Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ የ2017 ዓ/ም የመስቀል ደመራ በዓል አከባበር በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ። #ኦርቶዶክስተዋሕዶ @tikvahethiopia
#Ethiopia

" በ2,575 የተለያዩ ደብሮችና ቦታዎች በሰላም ተከብሮ ተጠናቋል " - የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

በመላው ሀገሪቱ በተለይም #በአዲስ_አበባ መስቀል አደባባይ የተከበረው የ2017 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በሰላም መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አሳውቋል።

የፌዴራል ፖሊስ በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረገው ህዝብ ፣ ለሀይማኖት አባቶች ፣ ለበዓሉ አስተባባሪ ኮሚቴዎች ፣ ለወጣቶችና በተለይ ደግሞ  የተሰጣቸውን ግዳጅ በሚገባ ለተወጡት የፀጥታ እና ደኅንነት ኃይሎች ምስጋና አቅርቧል።

በሌላ በኩል ፤ የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ
የዘንድሮው የመስቀል ደመራ በዓል በመስቀል አደባባይ ጨምሮ በ2,575 የተለያዩ ደብሮችና ቦታዎች በሰላም ተከብሮ መጠናቀቁን አሳውቀዋል።

ከንቲባዋ ፥ " በዓሉ በድምቀት እንዲከበር አስተዋፅዖ ላደረጉ የሀይማኖት አባቶች ፣ የከተማው ወጣቶች ፣ ሲያስተባብሩ ለነበሩ በየደረጃው ያሉ አመራሮች እንዲሁም ዶፍ ዝናብ ሳይበግራቸው በዓሉ ደማቅ በሆነ መንገድ እንዲከበር ላደረጉ የጸጥታ ሃይሎችና የከተማው ነዋሪዎች ሁሉ በከተማ አስተዳደሩ ስም ምስጋና እናቀርበላ " ብለዋል።

#የኢትዮጵያኦርቶዶክስተዋሕዶቤተክርስቲያን
#Ethiopia #AddisAbaba

@tikvahethiopia
2024/09/27 07:30:28
Back to Top
HTML Embed Code: