Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TIGRAY

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ በዓዲግራት ምን አሉ ?

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን ዋና ከተማ ዓዲግራት ህዝባዊ ውይይት አካሂደዋል።

" ህዝቡ ስጋት ላይ የሚጥል ሁኔታ ለመቅረፍ ከናንተ መሃል ተገናኝተናል " ብለዋል።

" የትግራይ መልሶ ግንባታ ጋሃድ እንዲሆን በመደጋገፍ መስራት ይገባናል " ሲሉ አስገንዝበዋል።

" በውስጣች በተፈጠረው መፎካከር መስራት የሚገቡን አልሰራንም " ያሉት አቶ ጌታቸው " አብዛኛው ጊዚያችን በጭቅጭቅና በጎሪጥ በመተያየት ነው ያሳለፍነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

" ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በማህበራዊ አገልግሎት መልሶ ግንባታ ጥሩ እንቅስቃሴ አድርገናል ፤ ጅምሮቻችን ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በውስጣችን የታዩ ድክመቶችን ማረምና የጋራ መፍትሄ ለመሻት መስራት ይጠበቅብናል " ብለዋል።

" በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት ሁሉም በጠላት ስር የሚገኙ አከባቢዎች  ወደ ነባር አስተዳደራቸው መመለስ አለባቸው ብለን እየሰራን ነው " ያሉት አቶ ጌታቸው " የሰላም ስምምነቱ በተሟላ መልኩ እንዲተገበር እንደ መንግስት ጠንክረን እንሰራለን " ሲሉ ተናግረዋል።

" የህዝባችን ሰላም በማረጋገጥ በኩል ዓለም ከኛ ጋር ናት ይህንን እንዲቀጥል ግን ውስጣዊ አንድነታችን እንዳይላላ ያለማቋረጥ መስራት አለብንም " ብለዋል።

በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ዓዲግራት ሲደርሱ በልዩ አጀብ በፈረሰኞች የተደገፈ አቀባበል ነበር የተደረገላቸው።

በአቀባበሉ የተገኙ የዓዲግራት ከተማ ወጣቶች ፦
👉 የጥይት ድምፅ እንጠየፍ !! 
👉 መሰረታዊ ለውጥ እንፈልጋለን !!" 
👉 ተፈናቃዮች ይመለሱ ግዛታዊ አንድነት ይከበር !!
👉 ትግራይ በሳይንስና ጥበብ እንጂ በጥይት አፈሙዝ አትመራም !!
👉 ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንደግፋለን !!
የሚሉና ልሎች መፈክሮች በመያዝ ድምጻቸውን አሰምተዋል።

በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ በተመራ የጊዚያዊ አስተዳደሩ አመራሮች ቡድን ምክትል ፕሬዜዳንት ጄነራል ጻድቃን ገብረትንሳኤ ነበሩበት።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የNGAT ፈተና መቼ ይሰጣል ? ትምህርት ሚኒስቴር ፥ የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ተጨማሪ የምዝገባ ጊዜ እና የፈተና ቀንን አሳውቋል። በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ያላቸው እና በተለያዩ ምክንያቶች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ ያመለጣቸው አመልካቾች እስከ ነሐሴ 26/2016 ዓ.ም ድረሰ በ https://ngat.ethernet.edu.et በኩል…
#NGAT : የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የሚሰጥበት ቀን እና ሰዓት ይፋ ተደርጓል።

ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነውን የትምህርት መስኮችና የመግቢያ ፈተና የሚሰጥባቸውን መርሐግብር ከላይ ይመልከቱ።

ፈተናው ነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል።

Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#NGAT : የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የሚሰጥበት ቀን እና ሰዓት ይፋ ተደርጓል። ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነውን የትምህርት መስኮችና የመግቢያ ፈተና የሚሰጥባቸውን መርሐግብር ከላይ ይመልከቱ። ፈተናው ነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል። Via @tikvahuniversity
NGAT_EXAM_SCHEDULE_FFF1.xls
33.5 KB
#NGAT : ነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜን 1 / 2016 ዓ.ም የሚሰጠው የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የሚሰጥበት ቀንና ሰዓት፣ የመፈተኛ ማዕከላት እና የትምህርት መስኮች

ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘ የመጨረሻ መርሐግብር ከላይ ተያይዟል።

Via @tikvahuniversity
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ ፦ ይህ #ድብድብ ከሶማሊያ ተገንጥላ ራሷን በምታስተዳድረው #ሶማሌላንድ ፓርላማ ውስጥ የተከሰተ ነው።

ምንድነው የተፈጠረው ?

ዛሬ የፓርላማ አባላቱ ሞሃመድ አቢብ በተባለ የፓርላማ አባል ያለመከሰስ መብት መነሳት ጉዳይ አስቸኳይ ስብሰባ ነበራቸው።

ሞሀመድ አቢብ እጅግ የሚታወቁና አውዳል ላይ ብዙ ተከታይ ያላቸው ፖለቲከኛ ሲሆኑ ገዢዎችን በመኮነን ለውጥ እንዲመጣ የሚታገሉ ናቸው ይባልላቸዋል።

የሶማሌላንድ መንግሥት እኚህን ፖለቲከኛ ከዛሬ 3 ቀን በፊት ከተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ፣ ዱባይ ሲመለሱ ሀርጌሳ ኤርፖርት ላይ ጠብቆ አስሮ እስር ቤት አስገብቷቸዋል።

ያሰራቸው በሀገር ክህደት እና የሶማሌላንድ ሪፐብሊክን ከሚቃወሙ ቡድኖች ጋር አብረዋል በሚል ነው።

ይህ በደጋፊዎቻቸው ዘንድ ቁጣን ቀስቅሷል።

መንግሥት ፓርላማውን አስቸኳይ ስብሰባ አስቀምጦ ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ በጠቅላይ አቃቤ ሕግ የውሳኔ ሀሳብ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም ከተገኙት 57 አባላት ውስጥ 51 አባላት ተቃውመዋል።

ታዲያ በዚህ ጉዳይ ላይ ነው ፓርላማ ውስጥ ክርክር ሲደረግ በሁለት አባላት መካከል የለየለት ድብደብ እና የቡጢ መሰነዛዘር፣ እቃ መወራወር የደረሰ መነጋገሪ ክስተት የተከሰተው።

ተደባዳቢ የፓርላማ አባላቱ መጎዳታቸው ተነግሯል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ቱርክ #ኢትዮጵያም ያለችበትን የBRICS ስብሰብ ትቀላቀል ይሆን ? ባለፈው ሳምንት የቱርክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃካን ፊዳን የBRICS አባሏን ቻይናን ጎብኝተው ነበር። በጉብኝታቸው ወቅት ከቻይና ባለስልጣናት ጋር መክረዋል። በወቅቱ ሀገራቸው ቱርክ የBRICS ስብስብን የመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት ተጠይቀው ፥ " በእርግጥም #እንፈልጋለን። ለምን አንፈልግም ? " ብለዋል። " በእርግጥም ፤ የBRICS…
#BRICS+

የNATO አባል ሀገሯ ቱርክ የBRICS አባል ለመሆን ይፋዊ ጥያቄ አቀረበች።

ቱርክ የBRICS አባል ለመሆን በይፋ ማመልከቻ ማቅረቧን የቱርክ ገዥ ፓርቲ ቃል አቀባይ ኦመር ሴሊክ አረጋግጠዋል።

ቃል አቀባዩ " ፕሬዝደንታችን የBRICS አባል መሆን እንደምንፈልግ ደጋግመው ተናግረዋል። ጉዳዩ በሂደት ላይ ነው " ብለዋል።

" በአባልነት ሂደት ላይ ያለውን እምርታ ለህዝብ እናሳውቃለን " ሲሉም ተናግረዋል።

ሀገሪቱ ከዚህ ቀደም የBRICS+ ስብስብን የመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት ማሳወቋ የሚዘነጋ አይደለም።

ቱርክ የ #NATO አባል ሀገር እንደሆነች ይታወቃል።

#BRICS+ ኢትዮጵያን ጨምሮ የሩስያ ፣ የብራዚል ፣ የቻይና ፣ የህንድ ፣ የደቡብ አፍሪካ ፣ የኢራን ፣ የግብፅ ፣ የዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ ስብስብ ነው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡
- Tag ሲያደርጉን ለ Facebook @ TecnoEt ፣ ለ Instagram @ TecnoMobileEthiopia እና ለ TikTok @ TecnoEt ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።)
- በተጨማሪም #TecnoEt2017 ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈 #የነዋሪዎችድምፅ “ ግድያና እገታ የሚፈጸመው መሀል ከተማ ላይ ነው፡፡ ለዛውም ፖሊስ ጣቢያ ባለበት አጠገብ፡፡ ዛሬ ህዝቡ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥቷል፡፡ ፖሊስና ሚሊሻ ወደ ህዝቡ ነው የተኮሰው ” - ነዋሪዎች በአማራ ክልል፣ ጎንደር ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች በተለይ ከሦስት ወራት ወዲህ " በታጠቁ አካላት አማካኝነት ግድያ፣ እገታና ዝርፍያ " በመበራከቱ ሰቆቃ ላይ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡…
🔈 #የዜጎችድምጽ

በኢትዮጵያ ውስጥ ከቅርብ አመታት ወዲህ እጅግ እየተስፋፋና እየተባባሰ የመጣው የእገታ ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል።

ሰዎች ይታገታሉ ፤ ገንዘብ ይጠየቃል ፤ አንዳንዴማ ጭራሽ የገንዘብ ዝውውር በባንክ ይፈጸማል።

አጋቾች ዘገያችሁ በማለትም ታጋቾችን ይገድላሉ።

ህጻን፣ አዛውንት፣ ወጣት፣ ሴት ፣ ሀብታም ፣ ገንዘብ የሌለው የሚቀር የለም ይታገታል።

ድርጊቱ በተለይ አማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ላይ በስፋት የሚስተዋል ሲሆን ትግራይ ውስጥ ጦርነቱ ከቆመ ወዲህ እገታ ሲፈጸምና ሰው ሲገደልም ተሰምቷል።

አማራ ክልል ከዚህ ቀደምም እገታ ይፈጸም የነበረ ሲሆን ህዝቡ " የመፍትሄ ያለህ !! "እያለ ሲጮህ ነው የኖረው ባለፉት ዓመታ ግን በክልሉ ካለው የጸጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ እገታ እጅግ ተባብሷል።

ሰው ይታገታል ፤ ድሃው ቤተሰብ ብር አምጣ ይባላል ብር መላክ ሳይችል ሲቀር ታጋች ተገድሎ ይጣላል ፤ አዘገያችሁ እየተባለም መግደል ተጀምሯል።

አሽከርካሪዎች ተዘዋውረው ስራ መስራት ፈተና ሆኖባቸዋል። ወጥቶ መግባት ብርቅ ሆኗል። በዚህ የተማረረው ዜጋ አካባቢውን ጥሎ ለመውጣት እየተገደደ ነው። ያውም ያለው። የሌለው አማራጭ ስላጣ እዛው በሰቀቀን ይኖራል።

አሁን አሁን ግን እገታ ብቻ ሳይሆን ሰዎችን ማሸበር የተያያዘ ስራ ይመስላል። ብር ተሰጥቶ እንኳን ታጋች ተገድሎ ይጣላል። ህዝቡንና ህብረተሰቡን ተስፋ የማስቆረጥ ፤ በስነልቦና የመጉዳት ነገር !

ኦሮሚያም በተመሳሳይ ዓመታት አልፈዋል።

እጅግ በሚያስገርምና ጥያቄንም በሚፈጥር ሁኔታ አንድ ቦታ ላይ ብዙ ጊዜ ተደጋግሞ እገታ ይፈጸማል።

ተማሪ ፣ ሰላማዊ መንገደኛ ሳይቀር ታፍኖ ተወስዶ ቤተሰብ ብር ይጠየቃል። ሰው ይገደላል።

አንዳንድ ቦታዎች ጭራሽ መንገድ ሄዶ መመልስ ብርቅ ነው። ሰው አቅም የለው በአየር ትራንስፖርት እንዳይጠቀም ህይወቱን አስይዞ ለኑሮው ለስራው ሲል ይጓዛል።

ለመሆኑ አንድ ቦታ ላይ ተደጋግሞ እገታ ሲፈጸም ዘላቂ እርምጃ የማይወስደው ለምንድነው ? ፣ ሌላው ይቅር ችግሩን መፍታት ከተፈለገ የደህንነት ካሜራዎችን እንኳን እየተጠቀሙ ፣ የስልክ መስመሮችን እያጠኑ መፍትሄ መስጠት ለምን አልተቻለም ? ይህ የብዙዎች ጥያቄ ነው።

አንድ መስመር ላይ ዓመታት ሙሉ ሰው እየታገተ ገንዘብ ሲጠየቅ ችግሩን በዘላቂነት እንዲፈታ አለማድረግ ትልቅ ጥያቄ ነው የሚያስነሳው።

ትግራይ ላይ ከጦርነት ማግስት ሰዎችን አግቶ ብዙ ሚሊዮን ብር መጠየቅ የተለመደ ሆኗል። በዚህ ዓመት በርካቶች ታግተው ገንዘብ ተጠይቆባቸዋል።

ከእገታ በኃላ የተገደለም አለ።

በእርግጥ የሰላም መጥፋት ለእንዲህ ያለው ስርዓት አልበኝነት በር እንደሚከፍት የታወቀ ቢሆንም ችግሩን ከምንጩ ለማድረቅ ሁሉንም አቅም አሟጦ በመጠቀም ለምን አልተሰራም ?

ብዙዎች በእገታና ግድያ ተግባራት መሯቸዋል።

ከዓመታት በፊት በዚህ በሰፋ ልክ ያልተለመደ አሁን ግን ልክ ፋሽን እየሆነ የመጣን ተግባር ከምንጩ ለምን ማድረቅ እንዳልተቻለ የብዙዎች ጥያቄ ነው።

#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Ethiopia 🇪🇹 #Africa #China

የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ቻይና ውስጥ ተሰባስበዋል።

በቻይና የተሰባሰቡት ለቻይና አፍሪካ የመሪዎች መድረክ ነው።

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና ሉዑካቸው ቻይና ይገኛሉ።

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ፥ የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ደማቅ አቀባበል እንዳደሩጉላቸው ገልጸዋል።

ጠቃሚ ውይይት ማድረጋቸውንም አመልክተዋል።

" ኢትዮጵያ የቻይናን ያልተቋረጠ ዘርፈብዙ ድጋፍ በእጅጉ ታደንቃለች። " ያሉት ጠ/ሚኒስትሩ " እንደ ሀገር የተለያዩ ተግዳሮቶችን ብናስተናግድም በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢንደስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በቴሌኮሙኒኬሽን እና ሌሎች ዘርፎች ትርጉም ያላቸው የለውጥ ርምጃዎች ተራምደናል " ብለዋል።

" በዚህ የእድገት ጎዳና የቻይና ኢንቨስትመንቶች ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል ፤ በቱሪዝም ብሎም በወረቀት እና እንደ ፐልፕ ያሉ ተያያዥ ግብዓቶች ኢንደስትሪንም ለማሳደግ እምቅ አቅም አለ። " ሲሉ ገልጸዋል።

በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ትብብር የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

@tikvahethiopia
2024/10/01 07:39:27
Back to Top
HTML Embed Code: