Telegram Web Link
#DStv

💥ደማቅ ጨዋታ ! የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የለንደን ደርቢ ጨዋታ 💥

⚽️ ደማቁ የኢንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ወደ ሜዳ ይመለሳሉ! አርሰናል የለንድን ተቀናቃዩን ቶተንሀም ዛሬ ከሰዓት 10፡00 ሰዓት በቶተንሃም ሜዳ ይገናኛሉ!

🤔 አርሰናል እያሳየ የለውን ብቃት መቀጠል ይችላል? የእናንተን ግምት ያጋሩን
👉 ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ለመከታተል ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👉 የዲኤስቲቪን ዲኮደር በ1,199 ብር ከ1 ወር ነፃ የሜዳ ፓኬጅ ጋር ያገኛሉ።

የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://bit.ly/2WDuBLk

#PremierLeagueAllonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው
እንኳን ለ1499ኛው ለታላቁ ነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ።

መልካም በዓል !

@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 ትምህርት ዘመን መደበኛ ትምህርት ነገ ሰኞ መስከረም 6 ቀን 2017 ዓ/ም እንደሚጀምር የከተማው ትምህርት ቢሮ ገልጿል።

@tikvahethiopia
#Amhara

" የፋኖ ኃይሎች ወደ ድርድር መግባትን በመርህ ደረጃ ይቀበሉታል፡፡ ነገር ግን በመንግሥት ላይ እምነት የላቸውም " - የአማራ ክልል የሰላም ካውንስል

በአማራ ክልል በሚፋለሙት የፌዴራል መንግሥት እና የፋኖ ኃይሎች መካከል ያለው ሥር የሰደደ አለመተማመን ሰላም ለማውረድ የሚያደረገው ጥረት ፈተና እንደሆነበት፣ የአማራ ክልል የሰላም ካውንስል አስታውቋል።

የካውንስሉ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ እያቸው ተሻለ ምን አሉ ?

(ለሪፖርተር ጋዜጣ)

- የፌዴራል መንግሥት አመራሮችን ለማግኘት ጥረት ተደርጎ ነበር ግን አልተሳካም። እስካሁን ከፌዴራል መንግሥት በኩል ተገናኝቶ መወያየት የተቻለው ከሰላም ሚኒስቴር ጋር ብቻ ነው። የሰላም ሚኒስቴርም ካውንስሉ የሚያቀርበውን ጥሪ እንደሚቀበል አሳውቋል።

- ከተለያዩ የፋኖ ኃይሎች ጋር ንግግር ተደርጓል። ወደ ድርድር መግባትን በመርህ ደረጃ ይቀበሉታል፡፡ ነገር ግን በመንግሥት ላይ እምነት የላቸውም። ' ጊዜ መግዣ ነው ' ብለው ያምናሉ፣ እኛንም የፈተነን ይኸው ያለመተማመን ችግር ነው።

- ከፌዴራል መንግሥት በኩል ካውንስሉ ተጨማሪ ሥራዎች ይጠብቁታል። የፌዴራል መንግሥት ለሰላም ዝግጁ መሆኑን መናገር ብቻ ሳይሆን ምቹ ሁኔታን መፍጠር አለበት።

- በሁለቱም ተፋላሚ ኃይሎች መካከል መተማመንን ለመፍጠር ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እገዛ ለማግኘት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር፣ ከኢጋድና ከአፍሪካ ኅብረት አመራሮች ጋር በቅርቡ ውይይት ተደርጓል።

- ከአሜሪካ ኤምባሲ ጋር ንግግር ተደርጓል፤ እነሱ ለማገዝም ዝግጁ ናቸው። በካውንስሉ በኩል ደግሞ እየደረሰ ካለው ጉዳት አንፃር " የአማራ ክልል ሁኔታን ችላ ብላችሁታል " ብለናቸዋል።

- የአሜሪካ አምባሳደርን ጨምሮ ከስድስት ዲፕሎማቶች ጋር ውይይት ተደርጓል። በውይይቱም የክልሉን የሰላም ዕጦት ችላ ማለታቸውን ተጠቁሞ ዲፕሎማሲያዊ ተፅዕኖ ማሳደር እንደሚገባቸው ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

- ዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ ካውንስሉ የሚያደርገውን ጥረትም ሆነ ድርድሩ እንዲሳካ ለማገዝ ፈቃደኛ ነው። ነገር ግን በፋኖ አደረጃጀት ላይ ጥያቄ ማቅረቡን ገልጸዋል፡፡ 

ካውንስሉ አግኝቼ አናገርኳቸው የሚላቸው የፋኖ ኃይሎች እነማን ናቸው ? የትኛውን የአደረጃጀትስ ነው ያናገረው ? ለዚህ ጥያቄ ፦

" ይህንን መናገር አያስፈልግም፣ ምክንያቱም አንዳንዶች ነገሩን ' እገሌ ሊደራደር ነው ' በማለት መበሻሸቂያ አድርገውታል፡፡ በመሆኑም ከየትኛው የፋኖ አመራር ጋር እንደተወያየን መግለጽ ጠቃሚ አይደለም።

' እገሌ ሊደራደር ነው ' የሚለውን ጉዳይ የፋኖ ኃይሎች እንደ መበሻሸቂያ እየተጠቀሙበት ስለሆነ፣ ካውንስሉ የተደራጀ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ በፋኖ በኩል እገሌ እንዲህ ብሏል ከማለት እንቆጠባለን። " ሲሉ መልሰዋል።

የፋኖ ኃይሎች ድርድርን በመርህ ደረጃ እንደሚቀበሉት ነገር ግን " የፌዴራል መንግሥት ድርድሩን እንደ ጊዜ መግዣነት ሊጠቀምበት ነው " የሚል እምነት እንዳላቸው ተገልጿል።

ከዚህ በተጨማሪም ካውንስሉን" ሀቀኛ ድርድር ለማድረግ ሳይሆን ለማምታታት ነው " የሚል ሐሳብ እንዳላቸው ተጠቁሟል።

ይሁንና አለመተማመኑን ለመቅረፍ የሁሉንም አካላት ቅንነት ካውንስሉ እንደሚፈልግ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጠው ቃል አመላክቷል።

#Amahra #Ethiopia

@tikvahethiopia
For Rahel W/Selassie, Jasiri was the transformative environment she was looking for. She was able to find like-minded co-founders to establish her venture.

If you’re looking for a transformative environment like Rahel, consider applying to Jasiri.

Apply here 👉🏾 https://bit.ly/3A8rxtV

For more information, Join our telegram channel 👉🏾 @Jasiri4africa
#SafaricomEthiopia

💪🏾 በአዲስ አመት በአዲስ ሀይል TikTok ላይ የአንድ ደቂቃ ቪዲዮ ፖስት እያደረግን እስከ 400,000 ብር እንሸለም!
እስከ መስከረም 18 ብቻ!

የዲጂታል ሙዚቃ ውድድርን ለመቀላቀል፡
🎥 የአንድ ደቂቃ የራሳችን ሙዚቃ ቪዲዮ በTikTok ላይ እንፖስት
🏷 #1Wedefit እና #የምትኖሩበትከተማ አድራሻ ማስገባት እንዳንረሳ
📲የTikTok ደረገጽ @Safaricomet ታግ እናድርግ  እንዝፈን! እንላክ! እናሸንፍ!

መልካም ዕድል!
#1Wedefit #FurtherAheadTogether #DigitalMusicChallenge
" የመንግሥት ንብረትና ሐብት ለፓርቲ ሥራ ስለመዋሉ እንዲጣራልኝ ብጠይቀም ምላሽ አላገኘሁም " - ኢዜማ

" የመንግሥት ንብረትና ሐብት ለፓርቲ ሥራ እየዋለ ስለመሆኑ እንዲጣራልኝ ብጠይቀም ምላሽ አላገኘሁም ሲል " የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) አስታወቀ።

ኢዜማ " ብልጽግና ፓርቲ መንግሥትን እና ፓርቲን ባለመለየቱ እሳየ ያለው ቸልተኝነት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት እንቅፋት ይሆናል " ብሏል፡፡

በተጨማሪ ፓርቲው ለፌደራል ዋና ኦዲተር የመንግሥት ንብረትና ሀብት ለፓርቲ ሥራ መዋሉ በኦዲት እንዲጣራ ቢጠይቅም አጥጋቢ ምላሽ አለማግኘቱን አስታውቋል፡፡

ፓርቲው ባወጣው መግለጫ፤ " ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. ለፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የመንግሥት ንብረት እና ሀብት ለፓርቲ ሥራ መዋሉን ጠቅሰን በኦዲት እንዲጣራልን በደብዳቤ የጠየቅን ቢሆንም እስከ አሁን አጥጋቢ ምላሽ አላገኘንም " ሲል ገልጿል።

በተመሳሳይ ጥቅምት 07/2016 ዓ.ም. ለብልፅግና ፓርቲ አባላት ሥልጠና ከመንግሥት ካዝና ገንዘብ ወጥቶ መከፈል ስህተት መሆኑንና ሊታረም እንደሚገባ መግለጹን አስታውሷል።

" ይኼው ተግባር ከተጠናቀቀ ጥቂት ቀናት ባስቆጠረው ያለፈው ዓመት ብልፅግና ፓርቲ ከመንግሥት ንብረት የተለያዩ ተግባራትን እየፈጸመ ነው " ሲል ፓርቲው ገልጿል።

" ብልፅግና ፓርቲ የመንግሥት ሥልጣንን እንደያዘ ፓርቲ እያሳየ ያለው ዳተኝነትም በሀገራችን እውን ሆኖ ማየት ለምንፈልገው የመድብለ ፓርቲ እና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እንቅፋት መሆኑን በተደጋጋሚ በሚፈፅማቸው ስህተቶች እየተመለከትን ነው " ሲልም ተችቷል፡፡

ይህ ተግባር በአስቸኳይ የእርምት እርምጃ ካልተወሰደ ለሀገር ዴሞከራሲ ግንባታ ወደሚበጅ ትክክለኛ አሠራር እና ልምምድ ካልተመለሰ በስተቀር የሚያመጣው ቀውስ እና ይዞ የሚመጣው መዘዝ ቀላል አይደለም ብሏል።

" የሚመለከታቸው ዴሞክራሲያዊ ተቋማት ሰሞኑን ብልፅግና ፓርቲ ለሥልጠና የተጠቀመበትን ሀብትና ንብረት በትክክል ወደ መንግሥት ካዝና መመለሱን እንዲያረጋግጡ " ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

መንግሥትንና የሥራ ኃላፊዎቹን ተጠያቂ ለማድረግ፣ የተቋቋሙ ዴሞክራሲያዊ ተቋማትም በሀገር እና በሕዝብ የተጣለባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡና መንግሥትን ተጠያቂ እንዲያደርጉ እንዲሁም የሀገርን ሀብት ከሙስና እና ከምዝበራ እንዲታደጉ ሲል ፓርቲው ጠይቋል። #ኢዜማ #አሀዱ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 ትምህርት ዘመን መደበኛ ትምህርት ነገ ሰኞ መስከረም 6 ቀን 2017 ዓ/ም እንደሚጀምር የከተማው ትምህርት ቢሮ ገልጿል። @tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ2017

ዛሬ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የ2017 የትምህርት ዘመን ተጀምሯል።

በመዲናችን አዲስ አበባ በሁሉም የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች ትምህርት ተጀምሯል።

በተለያዩ የክልል ከተሞችም የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ተጀምሯል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

'' በዚህ ጦርነት ውስጥ ማን እየተጠቀመ እንዳለ ማወቅ አልቻልኩም '' - የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት

" በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች በመንግስት እና በታጣቂዎች መካከል እየተደረገ ያለው ግጭት ዓላማው ሊገባኝ አልቻለም " ሲል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ገለጸ።

ም/ቤቱ ይህን ያለው ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ በሰጠው ቃል ነው።

የም/ቤቱ ዋና ሰብሳቢ ደስታ ዲንቃ ፥ " በሁለቱ ክልሎች ያለ መፍትሄ የቀጠለው ግጭት የጋራ ምክር ቤቱን በእጅጉ አሳስቦታል " ብለዋል።

" ንጹሃንን እየገደለ፣ እያሰቃየ እና የሀገርን ሀብት እያወደመ ያለውን ግጭት ሁለቱም አካላት ቆም ብለው አስበው ምን እንዳመጣ እራሳቸውን ሊጠይቁ " ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

" ንጹሃን፣ ባለስልጣናት እና የባለስልጣናት ልጆች እየተገደሉ እየታፈኑ ነው " ያሉት ዋና ሰብሳቢው " በዚህ ጦርነት ውስጥ ማን እየተጠቀመ እንዳለ ማወቅ አልቻልኩም " ሲሉ አስረድተዋል፡፡

" በጦርነቱ እንደ ሀገር ሀገር እየተጎዳ ነው፣ እንደ ህዝብ ህዝብ እየተጎዳ ነው ፣እንደ ዜጋ ዜጎች እየተጎዱ ነው ፣እንደ ታሪክ ታሪክን እያበላሽን ነው ምን ዓይነት ስሌት አስልተን እንደምንረጋጋ አላውቅም " ብለዋል፡፡

በሀገሪቱ በመንግስት እና በታጣቂዎች መካከል እየተደረገ ያለው ግጭት ውድመት እያስከተለ ቀጥሏል ያሉት አቶ ደስታ ችግሩን በንግግር ለመፍታት በሁለቱም ወገን ፍላጎት አይታይም ሲሉ ወቅሰዋል፡፡

" አንዱ በአንዱ ላይ የበላይ ለመሆን ከሚደረግ ሩጫ የዘለለ ግጭቱን በንግግር የመፍታት ፍላጎት እየተመለከትን አይደለም " ሲሉ ገልጸዋል።

" ታጣቂዎች ሆኑ መንግስት ችግሩን በንግግር ከመፍታ ይልቅ ግጭቱን ስም ለማጠልሸት አንዱ ሌላውን ለመወንጀል እና የህዝብ ድጋፍ ለማግኝት እየተጠቀሙበት ነው " ብለዋል።

ምክር ቤቱ በመንግስት እና በታጣዊዎች መካከል እየተካሄደ ያለው ግጭት ሁለቱም አካላት እቆምለታለሁ ፣ እቆረቆርለታለሁ የሚሉትን ህዝብ እና ሀገርን እያወደመ መሆኑን አውቀው በንግግር ችግራቸውን እንዲፈቱ ለሬድዮ ጣቢያው በሰጠው ቃል ጠይቋል፡፡

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TPLF

በእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ቡድን የሚመራው ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 16 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ማባረሩና ከነበራቸው ድርጅታዊ ሃላፊነት ማንሳቱን አስታወቀ።

ድርጅቱ መስከረም 6/2017 ዓ.ም አካሄድኩት ያለውን ስብሰባ አስመልክቶ ባወጣው ባለ ሦስት ገፅ መግለጫ :- 

1. አቶ ጌታቸው ረዳ 
2. አቶ በየነ ምክሩ
3. ፕ/ር ክንደያ ገ/ሂወት
4. ዶ/ር ሓጎስ ጎዲፈይ
5. ወ/ሮ ኣልማዝ ገ/ፃዲቕ
6. አቶ ረዳኢ ሓለፎም
7. ወ/ሮ ሰብለ ካሕሳይ
8. አቶ ኢሳያስ ታደሰ
9. አቶ ሰለሞን መዓሾ
10. አቶ ሺሻይ መረሳ
11. ዶ/ር ገ/ሂወት ገ/ሄር 
12. አቶ ርስቁ አለማው
13. አቶ ሃፍቱ ኪሮስ
14. አቶ ብርሃነ ገ/የሱስ
15. አቶ ሩፋኤል ሽፋረ 
16. አቶ ነጋ ኣሰፋ 

ከአባልነትና ከድርጅት ሃላፊነት " አባርሪያችኃለሁ " ብሏል።

የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ህወሓት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና የነፈገውና የድርጅቱ ምክትል ሊቀ መንበር አቶ ጌታቸው ረዳና በርካታ የማእከለዊ ኮሚቴ አባላት " ህገወጥ " ያሉትን 14ኛ ጉባኤ በማካሄድ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል መልሶ የድርጅቱ ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡ ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaMekelle  

@tikvahethiopia 
#AASTU #ASTU

በ2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብተው በአፕላይድ ሳይንስና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ትምህርታቸውን መከታተል ለሚፈልጉ ጥሪ ቀርቧል።

ዩኒቨርሲቲዎቹ በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና 50% እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን ተጨማሪ የመግቢያ ፈተና በቀጥታ (online) በመስጠት ነው የሚቀበሉት።

የትምህርት መስኮቹ ምን ምን ናቸው ?

/ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ /

#ኢንጂነሪንግ ፦ አርክቴክቸር፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ፣ ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ ኬሚካል ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሪካል እና ኮምፒዩተር ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሮ መካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ፣ ማይኒንግ ኢንጂነሪንግ ፣ ኢንቫይሮሜንታል ኢንጂነሪንግ

#አፕላይድሳይንስ ፦ ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ፣ ፉድ ሳይንስ፣ አፕላይድ ኒውትሪሽን ፣ ጂኦሎጂ፣ ባዮቴክኖሎጂ

/ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ /

#ኢንጂነሪንግ ፦ አርክቴክቸር፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ፣ ወተር ሪሶርስ ኢንጂነሪንግ ፣ ኬሚካል ኢንጂነሪንግ ፣  ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ ማቴሪያል ሳይንስና ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሪካል ፓወር እና ኮንትሮል ኢንጂነሪንግ፣ ኤሌክትሮኒክስ እና ኮሚኒኬሽን ኢንጂነሪንግ፣ ኮምፒዩተር ሳይንስ ኢንጂነሪንግ፣ ሶፍት ዌር ኢንጂነሪንግ

#አፕላይድሳይንስ ፦ አፕላይድ ቦዮሎጂ፣ አፕላይድ ኬሚስትሪ፣ ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ፣ ፋርማሲ፣ አፕላይድ ፊዚክስ ፣ አፕላይስ ጂኦሎጂ፣ አፕላይድ ማቲማቲክስ

የምዝገባ ጊዜ፡- ከመስከረም 06 እስከ መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሆነ ተገልጿል።

ምዝገባው የሚጠናቀቀው መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት ላይ ነው።

የምዝገባ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች በማንኛውም ስፍራ በኢንተርኔት (online https://stuoexam.astu.edu.et ወይም www.aastu.edu.et / www.astu.edu.et ድረገጽን በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ፡፡

ፈተናው የሚሰጥበት ቀን በድህረ ገጽ የምዝገባው ቀን ካበቃ በኋላ ይደረጋል።

ፈተናው የሚሰጥበት ቦታ ፤ በምዝገባ ወቅት በመረጡት ዩኒቨርሲቲ (የፈተና ጣቢያ) በአካል በመቅረብ ይሆናል፡፡

NB. ለምዝገባና ለፈተና ምንም አይነት ክፍያ የማይጠየቅ ሲሆን የፈተና ጣቢያዎቹ ያላቸው የመፈተኛ ቦታ ውስን በመሆኑ ፍላጎቱ ያላቸው አመልካቾች ይህን አውቀው ቅድሚያ እንዲመዘገቡ ተብሏል።

@tikvahethiopia
ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በፕሮፌሰር በየነ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።

ፕሮፌሰር በየነ ረዘም ላለ ጊዜ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውንም ጠቁመዋል።

" በኢትዮዽያ ገንቢ የፖለቲካ ባህል ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ የሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ምልክት ነበሩ " ሲሉም ገልጸዋል። 

@tikvahethiopia
2024/09/30 10:21:56
Back to Top
HTML Embed Code: