Telegram Web Link
#መምህራን

" የአማራ ክልል ከማንም ጋር የሚወዳደር አይደለም ፤ መምህራን ጥይት በላያቸው ላይ እያፏጨ ነው ያስተማሩት " - ማኀበሩ

የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር / ኢመማ / በአማራ ክልል የሚገኙ መምህራን ከባድ የሚባል ፈተና ለመጋፈጥ እየተገደዱ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

ቃሉን ለቲክቫህ የሰጠው ማኀበሩ፣ መምህራኑ በከፋ የጸጥታ ችግር ውስጥ ሆነው እየሰሩ ባለበት እንኳ ደመወዛቸው እየተቆረጠባቸው መሆኑን ገልጿል።

" የአማራ ክልል መምህራን የሚያስተምሩበት ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ወታደር፣ 'ፋኖ' እየሰፈሩ በዚያ ችግር ውስጥ ሆነው እንኳ መስዋዕትነት ከፍለዋል " ብሏል።

" አማራ ክልል ከማንም ጋር የሚወዳደር አይደለም " ያለው ማኀበሩ፣ ሚዲያዎች ግን ትኩረት እየሰጡት ባለመሆኑ ከአሁን ወዲያ ትኩረት እንዲሰጡ ጥሪ አቅርቧል።

በጣም ከአቅም በላይ በሆነባቸው አካባቢዎች ካልሆነ በስተቀር በጸጥታ ችግር ውስጥ የሚገኙት መምህራኑ ትምህርት እንዳይቋረጥ ጥረት ማድረጋቸውን አስረድቷል።

" ሱፐር ቫይዘር በሌለበት፣ የትምህርት መዋቅር እዚህ ግባ በሚባል ደረጃ በማይንቀሳቀስበት ሁኔታ አማራ ክልል የሚገኙ መምህራን ኮሚትመንት ወስደው እየሰሩ ነው " ሲል አክሏል።

" የአማራ ክልል መምህራን ጥይት በላያቸው ላይ እያፏጨ፣ በላያቸው ላይ የጥይት ሀሩር እየተወረወረ ነው ያስተማሩ። ይሄ በደንብ መታወቅ አለበት " ነው ያለው።

" መምህራን በዚህ ኮሚትመንት ልክ እየሰሩ ደመወዛቸው እየተቆረጠ ነው " ሲልም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

" በአንድንድ ምክንያቶች ሁለት ወራት፣ ሦስት ወራት ደመወዝ የተቆረጠባቸው አሉ " ያለው ማኀበሩ፣ " ግን ያ ደግሞ ውዝፉ ጭምር እየተከፈለ ነው " ብሏል።

የ8ኛ ፣ 6ኛ፣ 12ኛ ክፍል ፈተና ያልወሰዱ ተማሪዎች በቀጣይ የሚወስዱበት መንገድ እንዲመቻችም አሳስቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#Gofa

ዛሬ ከረፋዱ 4:00 ሰዓት አካባቢ፤ በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰ ድንገተኛ የመሬት ናዳ አደጋ የበርካታ ሰዎች ሕይወት አልፏል።

የወረዳው ዋና አስተዳደር ፥  እሰካሁን በተደረገው ፍለጋ ከ 20 በላይ አስከሬን መገኘቱን አመልክቷል።

የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል ተገልጿል።

በስፍራው ለነፍስ አድን ተግባር የተሰበሰቡ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ  የአካባቢው ነዋሪዎች የአደጋው ሰለባ መሆናቸውን ተሰምቷል።

በአደጋው ሰለባ ከሆኑት ሰዎች መካከል የወረዳው ፖሊስ አባላትን ጨምሮ ሴቶችና ሕፃናት እንደሚገኙ ተገልጿል።

በአሁኑ ሰዓት የአስክሬን ፍለጋና የነፍስ አድን ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

መረጃው ከገዜ ጎፋ ወረዳ ነው የተገኘው።

@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia

የሙዚቃ ወዳጆች ወዴት ናችሁ?! ፈጠን ፈጠን እያልን ሙዚቃችንን እንቅዳ እንጂ! የ1፟ደቂቃ መወዳደሪያ ሙዚቃችንን እያቀነቀንን ዛሬውኑ ውድድሩን እንቀላቀል! ማን ያውቃል?!🤯 የ400,000 ብር እድለኛ እናንተ ብትሆኑስ?!  አሁኑኑ የአንድ ደቂቃ ቪዲዮአችንን እንላክ!

የዲጂታል ሙዚቃ ውድድርን ለመቀላቀል፡
🎥 የአንድ ደቂቃ የራሳችን ሙዚቃ ቪዲዮ በTikTok ላይ እንፖስት
🏷 #1Wedefit እና #የምትኖሩበትከተማ አድራሻ ማስገባት እንዳንረሳ
📲የTikTok ደረገጽ @Safaricomet ታግ እናድርግ እንዝፈን! እንላክ! እናሸንፍ!

መልካም ዕድል!

#SafaricomEthiopia
#1Wedefit
TIKVAH-ETHIOPIA
" የሚዲያ ዘመቻችሁን እንድታቆሙ እንጠይቃለን " - የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ፥ " በሕገ-ወጥ መንገድ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይለማ የቆየ 280,000 ካሬ ሜትር ለልማት እንዲውል ማድረግ ሕገ- መንግስትን ማስከበር እና ማክበር እንጂ የሚያስወቅስ ጉዳይ አይደለም " አለ። ይህን ያለው ዛሬ ባወጣው ማሳሰቢያ ነው። አስተዳደሩ ፥ " ሕግ እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን ማስከበር የአንድ…
#Update

“ ሁለቱንም አካላት ፊት ለፊት ለማገናኘት የጋራ መድረክ ይዘናል ” - የኃይማኖት ተቋማት ጉባዔ

የኢትዮጵያ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታዋን የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር “በጉልበት ሊወስደው ነው” ስትል በተደጋጋሚ ቅሬታ ማቅረቧ ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቅሬታው ምላሽ የጠየቀው የከተማ አሰተዳደሩ በበኩሉ፣ “ መሬቱ በNGO እጅ የነበረ ነው ” የሚል ምላሽ ሰጥቶ ነበር።

ይህንኑ የከተማ አስተዳደሩን ምላሽ የተመለከተችው ቤተክርስቲያኗ፣ “ መሬቱ በጭራሽ በNGO እጅ ገብቶ አያውቅም ከመጀመሪያው ጀምሮ የቤተ ክርስቲያኗ እጅ የነበረ ነው ” የሚል አጸፋ መሰጠቷ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ኃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ስለጉዳዩ ምን አለ ?

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሁለቱም አካላት በጋራ ተወያይተው ችግራቸውን እንዲፈቱ በተናጠል እንዳነጋገራቸው ገልጿል።

የጉባዔው ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ሁለቱንም አካላት ፊት ለፊት ለማገናኘት የጋራ መድረክ ይዘናል ” ብለዋል።

“ ህዝቡ ወዴት ይሄዳል ? ሰው ሲያኮርፍ ወዴት ያመራል ? የሚሉ ጉዳዮች ይኖሬሉ ” ያሉት ዋና ፀሐፊው፣ “ ስለዚህ ይህንን ቁጭ ብሎ Manage ማድረግ ያስፈልጋል ” ሲሉ ተናግረዋል።

ሁለቱም አካላት በጋራ ለመነጋገር ፈቃደኞች እንደሆኑ ነገር ግን ጉዳዩ ገና በሂደት ላይ እንደሆነ፣ ወደ ስምምነት እንዲመጡ ለማድረግ ጉባዔው የጋራ መድረክ እንዳዘጋጀ አስረድተዋል።

የከተማ አስተዳደሩን በተናጠል እንዳወያዩ፣ ቤተ ክርስቲያኗን ለማወያዬት በሂደት ላይ እንደሆኑ የገለጹት ዋና ፀሐፊው፣ “ አንድ ሳምንት ሊፈጅብን ይችላል ጨፌ ስብሰባ ስለገቡ ዋናዎቹ። የጋራ ፕሮግራም ይዘናል እንወስናለን ” ብለዋል።

ጉባዔው ሁለቱም አካላት የቃላት ውርዋሮ አቁመው ወደ ስምምነት እንዲመጡ የማግባባት ሥራ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
Tassa Tassa Tassa 😭

በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በደረሰው ድንገተኛ የመሬት ናዳ አደጋ የሟቾች ቀጥር ከ55 በላይ ደርሷል።

የአስከሬን ፍለጋው አሁንም ቀጥሏል።

የመሬት ናዳ አደጋው ዛሬ ከረፋዱ 4:00 ሰዓት አካባቢ ነበር የደረሰው።

እስከ አሁን ከ55 በላይ አስከሬን ተገኝቷል።

የሟቾች ቁጥር አሁንም ከዚህ ሊያሻቅብ እንደሚችል ይገመታል።

ሌሊት የዘነበውን ከፍተኛ ዝናብ ተከትሎ ነው የመሬት ናዳው የደረሰው።

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

በአቢሲንያ ቪዛ ካርድዎ ላይ ከፊት እና ጀርባ የሚገኘውን ቁጥር እና የካርዱ አገልግሎት የሚያበቃበትን ቀን ብቻ በመጠቀም ካሉበት ሆነው ክፍያዎችን በኦንላይን በቀላሉ ማከናወን ይችላሉ።
ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ! https://www.tg-me.com/BoAEth

አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!


#BankofAbyssinia #Banking #VisaCard #Visa #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
የ13ኛ ዙር #ንቁ_ተሳታፊ 10 ጊ.ባ ወርሃዊ የሞባይል ጥቅል አሸናፊዎች እንኳን ደስ አላችሁ!

ትክክለኛውን የኢትዮ ቴሌኮም https://twitter.com/ethiotelecom እና የቴሌብር https://twitter.com/telebirr የትዊተር ገጾች በመከተል መልዕክቶችን ላይክ፣ ኮሜንት እንዲሁም ሼር በማድረግ 10 ጂቢ ወርሃዊ የኢንተርኔት ጥቅል ሽልማት በዕጣ ያሸንፉ!

ዕድለኞች በትዊተር ገጾቻችን በውስጥ መልዕክት የስልክ ቁጥርዎን በ24 ሰዓት ውስጥ ይላኩልን!

ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #TPLF " ' አቶ ጌታቸው ሰብሰባው ረግጠው ወጡ ' ተብሎ በተለያዩ የማህበራዊ የትስስር ገፆች የሚሰራጨው ወሬ ልክ አይደለም " - የስብሰባው ተሳታፊ ከሰሞኑን ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ስብሰባ ላይ ነበር የከረመው። ስብሰባው 11 ቀናትን የፈጀ ነበር። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የትግራይ ክልል ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 5 የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ አበላት ከድርጅቱ የከፍተኛ…
#TPLF

" ህወሓት በሁለት ኔትወርክ ተከፍሎ እየታመሰ ነው " - የቁጥጥር ኮሚሽን ሊቀመንበር ተክለብርሃን ኣርአያ

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ለ11 ቀናት ያካሄደው ዝግ ሰብሰባ የአቋም መግለጫ በማውጣትና በያዝነው ወርሃ ሀምሌ ጉባኤ ለማካሄድ ወስኖ ማጠናቀቁ መዘገባችን ይታወሳል።

ህወሓት ዝግ ስብሰባው በማስመልከት የድርጅቱ የቁጥጥር ኮሚሽን ሊቀመንበር ተክለብርሃን ኣርአያ ከድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ቃለ-መጠይቅ አካሄደዋል።

ሊቀመንበሩ በቃለ-መጠይቃቸው ምን አሉ ?

ስብሰባውና ግምገማው ከመጀመሪያው በውጭ የተጠናቀቀ መጠላለፍ እና ተንኮል ያየለበት እንደነበር ጠቁመዋል።

" የአመራር አንድነት አልነበረም " ሲሉ ገልጸዋል።

ስብሰባውና ገምገማው በሁለት ኔትወርክ የተከፈለ እንደነበረ ገልጸውል።

" በሰብሰባው የመናገር አድል ያገኘው ደጋፊ እንጂ ተቃዋሚ አድሉ ተነፍጎታል " በማለት አብራርተዋል።  

፣ የመናገር እድል ያገኙ ደጋፊዎች ለአንድ ወይም ለግማሽ ሰአት ብቻቸው በመናገር የሰብሰባ ጊዜ ሲያባክኑ ታይተዋል " ያሉት ተክለብርሃን " ስብሰባውና ገምገማው ነፃና ዴሞክራሲያዊ አልነበረም " ሲሉ ተናግረዋል።

አመራሩ በኔትወርክ እየታመሰ ነው ሲሉም አክለዋል።

" የተፈጠረው ችግር ለማጣራት የተቋቋመው ኮሚቴ በህወሓት ውስጥ ሁለት ኔትወርክ መኖሩ አረጋግጧል " የሚሉት ሊቀመንበሩ  " ኔትወርኩ ሳይበጣጠስ የአመራር አንድነት አይረጋገጥም " ሲሉ ተናግረዋል።

" ስብሰባውና ገምገማው አሰልቺ ከመሆኑ የተነሳ ' ተሰበሰብኩ አልተሰበሰብኩ ለውጥ የለውም ' በማለት መድረኩ ረግጠው የወጡ አመራር አሉ " ብለው ፣ ግምገማው የሚፈለገውን ፍሬ አላፈራም "  በማለት ጨምረዋል።  

" ድርጅቱ ጉባኤውን እንዲያካሂድ እንደግፋለን ቢሆንም ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እንጂ አሁን ባለበት አፋኝ አካሄድ መሆን የለበትም " ሲሉ የመፍትሄ ሃሳብ አቅርበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
Tassa Tassa Tassa 😭 በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በደረሰው ድንገተኛ የመሬት ናዳ አደጋ የሟቾች ቀጥር ከ55 በላይ ደርሷል። የአስከሬን ፍለጋው አሁንም ቀጥሏል። የመሬት ናዳ አደጋው ዛሬ ከረፋዱ 4:00 ሰዓት አካባቢ ነበር የደረሰው። እስከ አሁን ከ55 በላይ አስከሬን ተገኝቷል። የሟቾች ቁጥር አሁንም ከዚህ ሊያሻቅብ እንደሚችል ይገመታል። ሌሊት የዘነበውን ከፍተኛ ዝናብ ተከትሎ ነው የመሬት…
#ጎፋ 🕯

በጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ፣ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በመሬት ናዳ ሳቢያ የሞቱ ወገኖች አስከሬን ፍለጋ እንደቀጠለ ነው።

እስከአሁን በሰው ኃይል በተደረገ ቁፋሮ የ157 ሰዎች አስከሬን ተገኝቷል።

እስከአሁን ህፃናትን ጨምሮ 105 ወንዶች እና 52 ሴቶች በአደጋው መሞታቸው ተረጋግጧል።

የተረፉ የቤተሰብ አባላትን ወደ አንድ ቦታ የማሰባሰብ ስራም እየተሰራ ነው።

የሟቾች ቁጥር ከዚህ በላይ ሊያሻቅብ እንደሚችል ተመላክቷል።

የነፍስ አድን ሥራው አሁንም ቀጥሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈#የሰራተኞችድምጽ " የደመወዝ ጥያቄ እንዳንጠይቅ በፖሊስ መደብደባችንን እና መታሰራችን የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልን !! " - የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎች እና ሰራተኞች " ከግንቦት ወር ጀምሮ ደመወዝ አልተከፈለንም " ያሉ የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የጤና ባለሙያዎችና ሰራተኞች ያሉበትን ችግር እና ቅሬታቸውን ለመግለጽ ወደዞን መምሪያ በመሄድ ላይ ሳሉ በፖሊስ ተደብድበው መመለሳቸውን…
#Update

° " የተቆራረጠ ደሞዝ አንወስድም ምክኒያቱም ካሁን በፊትም እንዲሁ ተደርገናል " - የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰራተኞች

° " የተፈጠረው የካሽ እጥረት በመሆኑ ወደስራ ተመለሱ " - የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ


የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰራተኞች " ከግንቦት ወር ጀምሮ ደሞዝ አልተከፈለንም " በሚል ስራ አቁመው ወደ ዞኑ ጤና መምሪያ ጥያቄ ለማቅረብ ለመሄድ ሲሞክሩ በሀድያ ዞን ፖሊስ ተደብድበው ወደ ሆሳዕና ከተማ እንዳይገቡ መደረጋቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው ይታወሳል።

ጉዳዩን ከምን ደረሰ ? ስንል ጥያቄ ያቀረብንላችሁ ሰራተኞቹ አሁንም ስራ እንዳቆሙ መሆኑን በመግለጽ የተፈቀደውን የአንድ ወር ደሞዝ እንዳይወስዱ በ2015 ዓ/ም በዚህ መልኩ እንደተቃጠለው ገንዘባቸው እንዳይሆን ስጋት እንደገባቸው ገልጸዋል።

ሰራተኞቹ አሁን ላይ ውይይት አድርገዉ አንዳች ውሳኔ ላይ ለመድረስ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን በመግለጽ በቅርቡ አቋማቸውን እንደሚገልጹ ነግረዉናል።

የሰራተኞቹን ስራ ማቆም ተከትሎ በስራ ላይ  ችግር አልተፈጠረም ወይ ? ስንል ጥያቄ ያቀረብንላቸው የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ  አብርሀም ሎምቤ ፥ " ስራ ያላቆሙ ሰራተኞች በጫና ውስጥ ሆነው እየሰሩ ቢሆንም ስራ ያቆሙ ሰራተኞች ወደስራ ገበታቸው ተመልሰው ብንነጋገር የተሻለ ነው " ብለዋል።

ለምን የሰሩበትን ክፍያ አትሰጧቸውም ? በሚል ላነሳነው ጥያቄ " የካሽ እጥረት ነው የተፈጠረው ፤ የካሽ እጥረት እንደሀገር የሚገጥም በመሆኑ ክፍያቸው አይቀርባቸውም " ሲሉ መልሰዋል።

በሌላ በኩል ስራቸውን ያቆሙ ሰራተኞች ወደስራ መመለሳቸውን በደብዳቤ እየገለጹ የአንድ ወር ደሞዝ ይውሰዱ ስለተባለው ጉዳይ የጠየቅናቸው አቶ አብርሀም " ዋናው ወደስራ መመለሳቸው በመሆኑ በቃልም ቢሆን ከሰው ሀብት ጋር ተነጋግረን ስራ መጀመር ይችላሉ " ብለዋል።

ሰራተኞች ግን ባለሙያ ሆስፒታል ውስጥ እንደሌለ እየታወቀ ማስታወቂያው የተነገረው ብለዋል።

" ሲጀመር የሰኔዉ ላይ ለመወያየት ቀድሞ የግንቦት የት ነዉ ያለዉ ስላልን ነዉ ይሄ ሁሉ በደል የደረሰብን። " ሲሉ ገልጸዋል።

" አሁንም የግንቦት ላባችን እንዳይበላ ሁሉም ይወቅልን " ብለዋል።

ሰራተኞቹ አስገዳጅ ሁኔታ ተፈጥሮ የሰኔ ላይ እንዲፈርሙ ከተደረጉ በኃላ የግንቦቱ ክፍያቸው ተበልቶ ሊቀር ይችላል ሚል ስጋት እንዳላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
2024/09/30 18:13:12
Back to Top
HTML Embed Code: