

የሐጅ አካውንት በመክፈት ለታላቁ መንፈሳዊ ጉዞ ራስዎን በፋይናንስ ማዘጋጀት እንደሚችሉ ያውቃሉ? በአቢሲንያአሚን የሐጅ ኒያዎትን ያሳኩ! 

አቢሲንያ አሚን ዕሴትዎን ያከበረ!


#የሐጅኒያ  #የሐጅጉዞ #አቢሲኒያአሚን
#AbyssiniaAmeen #IFB #bankofabyssinia
#Banking #BanksinEthiopia  #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
2023.pdf
3.9 MB
#ሪፖርት

የሀገራትን የረሃብ ደረጃ የሚለካው የረሀብ ኢንዴክስ (GHI) ሪፖርት ይፋ ተደርጓል።

በዚህም #ኢትዮጵያ 26.2 በመቶ በማስመዝገብ ከ125 ሀገራት ከመጨረሻዎቹ 101ኛ ደረጃን ይዛለች።

ኢትዮጵያ በ2022 ለይ ከ121 ሀገራት ውስጥ በ27.6 በመቶ በማስመዝገብ 104ኛ ደረጃም ይዛ ነበር።

በ2023 ሪፖርት የረሃብ ልኬቱ ቀንሶ 26.2 በመቶ ተሰጥቷታል።

ሪፖርቱ በየዓመቱ ይፋ የሚደረግ ነው።

በዚህ ጥናት ላይ የሀገራትን ደረጃ ለመስጠት ከሚዳሰሱ ዋና ዋና መሰረታዊ የሚባሉ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ፤ ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሕፃናት የምግብ እጥረት ፣ ሞትና የምግብ አቅርቦት ዋነኞቹ ናቸው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
2023.pdf
#ETHIOPIA

' አልያንስ 2015 ' የተባለው 8 የአዉሮጳ የልማት ድርጅቶች ያቀፉት ተቋም ሀገራት ያሉበትን የረሃብ አደጋ ደረጃ የሚያመላክተውን የዓለም አቀፍ የረሃብ ኢንዴክስ (Global Hunger Index) ይፋ አድርጓል።

በዚህ የረሃብ መለኪያ ሪፖርት ከ125 ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ከመጨረሻዎቹ 101ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።

የሰቆጣ ቃልኪዳን የፕሮግራም አስተባባሪ ዶክተር ሲሳይ ሲናሞ ምን አሉ ?

- ሪፖርቱ ሲዘጋጅ ሀገራት ካሉበት ደረጃ አንጻር የተለያየ ደረጃ ይሰጣቸዋል።
- የረሃብ ደረጃው ባለፉት 20 ዓመታት በተሰሩት ስራዎች ከ53 በመቶ ወደ 26.1 በመቶ ዝቅ ብሏል። በጣም alarming ከነበረበት ወደ serious ደረጃ ነው የወረደው።
- አሁንም ብዙ ስራ ይቀራል።
- በሀገራችን ያለው የምግብ እና የስርዓተ ምግብ ሁኔታ ብዙ መሰራት አለበት።
- ሪፖርቱ በየዓመት ነው የሚወጣው። በቀጣይ ወጣቶችን ማዕከል ባደረጉ ስራዎች ትኩረት በማድረግ ለመስራት ያለው ሁኔታ ለማሻሻል ይረዳል።
- በአፍሪካ ያለው ከፍተኛ የወጣት ቁጥር በግብርናው ዘርፍ አሰማርቶ መጠቀም አለመቻል አፍሪካ በምግብ ራሷን እንዳትችል አድርጓል።
- ኢትዮጵያ ውስጥ 70 በመቶ የስራ እድል የሚመነጨው ከግብርና ሆኖ እያለ ያላደገው የግብርና ዘርፍ የሚፈለገውን ያህል የስራ እድል እንዳይፈጠር እንቅፋት ሆኗል።

እንደ ዓለም አቀፉ ሪፖርት በኢትዮጵያ እና በዓለም ዙሪያ ለታየው በምግብ እራስን ያለመቻል ችግር ፦
የአየር ንብረት ለውጥ
በየቦታው የሚደረጉት #ጦርነቶች
የኢኮኖሚ መላሸቅ
የኮሮና ወረርሽኝ ዋነኞቹ ናቸው።

በከፍተኛ የምግብ እጥረት እና በረሃብ አደጋ ውስጥ ላሉ ሀገራት መፍትሄ ተብሎ የተቀመጠው መንግሥታት ፦

° ትልቅ አቅም ያላቸው ወጣቶችን ወደ ስራ ገብተው ውጤት እንዲያመጡ ቦታ መስጠት፤

° ብድር ማመቻቸት፤

° ለስራ የሚሆኑ የተለያዩ ስልጠናዎች ማመቻቸት ይኖርባቸዋል  የሚሉት ይገኙበታል።

በግብርናው ዘርፍ ለመዘናት የቆየው በበሬ ማረስ ተግባር ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በማዘመን በመጠንም በአይነትም ከፍ ያለ ምርት ማምረት ካልተቻለ ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት አሳስቢ ደረጃ ወደ መጨረሻው አስከፊ ደረጃ ልትደርስ ትችላለች ሲል ሪፖርቱ አስጠንቅቋል።

⚠️ ኢትዮጵያ በ2022 ሪፖርት ላይ 27.6 በመቶ በማስመዝገብ ከ121 ሀገራት 104ኛ ደረጃ ላይ ነበረች።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የዚህ መረጃ ምንጮች ፦ ሸገር ኤፍ ኤም ፣  የAlliance 2015 እና የGlobal Hunger Index ድረገጽ መሆናቸውን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
“ ልጅ ያለው የልጅን ነገር ያውቀዋል። ቶሎ ካልታከመች ክፍተቱ እየጨመረ ነገሮች ሁሉ ይከብዳሉ ” - የ9 ዓመቷ ታዳጊ እናት ልጃቸው ለየልብ ህመም የታመመችባቸው እናት ደጋግ ኢትዮጵያውያን እንዲያግዟቸው ተማጽኑ። ወ/ሮ መባ አላምረው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ሊያ የ3ኛ ክፍል ተማሪ 2ኛ ልጄ ናት። #ልቧ 15 ሚሊ ሜትር #ክፍተት አለው ” ብለዋል። የልብ ስፔሻሊቲ ዶክተርም፣ “ ‘ችግሩ ክፍተት…
#ተመስግናችኃል🙏

ከሳምንታት በፊት ' የልብ ክፍተት ' ችግር ስላለባት እና በአስቸኳይ መታከም ስላለባት የ9 ዓመቷ ብላቴና ሊያ የእገዛ መልዕክት ወደናተ ደርሶ ነበር።

በወቅቱም እናቷ ወ/ሮ መባ አላምረው ለህክምና 700 ሺ ብር መጠየቁን በመግለጽ አቅም ያለው ኢትዮጵያዊ ወገን ልጃቸውን ለመታደግ ትብብር እንዲያደርግላቸው ተማጽነው ነበር።

አሁን ላይ ጉዳዩ ከምን ደረሰ ? ስንል ጠይቀናል።

እናት ወ/ሮ መባ አላምረው ትላንትና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ “ እናንተ ልበ ቀናዎች ባደረጋችሁት ድጋፍ ጭምር የልጄ ሰርጀሪ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል ” ሲል መልካም ዜና አሰምተዋል።

ወ/ሮ መባ በሰጡት ቃል ፦

“ አሁን በጥሩ ጤንነት ላይ ትገኛለች። ከ4 ቀናት ቆይታ በኋላ፣ እሁድ ግንቦት 18 ቀን 2016 ዓ/ም ወደ ቤቷ ገብታለች። ሰርጀሪዋ በጣም ውጤታማ እንደሆነ ዶክተሯ ነግሮኛል።

እናተን እንድገናኝ የረዳኝን ሀይሌ ከፍያለው ከፈረንሳይ እንዲሁም ዶክተር ፈቀደ አግዋር ፈጣሪ እድሜ ያድልልኝ።

#መላው_ኢትዮጵያውያን ፣ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ማመን በማልችለው ፍቅር እና በፈጣን ምላሽ በአጭር ቀን ውስጥ ልጄ ህክምና እንድታገኝ አግዛችሁኛል። 

ቤተሰቦቼ ፣ ወዳጆቼ በሙሉ እርዳታችሁ ለዚህ ቀን ለማመስገን አድርሶኛል።

አሁንም ፀሎታችሁ አይለየኝ። አመሰግናለሁ ! ” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
(ኢትዮ ቴሌኮም)

እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን!

ቴሌብር በዲጂታል ሥነ-ምህዳሩ ላይ በነበረው የላቀ አበርክቶ የስትራይድ አዋርድ 2024 ኢኮሲስተም ሻምፒዮን  (Stride Award 2024 Ecosystem Champion) ተሸላሚ ሆነ!

የሽልማት መርሃግብሩን ያዘጋጀው የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሲሆን ኩባንያችን የዲጂታል ኢትዮጵያን ከመገንባት አንጻር በተለይም ለሀገራችን የዲጂታል ፋይናንስ መነቃቃት ላበረከተው የላቀ አስተዋጽዖ እውቅናው መበርከቱ ተገልጿል፡፡

ለዚህ ሽልማት ላበቃችሁን ለመላው የኩባንያችን ቤተሰቦች፣ ደንበኞቻችን፣ ባለድርሻ አካላት እና አጋሮቻችን ከልብ እናመሰግናለን!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #SmartAfrica #GSMA #ITU
2024/09/27 21:29:57
Back to Top
HTML Embed Code: