Telegram Web Link
#ስፖርት #ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኢትዮጵያ ፕሪሜየር ሊግ ሻምፒዮን ሆነ።

ቡድኑ ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ፍጻሜውን እስካገኘበት የሊጉ የመጨረሻ መርሃግብር ድረስ ከመቻል የእግር ኳስ ቡድን ጋር አንገት ለአንገት ተናንቆ ነው ሻምፒዮን የሆነው።

ዛሬ በተካሄደ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ መድህንን 2 ለ 0 ማሸነፍ ችሏል።

በዓመቱ 64 ነጥብ በመሰብሰብም ከመቻል በ1 ነጥብ በልጦ አጠናቋል።

መቻል በዓመቱ የፍጻሜ መርሃግብር ከድሬዳዋ ከተማ ጋር ተፋልሞ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ቢያሸንፍም በ1 ነጥብ ተበልጦ ዋንጫውን ተነጥቋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ በመጣበት አመት በታሪኩ የመጀመሪያው የሆነውን የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ዋንጫ ማሳካት ችሏል።

ቲክቫህ ስፖርት👇
https://www.tg-me.com/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethsport    
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia “... የፌደራል ፓሊስ በፓትሮል መንገድ ላይ ወጥቶ እንዲሰራ ሁሉ ተደርጓል ” - ትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር የድንበር ተሻጋሪ የከባድ መኪና #አሽከርካሪዎች አገር ውስጥ ከገቡ በኋላ በታጠቁ ኃይሎች እስከ ግድያ የሚድረስ ጥቃት እንደሚፈጸምባቸው መግለጻቸውን በተደጋጋሚ መረጃ ተለዋውጠን ነበር። አሽከርካሪዎቹ፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ እየሰጠ እንዳልሆነ…
“ ባለፉት 10 ቀናት 5 አሽከርካሪዎች በታጣቂዎች ተገድለዋል ” - ጣና የአሽከርካሪዎች ማኀበር

የአሽከርካሪዎች ግድያ፣ የተሳፋሪዎች እገታ፣ የህግ አግባብ የሌለው የ‘ኮቴ’ ክፍያ እንዳልቆመ ጣና የከባድ መኪና የአሽከርካሪዎች ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

“ በቅርቡ በአማራ ክልል ፤ ማክሰኝት አካባቢ አንድ ሹፌር ተገድሏል። ከዚያ በፊትም እዚያው ሌላ አሽከርካሪ ተገድሏል ” ሲል አመልክቷል።

ጥቃቱ በተለያዩ ክልሎች ሲፈጸም እንደሚስተዋል ጠቁሞ፣ “ በኦሮሚያ ክልል ‘55’ ተብሎ የሚጠራው አካባቢም አንድ አሽከርካሪ ተገድሏል ” ነው ያለው።

ከግድያው በተጨማሪ እገታም እንዳልቆመ ያስረዳው ማኀበሩ፣ “ በአጠቃላይ ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል 3 አሽከርካሪዎች ተገድለው፤ በታታ የነበሩ ተሳፋሪዎች ታፍነው መወሰዳቸው መረጃ ደርሶናል (ጫንጮ ወጣ ብሎ) ” ብሏል።

ማኀበሩ፣ ከዚህ ቀደምም ጥቃቱ በተደጋጋሚ ጊዜ ሲፈጸም እንደተስተዋለ አስታውሶ፣ “ ቅርብ ቀንም እነዚህ (ከላይ የተዘረዘሩት) ጥቃቶች ተፈጽመዋል ” ሲል አስረድቷል።

“ የአሁኑ ጥቃት የቅርብ ጊዜ ጥቃት ነው። ባለፉት 10 ቀናት ውስጥ 5 አሽከርካሪዎች በታጣቂዎች ተገድለዋል ” ያለው ማኀበሩ፣ ባለፉት ዓመታት ከ120 የሚበልጡ አሽከርካሪዎች በታጣቂዎች እንደተገደሉ አስታውቋል።

በተያያዘም፣ የ ‘ኮቴ’ እየተባለ የሚጠየቀው ከህግ አግባብ ውጪ የሆነ ከ2,000 ብር በላይ ክፍያ ኦሮሚያ ክልል ላይ አሁንም እንዳልቆመ፣ ከክልሉ ሳይወጡ ራሱ እስከ 5 ጊዜ ለመክፈል እንደሚገደዱ ሹፌሮች ተናግረዋል።

ማኀበሩ በበኩሉ፣ ይሄው ቅሬታ ትክክል መሆኑን አረጋግጦ፣ “ ከጂቡቲ ለሚጫን እቃ የ ‘ኮቴ’ የሚለው ቃል ራሱ ከአፍ ሊወጣ አይገባም ነበር” ሲል ወቅሷል።

በመንገድ ላይ ስለሚፈጸም የታጣቂዎች ጥቃት ምን እየሰራ እንደሆነ ከዚህ ቀደም የጠየቅነው የትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር፣ “ ከሚኒስቴር መ/ቤታችንም ሌላም አካል ዳይሬክሽን ተሰጥቶ፣ እንዲያውም ፌደራል ፓሊስ በፓትሮል መንገድ ላይ ወጥቶ እንዲሰራ ሁሉ ተደርጓል ” ማለቱ ይታወሳል።

የ‘ኮቴ’ ክፍያውን ቅሬታ በተመለከተም ችግሩ መኖሩን አምኖ፣ “ ከኦሮሚያ ክልል መንግስትም ጋር አውርተን መፍትሄ የምንሰጥ ይሆናል ” ነበር ያለው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#KUWAIT

ኩዌት ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የተገኘባቸውን ሰራተኞች " በህገወጥ መንገድ ያገኙትን ገንዘብ ሁሉ መመለስ አለባቸው " አለች።

" በሕግ ፊት አቆማቸዋለሁ " ብላለች።

ኩዌት፣ ከዚህ ቀደም ባደረገችው ሲቪል ሰራተኞች ያቀረቡትን የትምህርት ሰነድ የማጣራት ስራ የበርካታ ሰራተኞች መረጃ ሀሰተኛ ሆኖ ተገኝቷል።

ይህን ተከትሎ የሀገሪቱ መንግስት ጥፋተኛ ሆነው የተገኙ ሰራተኞች በህገወጥ መንገድ ያገኙትን የመንግስት ገንዘብ ሙሉ በሙሉ እንዲመልሱ ለማዘዝ ማቀዱን የኩዌት ጋዜጣ ዘግቧል።

በዚህም ሀሰተኛ ዲግሪ ፣ ማስተርስ ፣ ዶክትሬት ሆነ ሀሰተኛ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ሰነድ ያለው ሰራተኛ ስራውን ሙሉ በሙሉ መልቀቅና በሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃው በማታለል ከተቀጠረበት ጊዜ ጀምሮ ያገኘውን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ መመለስ ይጠበቅበታል ተብሏል።

እነዚህ ሰዎች ገንዘቡን መመለስ ብቻ ሳይሆን ወደ ሕግ ፊት እንዲቀርቡ ተደርጎ በሕግ እንደሚጠየቁ ተነግሯል።

Via @tikvahethmagazine
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" የሩዋንዳ እቅድ (ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ መላክ) ገና ከጅምሩ ሞቶ የተቀበረ ነው " - አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር

ከሰሞኑን ዩናይትድ ኪንግደም (UK) አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር አግኝታለች።

አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር የሌበር ፓርቲ መሪ ሰር ኪር ስታርመር ናቸው።

ፓርቲው የሪሹ ሱናክን የወግ አጥባቂ (ኮንሰርቫቲቭ) ፓርቲ በከፍተኛ ብልጫ ነው ዘርሮ ያሸነፈው።

በከፍተኛ ብልጫ የተሸነፉት ሱናክ ፥ " የሕዝቡን ቁጣ ሰምቻለሁ። ለዚህ ሥራ ያለኝን ነገር ሁሉ ሰጥቻለሁ። ይሁን እንጂ የዩናይትድ ኪንግደም (UK) መንግሥት መለወጥ እንዳለበት ግልጽ የሆነ መልዕክታችሁን አስተላልፋችኋል፤ የሚተካኝም ሲገኝ ከፓርቲ መሪነት እለቃለሁ " ብለዋል።

በሌላ በኩል የምርጫ ውጤቱን ተከትሎ ስልጣን የተረከቡት አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪር ስታርመር ዛሬ የመጀመሪያ መግለጫቸውን ሰጥተዋል።

በዚህም ፥ በጥገኝነት ጠያቂዎች / ስደተኞች ጉዳይ የቀድሞው የወግ አጥባቂ መንግሥትን ፖሊሲ እንደማያስቀጥሉ በይፋ አሳውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ " የሩዋንዳ እቅድ (ጥገኝነት ጠያቂዎችን /ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ መላክ) ገና ከጅምሩ ሞቶ የተቀበረ ነው " ብለዋል።

መንግስታቸው ፥ የቀድሞው አገዛዝ በህገወጥ መንገድ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም የገቡ ጥገኝነት ጠያቂዎች / ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ ለመላክ የጀመረውን ስራ እንደማይቀጥሉበት ተናግረዋል።

" ከሩዋንዳ ጋር የተደረሰው ስምምነት አይቀጥልም ውድቅም ይሆናል " ያሉት ጠ/ሚ ስታርመር  በዚህ የስደተኞች ጉዳይ ላይ የቀድሞው መንግስት ፖሊስ አይቀጥልም ብለዋል።

#UK
#Rwandascheme

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በታጣቂዎች የታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከምን ደረሱ ? ትምህርት ጨርሰው ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ረቡዕ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም ረፋድ 4 ሰዓት ገደማ ገብረ ጉራቻ መታገታቸውን  አይዘነጋም። ታጋቾቹን ከእገታ ለመልቀቅ አጋቾቹ ለአንድ ተማሪ 400 ሺህ ብር እንደጠየቁ ፤ ዩኒቨርሲቲውም ለትምህርት ሚኒስቴር ሪፓርት እንዳደረገ መረጃ ተለዋውጠን…
#Update

(ቅዳሜ ሰኔ 29/2016 ዓ/ም)

ስለ ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ታጋች ተማሪዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ?

በታጣቂዎች ስለታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲውን ፣ የግቢው የወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት እና የታጋች ቤተሰብን ምን አዲስ አለ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬም ጥያቄ አቅርቧል።

የታጋች ቤተሰቦች አጋቾቹ ወደ 20 የሚሆኑ ታጋቾችን ከትላንት ጀምሮ ወደ ማያውቁትና ጫካ በበዛበት ቦታ በቡድን ከፋፍለው በእግር እያጓጓዟቸው እንደሆነ ተናግረዋል።

ይህንን ነገር የሰሙት አጋቾቹ ደውለው " ልጆቻችሁ እንዲለቀቁ ገንዘብ አምጡ " ብለው በዛቱበት እና ከልጆቻቸው ጋር በስልክ በተገናኙበት ወቅት ነው።

አጋቾቹ ገንዘብ እንዲላክላቸው ፤ ለዚህም ትንሽ ጊዜ እንዲሰጡ ቢጠየቁም ለመስማት ፈቃደኞች እንዳልሆኑ የታጋች ቤተሰቦች ገልጸዋል።

የልጆቻቸው ደህንነት እጅግ በጣም በከፋ ጭንቀት ላይ እንደጣላቸው ገልጸው ልጆቻቸውን ወደ ሌላ አገር እንዳያስወጧቸው መከላከያ እና ፌደራል ፓሊስ ክትትል አድርገው እንዲታደጉላቸው ተማጽነዋል።

ቲክቫህ ያነጋገረው የወጌላዊያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረትን በበኩሉ፣ ትላንት መኪና እየጠበቁ የነበሩት መኪና አግኝተው ወደ ቤተሰብ ጉዞ ማድረጋቸውን ገልጿል።

ቀሪዎቹ ግን አሁንም ገንዘብ በታጋቾቹ እየተጠየቁ ነው ብሏል።

በታጋች ተማሪዎቹ ጉዳይ አዲስ ነገር አለ ? ሲል ቲክቫህ የጠየቃቸው የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ አንድ አካል ፥ ለበላይ ሪፓርት ከማድረግ ውጪ ምንም ማድረግ እንዳልተቻለ ገልጸዋል። 

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#Tigray

" በ9 ወር 270 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል ፤ 261 ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ፤ ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ንብረት ወድሟል " - የትራንስፖርትና መገናኛ ቢሮ

የትግራይ የትራንስፓርትና የመገናኛ ቢሮ ከሰሞኑን አንድ ሪፖርት ይፋ አድርጎ ነበር።

በዚህም በክልሉ ባለፉት 9 ወራት (ከመስከረም እስከ ግንቦት 2016 ዓ.ም) በትራፊክ አደጋ ምክንያት ብቻ 270 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።

261 ሰዎች ደግሞ ቀላል እና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

በንብረት ላይ የደረሰ ውድመት ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሆነ ተነግሯል።

በጥናት የተለየው የትራፊክ አደጋ መነሻ ምንድን ነው ?
- ከተፈቀደ ፍጥነት በላይ መንዳት
- ለእግረኞች ቅድሚያ አለመስጠት
- ከተፈቀደ መስመር ውጪ ማሽከርከር
- ርቀት ጠብቆ አለማሽከርከር
- የአሽከርካሪዎች አቅም ማነስ ናቸው።

እግረኞች ዜብራ ተጠቀመው መንገድ አለማቋረጥ እና ቀኝ መስመር ይዘው መጓዝ በተጨማሪነት የአደጋ መነሻዎች ሆነው ተጠቅሰዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
#DStvEthiopia

ሁሉንም ታላላቅ ሊጎች ለሁላችንም!

ሁሉንም ወሳኝ ጨዋታዎች ፣ ደማቅ ግጥሚያዎች ፣ የዋንጫ ፍልሚያዎች በዲኤስቲቪ!

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ፣ ቻምፒዮንስ ሊግ ፣ ላሊጋ ፣ ሴሪአን ጨምሮ ከጨዋታ እስከ ትንታኔ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ ... ሁሉም በዲኤስቲቪ!

እንደየምርጫዎ በሁሉም ፓኬጅ ላይ ኳስ ያለው ዲኤስቲቪ!

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#DStvEthiopia
#ሁሉምያለውእኛጋርነው
#DStvSelfServiceET
TIKVAH-ETHIOPIA
#NationalExam " የኦንላይን ፈተናው አልቀረም። የሚሰራጨው ሀሰተኛ መረጃ ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም የ 12ተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብና በወረቀት እንደሚሰጥ መግለጹ ይታወቃል። ሆኖም በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የበይነ መረብ ፈተናው እንደቀረ ተደርጎ መረጃ እየተሰራጨ መሆኑን ገልጿል። ሚኒስቴሩ ይህ በፍጹም ከእውነት የራቀ ሃሰተኛ…
#ATTENTION🚨

" የበይነ መረብ (ኦንላይን) ተፈታኞች በተመደባችሁበት የፈተና ጣቢያ ተገኝታችሁ ፈተናውን እንድትወስዱ እናሳስባለን " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ፈተና በበይነ መረብ (ኦንላይ) እንዲሁም በወረቀት እንደሚሰጥ በዛሬው ዕለት በድጋሚ አሳወቀ።

በሁለቱም መንገድ ለሚሰጠው ፈተና ዝግጅት ተደርጓል ብሏል።

ትላንት እና ከትላንት በስቲያ በአዲስ አበባ ያሉ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች " የበየነ መረብ (ኦንላይን) ፈተና ቀርቷል " እያሉ ለተማሪዎች መናገራቸውን እና የጽሁፍ መልዕክት በቴሌግራም ላይ መለጠፋቸውን የተማሪ ወላጆች እንዲሁም ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

እንዲህ ያለው ውሳኔ የሚተላለፈው ከማዕከል ከትምህርት ሚኒስቴር ሆኖ ሳለ ፥ ትምህርት ቤቶቹ ውሳኔውን ማን እንዳሳለፈ በይፋ ያሉት ነገር ሳይኖር በደፈናው " ቀርቷል " የሚል ነገር ብቻ ነው የነገሯቸው።

በኋላም እራሳቸው ት/ቤቶቹ ቀድሞ ያሰራጩትን ያልተረጋገጠ መረጃ በማጥፋት የኦላንይን ፈተናው እንዳልቀረ መልሰው ገልጸዋል።

ዛሬ እሁድ ትምህርት ሚኒስቴር የበየነ መረብ (ኦንላይን) ፈተናው በፍጹም እንዳልቀረ በድጋሜ አረጋግጧል።

ብሔራዊ ፈተናውን በበይነ መረብ (ኦንላይን) እና በወረቀት ለመፈተን ዝግጅቱን አጠናቅቆ የተማሪዎችን የመፈተኛ ቀን እየተጠባበቀ እንደሚገኝም አሳውቋል።

" ፈተናውን አስመልክቶ የተሳሳቱ መልዕክቶች በየጊዜው ትክክለኛ የትምህርት ሚኒስቴር ባልሆኑ ገጾች እየተለቀቁ ይገኛሉ " ሲልም ገልጿል።

ለተማሪዎች፣ ወላጆችና አሳዳጊዎች ባስተላለፈው መልዕክት ፈተናው ከዚህ ቀደም እንደተገለጸው በበይነ መረብ (ኦንላይን) እና በወረቀት እንደተማሪዎች የቀደመ ምርጫ መሰረት ይሰጣል ብሏል።

አስቀድመው በወረቀት የመረጡ ወደተመደቡበት ዩኒቨርስቲ፣ በበይነ መረብ (ኦንላይን) የመረጡም በተመደቡበት የፈተና ጣቢያ ተገኝተው ፈተናውን እንዲወስዱ በጥብቅ አሳስቧል።

የትምህርት ሚኒስቴር ፤ ተማሪዎች ከላይ በምስሉ እንደተያያዘው አይነት ከሃሰተኛ ወሬ ራሳቸውን በመከላከል ለፈተናው የሚያደርጉትን ዝግጅት እንዲቀጥሉ አሳስቧል።

ለማንኛውም መረጃ ከትምህርት ሚኒስቴር ብቻ እንዲከታተሉም አደራ ብሏል።

#TikvahEthiopia
#NationalExam
#MoE

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#NationalExam

የ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ተፈታኞች ወደ ዩኒቨርሲቲዎች መግባት ጀምረዋል።

ተፈታኞች ከትናንት ሰኔ 29/2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ዩኒቨርሲቲ እየገቡ ናቸው።

ከትግራይ ክልል ውጪ በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ/ም ይሰጣል።

በትግራይ ክልል ፈተናው ከሐምሌ 2 እስከ ሐምሌ 12 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ ይሰጣል።

በትግራይ በቀድሞ ስርዓተ ትምህርት የተማሩና በ2013 እና በ2014 የትምህርት ዘመን መፈተን የነበረባቸው ተፈታኞች ናቸው ፈተናቸውን የሚወስዱት።

ትምህርት ሚኒስቴር የዘንድሮውን ብሔራዊ ፈተና በወረቀት እንዲሁም የተመረጡ ተማሪዎች ደግሞ በኦንላይን እንደሚወስዱት አሳውቋል።

ዘንድሮ ከ700 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተናው ይቀመጣሉ።

የፀጥታ ችግር ባለባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም ሁለተኛ ዙር ፈተና ይዘጋጅላቸዋል።

@tikvahethiopia
#Africa

" በኮንፌዴሬሽን ለመዋሃድ ተስማምተናል " - በመንፈንቅለ መንግስት የመጡት የሶስት ሀገራት መሪዎች

ቡርኪናፋሶ ፣ ኒጀር እንዲሁም ማሊ በኮንፌደሬሽ ለመዋሃድ ተስማሙ።

በመፈንቅለ መንግስት ወደ ስልጣን የመጡት የቡርኪናፋሶ ፣ ኒጀር እና ማሊ ወታደራዊ ሁንታዎች በኮንፌደረሽን ለመዋሃድ ማስማማታቸው ተሰምቷል።

ከምዕራብ አፍሪቃ የኢኮኖሚ ማሕበረሰብ ጥምረት (ECOWAS) ፍቺ መፈጸማቸውንም ገልጸዋል።

የ3ቱም ሃገራት ወታደራዊ ሁንታዎች ስልጣን ለሕዝብ እንዲያስረክቡ ከዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ በተለይ ደግሞ ECOWAS ብርቱ ውትወታ እና ማዕቀብ ሲደረግባቸው ነበረ።

ጥምረቱ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት እንደሚያደርግ ከገለጸ በኋላም ከሶስቱም ሃገራት ብርቱ ትችት ሲደርስበት ቆይቷል።

ሀገራቱ ECOWASን የቀድሞ ቅኝ ገዢያቸው " የፈረንሳይ ጉዳይ ፈጻሚ " በማለት ክፉኛ ሲወቅሱት ነበረ።

ይህንንም ተከትሎ ከፈረንሳይ ጋር የነበራቸውን ወታደራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ግኑኝነትን በማቋረጥ ወደ ሩስያ አማትረዋል።

አሁን ደግሞ የስስቱም ሃገራት መሪዎች በኒጀር ዋና ከተማ ኒያሚ ባካሄዱት ስብሰባ " የሳሕል ሃገራት ኮንፌደሬሽን መንግስት " በሚል ለመዋሃድ መስማማታቸውን እና መፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።

ሀገራቱ በድምሩ 72 ሚሊዮን ህዝብ ያላቸው ሲሆን 3ቱም በታጣቂ ቡድኖች በሚፈጠር አለመረጋጋት እየተፈተኑ ይገኛሉ።

አሁኑን ስምምነት ተከትሎ በጸጥታ ጉዳዮች አብረው እንደሚሰሩ የኢኮኖሚ ትስስራቸውንም እንደሚያጠናክሩ ይጠበቃል።

ECOWAS በዛሬው ዕለት ስብሰባ የተቀመጠ ሲሆን ይህ የኮንፌደሬሽን ምስረታ ጉዳይ ዋና የመዋያያ አጀንዳው እንደሚሆን  ተዘግቧል።

መረጃው የአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ፣ የዶቼቨለ ሬድዮ እና አናዱሉ ነው።

@tikvahethiopia
#ፎቶ

አንጋፋው የአዲስ አበባ ስታዲዮም ከኮቪድ -19 ወረርሽኝ በኋላ እጅግ ከፍተኛ የተመልካች ቁጥር ተገኝቶበታል የተባለለትን የእግር ኳስ ፍልሚያ ዛሬ አስተናገደ።

ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ " #የኢትዮጵያ_ዋንጫ " የፍጻሜ ፍልሚያ ተደርጓል።

በዚህም ኢትዮጵያ ቡና ፥ ወላይታ ዲቻን በማሸነፍ ዋንጫውን አንስቷል።

የአዲስ አበባ ስታዲዮምም ከጫፍ እስከ ጫፍ በእግር ኳስ ተመልካች ተሞልቶ ነበር።

ስታዲዮሙ ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ በኋላ በዚህ ልክ እጅግ የበዛ ተመልካች አላስተናገደም ተብሏል።

ላለፉት ዓመታት እድሳት ሲደረግለትም ነበር።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ፤ ከእድሳቱ በኃላ ለህዝብ ክፍት ተደረጎ በተካሄደው በዛሬው የፍጻሜ ጨዋታ በደጋፊዎች የተወሰኑ ወንበሮች የተነቃቀሉ ሲሆን የተጠባባቂ ተጫዋጮች ወንበሮችም ላይም ጉዳት መድረሱ ተነግሯል።

ከቀናት በፊት ጨዋታውን አስመልክቶ በተዘጋጀ የጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ባህሩ ጥላሁን ፥ " ስታዲየም ውስጥ ያሉ ንብረቶች የህዝብ ሀብትና የመንግስት ንብረት ናቸው ፤ ከፍተኛ ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል ስሜታዊነት ባይጎላ " ሲሉ የአደራ መልዕክት አስተላልፈው ነበር።

More : @tikvahethsport

@tikvahethiopia
2024/09/29 20:26:53
Back to Top
HTML Embed Code: