Telegram Web Link
#SafaricomEthiopia

* 400,000 ብር?? * በዛ ላይ ደግሞ አስቡት የእናንተ ሙዚቃ በመላው ኢትዮጵያ ሲደመጥ...እናንተ ችሎታው ይኑራችሁ የቀረውን በእኛ ጣሉት! አሁኑኑ የአንድ ደቂቃ ቪዲዮአችንን እንላክ!

የዲጂታል ሙዚቃ ውድድርን ለመቀላቀል፡
🎥 የአንድ ደቂቃ የራሳችን ሙዚቃ ቪዲዮ በTikTok ላይ እንፖስት
🏷 #1Wedefit እና #የምትኖሩበትከተማ አድራሻ ማስገባት እንዳንረሳ
📲የTikTok ደረገጽ @Safaricomet ታግ እናድርግ

እንዝፈን! ፖስት እናድርግ! እናሸንፍ!

መልካም ዕድል!
እንዳያመልጣችሁ!

#SafaricomEthiopia #1Wedefit
TIKVAH-ETHIOPIA
#EthiopianAirlines🇪🇹 " የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ውሳኔውን መልሶ እንዲያጤነው እንጠይቃለን ፤ ይህ የማይሆን ከሆነ የሚጎዱት ወደ ኤርትራ የሚጓዙ ተጓዦች ናቸው " - " አቶ መስፍን ጣሰው የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ የሚያደርገው በረራ ከመስከረም 30 / 2024 ጀምሮ እንዲቆም የሚያሳውቅ ደብዳቤ መላኩን ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው…
#Ethiopia : የኢትዮጵያ አየር መንገድ በህይወት ያሉ እንሰሳትን በማጓጓዝ ላይ ስለሚቀርበው ቅሬታ ምን ምላሽ ሰጠ ?

የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ፦

" ይህ ጉዳይ ዓለም አቀፍ አሰራር ስለሆነ መስፈርቱን ጠብቀን አገልግሎቱን እንሰጣለን።

ጫጩት እናጓጉዛለን፤ በጎች የምናጓጉዝበት ጊዜ ነበረ፤ ፍየሎች እናጓጉዛለን። በአንድ ወቅት አሁን እንኳን አይደለም ላሞችና በሬዎች በህይወት እያሉ እናጓጉዝ ነበረ።  አሁን ዝንጀሮዎች አጓጓዛችሁ ነው የሚሉን።

ህጋዊ ፈቃድ የተሰጠው ከአሜሪካም ከሌላም ሀገር ህጋዊ ፈቃድ የተሰጠው ድርጅት እስከመጣ ድረስ ያንን የዓለም አቀፍ ህጉን ተከትለን እናጓጉዛለን።

ጥያቄ የእንስሳት ተቆርቋሪ ነን የሚሉ አካላት ናቸው የሚያነሱት መነሻቸው ' ዝንጀሮዎቹ  ወደ እዛ ሄደው ለላብራቶሪ አገልግሎት ነው የሚውሉት ' የሚል ነው። ይሄ ግን ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ኃላፊነት አይደለም።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የንግድ ተቋም ነው እንደ ንግድ ተቋም ነው የሚሰራው። "


#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia : የኢትዮጵያ አየር መንገድ በህይወት ያሉ እንሰሳትን በማጓጓዝ ላይ ስለሚቀርበው ቅሬታ ምን ምላሽ ሰጠ ? የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ፦ " ይህ ጉዳይ ዓለም አቀፍ አሰራር ስለሆነ መስፈርቱን ጠብቀን አገልግሎቱን እንሰጣለን። ጫጩት እናጓጉዛለን፤ በጎች የምናጓጉዝበት ጊዜ ነበረ፤ ፍየሎች እናጓጉዛለን። በአንድ ወቅት አሁን እንኳን አይደለም ላሞችና በሬዎች በህይወት…
#Ethiopia : የኢትዮጵያ አየር መንገድ " #ወታደሮችን ያጓጉዛል " በሚል ለሚነሳትበት ቅሬታ ምን ምላሽ ሰጠ ?

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሀገር ውስጥ ባሉ ግጭቶች ላይ ' ወታደር በማጓጓዝ ይሳተፋል ' የሚል ቅሬታዎች ይነሱበታል።

ይሄ ጉዳይ ከዓለም አቀፍ የበረራ ህጎች ጋር አይጻረርም ወይ ? በሚል የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ተጠይቀው ምላሽ ሰጥተዋል።

አቶ መስፍን ጣሰው ምን አሉ ?

" ወታደሮች በአውሮፕላኖች የሚሄዱበት አሰራር አለ።

በዚህ ረገድ አየር መንገዱ ዓለሞ አቀፍ አሰራሮችን ጠብቆ ነው የሚሰራው።

ለማሳያነት አየር መንገዱ ሁለት አውሮፕላኖችን መድቦ ለUN ወታደር ብቻ የሚያጓጉዝበት አሰራር አለ።

በተለይ አንደኛው አውሮፕላን ለዚሁ ግልጋሎት ብቻ የተመደበ ነው።

ሰላም አስከባሪ ወታደሮችን ከሀገር አገር አጓጉዘናል ፣ የአፍሪካ ጸጥታ አስከባሪ ወታደሮችን ስናጓጉዝ ነው የኖርነው፤ እናጓጉዛለን፥ ያ ማለት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጦርነት ላይ ተሳተፈ ማለት አይደለም።

ይሄን ሁሉ ስናደርግ ገንዘብ እያስከፈልን እኮ ነው።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወታደሮችን ከአንድ ከተማ ወደ ሌላ ከተማ ወታደር አንዲያጓጉዝ ጥያቄ ቀርቦለት ያውቃል።

ውሰዱልን ተብለን ተጠይቀን ነበር በዛ መሰረት ገንዘብ አስከፍለን ወታደሮችን ልክ ለUN እንደምናደርገው አድርገናል።

ወታደሩ ምን ያደርጋል ያ የእኛ ኃላፊነት አይደለም። ነገር ግን ወታደር በአውሮፕላን ሲጓዝ መደረግ ያለባቸው መስፈርቶች አሉ እነዛን አድርገን እንሰራለን።

ከዚህ በፊት ' ወታደሮች ስለምታጓጉዙ አውሮፕላኖችን ፋይናንስ አናደርግላችሁም ' ተብለን እናውቃለን እኛ አሰራራችንን አስረድተን፤ አሰራራችን ከዓለም አቀፉ አሰራር ጋር አብሮ የሚሄድ መሆኑን ካረጋገጡ በኋላ አውሮፕላኖቻችንን እንድናመጣ አድርገውናል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የንግድ ተቋም ነው እንደ ንግድ ተቋም ነው የሚሰራው። "

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#Ethiopia

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ 87 በመቶ የሚሆኑት የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የዘንድሮውን የመውጫ ፈተና ማለፍ እንዳልቻሉ ተናግረዋል።

22 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን ገልጸዋል።

የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ካስፈተኗቸው አጠቃላይ ተማሪዎች መካከል ማሳለፍ የቻሉት 13 በመቶ ብቻ ነው ብለዋል።

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ አጠቃላይ ካስፈተኗቸው ተማሪዎች 58 በመቶ ማሳለፋቸውን ገልጸዋል፡፡

በዚህ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃዎች ይኖሩናል።

#ETA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የግል ባንኮች የውጭ ምንዛሪ ተመን ምን ይመስላል ? እካሁን በርካታ የግል ባንኮች የዕለቱን የምንዛሪ ተመን ይፋ አልደረጉም። ከግል ባንኮች መካከል የሆኑት አዋሽ ባንክና የኦሮሚያ ሕብረት ስራ ባንክ ግን ተግባራዊ በተደረገው የፖሊሲ ማሻሻያ መሰረት ዕለታዊ የውጪ ምንዛሬ ተመኑን ይፋ አድርገዋል። ባንኮቹ ጥዋት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይፋ ካደረገው የምንዛሪ ተመን ጋር ተመሳሳይ አይነት…
#Ethiopia

ተግባራዊ በተደረገው የፖሊሲ ማሻሻያ መሰረት የግል ባንኮች ዕለታዊ የውጪ ምንዛሬ ተመናቸውን ይፋ እያደረጉ ይገኛሉ።

ከላይ የተወሰኑ ባንኮች የዛሬ ዕለታዊ ምንዛሬ ተያይዟል።

ከላይ ከተያያዙት የአብዛኞቹ ቀደም ብሎ ይፋ ካደረገው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የምንዛሬ ተመን ጋር ተመሳሳይ ነው።

በአንጻሩ ሲዳማ ባንክ የውጭ ምንዛሬው ከሌላው ከፍ ያለ ነው።

ሲዳማ ባንክ አንዱን የአሜሪካ ዶላር በ76 ብር ከ2311 ሳንቲም እየገዛ በ77 ብር ከ7557 ሳንቲም እየሸጠ ነው።

ፓውንድ ስተርሊንግ በ93 ብር ከ7163 ሳንቲም እየገዛ በ95 ብር ከ5906 እየሸጠ ይገኛል።

ዩሮ በ82 ብር ከ6574 ሳንቲም እየገዛ በ84 ብር ከ3105 ሳንቲም እየሸጠ ይገኛል።

ዛሬ ተግባራዊ በተደረገው በገበያ ላይ የተስመረተ የውጭ ምንዛሬ ተመን / Floating exchange rate ባንኮች ከደንበኞቻቸው ጋር በሚያደርጉ ነጻ ድርድር የውጭ ምንዛሬ መግዛት እና መሸጥ እንዲችሉ ይፈቅዳል።

በመሆኑም በዕለቱ ፍላጎት ገበያው ይወሰናል።

ብሔራዊ ባንክ ከአሁን በኋላ ለባንኮች አንድ ዶላር በዚህ ብር መንዝሩ አይልም ፤ ስራው ገበያውን በማረጋጋት ላይ ያተኮረ ነው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
FXD012024-FOREIGN-EXCHANGE-1-1.pdf
22.8 MB
NATIONAL BANK OF ETHIOPIA FOREIGN EXCHANGE DIRECTIVE NO. FXD/01/2024

በዚህ መመሪያ መሰረት የውጭ ምንዛሪ ማግኘት የሚችሉት እነማን ናቸው ?

➡️ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት የተፈቀደላቸው የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ከኢትዮጵያ ውጭ የሚጓዙ ኢትዮጵያዊውያን ወይም በአገሪቱ ውስጥ የሚኖር የውጭ ዜጎች ናቸው።

➡️ ምንዛሪ ለማግኘት የሚፈልጉ ግለሰቦች ለበዓል ፣ ለትምህርት ፣ ለህክምና ጉዞዎች እና ሌሎች የግል ጉዳዮች እንደሚጓዙ የሚያሳይ ፓስፖርት፣ ሕጋዊ የመግቢያ ቪዛ እና የአየር ትኬት የማቅረብ ግዴታ ተጥሎባቸዋል።

➡️ ተጓዦች ከምንዛሪ ቢሮዎች እስከ 5 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ወይም የዚህ አቻ የሆነ የሌላ አገር ገንዘብ በጥሬ ወይም በክፍያ መፈጸሚያ ካርድ (debit card) አማካኝነት ማግኘት ይችላሉ።

➡️ የውጭ ምንዛሪ የባንክ ሂሳብ ያላቸው ተጓዦች እስከ 10 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ድረስ ማግኘት ተፈቅዶላቸዋል።

በብሔራዊ ባንክ ካልተፈቀደ በስተቀር ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ነዋሪ በአንድ ጉዞ ላይ ከ10,000 የአሜሪካን ዶላር ወይም ተመጣጣኝ ገንዘብ በካሽ መያዝ አይችልም።

➡️ ለንግድ የሚጓዙ ግለሰቦችም የውጭ ምንዛሪ ማግኘት ይችላሉ።

➡️ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ፣ ፓስፖርት እና የአየር ትኬት ለሚያቀርቡ ለንግድ ድርጅት ተወካዮች የውጭ ምንዛሪ መሸጥ እንዲችሉ ተፈቅዷል። እነዚሁ ቢሮዎች ፦
- ለንግድ ድርጅቶች፣
- ለበጎ አድራጎት ተቋማት
- ለሃይማኖት ማኅበራት፣
- ለንግድ ትርኢቶች፣
- ለቱሪዝም
- ለባህል እና ለስፖርቶች አዘጋጆች የውጭ ምንዛሪ መሸጥ ይችላሉ።

➡️ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ለመንግሥት ተጓዦች ለምግብ፣ ለማረፊያ እና ሌሎች ተያያዥ ወጪዎች ከ10 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ወይም ተመጣጣኝ ገንዘብ የማይበልጥ የውጭ ምንዛሬ ሊሸጡ ይችላሉ።

➡️ ነዋሪ ላልሆኑ የውጭ አገር ዜጎች እና ቱሪስቶች ብርን ወደ ውጭ ምንዛሬ ሊለውጡ የሚችሉበት አሠራርም አለ። ፓስፖርት፣ ትክክለኛ ቪዛ እና የአየር ትኬት የሚያቀርቡ ሰዎች ያለማስረጃ እስከ 500 የአሜሪካን ዶላር መለወጥ ይችላሉ። ከ500 ዶላር በላይ መለወጥ የሚፈልጉ ከሆነ ፓስፖርት፣ ሕጋዊ ቪዛ፣ የአየር ትኬት እና ተመጣጣኝ የሆነው የውጭ ምንዛሪ በሕጋዊ መንገድ ወደ አገር ውስጥ ገንዘብ መቀየሩን የሚያሳይ የተረጋገጠ የባንክ ማስረጃ ማቅርብ ይጠበቅባቸዋል።

ተጨማሪ ከላይ ተያያዘውን ፋይል ከፍተው ያንብቡ !

#NBE #BBC #Ethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ethiopia

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቀደም ሲል በ38 የገቢ ንግድ ሸቀጦች ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ መነሳቱን በዛሬው ዕለት አሳውቋል።

ወደ ውጭ የሚደረግ የካፒታል ሂሳብ ፍስት እንደ በፊቱ የተገደበ እንደሆነ የውጭ ምንዛሪ ገበያው ለገቢ ሸቀጦችና አገልግሎቶች ነጻ መሆኑንም ገልጿል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዚህ ቀደም " ቅድሚያ የማይሰጣቸው " ተብለው የተለዩ 38 ዓይነት ምርቶች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ እግድ ጥሎ የነበረው የህገወጥ የምንዛሬ ገበያውን ይበልጥ ለማውረድ በማሰብ እንደነበር መገለጹ የሚዘነጋ አይደለም።

በወቅቱ 2014 ዓ/ም ላይ የአንድ የአሜሪካ ዶላር በባንክ ምንዛሬ 50 ብር ነበር ፤ አሁን ከ76 ብር ተሻግሯል።

አሁን እገዳው ተነስቶላቸዋል ከተባሉት 38ቱ የገቢ ንግድ ሸቀጦች ውስጥ ፦
➡️ የተገጣጠሙ የቤት አውቶሞቢሎች እና ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎች (የነዳጅ)
➡️ የተገጣጠሙ የሞተር ሳይክሎች
➡️ አርቴፊሻል ጌጣጌጦች
➡️ የታሸጉ ምግቦች
➡️ የተለያዩ የጸጉር ጌጣጌጦች
➡️ ከሴራሚክ እና ፖርስሊን የተዘጋጁ የቤት እቃዎች
➡️ የውበት ወይም የመኳካያ ዝግጅቶች
➡️ ሽቶዎች
➡️ የቤት እና የቢሮ እቃዎች ይገኙበታል።

(ወደ ሀገር እንዳይገቡ እግድ ተጥሎባቸው የነበሩ የገቢ ንግድ ሸቀጦችን ዝርዝር ከላይ ይመልከቱ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ውሎ ማደር፣ ወጥቶ መግባት በአንዳንድ የሀገራችን አካባቢዎች ስጋት ከሆነ ሰነባብቷል ! " - ቋሚ ሲኖዶስ ቋሚ ሲኖዶስ ፥ ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የምሕላ ጸሎት እንዲፈጸም አወጀ። በሀገር አስተማማኝ ሰላም ሲጠፋ በጾም በጸሎት በመወሰን ፣ ምሕላ ይታወጃል። ምሕላ የሚታወጀው ልባዊ በሆነ ተማሕጽኖ ሁሉን ማድረግ…
🔈#ማስታወሻ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ

" ሁሉም የቤተክርስቲያናችን አገልጋዮችና ምእመናን ሀገራዊ ፦
- ሰላምን፣ 
- መረጋጋትን
- ፍቅርን
- አንድነትን ለማስፈን ጾም እና ጸሎት በታወጀበት የምሕላ ሳምንት ለገዳማውያኑ ፀጥታ ሲባል ወደ ገዳማት የምታደርጉትን ጉዞ ለጊዜው እንዲቆይ አድርጋችሁ መደበኛ ሥራችሁን በያላችሁበት ቦታ እየሠራችሁ እግዚአብሔር የገዳማውያኑን ጸሎት ሰምቶ ለሀገራችንና ለሕዝባችን ምሕረትን እንዲሰጥ በኅሊና ዝግጅት፣ በሐሳብ አንድነት ሆናችሁ በጾም በጸሎት እንድተጉ ቋሚ ሲኖዶስ መንፈሳዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ "


ቋሚ ሲኖዶስ ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የምሕላ ጸሎት እንዲፈጸም ማወጁ አይዘነጋም።

#ኢትዮጵያ🙏

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#IMF : የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ኢትዮጵያ በጠየቀችው ብድር ላይ ለመወያየት ነገ ሰኞ ሐምሌ 22 / 2016 ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ብሎምበርግ ድረገጽ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የመረጃ ምንጮችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና ከዓለም ባንክ ጋር የምታደርገው ድርድር ከተሳካ በቀጣይ አመታት 10.5 ቢሊዮን ዶላር ልታገኝ እንደምትችል…
#Update

የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) አስፈጻሚ ቦርድ ለኢትዮጵያ የሚሆንና መጠኑ 2.556 ቢሊዮን SDR (የኮታው 850% ወይም ወደ 3.4 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ) የሆነ የ4 ዓመት የተራዘመ የብድር አገልግሎት አቅርቦት ዛሬ አጽድቋል።

ይህ የ4 ዓመት ፓኬጅ፦
- የማክሮ ኢኮኖሚ ሚዛን መፋለስን መፍታትን
- በግል ዘርፉ ለሚመራ እድገት መሠረት መጣልን
- የመንግሥትን የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አፈጻጸምን የሚደግፍ ነው ተብሏል።

ውሳኔው ኢትዮጵያ ከባላንስ ኦፍ ፓይመንት ጋር የተያያዙ ፍላጎቶቿን እንድታሟላ ይረዳታት ተብሏል።

በተጨማሪ በጀቷን የሚደግፈውን የ766.75 ሚሊዮን SDR ወይም 1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር አካባቢ የሚሆን ገንዘብ ክፍያ ወዲያውኑ እንዲለቀቅ የሚያስችል እንደሆነ ተጠቁሟል።

(ዝርዝር መረጃ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
2024/10/01 09:26:46
Back to Top
HTML Embed Code: