Telegram Web Link
#ቀረጥ_ነጻ

ወደ አገር በሚገቡ እቃዎች ላይ ከተጣለው የማህበራዊ ልማት ቀረጥ ነጻ የሚሆኑ እቃዎችን ለመወሰን ገንዘብ ሚኒስቴር መመሪያ አውጥቷል።

ይኸው መመሪያ " መመሪያ ቁጥር 1023/2017 " ይሰኛል።

በዚህ መመሪያ መሰረት ፥ ለህብረተሰቡ በነጻ የሚሰጡ የትምህርት እና የጤና አገልግሎቶችን ለማስፋፋት እንዲሁም በሰው ሰራሽ እና በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ችግር ላይ የሚገኙ ወገኖችን ለመርዳት ከውጭ አገር በእርዳታ የሚላኩ እቃዎች የማህበራዊ ልማት ቀረጥ የተጣለበትን አላማ ለማሳካት የሚያግዙ በመሆኑ ከቀረጥ ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል።

ከማህበራዊ ልማት ቀረጥ ነጻ የተደረጉ እቃዎች ?

የሚከተሉት እቃዎች ከማህበራዊ ልማት ቀረጥ ነፃ ሆነው ወደ ሀገር ይገባሉ፡፡

1. ለሚከተሉት የማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ከውጭ አገር በእርዳታ የሚላኩ እቃዎች :-

ሀ/ በመንግስት ባለቤትነት ስር ያሉ ወይም ለህብረሰሰቡ ነጻ አገልግሎት የሚሰጡ :

- የትምህርት ተቋማት፣
- የጤና ተቋማት፣
- የሕጻናት፤ የሴቶች፤ የአረጋውያን፣ የአእምሮ ህመምተኞች እና የአካል ጉዳተኞች መርጃ ድርጅቶች

ለ/ በሰው ሰራሽ እና በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ለሚሰጡ ድርጅቶች ከውጭ አገር በእርዳታ የሚላኩ እቃዎች

2. ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ከቀረጥ እና ታክስ ነጻ ሆነው ወደአገር እንዲገቡ የተፈቀደ እቃዎች።

3. የአገር መከላከያ ሚኒስቴር፣ የፌዴራል እና የክልል ፖሊስ ተቋሞች፣ የብሔራዊ መረጃ እና ደሕንነት አገልግሎት እና ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በሕግ በተፈቀደው መሰረት ወደ አገር የሚያስገቧቸዉ የመከላከያ እና የህዝብ ደህንነት መሳሪያዎች፣ ለነዚሁ አገልግሎት የሚዉሉ ክፍሎችና እና አክሰሰሪዎች፡፡

4. በብሔራዊ ባንክ ወደ ሀገር የሚገቡ ሳንቲሞች፣ የገንዘብ ኖቶች እንዲሁም የብርና የወርቅ ጠገራዎች፡፡

ከቀረጥ ነፃ #የማይሆኑ እቃዎች ምንድናቸው ?

ከዚህ በታች የተዘረዘሩት እቃዎች ከማህበራዊ ቀረጥ ነጻ ሆነው ሊገቡ
#አይችሉም

ሀ/ ከ8 መቀመጫ በታች ያላቸው አውቶሞቢሎች  እና የእነዚህ መለዋወጫዎች።

ለ/ ባለአንድ ወይም ባለሁለት ጋቢና ፒካፕ ተሽከርካሪዎች እና የእነዚህ መለዋወጫዎች።

ሐ/ ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ ዕቃዎችና መሣሪያዎች።


በዚህ መመሪያ መሰረት ከቀረጥ ነጻ ሆነው ሊገቡ የሚችሉ እቃዎች ማስረጃዎች ማቅረብ የግድ ይላል።

ምን አይነት ማስረጃዎች መቅረብ አለባቸው ?

1. እቃዎቹ በእርዳታ የተገኙ መሆኑን የሚያረጋግጥ የእርዳታ የምስክር ወረቀት።

2. የእቃዎቹን ዝርዝር እና ዋጋ የሚያሳይ ኢንቮይስ፣

3. እቃዎቹ ለተገለጸው አላማ የሚውሉ መሆኑን እንዲሁም ስለእቃዎቹ አጠቃቃም ለገንዘብ ሚኒስቴር እና ለጉምሩክ ኮሚሽን ሪፖርት የሚቀርብ መሆኑ የሚያረጋግጥ አግባብ ባለው ከመንግስት መስሪያ ቤት የተጻፈ የድጋፍ ድብዳቤ።

#TikvahEthiopia #MinistryofFiance

@tikvahethiopia
Discover the unique opportunity to build a high-impact venture with the Jasiri Talent Investor Programme - Cohort 7!

This fully-funded 13-month program provides comprehensive support for aspiring entrepreneurs, including an introduction to understanding your 'why' and intensive residential training in Rwanda to help you dive deep into solving the problem you aim to address. You’ll also receive mentorship, coaching, and venture creation support.

Apply now and experience the difference!
👉🏾 https://bit.ly/3A8rxtV

For more information, Join our telegram channel 👉🏾 @Jasiri4africa
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡
- Tag ሲያደርጉን ለ Facebook @ TecnoEt ፣ ለ Instagram @ TecnoMobileEthiopia እና ለ TikTok @ TecnoEt ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።)
- በተጨማሪም #TecnoEt2017 ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update (No.9) በታጣቂዎች የታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከምን ደረሱ ? ሁለት አውቶብስ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ትምህርት አጠናቀው ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ በነበረበት ወቅት " ገርበ ጉራቻ " ላይ መታገታቸው ይታወሳል። የታገቱት ሰኔ 26/2016 ዓ/ም ረፋድ 4 ሰዓት ገደማ ሲሆን፣ ከታገቱ ወር አልፏቸዋል። ሁለት ታጋቾች 50 ሺህ እና 300 ሺህ ብር ከፍለው ከእገታ መለቀቃቸውን፣…
#Update (No.10)

“ ግማሽ፣ ግማሽ ሚሊዮን ብር ከፍለን ልጆቻችንን በገንዘባችን ገዝተናል፡፡ አሁንም ያልተለቀቁ ልጆች አሉ ” - የተማሪ ወላጆች

ትህምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ የነበሩ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ዓመት ሁለት አውቶብስ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በ“ሸኔ”
ታጣቂዎች እንደታገቱ የተሰማው ረቡዕ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም ነበር፡፡

ተማሪዎቹ የታገቱት “ገርበ ጉራቻ” የሚባል ቦታ ሲደርሱ ከጠዋቱ 4 ሰዓት ገደማ እንደነበር ከገለባ ክምር ተደብቆ ያመለጠ ተማሪ በወቅቱ ለቲክቫህ ኢትዮጰያ መግለጹ ይታወሳል፡፡

ከዚያ በኋላ ደግሞ 50 ሺሕ እና 300 ሺሕ ከፍለው የተለቀቁ ተማሪዎች እንዳሉ፣ ታጣቂዎች የጠየቁትን ገንዘብ ካልሰጡ ታጋች ተማሪዎቹን እንደማይለቋቸው በመግለጻቸው ወላጆች አቅም ስለሌላቸው ባነበር አሰርተው ለልማና አደባባይ ለመውጣት መገደዳቸውንም አሳውቀናችሁ ነበር፡፡

ከዚያ በዘለለም ከሳምንታት በፊት የተወሰኑ ተማሪዎች ገንዘብ ከፍለው ከእገታ መለቀቃቸውን አንድ ከእገታው ያመለጠ ተማሪ በቲክቫህ በኩል መግለጹ ይታወሳል፡፡

የታጋቾቹ ጉዳይ አሁንስ ከቶ ከምን ደረሰ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ካነጋገራቸው የታጋች ቤሰቦች መካከል በደቡብ ክልል የሚገኙት፣ “ ግማሽ፣ ግማሽ ሚሊዮን ብር ከፍለን ልጆቻችንን በገንዘባችን ገዝተናል፡፡ አሁንም ያልተለቀቁ ልጆች አሉ ” ብለዋል፡፡

በታጣቂዎቹ ታግተው የነበሩ የደቡብ ክልል ተማሪዎች ቤተሰብ የትም አምጥተው ገንዘቡን በመላካቸው እንደተለቀቁ ገልጸው፣ ልመና በወጡበት ወቅት እርዳታ ላደረጉላቸው ሁሉ ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ትምህርት እንዲማሩ የላኳቸው፣ እራሳቸው እየከፋቸው በተቻላቸው መጠን ምንም ሳያጎድሉ ያሳጓቸው ልጆቻቸው ሰውነታቸው ተጎሳቁሎ፣ ድብደባና ረሃብ ተፈራርቆባቸው እንደገኟቸው አስረድተው፣ የሀገር ተረካቢ ትውልድን በዚሁ መልኩ ማሰቃየት ጥሩ ዓርዓያ የለውም ሲሉ ተናግረዋል።

የተደፈሩ ሴት ተማሪዎች እንዳሉ የገለጹት የተማሪ ወላጆች፣ " እነዚህ ተማሪዎችን በድጋሚ ወደ ትምህርት የምንልክበት፣ እነርሱስ የሚሄዱበት ምን አይነት ሞራል ይኖራል ? " ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ከእገታ የተለቀቁ ተማሪዎች ስልካቸውንና ልባሳቸውን ሙሉ እንደተዘረፉም ገልጸዋል፡፡

#TikvahEthiopiaFamlyAA

@tikvahethiopia
7 ዓመት ?

" ለአራት በመሆን 15 ዓመት ታዳጊ አስገድደው የደፈሩ ተከሳሾች በ7 አመት ጽኑ እስራት ተቀጡ " ይለናል ከአመያ ወረዳ የተገኘው መረጃ።

ተከሳሽ ፦
- አስፋቸው አለሙ፣
- አሻግሬ አበራ፤
- ማቲዎስ ደዋና
- አስማማው አሉላ የተባሉ ግለሰቦች (ከላይ ፎቷቸው ተያይዟል) በአመያ ዙሪያ ወረዳ ኦፓላሼ ቀበሌ በቀን 27/10/2016 ዓ.ም በግምት 8:00 አካባቢ ጫሬ ዶቄ ቀበሌ ቤተሰብ ለመጠየቅ ወደ ኦፓላሼ ቀበሌ እየሄደች የምትገኝ የ15 አመት ታዳጊ አስገድደው ደፍረዋል።

" ግለሰቦቹ በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው በመሀኘታቸው ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች እያንዳንዳቸው 7 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጥተዋል " ተብሏል።

አራተኛ ተከሳሽ ዕድሜው 10-13 ዓመት ውስጥ መሆኑ ተከሳሹ አዋቂ እስረኞች ጋር አብሮ መታሰር የማይችልና እንደዚህ ዓይነት ታዳጊ እስረኞችን የሚቀበል ማረምያ ተቋም ባለመኖሩ ቤተሰቡ ፈርሞ ወስዶት ክትትልና በቁጥጥር እንዲያደርግ በማለት ፍርድ ቤት ወስኗል።

@tikvahethiopia
' ስካይ ላይት ሆቴል ' ውስጥ ተሸሽገው ነበር የተባሉ በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ኃላፊ ዛሬ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተነገረ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልደታ ክፍለ ከተማ የመሬት ልማት ጽ/ቤት ተወካይ ሃላፊ የነበሩት አቶ ቴዎድሮስ ፀጋዬ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ታሰሩ።

ግለሰቡ ሲፈለጉ ቆይተው ዛሬ ' ስካይ ላይት ሆቴል ' ውስጥ ተደብቀው ከነበሩበት መያዛቸውን የከተማ አስተዳደሩ አመልክቷል።

" ተጠርጣሪው በኮሪደር ልማት ስም ከመንግስት አሰራር እና ውሳኔ ውጪ  #በመደራደር ባልተገባ መንገድ ለግል ጥቅም ለማግኘት ሲሉ የካሳ ግምት በማናር ውስን የሆነዉን የህዝብ እና የመንግስትን መሬት ከአሰራር ውጪ በማሰተላለፍ ለግለሰቦች አላስፈላጊ ጥቅም በማዋል  ተጠርጥረው " መያዛቸው ነው የተገለጸው።

በተጨማሪ በክ/ከተማው ወረዳ 4 ዉስጥ በኮሪደር ልማት ኘላን ልማት ውስጥ የማይካተት ከመመሪያና አሠራር ዉጪ  6 መኖሪያ እና አንድ የንግድ ቤት የሆነውን  ከ ' ዋይልድ አፓርትመንት ' የተባለ ህንፃ ባለቤት ጋር ተመሳጥረው ቤቶቹን እንዲፈርሱ በማድረግና ለህንፃው ማስፋፊያ እንዲሆን የሰጡ መሆኑ ተመላክቷል።

የመንግስት ቤት ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ግለሰቦችም የእቃ የማጓጓዥያ ሳይከፈል እንዲነሱ በማድረጉ እንዲሁም " ምትክ ቦታ እስጣቿለው " ፤ " አንደኛ ቦታ አስቀይርላቿለው " እና የተለያዩ የማጭበርበር ወንጀሎችን በማድረግ ህብረተሰቡ ሲያደናግሩ ፤ ያልተገቡ ጥቅሞችን ሲያደርጉ ነበር ተብሏል።

ከተሸሸጉበት ' ስካይ ላይት ሆቴል ' ውስጥ የተያዙት ግለሰቡ " ከሀገር ውጪ ወተዋል " አስብለው እንደነበር ተገልጿል።

@tikvahethiopia
ቤንዚን ?

በአዲስ አበባ ቤንዚን ረጅም ሰዓት ሰልፍ ሳይሰለፉ ማግኘት ዘበት ከሆነ ሰነባብቷል።

ባለፉት ሳምንታት በትንሽ በትንሹ የጀመረው የቤንዚን ሰልፍ ከሰሞኑን እጅግ ብሶበታል።

በአንዳንድ ማደያዎች " ቤንዚን የለም " እየተባለ ሲለጠፍ ቤንዚን ያለባቸው ማደያዎች እጅግ በጣም ረጅም ሰልፍ ነው ያለው።

በዚህም ምክንያት የመኪና አሽከርካሪዎች ቀናቸውን በቤንዚን ሰልፍ ለማሳለፍ እየተገደዱ ይገኛሉ።

በሜትር ታክሲ አገልግሎት ላይ የተሰማሩ ዜጎችም ስራቸውን በአግባቡ ለመስራት ተቸግረዋል። ቀናቸውን ሁሉ በቤንዚን ሰልፍ ለማሳለፍ እየተገደዱ ናቸው።

በክልል ከተሞችም የቤንዚን ነገር ብሶበታል።

ቀድሞውንም ቤንዚን በማደያ እንደልብ በማንኛውም ሰዓት ማግኘት የማይቻልባቸው የክልል ከተሞች አሁንም ችግሩ እንዳለ ነው።

በክልል ከተሞች አሽከርካሪዎች ቤንዚን በማደያ " የለም " የሚባሉ ሲሆን በጀርባ ግን በየቦታው በህገወጥ መንገድ በጥቁር ገበያ ቤንዚን ሲቸበቸብ ይታያል።

ይህ ህዝብን እያማረረ ያለው የጥቁር ገበያ የነዳጅ ሰንሰለት መቼ እንደሚበጠስ አይታወቅም። ከዚህ ጀርባ እጃቸው የረዘመ አካላት መኖራቸውን ግን አሽከርካሪዎች ይናገራሉ።

ቤንዚን በክልል ከተሞች ከማደያ ውጭ በእጥፍ ዋጋ ነው የሚቸበቸበው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#DStvEthiopia #Gojo

🔥ከባድ ትንቅንቅ የማያጣው የ ማንቸስተር ሲቲ ከ አርሰናል በጎጆ ፓኬጅ

🏆 አስተማሪው ከ ተማሪው ጋር ይገናኛሉ! የቱ ቡድን 3 ነጥብ ይዞ ወደ ቀጣዩ ሳምንት ማለፍ ይችላል?

ይህንን ደማቅ ፍልሚያ በጎጆ ፓኬጅ በቀጥታ ይከታተሉ

🎉ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ወደ ጎጆ በማራዘም ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃትእስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ይከታተሉ!

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#DStvEthiopia #ሁሉምያለውእኛጋርነው
HEY Mobile !

Tab A9 - 19,500 ETB
•Tab A8 - 29,500 ETB
•Tab A9+ 5G - 31,000 ETB
•Tab S6 Lite - 47,000 ETB
•Tab S9 FE - 59,000 ETB
•Tab S9 +5G - 99,000 ETB
•Tab S9 Ultra - 129,000 ETB

Contact us :
0936222222 @heymobile1
0925927457 @eBRO4

@Heyonlinemarket
#ዋሪት !

ዘወትር የደንበኞቻችንን ፍላጎት ማርካት ቀዳሚ የሚያደርገው ዋሪት ዛሬም የበርካቶቻችሁን ጥያቄ መሰረት በማድረግ የአዲስ ዓመትን ቅናሽ እስከ መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ ማራዘሙን ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነው። የዋሪትን የውሃ ማጣሪያ ለየት የሚያደርገው ከሽያጭ በኋላ ለሚኖር ብልሽት አስተማማኝ የጥገና እና የመለዋወጫ አገልግሎት መስጠታችን !

ትክክለኛ ምርጫ!
ለተጨማሪ መረጃ: ☎️ 0911210706 / 07
TIKVAH-ETHIOPIA
#Amhara " ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዝገብ ነው እቅድ የተያዘው ከነሐሴ 20/2016 ዓ/ም ጀምሮ የተመዘገቡት ግን 1.7 ሚሊዮን ናቸው - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በየጊዜው የተኩስ ልውውጥ የሚስተዋልበት አማራ ክልል በ2017 የትምህርት ዘመን ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዘገብ እንዳቀደ፣ ከነሐሴ 20 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ…
#Amhara

“ የእኛ አብዛኛዎቹ ትምህርት ቤቶቻችን ደረጃ 2 ላይ ያሉ ናቸው፡፡ ደረጃቸው ዝቅተኛ ግን መማር ማስተማሩን ማስኬድ የሚችሉ እንደማለት ነው ” - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ

በአማራ ክልል በተለይ በጸጥታ ችግር ሳቢያ የግብዓት እጥረት ያለባቸው ትምህርት ቤቶች እንዳሉ፣ ይህም ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ ማነቆ እንደሆነባቸው ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገጸዋል፡፡

ለአብነትም እንደ መጽሐፍት፣ ወንበር መሰል ቁሳቁሶች እንደሌሉ፣ የወደሙ ትምህርት ቤቶች አለመጠገን፣ በግጭት የቀጠና ውስጥ የሆኑ አቅመ ደካማ ወላጆች ደግሞ ለልጆቻቸው እንኳ የትምህርት ግብዓት ማሟላት እንዳልቻሉ ነው ያስረዱት፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ለጉዳዩ ምላሽ እንዲሰጥ የክልሉን ትምህርት ቢሮ ጠይቋል፡፡

ቢሮው ምን ምላሽ ሰጠ ?

“ የግብዓት እጥረት አለብን ያሉ ትምህርት ቤቶች ይኖራሉ፡፡ ትክክል ነው፡፡ የግብዓት እጥረታቸው በሁለት መንገድ ነው የሚፈታው፡፡

አንደኛ የአካባቢውን ማህበረሰብ በማሳተፍ ነው፡፡ ሁለተኛ ደግሞ በክልል ደረጃ ደግሞ የሚሟሉ አሉ፡፡ ለምሳሌ መጽሐፍት በክልል ነው የምናሟላው፡፡

ከ14 ሚሊዮን በላይ መጽሐፍት ታትመው ስርጭት ተደርጓል፡፡ አሁንም በቀጣይ የሚሰራጩ አሉ፤ ከ1 ቢሊዮን በላይ በጀት የክልሉ መንግስት መድቦ አሁንም የሚታተሙ መጽፍት አሉ፡፡

እነርሱን አሳትመን እናሰራጫለን፡፡ የመምህራን ቅጥርም እናሟላለን፣ ትክክል ነው፡፡

የእኛ ክልል ትምህርት ቤቶች ሙሉ ግብዓት የተሟላላቸው፣ ስንታንዳርዳቸውን ያሟሉ አይደሉም፡፡

ትምህርት ቤቶች በ4 ደረጃ ይከፈላሉ፡፡ ደረጃ 1፣ 2፣ 3 እና ደረጃ 4 ተብለው፡፡ ደረጃ 4 የሚባል ትምህርት ቤት በክልሉ የለንም፡፡

ደረጃውን ያሟላ በጣም ኢንተርናሽናል እንደማለት ነው፡፡ ደረጃ 3 የሚባለው ደግሞ ለተማሪዎች መማር ማስተማር የተሻለ የሆነ ትምህርት ቤት ማለት ነው፡፡

የእኛ አብዛኛዎቹ ትምህርት ቤቶቻችን ደረጃ 2 ላይ ያሉ ናቸው፡፡ ደረጃቸው ዝቅተኛ ግን መማር ማስተማሩን ማስኬድ የሚችሉ እንደማለት ነው፡፡ ይሄ ማለት ብዙ ግብዓት የሚጎድላቸው ናቸው፡፡

ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 3ቱም ሳይንስ ቤተ ሙከራ እንዲሟላ፣ ደረጃውን የጠበቀ የኳስ ሜዳ እንዲኖረው፣ አጥር እንዲኖረው፣ ስታንዳርዱን እንዲያሟላ፣ ፋሲሊቲውን በማሟላት ረገድ መስራት የሚጠይቀን ሥራ አለ፡፡

እሱን በእቅድ ለመምራት ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ ግን ሙሉ የሕብረተሰቡን ተሳትፎ የሚጠይቅ ሥራ ነው፡፡

የእኛን ትምህርት ቤቶች በስንት ዓመት እንቀይራቸዋለን ደረጃቸውን ለማሻሻል ብለን አንድ በጣም ትልቅ የለውጥ እቅድ አቅደን ወደ ሥራ በገባን ማግስት ነው የጸጥታው ችግር የተፈጠረው፡፡

በዚህ ዓመት ውስጥ ትምህርት ቤቶቹን እንቀይራለን ብለን ነበር ዞሮ ዞሮ ወደ ሥራ መግባት አልተቻለም ”
ብሏል፡፡

የግብዓት እጥረት ላለባቸው ከባለሀብቶችና ባለንብረቶች ድጋፍ የማሰብሰብ ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
" መፍትሄ ሳይዘጋጅና በቂ ጥናት ሳይደረግ የተላለፈው ውሳኔ ፍጹም አግባብነት የሌለው ነው " - የትራንስፖርት ዘርፍ ላይ የተሰማሩ አካላት

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አማራጭ መፍትሔ ሳያዘጋጅና በቂ ጥናት ሳያካሂድ " ከ30 ዓመት በላይ አገልግሎት የሰጡ ድንበር ተሻጋሪ ተሽከርካሪዎች፣ አገልግሎት እንዳይሰጡ " ብሎ ውሳኔ አስተላልፏል ፤ ይህ ደግሞ አግባብነት የሌለውና ከትራንስፖርት ዘርፍ የሚገኘውን ኢኮኖሚዊ ጥቅም የሚያሳጣ ነው ሲሉ በዘርፉ የተሰማሩ አካላት ቅሬታቸውን አቀርበዋል።

የኅብረት ትራንስፖርት አክሲዮን ማኅበር መሥራችና ዋና ዳይሬክተር አቶ ባይሳ አየለ ምን አሉ ?

" የትንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ግልጽ የሆነ መመርያ ሳያወጣ፣ ለዓመታት አገልግሎት የሰጡ ድንበር ተሻጋሪ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት እንዳይሰጡ ብሏል። ይህ አግባብነት የለውም፡፡

ሚኒስቴሩ በዋናነት እነዚህ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት እንዳይሰጡ ያለበት ምክንያት፣ የአየር ብክለትን ለመከላከል አስቦ ነው። መንግሥት እንዲህ ዓይነት አሠራር ሲዘረጋ የብድር አገልግሎትና ተሽከርካሪዎች ከቀረጥ ነፃ የሚገቡበትን ሁኔታ ማመቻቸት ይኖርበታል።

በኢትዮጵያ 60 በመቶ የሆኑ ድንበር ተሻጋሪ ተሽከርካሪዎች ከ30 ዓመታትና ከዚያ በላይ አገልግሎት የሰጡ ናቸው፡፡ ተሽከርካሪዎቹ ደግሞ በምን ዓይነት ሁኔታ ነው የሚቀጥሉት የሚለውን መንግሥት ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር ጠለቅ ያለ ውይይት ማድረግ አለበት " ብለዋል።


የኢትዮጵያ ትራንስፖርት አሠሪዎች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኔ ዘሩ ምን አሉ ?

" ለከባድ ተሽከርካሪዎች የሚሆን የመሠረተ ልማት በአግባቡ ሳይሟላ መንግሥት በፍጥነት ተሽከርካሪዎቹ ወደ #ኤሌክትሪክ ይቀየሩ ማለቱ ትክክለኛ አካሄድ አይደለም።

በአሁኑ ወቅት ዕድሜያቸው ከ30 ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ድንበር ተሻጋሪ ተሽከርካሪዎቹ የማጓጓዝ አገልግሎት እንዳይሰጡ ፈቃድ በመከልከላቸው፣ እንዲቆሙ ተገደዋል።

ተሽከርካሪዎቹ በብቃትና በጥንካሬ የሚሰጡት አገልግሎት ከፍተኛ መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ አስተማማኝ አቅርቦት እስኪኖር ድረስ ተሽከርካሪዎቹ እንዲሠሩ መደረግ አለበት።

ዓመታዊ የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ለማደስ ጥያቄ ያቀረቡ አብዛኛዎቹ አክሲዮን ማኅበራት ተጨማሪ ተሽከርካሪዎች መግዛት ባለመቻላቸው ፈቃዳቸው አልታደሰም።

በዚህ ምክንያት አክሲዮን ማኅበራቱ ለጭነት አገልግሎት ሥራ በማንኛውም ጨረታ እንዳይሳተፉ ስለሚከለከል ተጨማሪ ተሽከርካሪዎች ለመግዛት ያለው የአቅም ውስንነት ታሳቢ በማድረግ የጊዜ ገደብ እንዲራዘምላቸው መደረግ ይኖርበታል።

ከ30 ዓመታት በላይ አገልግሎት የሰጡ ድንበር ተሻጋሪ ተሽከርካሪዎችን በተመለከተ፣ የተሻለ አሠራር እንዲፈጠርና የንብረቱ ባለቤቶችም ምቹ ሁኔታ እንዲያገኙ ለገንዘብ ሚኒስቴር፣ ለትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርና ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት በተለያዩ ጊዜያት ጥያቄ ብናቀርብም ምላሽ አልተገኘም " ብለዋል።

(ከሪፖርተር ጋዜጣ)

@tikvahethiopia
2024/09/29 20:32:00
Back to Top
HTML Embed Code: