Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray " እየተደረገ ያለውን እንቅስቃሴና መሳሳብ ህዝብ ስላልወደደው አሁኑኑ መቆም አለበት !! " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ም/ ፕሬዚደንትና የሰላምና ፀጥታ ሴክሬታሪያት ካቢኔ ሃላፊ ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር። በዚሁ ጋዜጣዊ መግለጫ ፥ " በአሁኑ ወቅት ለሁለት በተከፈለው ህወሓት መካከል እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴና መሳሳብ ህዝብ ስላልወደደው…
#TPLF

" በሕወሓት ውሳኔ መሰረት አቶ ጌታቸው ረዳ ከኤርትራ መንግስት ባለሥልጣናት ጋር ዱባይ ላይ ተገናኝተዋል " - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር)

ዛሬ የህዝባዊ ወያነ ትግራይ (ህወሓት) ሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ዛሬ በጽሕፈት ቤታቸው መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በአብዛኛው በእርሳቸው እና በፓርቲያቸው ዙርያ የሚቀርቡ ክሶች አስመልክተው ማብራርያ መስጠታቸው ነው የተነገረው።

በተለይ " ከኤርትራ ጋር ግንኙነት አላቸው " ተብሎ ለሚቀርበው ክስ ምላሽ ሰጥተዋል።

ደብረፅዮን (ዶ/ር) ፥ በሕወሓት ውሳኔ መሰረት አቶ ጌታቸው ረዳ ከኤርትራ መንግስት ባለሥልጣናት ጋር ከወራት በፊት በተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ፣ ዱባይ መገናኘታቸውን ገልጸዋል።

" ፕሬዝደንት ጌታቸው ከኤርትራ መሪዎች ጋር ግንኙነት አድርጓል። ሥራ አስፈፃሚው እና እኔ የማውቀው ግንኙነት ተደርጓል። " ብለዋል።

" ይህ መጥፎ አይደለም። ለሰላም ብለን ነው። ያለፈው በተጠያቂነት አሠራር ይታያል፥ አሁን ግን ወደ ችግር አታስገቡን፣ ወሰኖች ነፃ አድርጉ፣ ሰው ያግቱ ነበር አታግቱ ለማለት፣ እንስሳት ይዘርፉ ነበረ ሰዎች ያስሩ ነበር አቁሙ ለማለት ከኤርትራ መሪዎች ጋር በውጭ ሀገር ግንኙነቱ ተደርጓል " ሲሉ አስረድተዋል።

" ይህን ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ እንዲያውቁት ተደርጓል። እሳቸውም ከእናንተ ጋር ቅሬታ አላቸው ተገናኙ ብለዋል። ይህ የታወቀ ነው። ይህ ስህተት የለውም። ጌታቸው ግን አይጠቅስም፣ ' ሌሎች አሉ የሚገናኙ ነው ' የሚለው " ሲሉ አክለዋል።

መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
👏

በሀገር አቀፉ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከ600ው በተፈጥሮ እና በማህበራዊ ሳይንስ (575 እና 538) ከፍተኛውን ውጤት አምጥተው የሰቀሉት ሴት ተማሪዎች ናቸው።

ከዚህ ባለፈ እጅግ በርካታ ሴት ተማሪዎች ከ500 በላይ ውጤት በማምጣት የዘንድሮውን ፈተና ሰቅለዋል።

በተመሳሳይ በትግራይ ክልል በተሰጠው ከ700 ፈተናም ሴቶች ከፍተኛ አኩሪ ውጤት ነው ያስመዘገቡት።

ከላይ ለማሳያ የተወሰኑ ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ፎቶ ይያዝ እንጂ ሌሎችም በርከታ ሰቃይ ሴት ተማሪዎች አሉ።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ2017

እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሰን !

ፈጣሪ አዲሱን ዓመት ፦
- የሰላም
- የፍቅር
- የአንድነት
- ከተፈጥሮ ውጭ የሆነ የሰው ልጅ ሞት የማንሰማበት
- ደመ የማይፈስበት
- ሰው ታገተ፣ ተገደለ፣ ታፈነ የሚል ቅስምን ሰባሪ ዜና የማንሰማበት
- በመላ ሀገሪቱ ፍጹም እርጋታ ያለበት
- እናት የማታለቅስበት
- ሰው ወጥቶ ቀረ የማይባልበት
- ፍትሕ ለተነፈጉ ሁሉ ፍትህ የሚሰፍንበት
- ፍትሕ አጥተው የሚያነቡ ፍትሕ አግኝተው እንባቸው የሚታበስበት
- እየፈተነን ያለው የኑሮ ጫና መፍትሄ የሚያገኝበት
- በሰላም በነጻነት ያሻን ቦታ ወጥተን የምንገባበት
- በሁላችንም ዘንድ የማያስማሙን ጉዳዮች መፍትሄ የሚያገኙበት
- እርስ በእርስ ልክ እንደጠላት የማንተያይበት ፣ የማንሰዳደብበት
- እሮሮ፣ ስቃይ በደል የማንሰማበት
- ያዘንን ተስፋ የቆረጥን ፤ የምንጽናናበት ተስፋ የምናደርግበት
- ሰራተኞች ፣ ተማሪዎች ፍጹም የተሳካ ዓመት የሚያሳልፉበት
- ከምንም በላይ በሀገራችን የትኛውም ቦታ ሰላም ተረጋግጦ ፣ ስምምነት መጥቶ በሀገራችን ፍጹም ደስታ የምናገኝበት
- ሁሉም በአንድ መንፈስ ለእናት ሀገሩ " አለሁልሽ " ብሎ የሚቆምበት ያደርግል ዘንድ #ቲክቫህ_ኢትዮጵያ ይመኛል።

ፈጣሪ ምኞታችንን ያሳካልን !

መልካም አዲስ ዓመት !
ከዓመት ዓመት ያደረሰን ፈጣሪ ቀጣዩን እንድናይ ይርዳን !
ለሁላችሁም ረጅም እድሜን ከጤና ጋር እንመኛለን !

#TikvahEthiopiaFamily
#ቲክቫህኢትዮጵያቤተሰቦች

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

" ሰራተኞቹ ከሥራ ፈቃድ ወስደው ቤተሰብ ለመጠየቅ ሃና ማሪያም ተብሎ ወደ ሚጠራው ሰፈር ሲጓዙ ነበር " - የአዲስ አበባ ከተማ የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን

በአዲስ አበባ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 11 ዛሬ በደረሰ የትራፊክ አደጋ 3 የሆቴል መስተንግዶ ሠራተኞች ሕይወት አለፈ፡፡

አደጋው " ቀይ አፈር " ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ቀን 8፡20 ላይ ነው እንደደረሰ የአዲስ አበባ ከተማ የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል።

አንድ አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪ መንገድ ሲጠቀሙ የነበሩ እግረኞችን ገጭቶ ባደረሰው አደጋ ነው የ3ቱ ሰራተኞች ህይወት ያለፈው።

ሟቾቹ ሶስቱም ሴቶች ሲሆኑ ዕድሜያቸው ከ25-30 ይገመታል።

ሰራተኞቹ ከሥራ ፈቃድ ወስደው ቤተሰብ ለመጠየቅ " ሃና ማሪያም " ተብሎ ወደ ሚጠራው ሰፈር ሲጓዙ ነበር።

ከሟቾቹ ጋር አብራ ስትጓዝ የነበረች አንዲት ሴት እራሷን ስታ ሕክምና እየተከታተለች ትገኛለች።

በበዓል ወቅት መሰል አደጋ እንዳይከሰት አሽከርካሪዎች በጥንቃቄ እና በእርጋታ እንዲያሽከረክሩ የአዲስ አበባ ከተማ የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳስቧል። #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡
- Tag ሲያደርጉን ለ Facebook @ TecnoEt ፣ ለ Instagram @ TecnoMobileEthiopia እና ለ TikTok @ TecnoEt ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።)
- በተጨማሪም #TecnoEt2017 ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
#MesiratEthiopia

ድሬዳዋ ውስጥ ከሆናችሁ : ቢዝነስዎን ስኬታማ ለማድረግ እንደግፍዎታለን!
https://forms.gle/34U9fXkRmPxyZzsT6 ተመዝግበው ቦታዎን ያሲዙ።

🗓️ መስከረም 09, 2017 ዓ.ም
🕒 ከጠዋቱ 3:00 እስከ 7:00 ሰዓት
📍 በኤም ኤም ሆቴል (MM Hotel), ድሬዳዋ

የመስራት ስራ ፈጠራ ፕሮግራም Info Session ጥቅሙ ምንድን ነው?
- መስራት ምን እንደሆነና ቢዝነስዎትን እንዴት እንደሚደግፍ ያውቃሉ፣
- ፕሮግራሙን እንዴት መቀላቀል እንደሚቻል ያውቃሉ፣
- ስለሚሰጡት ድጋፎች እና ለሚኖርዎት ጥያቄ መልስ ያገኙበታል።
- በቴሌግራም ቦት በኩል ለሚሰጥ ሥልጠና መመዝገብ ይችላሉ።
#DStv

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የለንደን ደርቢ ጨዋታ 💥
⚽️ ደማቁ የኢንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ወደ ሜዳ ይመለሳሉ! አርሰናል የለንድን ተቀናቃዩን ቶተንሀም እሁድ መስከረም 5 ከሰዓት 10፡00 ሰዓት በቶተንሃም ሜዳ ይገናኛሉ!

🤔 አርሰናል እያሳየ የለውን ብቃት መቀጠል ይችላል? የእናንተን ግምት ያጋሩን
👉 ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ለመከታተል ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👉 የዲኤስቲቪን ዲኮደር በ1,199 ብር ከ1 ወር ነፃ የሜዳ ፓኬጅ ጋር ያገኛሉ።

የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://bit.ly/2WDuBLk
TIKVAH-ETHIOPIA
#የሀገር_ተስፋዎች 👏 በ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡት አንዷ የአዲስ አበባ ፣ ብስራተ ገብርኤል ትምህርት ቤት ተማሪዋ ማዕዶት እስክንድር ናት ፤ ተማሪዋ በተፈጥሮ ሳይንስ ከ600ው 573 በማምጣት ከሀገሪቱ 3ኛውን ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ሰቅላለች። @tikvahethiopia
#የሀገር_ተስፋዎች 👏

በ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በማህበራዊ ሳይንስ ከ600ው ከመላ ሀገሪቱ ከፍተኛውን ውጤት ያመጣችው የኢትዮ ፓረንትስ ት/ቤት ተማሪዋ ዎይናብ ሰለሞን ስትሆን ከ600ው 538 በማስመዝገብ ነው የሰቀለችው።

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
" እንደ ባሪያ ነው የምንታየው ፤ እባካችሁ ጭሁልን !! " - በማይናማር የሚገኙ ወጣቶች ማይናማር እና ታይላንድ ድንበር ላይ ከሚገኙ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የበየነ መረብ ማጭበርበር (Online Scam) ተግባራት ከሚፈጸምባቸው አንዳንድ ቦታዎች ቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክቶችን በቴሌግራም እየተቀበለ ይገኛል። እነዚህ ቦታዎች ላይ በርካታ የሀገራችን ወጣቶች ያሉ ሲሆን " ታይላንድ እንልካችኋለን " በሚል…
#Update

° " ብዙ አካላቸው የጎደለ ሰዎች አሉ፡፡ አካል እስከ ማጉደል ድረስ ነው ቅጣቱ " - ኢትዮጵያዊያን በማይናማር

° " መረጃው ትክክል ነው፡፡ ዜጎች ችግር ላይ ናቸው ተቋሙም ኃላፊነት ወስዶ ለወገኖቻችን ለመድረስ ጥረት እያደረገ ነው " - ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር

በማይንማርን ጨምሮ በአካባቢው የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን በከፋ ችግር ውስጥ እንደሆኑ ከወራት በፊት በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ድምጻቸውን አሰምተው እንደነበር ይታወሳል።

አሁንም ኢትዮጵያውያኑ የኢትዮጵያ መንግስት እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል።

መጀመሪያ ከአገር ሲወጡ የተዋዋሉት የሆቴል ቤት ሥራ አስኪያጅ፣ ሀኪም እና የመሳሰሉትን ሥራዎች ሊሰሩና ዳጎስ ያለ ክፍያ ሊፈጸምላቸው እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

ይሁን እንጅ ከዚያ ከደረሱ በኋላ ሽፍታ ወዳለበት የማይናማር ክልፍ እንደወሰዷቸው፣ ጭራሽ ደመወዝ እንደማይፈጽሙላቸው ፣ ከውላቸው ውጪ ዶላር ማጭበርበር እንደሚያሰሯቸው አስረድተዋል፡፡

የሌሎች አገር ዜጎች በአገራቸው መንግስት አማካኝነት እየተለቀቁ ቢሆንም ኢትዮጵያዊያኑ ግን የከፋ ስቃይ ውስጥ እንደሆኑ ገልጸው መንግስት እንዲደርስላቸው በአንክሮ ጠይቀዋል፡፡

ቤተሰቦቻቸው በበኩላቸው፣ መንግስት የልጆቻቸውን ሕይወት እንዲያተርፍላቸው ተማጽነዋል፡፡

ኢትዮጵያዊያኑ በዝርዝር ምን አሉ ?

" እያንዳንዱ ሰው የግድ በቀን 17 ሰዓት መስራት አለበት፡፡ የተሰራበት ደመወዝ ግን አይከፈልም፡፡ ገቢ ካላስገባ ቅጣት አለ፡፡ አለንጋም አላቸው ይገርፋሉ፡፡ ጨለማ ቦታ ላይ ወስደውም ያስራሉ፡፡

በአንድ ጊዜ ሦስት 20፣ 20 ሊትር ጀሪካን ያሸክማሉ፡፡ ሁለቱን በሁለቱ ትክሻቸው፣ አንዱን በእግርና እግር መካከል እንዲሸከሙ የሚገደዱ ኢትዮጵያዊያን አሉ፡፡

በተጨማሪ ብዙ ሰዎች ባሉበት አካባቢ ፊት ለፊት እንደ ማሳያ ተደርገን እንገረፋለን፡፡ በቀን አምስት ሰዓት ብቻ ነው የሚታረፈው፡፡

እጅና ኮምፒዩተር ለአፍታ ከቦዘኑ፣ የሆነ ስህተት ከተሰራ ድብደባ አለ፡፡ ምንም ነጻነት የሌለበት አገር ነው፡፡

ብዙ አካላቸው የጎደሉ ሰዎች አሉ፡፡ አካል እስከማጉደል ነው ቅጣቱ፡፡ እግራቸው፣ እጃቸው፣ ሁሉ ነገራቸው የተጎዳ ሰዎች አሉ " ሲሉ አስረድተዋል።

ኢትዮጵያዊያኑን ካሉበት የከፋ ችግር ለማውጣት ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥያቄ ያቀረብንላቸው  የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ ለጉዳዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

" በማይናማር የሚገኙ ዜጎቻችን ጉዳይ ይታወቃል፡፡ በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል በተለይ ሳወዝ ኤዢያ ካሉ ኤምባሲዎቻችን ውስጥ አንዱ ጃካርታ ነው፤ ኢንዶኖዢያ፡፡ ጉዳዩ እነርሱም ደርሷቸው እየጠከታተሉ ነው " ብለዋል።

" ይሄ መስመር በአጠቃላይ እንደ አዲስ የሕገ ወጥ ፍልሰት መንገድ ሆኖ ነው እየታዬ ያለው፡፡ እስከሁን ባልተለመደ ሁኔታ ወደዚህ አቅጣጫ ከዚህ ቀደም ከምናውቃቸው ትንሽ ወጣ ያለ ነው። ጉዳዩም ጥናት የሚፈልግ ሆኖ ነው የተገኘው " ሲሉ ተናግረዋል፡፡

" ዜጎች የትም አገር፣ የትም ቦታ ይሁኑ የመጀመሪያው መዳረሻ ችግራቸውን ለመፍታት ውጪ ጉዳይ እንደመሆኑ መጠን ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ክትትል እየተደረገበት ነው " ብለዋል።

ኢትዮጵያዊያኑ የአካል ጉዳት ጭምር እየደረሰባቸው በመሆኑ በፍጥነት እንዲደረስላቸው እየጠየቁ እንደመሆኑ  ከኤምባሲዎቹ ጋር ያለው ንግግራችሁ ተስፋ አለው ? በምን ደረጃ ላይ ነው ? የሚል ጥያቄ ቲክቫህ ለአምባሳደሩ አቅርቧል።

አምባሳደሩ በምላሻቸው፣ " እንደ አጋጣሚ ሆኖ ኢትዮጵያ ማይናማር ውስጥ ኤምባሲ የላትም፡፡ ምንም አይነት ዲፕሎማሲክ ውክልና የለንም " ብለዋል።

" ስለዚህ ከእርቀት ሆነው ነው ይህን ነገር የሚከታተሉት፡፡ መረጃው ትክክል ነው፡፡ ዜጎች ችግር ላይ ናቸው። ተቋሙም ኃላፊነት ወስዶ ለወገኖቻችን ለመድረስ ጥረት እያደረገ ነው " ሲሉ አክለዋል።

በችግር ላይ እንደሆኑ የሚነገርላቸው
ከ3000 በላይ ኢትዮጵያዊያን እንደሆኑ ነው፡፡ ተቋምዎስ ስንት እንደሆኑ ያውቃል? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄም ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል።

" ቁጥር ልንሰጥ አንችልም፡፡ ነገር ግን ቁጥራቸው 3000ም ሆኑ ሦስት ኢትዮጵያዊያን ችግር ላይ እስካሉ ድረስ ችግራቸው ችግራችን ሆኖ ተቋሙ ዜጎችን ለመታደግ ይንቀሳቀሳል " ነው ያሉት።

ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በጎርፍ ሊወሰዱ የነበሩ እናትና ልጅ በአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ህይወታቸዉን መታደግ ተቻለ።

ዛሬ መስከረም 2 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት ገደማ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ጀርመን ድልድይ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በጎርፍ ሊወሰዱ የነበሩ እናትና ልጅ በአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ጥረት ህይወታቸዉን ማትረፍ እንደተቻለ የእሳትና አደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ።

እናትና ልጇ በወንዝ ዳርቻ ካለዉ የጎመን ማሳቸዉ ዉስጥ ጎመን በመሰብሰብ ላይ ሳሉ በድንገት ደራሽ ጎርፍ ሊወስዳቸዉ የነበረ ቢሆንም በወንዝ መሀል ባለ ድንጋይ ጫፍ ላይ ሆነዉ ህይወታቸወን ማቆየት ችለዋል።

ይሁንና የጎርፉ መጠን እየጨመረ በመምጣቱ እናትና ልጁ በጎርፉ ሊወሰዱ በተቃረቡበት ሰዓት የኮሚሽኑ ጠላቂ ዋናተኞች ደርሰዉ ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸዉ የእናትና ለጇን ህይወት መታደግ እንደተቻለ ተገልጿል።

በአካባቢዉ ቀደም ሲል በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የ8 ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን በዚህ አካባቢ ከወንዙ የሚገኘዉን ዉሀ በመጠቀም የጎመንና ሌሎች ተክሎች ማሳ የሚገኝበት ነዉ።

በአሁኑ ሰዓት የክረምቱ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ባለመጠናቀቁ ባለማሳዎች ተክሎቹን ለመሰብሰብ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ የጎርፍ አደጋ ሊያጋጥም የሚችል በመሆኑ ጥንቃቄ እንዲደረግ ኮሚሽን መ/ቤቱ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡
- Tag ሲያደርጉን ለ Facebook @ TecnoEt ፣ ለ Instagram @ TecnoMobileEthiopia እና ለ TikTok @ TecnoEt ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።)
- በተጨማሪም #TecnoEt2017 ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
2024/09/30 10:37:17
Back to Top
HTML Embed Code: