Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈#የነዋሪዎችድምጽ " የምንኖረው በኮንሶና አካባቢው ነው። የመብራት ለቀናት መጥፋት እና መቆራረጥ ከፍተኛ ችግር በስራችን እና በህይወታችን ላይ እያደረሰ ነው። ለቀናት ሲጠፋ ችግሩን ለመንግስት እንዳንናገር ድንገት ይመጣል መጣ ስንል ደግሞ በአንድ ሰአት ውስጥ ሁለት ሶስቴ ይቆራረጣል። አሁን ላይ ስራ መስራት አስቸጋሪ ሆኗል። በመብራት የሚሰሩ ስራዎች በተለይም ጸጉር ቤቶች ፣ ብየዳና የማሽነሪ ስራዎች…
#Update

" ለኮንሶና አካባቢው የመብራት ችግር አርባምንጭ ላይ ተጨማሪ የመብራት ማስተላለፊያ ሰብስቴሽን ይገነባል " - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰመስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ

" ለኮንሶ ዞን የራሱ የሆነ ሀይል ማሰራጫ ነው የሚያስፈልገው " -  የኮንሶና አካባቢው ወጣቶች

ከሰሞኑ የኮንሶና አካባቢዉ ማህበረሰብ በመብራት ኃይል መቆራረጥና መጥፋት ስራ እስከመዝጋት መድረሳቸዉን ገልጸዉ  መንግስት መፍትሄ እንዲሰጣቸዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ማሰማታቸው ይታወሳል።

ከሰሞኑ በተካኬደው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ም/ቤት ስብሰባ ወቅት ጉዳዩን ያነሱት የክልሉ ርእሰመስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ " ለኮንሶና አካባቢው የመብራት ችግር አርባምንጭ ላይ ተጨማሪ የመብራት ማስተላለፊያ ሰብስቴሽን ይገነባል " ማለታቸው ተሰምቷል።

" በርእሰ መስተዳድሩ ንግግር ቅር ተሰኝተናል " ያሉ ግለሰቦች " በኮንሶና አካባቢዉ ሰላማዊ ሰልፍ እናካሂዳለን " በማለት በሶሻል ሚዲያ ቅስቀሳ ሲያደርጉ ተስተውለዋል።

ወጣቶቹ ለቅሬታቸዉ ምንጭ የሆነው የርእሰመስተዳድሩ ንግግር መሆኑን ጠቅሰዉ " ለኮንሶና አካባቢው ከባድ የመብራት ኃይል ችግር መፍትሄው ኮንሶ ላይ እንጅ አረባምንጭ ላይ ተጨማሪ ሰብስቴሽን መገንባት አይደለም "  ብለዋል።

በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸዉ የኮንሶ ዞን መንግስት ኮምዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ሰራዊት ቲቶ ፥ " የርእሰመስተዳድሩን ንግግር ተከትሎ የሶሻል ሚዲያ እንቅስቃሴዎች ቢኖሩም ከተማዋ ፍጹም ሰላማዊ መሆኑን ገልጸው ሁኔታውን በመጠቀም ችግር ለመፍጠር የሚያሴሩ እንዳሉ እናውቃለን " ብለዋል።

ኃላፊዉ አክለውም የመብራት ችግሩን ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው የክልል አመራሮችና ከፍተኛ የመብራት ኃይል  ባለስልጣናት ጋር ዉይይት እንደተካሄደ በመጥቀስ የአጭርና የረጅም ጊዜ እቅድ በማውጣት በአጭር ጊዜ ቅስጥ መፍትሄ ለመስጠት ተወስኖ እንቅስቃሴ መጀመሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
🔈#የመምህራንድምጽ

“ የ3 ወራት ደመወዝ አልተከፈለንም ” - የአፋር ክልል መምህራን 

“ ያልተመገበ መምህር ክፍል ግባ ቢባልም ሊገባ አይችልም ” - የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር


በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ የሚገኙ መምህራን ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው፣ በዚህም ቤተሰብ ራሱ ማስተዳደር እንዳልቻሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

መምህራኑ፣ “ የ3 ወራት ደመወዝ አልተከፈለንም። ታዲያ ቤተሰብስ እንዴት እናስተዳድር? ” ሲሉ በአንክሮ ጠይቀዋል።

ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው የሚመለከታቸውን አካላት እንደጠየቁ፣ ሆኖም መፍትሄ እንደሌለ፣ በዚህም ችግር ላይ እንደሆኑ አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበርም ቅሬታው አግባብ መሆኑን ገልጾ፣ “ እንደውም እስከ ርዕሰ መስተዳደሩ ቢሮ ድረስ ጋውናቸውን ለብሰው ሂደው በክልሉ ልዩ ኃይል ነው የተመለሱት ” ብሏል።

የማኀበሩ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አበበ ለቲክቫህ በሰጡት ቃል፣ “ ቅሬታቸው የቆዬ ነው። የ3 ወራት ደመወዝ ተባለ እንጂ ከ2012 ዓ/ም ጀምሮ የትምህርት ማሻሻያ፣ የደረጃ እድገት የማይሰጥበት አካባቢ አለ ” ብለዋል።

“ አሁን ላይ ደግሞ ደመወዝ ይቆረጣል። ለድርጅት ተብሎ ሁሉ ደመወዝ የሚቆረጥበት አካባቢ አለ ” ሲሉ ተናግረዋል።

መምህራኑ የ3 ወራት ደመወዝ እንደተቆረጠባቸው፣ በዚህም የክልሉ መምህራን ማኀበር፣ የክልሉ ትምህርት ቢሮ የሚመለከታቸውን አካላት ለማነጋገር  ጥረት እንዳደረጉ የገለጹት አቶ ሽመልስ፣ “ ታች ያለው አመራር የላይኛውን የሚሰማ አይደለም ” ብለዋል።

“ መምህራን ግን ለከፋ የመልካም አስተዳደር ችግር እየተጋለጡ ናቸው፤ እዚያ አካባቢም (ሰመራ) በጣም የከፋ ችግር ነው ያለው ” ሲሉ አክለዋል።

ታዲያ ማኀበሩ ለቅሬታው ምን ምላሽ አገኘ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ “ ቀደም ብለን ለርዕሰ መስተዳደሩ አቶ አወል አርባ ደብዳቤ ፅፈንላቸዋል። እሳቸውም ለታችኛው መዋቅር ችግሮቹ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ብለው በደብዳቤ አሳውቀዋል ” ብለዋል።

ሆኖም ከታች ያሉት አመራሮች ጉልበተኛ እንደሆኑ ነው አቶ ሽመልስ ያስረዱት።

“ አንድ መምህር ደመወዙ እየተቆረጠበት፣ ጉልበቱ ሌላ ጋ ከሆነ፣ ያልተመገበ መምህር ክፍል ውስጥ ግባ ቢባልም ሊገባ አይችልም። በጉልበት ቢገባ እንኳ ያስተምራል ወይ ? የሚለው ሌላ ጥያቄ ነው ” ብለዋል።

ይህ ድርጊት መማር ማስተማሩ ላይ በቀጣይ ከፍተኛ ጉዳት እንዳያስከትል ከፍተኛ ስጋት እንዳላቸው ገልጸው፣ “ ምስቅልቅሉ የወጣ አሰራር ነው ያለው ” ሲሉ ወቅሰዋል።

“ የታችኛው አመራር ለትምህርት የማያስብ፣ ለጊዜው ለፓለቲካ ተቆጥሮ የማሰጠውን አጀንዳ ብቻ ትኩረት አድርጎ የሚሰራ፣ መደማመጥ የሌለበት፣ ለትውልድ የማያስብ አመራር እያየሁ ነው ” ነው ያሉት።

በአማራ ክልል ያለው የመምህራን ቅሬታ በቀጣይ ይቀርባል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሁሉንም ታላላቅ ሊጎች ለሁላችንም!

ሁሉንም ወሳኝ ጨዋታዎች ፣ ደማቅ ግጥሚያዎች ፣ የዋንጫ ፍልሚያዎች በዲኤስቲቪ!

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ፣ ቻምፒዮንስ ሊግ ፣ ላሊጋ ፣ ሴሪአን ጨምሮ ከጨዋታ እስከ ትንታኔ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ ... ሁሉም በዲኤስቲቪ!

እንደየምርጫዎ በሁሉም ፓኬጅ ላይ ኳስ ያለው ዲኤስቲቪ!

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#DStvEthiopia
#ሁሉምያለውእኛጋርነው
#DStvSelfServiceET
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#EAES

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና መጠናቀቁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

ፈተናው በወረቀት እና በበይነ መረብ መሰጡቱን ገልጿል።

ዛሬ ፈተናቸውን ያጠናቀቁ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ ናቸው።

በተመሳሳይ መልኩ በትግራይ ክልል እየተሰጠ ያለው የመልቀቂያ ፈተና ነገ ከሰዓት በፊት ይጠናቀቃል።

@tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba

የትራፊክ ማኔጅመንት የራሱን የተቋሙን በከፍተኛ ቦታ ላይ የሚገኙ ኀላፊን ማብራሪያ " የእኔ አቋም አይደለም " አለ።

በአዲስ አበባ ከተማ የኮድ 2 ተሸከርካሪዎች በፈረቃ እዲንቀሳቀሱ ሊደረግ መሆኑን ይህም ከ2 እስከ 3 ወር ባለው ጊዜ ወደ ተግባር እንደሚገባ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ማሳወቁ ይታወቃል።

መ/ቤቱ ይህንን ያሳወቀው በአንድ ከፍተኛ አመራሩ ነው።

በዛሬው ዕለት ደግሞ እራሱ ባለስልጣን መ/ቤቱ " ይሄ ወደፊት በጥናት የሚሆን እንጂ በቅርቡ  ተግባራዊ የሚሆን አይደለም " ብሏል።

መ/ቤቱ ፤ " ' በአዲስ አበባ ከተማ  ጥዋት እና ማታ የሚታየውን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቀነስ ኮድ 2 ተሽከርካሪዎች በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ ሊደረግ ነው ' በሚል ርእስ በተቋሙ የትራንስፖርት ቁጥጥር ደንብ ማስከበር ኩነት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር /ተወካይ/ አቶ አያሌው ኢቲሳ ለሸገር ኤፍ ኤም የሰጡት ማብራሪያ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አቋም አይደለም "  ብሏል።

" ግለሰቡ ' ጎዶሎ ቁጥር እና ሙሉ ቁጥር የኮድ 2 ተሽከርካሪዎችን በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ የሚያደርግ የሕግ ማዕቀፍ መዘጋጀቱንና የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን፥ በሁለት እና በሶስት ወር ጊዜ ውስጥ በከተማው ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኮድ 2 ተሽከርካሪዎች ወደ ፈረቃ እንዲገቡ ይደረጋል ' ያሉት ከተቋሙ ያገኙትን መረጃ ተንተርሰው አይደለም " ሲል አክሏል።

"ጎዶሎ ቁጥርና ሙሉ ቁጥር ኮድ 2 ተሽከርካሪዎችን በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ የሚያደርግ የሕግ ማዕቀፍ ወደ ፊት ከመንግስት በሚሰጥ አቅጣጫ ተጠንቶ የሚሆን እንጂ በአሁኑ ወቅት ይህንኑ ተግባራዊ የሚደረግበት ሁኔታ የለም " ብሏል።

በአዲስ አበባ የኮድ 2 ተሽከርካሪዎች ከ2 እስከ 3 ወር ባለው ጊዜ በስራ መግቢያ እና መውጫ ሰዓት በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ ሊደረግ መሆኑን ያሳወቁት የአ/አ ትራፊክ ማኔጅመንት ፦
- የትራንስፖርት ቁጥጥር ደንብ/ማስ/ኩነት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
- የተቋሙ ተወካይ
- በተቋሙ ውስጥ የሚሰሩ
- የህግ ማዕቀፍም ተዘጋጅቶ ማለቁን በእርግጠኝነት የተናገሩ ሰው ናቸው።

ነገር ግን ይህ መረጃ ይፋ ከሆነ ከአንድ ቀን በኋላ ተቋሙ " የግለሰቡ ማብራሪያ እኛን አይወክልም ፤ ማብራሪያውን የሰጡት ከተቋሙ መረጃ አግኘትውም አይደለም " ብሏል።

ይህን ማስተባበያ የተመለከቱ አስተያየት ሰጪዎች ቀድሞውኑ የህዝቡ ትርታ ለማድመጥ የተደረገ ነው ብለውታል።

" እንዴት አንድ ተቋም የራሱን ሰራተኛና ከፍ ባለ ቦታ የሚገኝ ኃላፊ እኔን አይወክልም ይላል ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

በመሰረቱ ይህ ተግባራዊ ይደረግ ቢባልም የማይሆን እንደሆነ አስምረውበታል።

#AddisAbaba #ኮድ2

@tikvahethiopia
ወላጆች ልጆቻችሁን ጠብቁ !!

በክረምት የእረፍት ጊዜ ወላጆች ለልጆቻቸው በቂ ጥበቃ እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና ሥራ አመራር ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል አሳሰበ።

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ፣ ዛሬ (ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ.ም) ከቀኑ 8 ሰዓት ገደማ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ወረገኑ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ውሃ ባቆረ ጉድጓድ የገባ ታዳጊ ህይወቱ ማለፉን ገልጸዋል።

" ውሃ ባቆረ ጉድጓድ ዋና ለመዋኘት የገባ የ13 ዓመት ታዳጊ ህይወቱ አልፏል" ያሉት አቶ ንጋቱ፣ "የኮሚሽኑ ጠላቂ ዋናተኞች የታዳጊውን አስከሬን አውጥተው ለፖሊስ አስረክበዋል " ብለዋል።

" በአዲስ አበባ ታዳጊዎችና ወጣቶች በቂ የዋና ችሎታ ሳይኖራቸው ለዋና በሚል ውሃ ባቆሩ ጉድጓዶች እየገቡ ህይወታቸውን ያጣሉ " ነው ያሉት።

አሁን ትምህርት ቤቶች ዝግ ስለሆኑ ታዳጊዎችና ወጣቶች ለጨዋታ በሚል ድርጊቱን ስለሚፈጽሙ ወላጆች በቂ ጥበቃ እንዲያደርጉላቸው አሳስበዋል።

ኮሚሽኑ አደጋውን ለመከላከል የሚያሰችሉ በሚል በተደጋጋሚ የሚያስተላልፋቸውን የጥንቃቄ መልዕክቶች ህብረተሰቡ፣ በተለይ ወላጆች፣ ታዳጊዎችና ወጣቶች  እንዲተገብሩ ጠይቋል።

ችግሩ እየተደጋገመ መሆኑ የተመላከተ ሲሆን፣ በዚህ አደጋ ምን ያህል ታዳጊዎች ህይወታቸውን እንዳጡ በቀጣይ የሚዳሰስ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
አቢሲንያ በየዕለቱ እያስገረመን ነው፤ አሁን ATM ካርድ ቢረሳ ስልክ የATM ካርድን ስራ ይሰራል።
መተግበሪያውን በማውረድ ካርዶትን ዲጂታል ቪዛ ካርድ ያድርጉ።

ለአንድሮይድ ስልኮች https://play.google.com/store/apps/details?id=com.boa.apollo&hl=en&gl=US
አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!
#DigitalVisacard #Visa #ApolloVisacard #BoAVisacard #Visacard #Digitalethiopia #Apollodigitalbank #Apollodigitalproduct #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቪድዮ : የቀድሞ የአሜሪካ ፕ/ት ዶናልድ ትራምፕ የግድያው ሙከራ በተደረገባቸው ወቅት እሳቸው ቅስቀሳ ከሚያደርጉበት ስፍራ በቅርብ ርቀት በሚገኝ ጣሪያ ላይ የነበሩ የ " ሴክሬት ሰርቪስ " የስናይፐር ተኳሾች የግድያ ሙከራውን ባደረገው ሰው ላይ ምላሽ ሲሰጡ ታይተዋል። አንድ ተቀርጾ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨ ቪድዮ ሁለት የሴክሬት ሰርቪስ ስናይፐር ተኳሾች በፍጥነት ኢላማ አድርገው የግድያ ሙከራ ባደረገው…
#USA

የአሜሪካ የቀድሞ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ የሪፐብሊካን ፓርቲ እጩነታቸው ትላንት ተቀብለዋል።

ከቅዳሜው የግድያ ሙከራ በኋላ ሪፐብሊካኖች ለዶናልድ ትራምፕ ጠንካራ ድጋፋቸውን ከምን ጊዜውም በላይ አሳይተዋል። 

" የሁሉም አሜሪካውያን ፕሬዝዳንት እሆናለሁ " ያሉት ዶናልድ ትራምፕ ፦

- በሀገር ውስጥ ሕገወጥ ስደተኞችን ማባረር፣

- ኢኮኖሚውን ማሳደግ

- ግብር መቀነስን በዋና ግብነት አስቀምጠዋል።


በውጪ ግንኙነታቸውም የጋዛና የዩክሬይንን ግጭት መፍትኄ ከመስጠት ጀምረው ዓለምን ካጣችው ሰላም ጋር እንደሚያስታርቋት ቃል ገብተዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳሉ የዴሞክራቶች ፓርቲን በመወከል ተወዳድረው የአሜሪካ የቀድሞ ፕሬዚደንት የነበሩት ባራክ ዖባማ ፕሬዚደንት ጆ ባይደን እጩ የኋይት ሐውስ ተወዳዳሪ መሆናቸው እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል።

ባራክ ኦባማ ሁሉ የቀድሞዋ የምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲም ሥጋታቸውን ገልጠዋል። #DW

@tikvahethiopia
🔈#የሰራተኞችድምጽ

" የደመወዝ ጥያቄ እንዳንጠይቅ በፖሊስ መደብደባችንን እና መታሰራችን የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልን !! " - የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎች እና ሰራተኞች

" ከግንቦት ወር ጀምሮ ደመወዝ አልተከፈለንም " ያሉ የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የጤና ባለሙያዎችና ሰራተኞች ያሉበትን ችግር እና ቅሬታቸውን ለመግለጽ ወደዞን መምሪያ በመሄድ ላይ ሳሉ በፖሊስ ተደብድበው መመለሳቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

" ሰራተኞቹ ደመወዝ እና ጥቅማጥቅም ካየን ይሄው ሶስተኛ ወራችን ቢሆንም የሆስፒታሉ አመራሮችም ሆኑ ዞኑ ለጥያቄያችን ምላሽ መስጠት እንኳን አልፈለጉም " ብለዋል።

" ይህንም ተከትሎ ለሆስፒታሉ አመራር ከዚህ በላይ መታገስም ሆነ ችግሩን መቋቋም እንደማንችል በደብዳቤ አሳዉቀን ሁኔታውን በተጨማሪ ለሀድያ ዞን አስተዳደር ለማሳወቅ ስናቀና የዞኑ  ፖሊስ ደብድቦ መልሶናል " ሲሉ ተናግረዋል።

" በህዝብ ትራንስፖርት ተሳፍረን ስንሄድ የዞኑ ፖሊስ ዱራሜ ላይ አስቁሞ በሀይል በማስወረድና በመደብደብ  ወደመጣንበት እንድንመለስ አደረገን " የሚሉት ሰራተኞቹ ወደ ሾኔ ሲመለሱ መሪዎች ናቸው የተባሉ ጥቂት ሰዎች ለሰአታት ታስረው መፈታታቸው ገልጸዋል።

" ከችግራችን በላይ እየደረሰብን ያለውን ግፍ የኢትዮጵያ ህዝብ ይስማልን " ያሉት የሆስፒታሉ ሰራተኞች " በዚህ አመት ከተከለከልነው ደሞዝ ባለፈም በ2015 ዓ/ም ያልተከፈለ  ውዝፍ ገንዘብ ነበረን " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰራተኞችን የደረሰባቸውን ነገር እና ቅሬታቸውን ይዞ የሾኔ የመጀመሪያ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተእ ዶ/ር መሀመድን አህመድ አነጋግሯል።

እሳቸውም ሰራተኞቹ በደብዳቤ ስራ ማቆማቸውን ገልጸው ወደስራ መመለስ የሚፈልግ ደብዳቤ በማስገባት ስራ መጀመር እንደሚችልና የአንድ ወር ደመወዝም እንደሚከፈለው ገልጸዋል።

ሌሎች ቀሪ ክፍያዎችን በተመለከተ ወደፊት ለመክፈል መታቀዱን የገለጹት ኃላፊው ይህም ጉዳይ በክልልና በከተማ አስተዳደሩ የተያዘ መሆኑን ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደምም የዚህ ሆስፒታል የጤና ባለሙያዎች እና ሰራተኞች ከደመወዝ እና ከጥቅማጥቅም ጋር በተያያዘ እየደረሰባቸው ስላለው ችግር ማሳወቃቸው አይዘነጋም።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ገደብ የለሽ ከክፍያ ነጻ የመልዕክት ልውውጥ በቴሌብር ኢንጌጅ!!

ከግብይትና ገንዘብ ከማስተላለፍ ባሻገር ቪዲዮ፣ ድምጽ፣ ፎቶ፣ ጽሑፍ እና የተለያዩ ፋይሎችን በነጻ ማጋራት ያስችልዎታል፡፡

ቴሌብር ሱፐርአፕ http://onelink.to/fpgu4m ላይ ያገኙታል፡፡

ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ !

ለማንኛውም ጥያቄ፣ አስተያየት ወይም ቅሬታዎ በ https://www.tg-me.com/EthiotelecomChatBot ያግኙን!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #SmartAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
ያለሙትን አሳክተው እፎይ የሚሉበትን የተሻለ አማራጭ ይዘን እየመጣን ነው‼️
በቅርብ ቀን ይጠብቁን …
2024/09/30 14:25:28
Back to Top
HTML Embed Code: