Telegram Web Link
#ያንብቡ

የገንዘብ ሚኒስቴር በቁርጥ በተጣለ የኤክሳይዝ ታክስ ማስከፈያ ምጣኔ ላይ ማስተካከያ የተደረገበት መመሪያ አውጥቷል።

መመሪያው " በቁርጥ በተጣለ የኤክሳይዝ ታክስ ምጣኔ ላይ ማስተካከያ ለማድረግ የወጣ መመሪያ ቁጥር 1007/2016 " ይሰኛል።

አዲሱ የተስተካከለ መመሪያ ከከዚህ ቀደሙ ጭምሪ የተደረገበት ነው።

የአልኮል መጠጦች እና የፕላስቲክ ከረጢት(ፌስታል) ኤክሳይዝ ታክስ መጣኔ፦

➡️ ከብቅል የተዘጋጀ ቢራ - የተስተካከለው የኤክሳይዝ ታክስ ምጣኔ 40% ወይም 28 ብር በሊትር ከሁለቱ አንዱ የበለጠውን

➡️ ሙሉ በሙሉ በአገር ውስጥ ተመርቶ በበቀለ ገብስ የተመረተ ቢራ - የተስተካከለው 35% ወይም 23 ብር በሊት ከሁለቱ አንዱ የበለጠውን

➡️ ውሃን ሳይጨምር ቢያንስ ከክብደቱ 75% የሚያህለው በአገር ውስጥ ግብዓት የተመረተ ቢራ - የተስተካከለው የኤክሳይዝ ታክስ ምጣኔ 30% ወይም 21 ብር በሊትር ከሁለቱ አንዱ የበለጠውን

➡️ የሚፈሉ መጠጦች (ሲዳር፣ ፔሪ፣ ኦፓክ ቢራ፤ የሩዝ አልኮል መጠጥ)፣ የሚፈሉ መጠጦችና የአልኮል አልባ መጠጦች ድብልቅ፣ ስታውት፤ ሌሎች ከቢራ ጋር ተመሳሳይ የሆኑ መጠጦች፣ ዱቄት ቢራ፣ የአልኮል ይዘታቸው ከ7% ያልበለጠ - የተስተካከለው 40% ወይም 28 ብር በሊትር ከሁለቱ አንዱ የበለጠውን

➡️ በድብልቅ የተዘጋጁ፣ የአልኮል ይዞታቸው ከ7% ያልበለጠ ጥንካሬ ያላቸው መጠጦች - የተስተካከለው 40% ወይም 28 ብር በሊትር ከሁለቱ አንዱ የበለጠውን

➡️ የፕላስቲክ ከረጢት(ፌስታል) - የተስተካከለው 103 ብር በኪሎግራም

ትምባሆና የትምባሆ ውጤቶች የኤክሳይዝ ታክስ መጣኔ

🔵 ትምባሆ የያዙ ሲጋሮች፤ ቼሩትስና ሲጋሪሎስ - የተስተካከለው 30% + 644 ብር በኪሎግራም

🔵 ትምባሆ የያዙ ሲጋራዎች - የተስተካከለው 30% + 20 ብር በፓኬት (20 ፍሬ)

🔵 እንደ ትምባሆ ከሚያገለግሉ የተዘጋጁ ሲጋሮች፣ ቼሩትስና ሲጋሪሎስ እና ሲጋራዎች - የተስተካከለ 30%+20ብር በፓኬት ( 20 ፍሬ)

🔵 የሚጨስ ትምባሆ፣ በማናቸውም ምጣኔ እንደ ትምባሆ የሚያገለግሉ ነገሮችን የያዘ ቢሆንም (የፍራፍሬ ጣዕም እንዲኖራቸው የተደረጉም ያልተደረጉም የትምባሆና ግላይሰሮል ቅልቅል የያዘ ትምባሆ ለማጨስ የሚያገለግል በውሃ ማስተላለፊያ ቱቦ የሚጨስ መዓዛ ሰጭ ዘይት እና ምዝሞዙች ፣ ሞላሰስ ወይም ስኳር ከተጨመረባቸውም ካልተጨመረባቸው በስተቀር) - የተስተካከለው 30% + 644ብር ኪሎግራም

🔵 " የተዋሐደ " ወይም " እንደገና የተዘጋጀ " ትምባሆ - የተስተካከለ 30%+644 ብር በኪሎግራም

🔵 ሱረት፤ የትምባሆ ምዝምዞችና ኤስንሶች - የተስተካከለ 30%+644ብር በኪሎግራም

መረጃው የተላከው ከገንዘብ ሚኒስቴር ነው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Kenya የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በሀገሪቱ ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ የቀሰቀሰው የፋይናንስ ረቂቅ ሕግን እንደሚያስቀሩት / እንደማይፈርሙበት አስታውቀዋል። ሩቶ እዚህ ውሳኔ ላይ የተደረሱት ተቃውሞውን ተከትሎ ቢያንስ 20 ሰዎች ከተገደሉ በኋላ ነው። ፕሬዜዳንቱ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ፤ " ኬንያውያን በሕጉ ዙሪያ ያሰሙትን ተቃውሞ በደንብ ተከታትያለሁ፤ ስለዚህም ሕጉን እንደማይፈልጉት በግልጽ ተናግረዋል፤…
" በእስራት የምታቆዩበት ምንም ምክንያት የላችሁም ፤ ልቀቋቸው " - የናይሮቢ ፍርድ ቤት

ትላንት በኬንያ ናይሮቢ ከነበረው የፋይናንስ ረቂቅ ህጉ ተቃውሞ ጋር በተያያዘ ፖሊስ በርካታ ሰዎች በቁጥጥር ስር አውሎ ነበር።

የታሰሩ ሰዎች 24 ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ናይሮቢ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

ፍርድ ቤቱም " ከእስር ልቀቋቸው " ብሏል።

ዛሬ ረቡዕ ፍ/ቤት የቀረቡት 56 ሰዎች ሲሆኑ ፖሊስ " ልመርምራቸው 14 ቀን ይፈቀድልኝ " ሲል ጠይቆ ነበር።

ፍርድ ቤቱ ግን የፖሊስን ጥያቄ ውድቅ አድርጓል።

" ሰዎቹን የሚያሳስርና ዋስ የሚያስከለክል አንድም ጠንካራ ምክንያት ስለሌለ ከእስር ልቀቋቸው " ሲል አዟል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

ላለፉት ስድስት ቀናት በመላ አገሪቱ ሲሰጥ የቆየው የመውጫ ፈተና ተጠናቋል።

57 የመንግሥት እና 124 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን ማስፈተናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

ከመውጫ ፈተናው ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

በተለይ ከተነገርን ይዘት እና ከተዘጋጀው ብሉ ፕሪንት ጋር የሚገናኝ አይደለም ብለው ቅሬታ ካቀረቡት መካከል፦
- የማኔጅመንት
-የማርኬቲንግ ማኔጅመንት
- የሀይድሮሊክና ውሃ ሃብት
- የቬተርነሪ ሳይንስ
-የኸልዝ ኢንፎርማቲክስ ተማሪዎች ይጠቀሳሉ።

ከዚህም ባለፈ ፥ " የተሰጠን ሰዓት በቂ አልነበረም ፣ፈተና ዘግይቶ የመጀመር፣ ለፈተናው በቂ ሰዓት አለመመደብ ችግር ነበር " የሚል ቅሬታ ያቀረቡም አሉ።

የኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ ፈተናም በድጋሜ እንዲሰጥ ተደርጓል።

አጠቃላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተላኩለትን ቅሬታዎች ይዞ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራርን አነጋግሯል።

ከፍተኛ አመራሩ ፤ " የዘንድሮው 2016 የመውጫ ፈተና ከ220 በላይ ፕሮግራሞች ያለምንም ችግር Smoothly ነው የተሰጠው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡

" ከፈተናዎቹ ጋር የተያያዘም ምንም አይነት Issue አላጋጠመንም " ያሉት ኃላፊው፤ " አንድም ቅሬታ ለትምህርት ሚኒስቴር አልደረሰም " ብለዋል፡፡

ውጤት መቼ ይፋ ይደረጋል በሚል ላቀረብንላቸው ጥያቄ " በቅርብ ቀን ውስጥ ይፋ ይደረጋል " ብለዋል።

Via @tikvahuniversity
" ፍጹም ሀሰተኛ / የውሸት ይዘት ነው ተጠንቀቁ " - የጠ/ሚ ጽ/ቤት

በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሶማሌላንድ ጋር ያደረገውን የመግባቢያ ስምምነት (MoU) እንደሰረዘው ተደረጎ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው።

የጠ/ሚ ጽ/ቤት ያወጣው መግለጫ አስመስሎ አንድ የተቀነባበረ የጠ/ሚ ጽ/ቤት አርማ ያለበት መግለጫ በስፋት እየተዘዋወረ ይገኛል።

ይኸው መግለጫ ፦

- ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ከተለየችው ' ክልል ' ከሶማሌላንድ ጋር የተፈራረመችውን የመግባቢያ ስምምነት (MoU) እንደሰረዘችው ፤
- ኢትዮጵያ ከዩኬ፣ ከG7 እና ከሌሎች ሀገራት ጋር ተወያይታ የሶማሌላንድን ሉዓላዊ ሀገርነት የምትደግፍበት ማስረጃ እንዳላገኘች
- የኢትዮጵያ መንግሥት ከአሁን በኃላ ህጋዊ ያልሆነ ስምምነት ከሶማሌላንድ ጋር እንደማያደርግ
- ኢትዮጵያ ፤ የሶማሌላንድ ጉዳይ የሶማሊያ ስለሆነ ፖለቲካዊ ችግራቸውን በአንድ ሀገር ጥላ ስር እንዲፈቱ እንደምትተው ... የሚገልጽ ነው።

ይህ ግን ፍጹም ሀሰተኛና መግለጫው የተቀነባበረ ነው።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ምን አለ ?

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ፤ ከሶማሌላንድ ጋር ስለተፈጸመው የመግባቢያ ስምምነት በኦንላይን እየተዘዋወረ እና እየተሰራጨ ያለው መረጃ ፍጹም ሀሰተኛ / የውሸት ይዘት ስለሆነ ህዝቡ እንዲጠነቀቅ መክሯል።

በሀገር ውስጥ ፣ በቀጠናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች መግለጫም ሆነ መረጃ የሚሰጠው በይፋዊ የጽ/ቤቱ ገጾች / ቻናሎች ላይ ብቻ እንደሆነ አመልክቷል።

ሁሉም ሰው የጽ/ቤቱን ይፋዊ አርማ በመጠቀም ከሚሰራጩ  እንደዚህ አይነት የውሸት መረጀዎች / ይዘቶች እራሱን እንዲጠብቅ አደራ ብሏል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#BOLIVIA

ቦሊቪያ ውስጥ ወታደሮች የሀገሪቱን ፕሬዜዳንት ቤተመንግሥት በኃይል ሰብረው በመግባት መውረራቸው ተሰማ።

እንቅስቃሴው " መፈንቅለ መንግሥት " ሳይሆን እንዳልቀረ ተነግሯል።

የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ሉዊስ አርሴ የሀገሪቱን ጦር " መደበኛ ያልሆነ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው " በማለት አውግዘዋል።

ወታደሮቹ በአስቸኳይ ከቤተመንግሥት እንዲበተኑ ጠይቀዋል።

በቦሊቪያ ቴሌቪዥን ላይ የተሰራጨው ቪዲዮ አርሴ ከሠራዊቱ ዋና አዛዥ ጄነራል ጁዋን ጆሴ ዙኒጋ ጋር በቤተ መንግሥቱ ኮሪደር ላይ ሲፋጠጡና ሲነጋገሩ ታይተዋል።

አርሴ ፤ " እኔ የአንተ አለቃ ነኝ፣ ወታደሮቹንም እንድታስወጣ አዝዤሃለሁ እናም ለትዕዛዜ መገዛት አለብህ !! " ሲሉ ተደምጠዋል።

ዙኒጋ ወታደሮቹን ይዘው ወደ ቤተመንግሥት ሳይገቡ በፊት ውጭ ላይ ለሪፖርተሮች በሰጡት ቃል ፥ " ማጥፋት ይቁም፣ ሀገራችንን ወደ ድህነት መምራት ይቁም ፣ ሰራዊታችንን ማዋረድ ይቁም " ብለዋል።

የጦሩ አዛዥ ዙኒጋ ፥ " አዲስ የሚኒስትሮች ካቢኔ ይዋቀራል ፤ በእርግጠኝነት ነገሮች ይቀየራሉ፣ ሀገራችን ከዚህ በኋላ አሁን ባለው ሁኔታ መቀጠል አትችልም " ሲሉ ተደምጠዋል።

ፕሬዜዳንት አርሴ በቪድዮ ባሰራጩት መልዕክት ፥ ሀገሪቱን ከሚታየው የመፈንቅለ መንግሥት እንቅስቃሴ ለመታደግ ህዝቡ ተሰባስቦ እና ተደራጅቶ ወደ ጎዳና እንዲወጣና ዲሞክራሲውን እንዲታደግ ጥሪ አቅርበዋል።

#Bolivia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

በቦሊቪያ የተሞከረው መፈንቅለ መንግሥት ከሸፈ።

ሙከራው ሰዓታትን እንኳን አልቆየም።

የፕሬዜዳንቱን ቤተመንግሥት በኃይል ሰብረው ገብተው የወረሩት ወታደሮች ከቤተመንግሥቱ አካባቢ መሄዳቸው ተሰምቷል።

ፕሬዜዳንት ሉዊስ አርሴ ፤ ወታደሮችን እየመሩ ቤተመንግሥት የገቡትን የሠራዊቱን አዛዥ ጄነራል ጁዋን ጆሴ ዙኒጋን ከስልጣን አውርደው በሌላ ተክተዋል።

አዲሱ የሠራዊት አዛዥ ጆሴ ዊልሶን ሳንቼዝ ሁሉም ቤተመንግሥት የመጡ ወታደሮች ወደ የመጡበት ወታደራዊ ሰፈር /ክፍል እንዲመለሱ አዘዋል።

ይህን ተከትሎም ወታደሮቹ ከስፋራው ለቀው ሄደዋል።

ፕሬዝዳንት አርሴ አዲስ የአየር ኃይል አዛዥ እና የባህር ኃይል አዛዥም ሾመዋል።

ፕሬዝዳንቱ ወታደሮች ቤተመንግሥቱን ሰብረው መግባታቸውን እና መውረራቸውን ተከትሎ ህዝቡ በነቂስ ተደራጅቶ ወደ ጎዳና እንዲወጣና የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ እንቅስቃሴውን እንዲያከሽፍ እና ዴሞክራሲውን እንዲያስጠብቅ ጥሪ አቅርበው ነበር።

በዚህም በርካቶች የሀገሪቱን ባንዲራ ይዘው በቤተመንግሥቱ አካባቢ ተሰብሰበው ነበር።

ፕሬዝዳንቱ ሙከራው መክሸፉን ተከትሎ ህዝቡን  በእጅጉ አመስግነዋል።

ወታደሮችን እየመሩ ቤተመንግሥት የገቡት ጄነራል ጁዋን ጆሴ ዙኒጋን ምንም እንኳን የመፈንቅለ መንግሥቱ መሪ ነኝ ብለው በግልጽ ባይናገሩም ፥ " ጥፋት ይቁም ፤ ሀገራችንን ወደ ድህነት መምራት ይቁም፣ ሠራዊታችንን ማዋረድ ይቁም " ሲሉ ተደምጠው ነበር።

ጦሩ ዴሞክራሲን ወደነበረበት ለመመለስ እና የፖለቲካ እስረኞችን ነጻ ለማድረግ እንደሚጥርም ሲናገሩ ተደምጠዋል።

ዙኒጋን አዲስ የሚኒስትሮች ካቢኔ እንደሚቋቋም ከአሁን በኃላ ሀገሪቱ አሁን ባለው መንገድ እንደማትቀጥልም ገልጻው ነበር።

ጄነራል ዙኒጋን ከሽፏል ከተባለው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በኃላ ቀጣይ ዕጣፋንታቸውን እና በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለጊዜው አልታወቀም።

ቦሊቪያ 🇧🇴 ፦ በደቡብ አሜሪካ የምትገኝ ከ12 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚኖሩባት ሀገር ናት።

#Bolivia
#failedcoup

@tikvahethiopia
" እስራዔል ምዕራባውያንን ተማምና ጦርነቱን የምታሰፋ ከሆነ ቱርክ ሊባኖስን ለመደገፍ ትገደዳለች " - ቱርክ

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን፣ " እስራዔል የጦርነቱን አድማስ የማስፋት ፍላጎት አላት " ሲሉ ተናግረዋል፡፡

" እስራዔል ትኩረቷን ሊባኖስ ላይ አድርጋለች፤ የምዕራቡ ኃይሎች ከሁነቱ ጀርባ ሆነው እስራዔልን እየገፋፉ ነው " ብለዋል ፕሬዝዳንቱ፡፡

ጠ/ሚ ኒታንያሁ ግጭቱን አስፍተው አካባቢያዊ ቀውስ ለመፍጠር ተዘጋጅተዋል ሲሉ ወቅሰዋል፡፡

" እስራዔል ምዕራባውያንን ተማምና ጦርነቱን የምታሰፋ ከሆነ ቱርክ ሊባኖስን ለመደገፍ ትገደዳለች " ብለዋል።

More 👇
https://www.tg-me.com/+LM-bJ8NzZMcxMjA8

#shafaqnews
@thiqaheth
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

ወታደሮችን እየመሩ የቦሊቪያው ፕሬዚዳንት አርሴ ቤተ መንግስትን በኃይል ሰብረው በመግባትና በመውረር የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ያደረጉት ጄነራል ሁዋን ሆዜ ዙኒጋ በሀገሪቱ ፖሊስ በቁጥጥር ስር ውለው እስር ቤት ገብተዋል።

@tikvahethiopia
2024/10/01 04:51:32
Back to Top
HTML Embed Code: