Telegram Web Link
#DStvEthiopia

✈️ አውሮፓ እንሂድ

🏆የምትወዱዋቸውን የአውሮፓ ታላላቆችን የዋንጫ ፍልሚያ 5 ቀን ቀረው!

⚽️በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የአውሮፓ ዋንጫ ሊጀመር ነው! በጀርመን የሚደረጉትን ደማቅ ጨዋታዎችን ሁሉንም በቀጥታ በዲኤስቲቪ በጎጆ ፓኬጅ በ350 ብር ይከታተሉ!

የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2

#Euro2024 #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
የሐሳብ መድረክ 💬

https://www.tg-me.com/+01D5gVgONq8yMjE8

" መብቷ ነው / መብቱ ነው ? "

ምንድነው መብቱ ነው ? መብቷ ነው ?

የሌላ ሰዎች ልጆች ሲሆኑ እንደፈለጉ ይሁኑ እድሜዋ/ው ነው ፤ መብቷ ነው / መብቱ ነው ... የእኛ ልጆች ሲሆን የምን መብት ነው ? ስነ-ስርአት ትያዝ / ይያዝ የሚል አመለካከት በማህበረሰባችን ውስጥ ትልቅ ቀውስ ይፈጥራል።

የኛ ልጆች ሲሆኑ ወደ ቤተክርስቲያን / ወደ መስጂድ የሌሎች ሲሆኑ " እድሜያቸው ነው መብታቸው ነው የፈለጉበት ይሂዱ " ማለት ፤ አልፈ ሲልም ከነሱ ጋር ባልተገባ ቦታ ዝቅ ብሎ መለዋል ጉዳቱ የከፋ ነው።

ሁሉም ነገር ገደብ ሲኖረው ጥሩ ነው።

ዛሬ የፈለጉበት ይዋሉ የተባሉ ልጆች ነገ የኛንም ልጆች ይዘው እንደማይጠፉ ምን ያህል እርግጠኞች ነን ?

ሁሉም ታዳጊ ልጆች ልጆቻችን ናቸው ብለን ወደ ጥሩ ቦታ እንምራቸው። ከተሳሳተ መንገዳቸው እናርማቸው። ነግበኔ ነው እንበል !

በናውስ (Nous) የሐሳብ መድረክ...እርሶም በውስጦ የሚመላለሰውን የሚናገሩበት ቦታ ያጡትን ጠቃሚ #ሐሳብ_ያጋሩ👇
https://www.tg-me.com/+01D5gVgONq8yMjE8

@NousEthiopia
#ደመወዝ

° " ደመወዝ በአግባቡ #እየተከፈለን_አይደለም ፤ የሚመለከተዉ አካል ካላናገረን ማስተማር አንችልም " - የከምባ ወረዳ መምህራን

° " በየሶሻል ሚዲያ ' ደመወዝ አልተከፈለንም ' እያሉ ገጽታችንን የሚያበላሹትን በህግ እንጠይቃለን " - የዞኑ ትምህርት መምሪያ ሀላፊ

° " ያልተከፈላቸው መምህራን
#ስራ_ስለማቆማቸው መረጃ አለኝ " - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር

ከሰሞኑ በጋሞ ዞን ከምባ ወረዳ መምህራን " ደሞዝ በአግባቡ እየተከፈለን አይደለም " በማለት ቅሬታቸዉን አሰምተዋል።

" ዞኑ ውስጥ ካሉት ሀያ ክላስተሮች ተለይተን ደመወዝ አልተከፈለንም " ያሉ መምህራን ስራ ማቆማቸውንና የሚመለከተው አካል ካላናገራቸው ስራ እንደማይገቡ በመግለጽ ቅሬታቸዉን አቅርበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ይህንን የመምህራን ጉዳይ ሰምቶ ይመለከታቸው ያላቸውን አካላት ማለትም ፥ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበርና የዞኑን ትምህርት መምሪያ አነጋግሯል።

የክልሉ መምህራን ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ አማኑኤል ጳዉሎስ ምን አሉ ?

አቶ አማኑኤል ፥ " በዞኑ በከምባ ወረዳ #ለመምህራን እየተከፈለ ያለው ደሞዝ የተቆራረጠና አግባብ ባልሆነ መልኩ እየተፈጸመ ነው " ብለዋል።

አክለውም ፤ " በክላስተር ተቆራርጦ ከመክፈሉ ባለፈ በአንድ ትምህርት ቤት እንኳን ለጥቂት መምህራን ተከፍሎ ለአብዛኛው ደግሞ አለመከፈሉ ያበሳጫቸው መምህራን ስራ አለመግባታቸውን ተከትሎ ትምህርት ቤቶች ስለመዘጋታቸው መረጃ አለን " ብለዋል።

የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ሀላፊው አቶ አብርሀም አምሳሉ ምን አሉ ?

አቶ አብርሀም ፤ " ያለኝ መረጃ ለመምህራን ደመወዝ በአግባቡ እየተከፈላቸው መሆኑን እና ስራም እየተሰራ መሆኑን ነው " ብለዋል።

" ይሁንና በየሶሻል ሚዲያው ላይ የአካባቢውን ገጽታ ለማጠልሸት በማሰብ ' ደመወዝ አልተከፈለንም ' እያሉ የሚንቀሳቀሱ አካላት ወሬውን እያናፈሱት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

" እነዚህ አካላት በህግ እየተጠየቁ ሲሆን ወደፊትም ይጠየቃሉ " ብለዋል።

ምን አልባት ያልተከፈላቸዉ መምህራን ካሉ የዲስፕሊን እና መሰል ችግር ያለባቸው ሊሆኑ ይችላሉ ሲሉ አክለዋል።

በተጨማሪም በአካባቢው ላይ ትምህርት መቋረጡን የሚመለከት መረጃ እንደሌላቸዉ በመግለጽ ችግር ተከስቶ ከሆነ እንደሚስተካከል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray በትግራዩ ጦርነት ምክንያት በየቦታው የተቀበሩ እና የተጣሉ ተተኳሾች፣ ፈንጂዎች አሁንም በሰው ህይወት ላይ አደጋ ማድረሳቸው ቀጥሏል። ዛሬ ዓርብ ግንቦት 16 / 2016 በተጣለ ተተኳሽ ባል እና ሚስት ህይወታቸው አልፏል። አደጋው ያጋጠመው በትግራይ ክልል ፣ በማእከላዊ ዞን ቆላ ተምቤን ምረረ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ሲሆን በተተኳሹ ምክንያት የባል ህይወት ወድያው አልፏል። የሟች ሚስት ወደ…
#Tigray🚨

በሓውዜን ወረዳ በተጣለ ተተኳሽ #የ4_ሰዎች ህይወት ጠፋ።
 
በትግራዩ ጦርነት ምክንያት በየቦታው የተቀበሩ እና የተጣሉ ተተኳሾች ፣ ፈንጂዎች አሁንም በሰው ህይወት ላይ አደጋ ማድረሳቸው ቀጥሏል።

ሰኔ 1/2016 ዓ.ም በትግራይ ክልል በምሰራቃዊ ዞን ፤ ሓውዜን ወረዳ ማይጎቦ ቀበሌ ገበሬ ማህበር በፈነዳ ተተኳሽ የ4 ወገኖች ህይወት #ተቀጥፏል

ከአራቱ የአደጋው ሰለባዎች ሶስቱ የአንድ ቤተሰብ አባል ናቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሓውዜን ወረዳ ኮሙኒኬሽን ባገኘው መረጃ  ፥ ሟቾቹ ከ 9 እስከ 14 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ገና ትንንሽ ልጆች ናቸው።

ከሰላም ስምምነቱ በኋላ የሰኔ 1/2016 ዓ/ም አደጋን ጨምሮ በትግራይ የተለያዩ ወረዳዎች በተጣሉ እና በተቀበሩ  ተተኳሾችና ፈንጂዎች ከ107 ሰዎች ላይ የሞት ፣ የአካል መጉደል አደጋ ደርሷል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

ከ3500 ዶላር እስከ 10 ሺ ዶላር የሚያሸልመው ለግብርና መሻሻል የሚረዱ የቴክኖሎጂ ውድድር መጀመሩን " አዩቲ ኢትዮጵያ ቻሌንጅ " ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

ሄፈር ኢንተርናሽናል የውድድሩ አዘጋጅ ባሳወቀው መሠረት፣ የውድድሩ ዓላማ የአርሶ አደሮች ምርታማነትን መጨመር የሚያስችሉ፣ ድካም የሚቀንሱ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሀሳብ ማቅረብ ነው።

ወድድሩ ሲካሄድ የአሁኑ ለሶስተኛ ጊዜ ሲሆን፣ የሚወዳደሩት ከ18 - 30 የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እንደሆኑና ተገልጿል።

የፈጠራ ሀሳባቸውን በ #ኦንላይን ማስገባት እንዳለባቸው ተመላክቷል።

የውድድሩ አሸናፊዎች በምን መልኩ ይለያሉ ?

➡️ ተወዳዳሪዎቹ ከሚያቀርቧቸው የቴክኖሎጂ ሀሳቦች 30ዎቹ በዳኞች ይመርጣሉ፣
➡️ ዳኞች በተገኙበት 30ዎቹ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ፣
➡️ ከ30ዎቹ 10 ሀሳቦችን ዳኞች ይመርጣሉ፣
➡️ 10ሩ ተወዳዳሪዎች ለ10 ቀናት ይሰለጥናሉ፣
➡️ ከስልጠናው በኋላ የመጨረሻ የ3 ተወዳዳሪዎች ሀሳብ ይመረጣል።

የሽልማት አሰጣጡ በምን መልኩ ነው ?

1ኛ ለወጣው 10 ሺህ ዶላር፣

2ኛ ለወጣው 6 ሺህ 500 ዶላር፣

3ኛ ለወጣው ሀሳብ ደግሞ 3 ሺህ 500 ዶላር የሥራ ማስጀመሪያ እና የማበረታቻ ሽልማት ይደረግላቸዋል።

ከዚህ ቀደም በተካሄዱት 2 ውድድሮች የተለያዩ የግብርና ዘርፍ ላይ ያተኮሩ አጠቃላይ 12 የፈጠራ ቴክኖሎጂዎች ተግባር ላይ መዋላቸው ተነግሯል።

ማመልከቻ ፦ https://ayute-ethiopia.et/apply-here/

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@TikvahEthiopia
#CPPI #WorldBank

የዓለም ባንክ ከኤስ ኤንድ ፒ ግሎባል ማርኬት ኢንተለጀንስ ጋር የሚያዘጋጀው የኮንቴይነር ወደብ የአፈጻጸም መለኪያ (Container Port Performance Index - CPPI) የ2023 ደረጃ ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርጓል።

ይህ መለኪያ ወደቦች የመረከብ አቀባበላቸውንና እንዴት እንደሚያስተናግዱ በአጠቃላይ ያላቸውን የስራ ቅልጥፍና እና አፈጻጸም የሚለካ ነው።

በዚህም ከ409 ወደቦች የራስ ገዟ #ሶማሌላንድ " #በርበራ " ወደብ 106ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

የሶማሊያ ፤ " #ሞቃዲሾ " ወደብ ደግሞ 166ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

የ " #ጅቡቲ " ወደብ ከመጨረሻ ተርታ 379ኛ ደረጃ ላይ ነው የተቀመጠው።

በዚህ የዓለም ባንክ የአፈጻጸም መለኪያ የበርበራ ወደብ ከሞቃዲሾ እና ጅቡቲ ወደቦች የተሻለ ደረጃ ተሰጥቶታል።

በአጠቃላይ ዓለም አቀፍ ደረጃ ከተሰጣቸው ከ405 ወደቦች በመጨረሻ ተርታ ማለትም 379 ላይ የተቀመጠው የጅቡቲ ወደብ በሀገሪቱ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታ ፈጥሯል።

የጅቡቲ ወደብ በ2022 ከዓለም የተሰጠው ደረጃ 26ኛ ሲሆን በ2023 መለኪያ 379ኛ ላይ መቀመጡ ጅቡቲን አላስደሰተም።

ሀገሪቱ " የ2023 ደረጃ አሰጣጥ ምክንያታዊነት የጎደለው በመሆኑ ያሳስበናል " ያለች ሲሆን " ምን አይነት ሳይንስ ነው የሚያብራራው በዓለም ደረጃ ከ350 በላይ ነጥብ መጣል ? " ስትል ጠይቃለች።

በአንድ ዓመት ውስጥ እንዲህ ያለው ደረጃ መሰጠቱ በመለኪያው ላይ የተዓማኒነት ጥያቄ እንደሚያስነሳ ገልጻለች።

ጅቡቲ ፥ " ደረጃ አሰጣጡ ነጻ እና ከተእጽኖ የጸዳ ነው ወይ ? " ስትል ጠይቃ " ለማንኛውም አድሏዊም ሆነ አልሆነ ጅቡቲ ከሰሃራ በታች እና ምስራቅ አፍሪካ ትልቁ እና ቀልጣፋ ማዕከል ናት " ብላለች።

ሙሉ ዶክመንቱን በዚህ ያግኙ ➡️ CPPI 2023

#WorldBank

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
የሕብረት ባንክ ማህበራዊ ገፆቻችንን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!

ቴሌግራም: https://www.tg-me.com/HibretBanket
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/HibretBank
ሊንክዲን: https://www.linkedin.com/company/hibretbank/
ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/hibretbank/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@hibretbanket

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
#ሪልስቴት #አዲስአበባ

° “ ብራችንን እኔ አውጥተን ተሰቃየን ” - የኖህ ሪልስቴት ቤት ገዥዎች

° “ የመብራት፣ የውሃ፣ የውሃ ታንከር ጥያቄ አለ ትክክል ነው ” - ኖህ ሪልስቴት

በአዲስ አበባ ከተማ ፤ በኖህ ሪልስቴት ' የኖህ አያት ግሪን ፖርክ ቤት ' ገዢዎች ኖህ የገባውን ውል በመዘንጋት የቤት መሠረተ ልማቶችን እያሟላ እንዳልሆነ እና በጠበቃቸው በኩል ምላሽ እንዲሰጣቸው ቢጠይቁም መፍትሄ እንዳላገኙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አማረዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ የገቡበት ቤት፦
- ውሃ፣
- መብራት፣
- ጀነሬተር
- የውሃ ታንከር የሚባሉ መሠረት ልማቶች እንደሌሉ ገልጸዋል።

ቤት ገዢዎቹ ከዚህ ቀደም፣ “ ቅሬታ ባቀረብንበት ወቅት የኖህ ጠበቃ በ1 ወር ከ 15 ቀን ጊዜ ውስጥ የጋራ መሠረተ ልማቶች አጠናቀው እንደሚያስረክቡ ቃል ተገብቶልን ነበር ” ሲሉ አስታውቀዋል።

“ እስካሁን እንኳን ሊጨርሱ ምንም እንቅስቃሴ የለም ” ብለው፣ “ ቤት ውስጥ የገቡ ቤት ገዢዎች ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠዋል። መብራት የለም፣ ውሃ የለም፣ ውሃ ታንከር የለም ” በማለት አማረዋል።

“ እነዚህ መሰረተ ልማቶችን ውላችን ላይ አሟልተው እንደሚሰጡን ተስማምተን ነው ቤቱን የገዛነው። ኖህ ውሉን ጥሷል ” ነው ያሉት።

“ ይባስ ብሎ ቤት ገዢ #የቤት_ክራይ_ሽሽት ወደገዛው ቤቱ መሰረታዊ ነገር ባልተሟላበት ሁኔታ ለመግባት ተገዶ መብራት በሳይቱ ዙርያ ካሉ ቤቶች በህገወጥ መንገድ ለመቀጠል ተገዷል ” ሲሉ አክለዋል።

“ ግቢው በተጠላለፈ የኤሌትሪክ ገመድ በገመድ ሆኗል ” ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ “ ይህ ለሚኖሩት ሰዎችም ሆነ ለልጆቻቸው ትልቅ አደጋ ይፈጥራል ” ሲሉ አስረድተዋል።

ሁነቱን የሚያሳይ ቪዲዮም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ልከዋል።

በጠበቃቸው በኩል ኖህ ምላሽ እንዲሰጣቸው ቢጠይቁም ምላሽ እንዳልሰጣቸው አስረድተው " የመፍትሄ ያለህ " ብለዋል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላኩት ጠበቃቸው ለኖህ ሪልስቴት የጻፈው ደብዳቤ ፥ ኖህ የቤቶቹን መሠረተ ልማት እያሟላ እንዳልሆነ፣ ምላሽ እንዲሰጥ ቢጠይቅም ምላሽ እንዳልሰጠ ያትታል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ቅሬታ አቅራቢዎቹ ላነሷቸው እያንዳንዱ የቅሬታ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲሰጥ ኖህ ሪልስቴትን ጠይቋል።

የድርጅቱ የሕግ አማካሪ እና ጠበቃ አቶ ዮሴፍ ደስታ በሰጡት ቃል፣ “ የመብራት፣ የውሃ፣ የውሃ ታንከር ጥያቄ አለ ትክክል ነው ” ብለዋል።

ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-06-10

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

" መኪና አቁሞ መሄድ ፍጹም የተከለከለ ነው " - ፖሊስ

የኮሪደር ልማት ስራዎቻቸው ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት በተደረጉት መንገዶች ላይ ተሸከርካሪዎችን አቁሞ መሄድ ክልክል መሆኑን አዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ከ5ቱ የኮሪደር ልማት ስራዎች ውስጥ ፦

➡️ ከአራት ኪሎ እስከ ቅ/ማሪያም ቤ/ክርስቲያን መታጠፊያ
➡️ ከቴዎድሮስ አደባባይ እስከ መሐሙድ ሙዚቃ ቤት እንዲሁም
➡️ ከቀይ ባህር ኮንዶሚኒየም በደጎል አደባባይ እስከ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን አቅጣጫ መንገዱ ትላንት ተከፍቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ ለአገልግሎት ክፍት በተደረጉት መንገዶች ላይ ተሸከርካሪዎችን አቁሞ መሔድ ፍጹም ክልክል መሆኑን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
#Malawi

ዛሬ የማላዊውን ምክትል ፕሬዝዳንት ሳውለስ ቺሊማን እና ሌሎች 9 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ አውሮፕላን ተሰውሯል።

እንደ አገሪቱ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት መረጃ አውሮፕላኑ የማላዊ መከላከያ ኃይል ንብረት ነው።

ጥዋት ከሀገሪቱ ዋናው ከተማ ሊሎንዌ ከተነሳ በኋላ " ከራዳር ዕይታ ውጪ " ሆኗል። ምን ውስጥ ይግባ አይታወቅም።

የአገሪቱ የአቪዬሽን ባለሥልጣናት ከአውሮፕላኑ ጋር ግንኙነት ለማድረግ ሞክረው ነበር ግን አልቻሉም።

የሀገሪቱ ፕሬዝዳንትም #የፍለጋ እና #ነፍስ_የማዳን ተልዕኮ እንዲካሄድ አዘዋል።

ም/ ፕሬዝዳንቱ መንግሥትን ወክለው በአንድ የቀድሞ የም/ቤት አባል የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ለመገኘት ነበር በረራ የጀመሩት።

አብረዋቸው በርካታ የፓርቲያቸው ባለሥልጣናት ነበሩ።

Credit : #BBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Malawi ዛሬ የማላዊውን ምክትል ፕሬዝዳንት ሳውለስ ቺሊማን እና ሌሎች 9 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ አውሮፕላን ተሰውሯል። እንደ አገሪቱ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት መረጃ አውሮፕላኑ የማላዊ መከላከያ ኃይል ንብረት ነው። ጥዋት ከሀገሪቱ ዋናው ከተማ ሊሎንዌ ከተነሳ በኋላ " ከራዳር ዕይታ ውጪ " ሆኗል። ምን ውስጥ ይግባ አይታወቅም። የአገሪቱ የአቪዬሽን ባለሥልጣናት ከአውሮፕላኑ ጋር ግንኙነት ለማድረግ…
#Malawi

የማላዊ ምክትል ፕሬዜዳንት ሳውለስ ቺሊማን እና ሌሎች ባለስልጣናትን ይዞ ከራዳር እይታ ውጭ የሆነውን እና የገባበት ያልታወቀውን አውሮፕላን ፍለጋ እየተካሄደ ነው።

ፍለጋው እየተካሄደ ያለው በመከላከያ ወታደሮች ፣  በፖሊስ አባላት እንዲሁም በሌሎች ሲቪል ዜጎች እንደሆነ ተነግሯል።

የሀገሪቱ መንግስት #ያሰማራው_ኃይል እንዲህ አይነቱን ፍለጋ ለማድረግ አቅም ስለሌለው እና ምንም ማድረግ ስለማይችል ልክ እንደ ማንኛውም ሲቪል እየተንቀሳቀሰ ነው እየፈለገ ያለው።

ምናልባትም " አውሮፕላኑ ወድቆ ይሆናል " ተብሎ በታሰበበት ጫካ ውስጥ ፍለጋ በእግር እና በመኪና እየተካሄደ እንደሚገኝ ነው የተሰማው።

በርካታ የሀገሪቱ ዜጎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ም/ፕሬዜዳንቱ እና አብረዋቸው ያሉት ሰዎች " ጥሩ ነገር አልገጠማቸውም " የሚል ስጋታቸውን እያጋሩ ነው።

ም/ፕሬዜዳንቱ አብረዋቸው በርካታ የፓርቲያቸው ባለሥልጣናት ነበሩ።

የሀገሪቱ መንግሥት ለእንደዚህ አይነት አደጋ ወቅት የሚሆን ዝግጁነትና ለፍለጋ የሚሆኑ መሳሪያዎችን እንኳን አላሟልም በሚል እየተተቸ ነው።

አውሮፕላኑም ከተሰወረ ከረጅም ሰዓታት በኃላ ነው ለህዝቡ ያሳወቀው።

በቅርቡ ፥ የኢራን ፕሬዝዳንት የነበሩት ኢብራሂም ራኢሲ እና ሌሎች ከፍተኛ የሀገሪቱ ባለስልጣናት በስራ ጉዳይ ሲጓዙበት የነበረ ሄሊኮፕተር ጫካ ውስጥ ተከስክሶ ሁሉም መሞታቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia
2024/09/28 13:19:52
Back to Top
HTML Embed Code: