Telegram Web Link
የዶክተር ዳንኤል በቀለ የሥራ ጊዜ አበቃ።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀለ የሥራ ጊዜ አብቅቷል።

የሕዝብ ተወካዮች ም/ ቤት አፈ ጉባዔ ታገሠ ጫፎ ዋና ኮሚሽነሩን አሰናብተዋል።

ዶክተር ዳንኤል በቀለ ሰኔ 25 ቀን 2011 ዓ/ም ነበር የተሾሙት።

በአምስት ዓመታት የሥራ ቆይታቸው ተቋማቸው እጅግ በርካታ የሰብዓዊ መብት ሪፖርቶችን ለህዝቡ ይፋ አድርጓል።

ዛሬ የዶክተር ዳንኤል በቀለ የሥራ ዘመን ማብቃቱን በተመለከተና የዓመታዊ የሰብዓዊ መብቶች ሪፖርት በኮሚሽኑ ይፋ ይደረጋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የዶክተር ዳንኤል በቀለ ስንብትን እንዲሁም የዓመታዊ የሰብዓዊ መብት ሪፖርቱን ተከታትሎ ያደርሳችኋል።

Photo Credit - ENA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የዶክተር ዳንኤል በቀለ የሥራ ጊዜ አበቃ። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀለ የሥራ ጊዜ አብቅቷል። የሕዝብ ተወካዮች ም/ ቤት አፈ ጉባዔ ታገሠ ጫፎ ዋና ኮሚሽነሩን አሰናብተዋል። ዶክተር ዳንኤል በቀለ ሰኔ 25 ቀን 2011 ዓ/ም ነበር የተሾሙት። በአምስት ዓመታት የሥራ ቆይታቸው ተቋማቸው እጅግ በርካታ የሰብዓዊ መብት ሪፖርቶችን ለህዝቡ ይፋ አድርጓል። ዛሬ…
#EHRC

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዛሬ ዓመታዊ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ሁኔታ ሪፖርት ይፋ ያደርጋል።

የዛሬው ሪፖርት ለሦስተኛ ተከታታይ ዓመት የሚቀርብ ነው።

ሪፖርቱ ከሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. ያለውን ጊዜ የሚሸፍን ነው፡፡

ይኸው ሪፖርት በሚሸፍነው ጊዜ የነበረውን የሀገራዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ጠቅለል ባለ መልኩ ይቃኛል።

በትኩረት ዘርፎች (Thematic Areas) የተስተዋሉ እና የተለዩ ቁልፍ እመርታዎች፣ ዋና ዋና አሳሳቢ ጉዳዮች፣ ተግዳሮቶች እና ምክረ ሐሳቦችን ጨምሮ ልዩ ትኩረት የሚሹ የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮችም ተካትተዋል።

ላለፉት ዓመታት በርካታ የሰብዓዊ መብት ሪፖርቶችን ለህዝብ ይፋ እንዲደረግ ሲመሩ የቆዩት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀለ የሥራ ጊዜያቸው በማብቃቱ ይሰናበታሉ።

(ዓመታዊ ሪፖርቱ እንደደረሰን እንልክላችኋለን)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EHRC የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዛሬ ዓመታዊ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ሁኔታ ሪፖርት ይፋ ያደርጋል። የዛሬው ሪፖርት ለሦስተኛ ተከታታይ ዓመት የሚቀርብ ነው። ሪፖርቱ ከሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. ያለውን ጊዜ የሚሸፍን ነው፡፡ ይኸው ሪፖርት በሚሸፍነው ጊዜ የነበረውን የሀገራዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ጠቅለል ባለ መልኩ ይቃኛል። በትኩረት ዘርፎች…
#Update

ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ የኃላፊነት ቦታውን ይረከባሉ።

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን መግለጫ ሰጥቷል።

ላለፉት 5 አመታት ያገለገሉት ዶ/ር ዳንኤል በቀለ የአገልግሎት ጊዜያቸው ማብቃቱን አሳውቀዋል።

በሕ/ተ/ም/ ቤት ዋና ኮሚሽነር እስኪሰይም ድረስ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ የኃላፊነቱን ቦታ እንደሚረከቡ ተገልጿል።

ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ " ከዛሬ ጀምሮ ፓርላማው ስለተዘጋ በሚቀጥለው ሲከፍቱ ነው የዕጩዎች ሂደቱ የሚጀምረው እስከዛው ድረስ በአዋጁ መሰረት ምክትል ዋና ኮሚሽነር ተረክቦ ይሰራል ስለሚል እኔ ነው የምሰራው " ብለዋል።

@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ_ዓመታዊ_የሰብአዊ_መብቶች_ሁኔታ_ሪፖርት_ከሰኔ_ወር_2015_ዓ_ም_እስከ_ሰኔ_ወር_2016_ዓ.pdf
7.8 MB
#ኢሰመኮ : የትጥቅ ግጭቶች ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት ዋነኛ ምክንያት ሆነው መቀጠላቸውን ኢሰመኮ አሳውቋል።

ይህም  " አካታችና ተዓማኒ የሆነ ሰላማዊ መፍትሔ እና የሽግግር ፍትሕ ሂደት አፋጣኝ አስፈላጊነት አመላካች ነው "
ብሏል።

ይህን ያለው ዛሬ ይፋ ባደረገው 3ተኛው የኢትዮጵያ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ሪፖርት ላይ ነው።

ሪፖርቱ ባለ 132 ገጽ ሲሆን ከሰኔ ወር 2015 ዓ/ም እስከ ሰኔ ወር 2016 ዓ/ም ያለውን ጊዜ ይሸፍናል።

(ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ተጨማሪ የሥራ ዘመን መቀጠል የሚችሉበት እድል ነበር ?

" ቴክኒካሊ ይቻላል ማድረግ (በኃላፊነት ቦታው ላይ መቀጠል)  ፤ ... ሙሉ በሙሉ በፍላጎቴ ነው ላለመቀጠል የወሰንኩት " - ዶክተር ዳንኤል በቀለ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀለ የ5 ዓመት የሥራ ዘመን አብቅቷል።

ምንም እንኳን ዶክተር ዳንኤል ለተጨማሪ የኃላፊነት ዘመን በቦታው ላይ ለመቆየት እድል ቢኖራቸውም ለ2ኛ ዙር የኃላፊነት ዘመን መቀጠል እንደማይፈልጉ ወስነዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ም/ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለን የዋና ኮሚሽነሩ ስልጣናቸው ሊራዘም ይችል ነበር ወይ ? ሲል ጠይቋል።

እሳቸውም ፦

" አንዱ የሪፎርሙ ሀሳብ የኃላፊነት ጊዜው ሲያልቅ ሊለቅ ይችላል የሚል ነው። ሌላ የሚከተለውን ሰው እንዲያመጣ።

ሁል ጊዜ ቢሆን እስከመጨረሻ ድረስ በአዋጁ ላይ የተቀመጠውን ለጥጦ መጠቀም ሳይሆን አንዳንድ ጊዜ አንድ የኃላፊነት ዘመን / ዙር ጨርሶ ሌላ ሰው ይምጣ ፤ በተለይም ውስጥ ያለ ሰው መተካት ይቻላል ነው።

ዋና ኮሚሽነሩ እራሳቸው ናቸው ከዚህ በኃላ ለሁለተኛ የኃላፊነት ዘመን አልሄድም ብለው የወሰኑት " ሲሉ መልሰዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚሁ ጉዳይ ላይ ዶክተር ዳንኤል በቀለንም አነጋግሯቸዋል።

ሁለተኛ ዙር ላለመቀጠል በራስዎት ፍላጎት ወስነው ነው ? ቢፈልጉ ሕጉ ይፈቅድሎታል ? ሲል ጠይቋል።

ዶክተር ዳንኤል ፥ " አዎን !!! በራሴ በፍላጎቴ ነው። ቴክኒካሊ ይቻላል ማድረግ (በኃላፊነት መቀጠል) ከተቋም ግንባታ አንጻር እኔ እንደዛ አልመክርም ምክንያቱም ተቋም መገንባት ማለት አንድ ሰው ዝም ብሎ መቀጠል ሳይሆን (renewal ስለሚፈቅድ) ተቋም ፈጥረህ ከዛ ማሸጋገር ይመስለኛል። ሙሉ በሙሉ በፍላጎቴ ነው ላለመቀጠል የወሰንኩት " ብለዋል።

በቀጣይ የት ሊሰሩ ይችላሉ ? የሚለውን በተመለከተ " ያህንን ለማሰብ ጊዜም አላገኘሁም። እስካሁን ምንም አላውቅም። ቀጣይ ስራዬ ምን እንደሆነ አልወሰንኩም። " ሲሉ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
ዳታ በሽ በሽ! ... በሱፐርአፕ እስከ 80% ቅናሽ!

በአዲሱ ልዩ የሱፐርአፕ ጥቅል በአንድ ላይ ተሰናድተው በቴሌብር ሱፐርአፕ በቀረቡት የቲክቶክ፣ ዩቲዩብ፣ ፌስቡክ፣ ቴሌግራም እና ኢንስታግራም ጥቅሎች ዘና ፈታ እያሉ፤ ቁም ነገር ይገብዩ።

ጥቅሎቹን በዕለታዊ፣ ሳምንታዊ እና ወርሃዊ አማራጮች በቴሌብር ሱፐርአፕ ብቻ http://onelink.to/fpgu4m ያገኟቸዋል!

ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
#NationalExam

" የኦንላይን ፈተናው አልቀረም። የሚሰራጨው ሀሰተኛ መረጃ ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም የ 12ተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብና በወረቀት እንደሚሰጥ መግለጹ ይታወቃል።

ሆኖም በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የበይነ መረብ ፈተናው እንደቀረ ተደርጎ መረጃ እየተሰራጨ መሆኑን ገልጿል።

ሚኒስቴሩ ይህ በፍጹም ከእውነት የራቀ ሃሰተኛ መሆኑን አሳውቋል።

ፈተናው በሁለቱም በወረቀት እንዲሁም በኦንላይን እንደሚሰጥ አረጋግጧል።

ተማሪዎች ይሄን ተገንዝበው ዝግጅታቸውን እንዲቀጥሉ አሳስቧል።

ትምህርት ሚኒስቴር " ፈተናውን የተሳካ ለማድረግ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጥምረት እየሰራን ነው ለዚህም ከፍተኛ ዝግጅት ተደርጓል " ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update “ ለትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ሪፓርት አድርጌአለሁ ” - ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፣ ገብረ ጉራቻ ላይ በታጣቂዎች የታጋቱ ተማሪዎች ቤተሰቦች በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ናቸው ፤ ምን እየተሰራ ነው ? ሲል ደባርቅ ዩኒቨርሲቲን ጠይቋል። የዩቨርሲቲ ተወካይ ፕሬዚዳንት ዶክተር አስማማው ዘገዬ፣ “ ጉዳዩን ሰምተናል። ከዚህ ድርጊት ያመለጡ ተማሪዎች ነግረውናኛል ” ብለዋል።…
#Update

በታጣቂዎች የታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከምን ደረሱ ?

ትምህርት ጨርሰው ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ረቡዕ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም ረፋድ 4 ሰዓት ገደማ ገብረ ጉራቻ መታገታቸውን  አይዘነጋም።

ታጋቾቹን ከእገታ ለመልቀቅ አጋቾቹ ለአንድ ተማሪ 400 ሺህ ብር እንደጠየቁ ፤ ዩኒቨርሲቲውም ለትምህርት ሚኒስቴር ሪፓርት እንዳደረገ መረጃ ተለዋውጠን ነበር።

ዛሬስ ምን አዲስ አለ ?

የተወሰኑ ታጋቾች ከእገታ ቢለቀቁም የተወሰኑት ግን አሁንም እንዳልተለቀቁ፣ ቤተሰቦቻቸው እና በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ የወንጌላዊያን የክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የታጋች ቤተሰቦች በገለጹት መሠረት፣ 150 የሚሆኑ ተማሪዎች ዛሬ ወደ አዲስ አበባ እየተመለሱ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ ግን እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር ካልከፈሉ እንደማይለቀቁ ተነግሯቸዋል።

በዛሬው ዕለት ወደ አዲስ አበባ ከተማ እየተመለሱ ነው የተባሉት ተማሪዎች በአጋቾች ስር ከነበሩት መካከል እና በተለያዩ ቦታዎች ተደብቀው ከእገታ ማምለጥ የቻሉ መሆናቸውን ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ተናግረዋል።

የወንጌላዊያን ተማሪዎች ህብረት በበኩሉ፣ አሁንም ገና በአጋቾች እጅ ያሉ ፣ ወደ ቤተሰብ መመለስ እየቻሉ ተሽከርካሪ ያላገኙ ፣ የተወሰኑት ታጋቾች ግን እንደተለቀቁ ማረጋገጡን ጠቁሟል።

ተለቀቁ የተባሉትም ከአጋቾቹ ጋር ተግባብተው እንጂ ገንዘብ ከፍለው እንዳልሆነ የተመላከተ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ በችግር ላይ እንደሆኑ መረጃው እንደደረሰው ገልጿል።

ታጋቾቹ በትልቅ ጫካ ታጉረው እንደሚገኙ እና ገንዘብ እየተጠየቁ መሆናቸውን የታጋች ቤተሰቦች ጠቁመዋል።

በዚህ ኑሮ ውድነት ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደማያገኙ ለገልጸው መንግስት ለታጋቾች እንዲደርስላቸው በእንባ ታጅበው ተማጽነዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር በጉዳዩ ዙሪያ ምን እየሰራ እንደሆነ ለመጠየቅ የተደረገው ሙከራ ተደጋጋሚ ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ ባለመሆኑ ለጊዜው ሳይሳካ ቀርቷል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NationalExam " የኦንላይን ፈተናው አልቀረም። የሚሰራጨው ሀሰተኛ መረጃ ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም የ 12ተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብና በወረቀት እንደሚሰጥ መግለጹ ይታወቃል። ሆኖም በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የበይነ መረብ ፈተናው እንደቀረ ተደርጎ መረጃ እየተሰራጨ መሆኑን ገልጿል። ሚኒስቴሩ ይህ በፍጹም ከእውነት የራቀ ሃሰተኛ…
#ተጨማሪ #ብሔራዊ_ፈተና

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በኦንላይን ከሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ጋር በተያያዘ አንድ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር አናግሯል።

አመራሩ ፥ " የኦንላይን ፈተናው አልቀረም " ሲሉ አስረግጠው ተናግረዋል።

በየማህበራዊ ሚዲያው " የኦንላይን ፈተና ቀርቷል ፤ ሁሉም ተፈታኝ ፈተናውን በወረቀት ይወስዳል " እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ፍጹም ሀሰተኛ መረጃ እንደሆነም አረጋግጠዋል።

ተማሪዎች በሀሰተኛ መረጃ ሳይረበሹ ለፈተናው ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ተብሏል።

ከዚህ በተጨማሪ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት  ፥ የ2016 ዓ.ም የ12ተኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በኦንላንይ እና በወረቀት እንደሚሰጥ አረጋግጧል።

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ የበይነ መረብ ፈተናው እንደቀረ ተደርጎ እየቀረበ ያለው መረጃ  ሃሰተኛ ነው ብሏል።

ፈተናው በሁለቱም በወረቀት እንዲሁም በኦንላይን እንደሚሰጥ አሳውቋል።

@tikvahuniversity @tikvahethiopia
#AmahraRegion

አቶ አህመድ አሊ ዛሬ በታጣቂዎች በተተኮሰባቸው ጥይት መገደላቸው ተሰማ።

በአማራ ክልላዊ መንግሥት ፣ የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ ዛሬ በከሚሴ ከተማ ከሚገኝ መስጅድ ጁምአ ሶላት ሰግደው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ በታጣቂዎች በተተኮሰባቸው ጥይት መገደላቸው ተነግሯል።

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ባወጣው የሀዘን መግለጫ " ግድያው የተፈጸመው በጽንፈኛው የሸኔ ታጣቂ ቡድን ነው " ብሏል።

አቶ አህመድ ከዋና አስተዳዳሪነታቸው በተጨማሪ የአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል በመሆን ማገልገላቸው ተገልጿል።

#AmharaRegion
#OromooZone

@tikvahethiopia
#Chapa

በዲጂታል ክፍያ ከሚፈፀሙ ማጭበርበሮች ንቁ በመሆን ራሶን ይጠብቁ!

🚫አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎች ሲኖሩ ወደ 📞8911 በመደወል ሪፖርት ያድርጉ

🌐 ለበለጠ መረጃ ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ፡ https://chapa.co/

#chapa #chapapayments #Fraudawareness #Digitalpayment

Website |Telegram | Instagram | Facebook |LinkedIn |X
TIKVAH-ETHIOPIA
#WKU " አሳይመንቱን ቤት ድረስ አምጥተሽ ስጪን " በማለት ተማሪውን ደፍሯል የተባለው የዩኒቨርሲቲ መምህር ጉዳዩ በፍርድ ቤት እየታየ ይገኛል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰሞኑን ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ #ሴት ተማሪዎች መልዕክቶችን ተቀብሏል። ይህም " የሴቶች ጥቃት አሳስቦናል " የሚል ነው። ተማሪዎቹ የመደፈር እና የጥቃት ወንጀል በመምህር ሳይቀር መፈጸሙን በመግለጽ ስጋታቸውን ገልጻዋል። በየጊዜው እንዲህ…
#Update

ተማሪውን በመድፈር የተከሰሰው የዩኒቨርሲቲ መምህር በ9 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጥቷል።

ከሳምንታት በፊት በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ መምህር ስለተደፈረች ተማሪ እና ሂደቱም በሕግ እንደተያዘ መረጃ ተለዋውጠን ነበር።

ይኸው መምህር በ9 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጥቷል።

ተከሳሽ አየለ ሀይሉ ሞላ  ይባላል።

የካቲት 16 ቀን 2016 ዓ.ም በግምት ከረፋዱ 9፡00 ሰዓት ላይ የሚያስተምራትን የወልቂጤ ዩንቨርሲቲ ተማሪ " የተበላሸብሽን ዉጤት አስተካክልሻለሁ ፤ አሳይመንት ይዘሽ ኢስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን አካባቢ ነይ " ሲል ይቀጥራታል።

የግል ተበዳይ ተማሪ ነይ ወደ ተባለችበት ቦታ ለመሄድ በጉዞ ላይ ሳለች ተከሳሽ በወልቂጤ ከተማ ጉብሬ ክ/ከተማ ከሚገኘዉ  የመምህራን መኖሪያ አፓርታማ ላይ ሆኖ  የግል ተበዳይን ጠርቶ ወደ መኖሪያ ክፍሉ እንድትገባ  ያደርጋታል።

ተከሳሽ የግል ተበዳይን ውጤት ለማስተካከል ሴትነቷን ለመጠቀም ያቀረበላትን ጥያቄ " አልቀበልም " ስትል በእምቢታ ትፀናለች።

ተከሳሽ ካንተ ጋር አልተኛም ስትል አሻፈረኝ ያለችውን የግል ተበዳይ በጥፊ እያላጋ  ከለፈቃዷ በኃይል አስስገድዶ እንደደፈራት  የተከሳሹ የክስ መዝገብ ያስረዳል።

ተከሳሽ የተከሰሰበት ክስ የወልቂጤ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በችሎት ቀርቦ የተነበበለት ክስ የወንጀል ድርጊቱ " አልፈፀምኩም " ሲል ክዶ ተከራክሯል።

ዐቃቤ ህግም የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን አስቀርቦ አሰምቷል። በዚህም ግለሰቡ የወንጀል ተግባሩን መፈፀሙ አረጋግጧል።

ተከሳሽ የመከላከያ ምስክር አስቀርቦ ቢያሰማም ክሱን ማስተባበል ባለመቻሉ ፍርድ ቤቱ ተከሳሹን ጥፋተኛ ሲል ብይን ሰጥቷል።

ፍ/ቤቱ መምህሩን በ9 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ፥ " የዚህ መምህር የቅጣት ዉሳኔ በመሰል ችግር ዉስጥ ለተዘፈቁ መምህራን የማስጠንቀቂያ ደወል ይሁን " ሲል አስጠንቅቋል።

https://www.tg-me.com/tikvahethiopia/88052

#CentralEthiopiaPolice

@tikvahethiopia
#Kenya

የኬንያው ፕሬዝዳንት ተቃውሞ በተደራጀባቸው ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ቀርበው ከወጣቶች ጋር ተወያዩ።

ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ያዘጋጁትን የፋይናንስ ሕግ ውድቅ እንዲያደርጉ ያስገደዳቸው የወጣቶች ተቃውሞ የተደራጀበት ማኅበራዊ ሚዲያ መድረክ ላይ ለውይይት መቅረባቸው ታሪካዊ ነው ተብሏል።

ሩቶ ትላንትና ከሰዓት በ ' X ' ስፔስ ላይ ቀርበው ከህዝብ ለሚነሳው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል።

' X ' ላይ ከተቃዋሚ ወጣቶቹ ጋር ለጥያቄ እና መልስ መቅረባቸው ፍጹም ያልተጠበቀ እንደነበር ተነግሯል።

ፕሬዝዳንቱ በውይይቱ ቀጥተኛ እና መሸፋፈን ያልታየባቸው ጠንካራ ጥያቄዎች ቀርበውላቸው ነበር።

መጀመሪያ ውይይቱ በጽህፈት ቤታቸው ይፋዊ ገጽ አስተናጋጅነት ሊካሄድ ነበር በኋላ ባገጠመ እክል ከፕሬዝዳንቱ ተቃዋሚዎች አንዱ በሆነ ኦሳማ ኦቴሮ በተባለ ግለሰብ ገጽ ገብተው ነው ምላሽ የሰጡት።

የውይይቱ ተሳታፊዎች ያለ ከልካይ የፈለጉትን ሲጠይቁ፣ ፕሬዝዳንቱ ሲናገሩ መሃል ላይ እየገቡ ሲመላለሱና ማብራሪያ ሲጠይቁ ነበር።

ተቃዋሚዎቹ ምን አሏቸው ?

መንግስታቸው እስካሁን ያስመዘገበውን ነገርና ባህሪያቸውን በተመለከተ አንስተው አብጠልጥለዋቸዋል።

በርካታ ሰላማዊ ተቃዋሚዎች በፖሊስ በጭካኔ መገደላቸውን አመልክተው " በሽብርተኛ አገር ውስጥ ነው እንዴ ያለነው? " በማለት ጠይቀዋቸዋል።

የመረጣችሁ ሰው በመሆኑ ቅድሚያ ለሰው ግድ ሊሰጣችሁ ይገባል ብለዋቸዋል።

ከዩኒቨርስቲ ተመርቆ ሥራ አጥ የሆነ አንድ የውይይቱ ተሳታፊ " በካቢኔዎት ውስጥ ብቃት የሌላቸው በርካታ ባለሥልጣናት አሉ " ብሏቸዋል።

➡️ ሙሰኛ እና የተቀመጡበት ቦታ የማይገባቸው በርካታ ሰዎች በመንግስት ውስጥ እንዳሉ ነግረዋቸዋል።

የተገደሉ ወይም የተጎዱትን ሰዎች ቤተሰቦች ለማነጋገር ሞክረዋል ወይ? ሲሉም ጠይቀዋል።

አንዳንዶች ውሸታም እና ሐዘኔታ የሌላቸው በሚል ከሰዋቸዋል።

ፕሬዝዳንቱ ምን መለሱ ?

● በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ ባለሥልጣናትን በሙሉ ለማባረር ቃል ገብተዋል።

● " እውነት ነው ፤ አንዳንድ ባለሥልጣኖቻችን አስጸያፊ ድርጊቶችን እንደሚያሳዩ እስማማለሁ ፤ እራሳቸውን እንዴት እንደሚያስተካክሉ እኔም ጉዳዩን በግሌ አንስቼላቸዋለሁ። ከዚህ የበለጠም አደርጋለሁ " ብለዋል።

● በተቃውሞው የተገደሉ ሰዎችን አሃዝ በማጋነን አንዳንዶችን " ግድየለሽ " ሲሉ ከሰው ቁጥሩ 25 መሆኑን ተናግረዋል።

● በጥይት የተገደለ የ12 ዓመት ህፃን እናት ማነጋገራቸውን ገልጸዋል።

● በተቃዋሚዎች ላይ ሲተኩስ በካሜራ እይታ ውስጥ የገባ የፖሊስ አባል ክስ እንዲመሰረትበት እንዳዘዙ ተናግረዋል።

NB. የኬንያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የሟቾች ቁጥር ከ40 በላይ እንደሆነ አሳውቋል።

● ሩቶ አምባገነን እንዳልሆኑ ተናግረዋል። " እኔ ፕሬዝዳንት ነኝ ትክክል !! ግን ፕሬዜዳንቱ ፍጹም ስልጣን የለውም ለዛም ነው ዴሞክራሲያዊ ሀገር የሆነው ቼክ ኤንድ ባላንስ አለ። ፕሬዝዳንቱ አምባገነን አይደለም " ብለዋል።

● ረቂቅ ሕጉን ማንሳታቸውን በማረጋገጥ ፣ ሕጉን በተመለከተ ግን የተሳሳተ ግንዛቤ መፈጠሩን ጠቅሰዋል። የሕጉ ዓላማ የኬንያውያንን ንግድ ማጠናከረ ነበር በማለተ የተካተቱትን ዕቅዶች ጠቃሚነት አብራርተዋል።

ታሪካዊ ነው በተባለውና ምንም አይነት ቁጥጥር ባልነበረው የ ' X ' ህዝባዊ ግልጽ ውይይት መድረክ ላይ ከ150,000 በላይ ሰዎች ታድመው ነበር። 

ከዚህ በፊት አንድ ፕሬዝዳንት ይህን ያህል በይፋ ወጥቶ እራሱን በማጋለጥ ከሕዝቡ በቀጥታ ለሚቀርቡለት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጠበት ጊዜ ባለመኖሩ ምክንያት ነው ታሪካዊ የተባለው።

ፕሬዝዳንት ሩቶ ሁልጊዜ በሚያስቆጡ እና ጠንከር ያሉ ጉዳዮችን በሚመለከት ክርክር ውስጥ ሲሳተፉ ይታያል።

በፖለቲካ ሕይወታቸው ፈታኝ ጥያቄዎችን እና ሁኔታዎችን ከመጋፈጥ ወደ ኋላ ሲሉም ታይተው አይታወቅም።

በመገናኛ ብዙኃን ዘንድ ከቀደምት ፕሬዝዳንቶች በበለጠ በራቸው ክፍት መሆኑ ይነገራል።


#BBCNEWS
#Kenyans
#CitizenTV

@tikvahEthiopia
2024/09/30 12:21:37
Back to Top
HTML Embed Code: