Telegram Web Link
#Abyssinia_Bank

ዕሴቶቻችሁንና የሸሪዓን መርሆች በማክበር የሚያገለግላችሁ አቢሲንያ አሚን  ለእርሰዎ የሚስማሙ በርካታ አገልግሎቶችን ይዟል።

አቢሲንያ አሚን ዕሴትዎን ያከበረ!

#AbyssiniaAmeen #IFB #bankofabyssinia
#Banking #BanksinEthiopia  #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#Tecno #Camon30Pro5G

ቴክኖ ሞባይል በአይነቱ የተራቀቀውን አዲሱን Tecno Camon 30 pro 5G ምርጫዎ ያድርጉ ሲል ይጋብዛል!

#Camon30Et #Camon30pro5GEt #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt
#Kenya #USA

የጎረቤት ኬንያ ፕሬዜዳንት በአሜሪካ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛሉ።

እ.ኤ.አ ከ2008 ወዲህ ወይም ከ16 ዓመት በኃላ ነው ዋይት ሃውስ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ መሪ በዚህ ደረጃ ተቀብሎ እያስተናገደ የሚገኘው።

አሜሪካን እየጎበኙ የሚገኙት ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ከፍ ያለ አቀባበል እና ከፍተኛ የቀድሞና የአሁን ባለስልጣናት በተገኙበት ልዩ እራት ግብዣ እንደተደረገላቸው ታውቋል።

ከፕሬዜዳንት ጆ ባይደንና ከሌሎች ባለልሰጣናት ጋር ተገናኝተው የሁለትዮሽ ውይይት ያደረጉም ሲሆን ሁነኛ ስምምነቶችም ከአሜሪካ መንግሥት ጋር መፈራረማቸው ተሰምቷል።

ሩቶ ከቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ባራክ ኦባማ ጋርም ተገናኝነትው መክረዋል።

በሌላ በኩል ፥ ኬንያ የሀገሪቱን የጸጥታ ስራዎች እና የሰላም ማስከበር ተልእኮዎቿን ለማሳደግ 16 በአሜሪካ የተሰሩ እጅግ ዘመናዊ ሄሊኮፕተሮች ልትቀበል እንደሆነ " ሲትዝን ቲቪ " ዘግቧል።

ይህ የፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በዋሽንግተን ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ ለኬንያ ካበረከቱት መልካም ነገሮች አንዱ ነው ተብሏል።

ሂሊኮፕተሮቹ እ.ኤ.አ ከ2024 እስከ 2025 መጨረሻ ናይሮቢ ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዋይት ሀውስ አስታውቋል።

ከዚህ በተጨማሪ ኬንያ በመስከረም ወር 150 " M1117 " የታጠቁ እጅግ ዘመናዊ የደህንነት ተሽከርካሪዎችን ትቀበላለች።

More ➡️ @thiqahEth

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
" ሲጀመር ‘የኮቴ’ ክፍያ አገር ውስጥ መጠየቅ አግባብ አይደለም " - ጣና የከባድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች ማኀበር

የከባድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች ፣ ሞጆ መግቢያ ‘ #የኮቴ ’ በሚል ታጣቂዎች አስቁመው 2,000 ብር እያስከፈሏቸው መሆኑን እየገለጹ ይገኛሉ።

ካሁን ቀደም ገንዘቡን ሲጠየቋቸው የነበረው አንዳንድ ጊዜ በቀን እንደነበር ፣ ከሰሞኑን ግን ቀንም ሌሊትም እየጠየቋቸው ከመሆኑም ባሻገር ድብደባና እንግልት እያደረሱባቸው መሆኑን አስረድተዋል።

ሰሞኑን አንዱን ሹሬር ሞጆ መግቢያ ከሌሊቱ 6 ሰዓት አስቁመው ገንዘብ እንደጠየቁት፣ ‘የለኝም’ ሲላቸው እንዳንገላቱት ገልጸዋል።

ሌላኛው ሹፌር ክፉኛ መመታቱን አመልክተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለ “ ኮቴ ” ክፍያው ምንነት ያውቅ እንደሆን የጣና የከባድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች ማኀበርን ጠይቋል።

ማኀበሩ ፤ " አሁን #ጂቡቲ ስንደርስ የሌላ አገር መሬት ስለምንረግጥ ‘ የኮቴ ’ እንከፍላለን። የተለመደ ነው። እዚህ ግን ‘የኮቴ’ እያሉ 2,000 ነው የሚጠይቁት። ይሄ ደግሞ ተገቢም አይደለም " ብሏል።

" ሞጆ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች ድርጊቱ አለ " ያለው ማኀበሩ ፣ አንድ ጊዜም ቢሆን መከፈሉ ከህግ አግባብ ውጪ ሆኖ ሳለ በድጋሚ ሌላ ቦታ ላይ እንደሚያስከፍሏቸው አስረድቷል።

ማኀበሩ ፤ " ሲጀመር ‘ የኮቴ ’ ክፍያ በአገር ውስጥ መጠየቅ አግባብ አይደለም " ብሎ፣ ከክፍያው ባሻገር አሽከርካሪዎቹ ገንዘቡን በሚጠይቁ መሳሪያ የታጠቁ ታጣቂዎች ድብደባ እንደሚፈጸምባቸው፣ የክልሉ አካላት ድርጊቱን ቢያውቁም መፍትሄ እንዳልሰጡ ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ቅሬታውን በተመለከተ ምላሽ ለማግኘት ወደ ክልሉ ባለስልጣናት ያደረገው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም።

Video Credit - ኪያ

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ( #INSA ) የ2016 ዓ/ም " National Cyber Talent Challenge Program " ማዘጋጀቱን ገልጿል።

በሳይበር ደህንነትና ተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ እና ፍላጎት ያላቸው በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ወጣቶች በሙሉ በዚህ ቻሌንጅ ላይ መሳተፍ ይችላሉ ተብሏል።

የታለንት መስኮች፦

- Cyber Security
- Cyber Development
- Embedded Systems
- Aerospace ናቸው።

ስልጠናው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለአንድ ወር ይሰጣል።

አመልካቾች በዌብሳይት  https://talent.Insa.gov.et በመግባት ከዛሬ ጀምሮ እስከ ግንቦት 30/ 2016 ዓ/ም መመዝገብ እንደሚችሉ ተገልጿል።

ለበለጠ መረጃ ደግሞ +251904311833 ፣ +251943579970፣ +251904311837 ላይ ስልክ መደወል ይችላል።

@Tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥቆማ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ( #INSA ) የ2016 ዓ/ም " National Cyber Talent Challenge Program " ማዘጋጀቱን ገልጿል። በሳይበር ደህንነትና ተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ እና ፍላጎት ያላቸው በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ወጣቶች በሙሉ በዚህ ቻሌንጅ ላይ መሳተፍ ይችላሉ ተብሏል። የታለንት መስኮች፦ - Cyber Security …
#INSA #ጥቆማ

የብሔራዊ የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ ምዝገባ መካሄድ ጀምሯል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በ2014 ዓ/ም እና በ2015 ዓ/ም ለሁለት ተከታታይ አመታት በሳይበር ደህንነት እና ተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ታዳጊ ወጣቶች በክረምት ፕሮግራም (Summer Program) አሰልጥኖ ማስመረቁን ገልጿል።

ተመራቂዎችንም ፦

° #እንደየችሎታቸው እና #እንደስራዎቻቸው ከተለያዩ ባለሀብቶች ጋር የማስተሳሰር፤

° ኢመደአን (INSA) ጨምሮ በተለያዩ ተቋማት #ተቀጥረው መስራት የሚችሉበት ሁኔታ እንዳመቻቸ አመልክቷል።

ባለፉት ሁለት አመታት የተከናወኑ የሳይበር ታለንት ልማት ፕሮግራሞችን መነሻ በማድረግ በ2016 በጀት አመት “ብሄራዊ የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ” ፕሮግራም መዘጋጀቱ ተገልጿል።

የዚህ ቻሌንጅ ዋና ዓላማ በሳይበር ደህንነት እና ተያያዥ መስኮች ልዩ ተሰጥዖ ያላቸዉን ሰዎች በመመልመል በዘርፉ ላይ ተጨባጭ ተጽዕኖ መፍጠር የሚችል ብሄራዊ የሳይበር ሰራዊት (National Cyber Army) መገንባት ነው ተብሏል።

በሳይበር ደህንነት እና ተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ እና ፍላጎት ያላቸው እና እድሜያቸው ከ11 አመት ጀምሮ ያሉ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በዚህ ቻሌንጅ ላይ መሳተፍ ይችላሉ ተብሏል።

መመዝገቢያ ጊዜ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ግንቦት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ነው።

መመዝገቢያ አድራሻው https://talent.insa.gov.et ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#USA #kenya

የጎረቤታችን ሀገር ኬንያን ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶን ተቀብለው እያስተናገዱ ያሉት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ኬንያን ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት መካከል የመጀመሪያዋ #የNATO_አባል_ያልሆነች (non-NATO) ዋና አጋር ሀገር እንደምታደርጋት ቃል መግባታቸው ተነግሯል።

@tikvahethiopia
#Ethiotelecom

iPhone 15 Pro Max is now available, offering you the ultimate smartphone experience!

Prepare to be fully immersed in a realm of advanced technology and unparalleled convenience.

Choose from an amazing selection of packages to get everything you need.

📱 iPhone 15 Pro Max +
🔌 Charger Head
🌐 100/50 GB Mobile Data and
🎧 AirPods 3rd Generation

You can get the devices from our premium business centers, Churchill avenue next to Lycée Gebre Mariam School.

#iPhone15ProMax
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
#ADHD

የስዊድን መንግሥት ፦
° ጥንቃቄ የጎደለው ትኩረት የማጣት፣
° ከፍተኛ የመቅበጥበጥ፣ 
° ብዙ የማውራት፣
° ግትርነት
° እራስን የመግዛት ቀውስ (ADHD -attention deficit hyperactivity disorder) ችግር በብዛት የሚታይባቸው ልጆች በሀገሪቱ ቁጥራቸው መጨመሩን ዛሬ አስታወቀ።

የሀገሪቱ የማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው ቃል የስዊድን የጤና እና ደህንነት ቦርድ መረጃ ADHD ተብሎ የሚገለጸው #የአእምሮ_ጤና_ችግር እ.ኤ.አ. ከ2022 ጀምሮ 10 በመቶ በሚሆኑ ወንዶች ልጆች ላይ እንዲሁም 6 በመቶ በሚሆኑት አዳጊ ሴት ልጆች ላይ በምርመራ መታየቱን ይፋ አድርጓል።

የችግሩ ተጋላጭ ልጆች ቁጥር ሊጨምርም ይችላል ተብሏል።

በመላው ዓለምም ከ5 እስከ 7 በመቶ የሚሆኑ ልጆች ለዚህ ችግር የተጋለጡ ናቸው።

ለዚህ ችግር የሚያጋልጡ ምክንያቶች ፦
- የተለያዩ እንደ ሊድ ወይም እርሳስ ባሉ ማዕድናት የተበከለ አካባቢ መኖር፣
- በእርግዝና ወቅት መድኃኒቶች፣ አልኮል ወይም ሲጋራ / ትንባሆ ማጨስ ማዘውተር ሊሆኑ እንደሚችሉ ይገመታል።

ከዚህም በተጨማሪ በደም አማካኝነት በዘር የአእምሮ ህመሞችም ሊተላለፉ እንደሚችሉ ነው የተገለጸው።

ይህ የአእምሮ ችግር (ADHD) ያለባቸው ልጆች ቁጥር ለምን እንደጨመረ መንስኤውን ለማወቅ ጥናቶች እየተካሄዱ ነው።

#DeutscheWelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥንቃቄ🚨 " በተጣሉ ተተኳሾች እና ፈንጂዎች 103 ሰዎች #ሞተዋል ፤ አካላቸው ጎድሏል " - የቆላ ተምቤን ወረዳ በትግራይ ማእከላይ ዞን የቆላ ተምቤን ወረዳ በጦርነቱ ምክንያት በርካታ ተተካሾች እና ፍንጂዎች ይገኛሉ። እጅግ አስከፊውና ደም አፋሳሹን ጦርነት ተከትሎ በአከባቢው የተቀበሩትና የተጣሉት ተተካሾችና ፈንጂዎች በበርካታ ሰዎችና እንስሳት ላይ የሞትና የአካል ጉዳት አደጋ በማድረስ ላይ እንደሆኑ…
#Tigray

በትግራዩ ጦርነት ምክንያት በየቦታው የተቀበሩ እና የተጣሉ ተተኳሾች፣ ፈንጂዎች አሁንም በሰው ህይወት ላይ አደጋ ማድረሳቸው ቀጥሏል።

ዛሬ ዓርብ ግንቦት 16 / 2016 በተጣለ ተተኳሽ ባል እና ሚስት ህይወታቸው አልፏል።

አደጋው ያጋጠመው በትግራይ ክልል ፣ በማእከላዊ ዞን ቆላ ተምቤን ምረረ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ሲሆን በተተኳሹ ምክንያት የባል ህይወት ወድያው አልፏል።

የሟች ሚስት ወደ ሆስፒታል ብትወሰድም ህይወቷን ማዳን አልተቻለም።

የቆላ ተምቤን ወረዳ በአስከፊው እና በደም አፋሳሹ የትግራይ ጦርነት በርካታ ውግያ ያስተናገደ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በአከባቢው ላይ የተቀበሩና የተጣሉ ተተኳሾችና ፈንጂዎች የማፅዳ ጉዳይ ትኩረት ይሻል ብለዋል የአከባቢው ነዋሪዎች።

ከፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በኋላ በቆላ ተምቤን ወረዳ ብቻ በተጣሉ ተተኳሾችና  ፈንጂዎች 103 ሰዎች ላይ የሞት የአካል መጉደል አደጋ መድረሱ በሚያዝያ ወር 2016 ዓ/ም የመጨረሻ ሳምንት ላይ መዘገባችን ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
                                       
@tikvahethiopia            
የአሜሪካ ኤምባሲ ሁለት ቀን ተዘግቶ ይውላል።

በአዲስ አበባ የሚገኘው የኤሜሪካ ኤምባሲ ሰኞ እና ማክሰኞ ዝግ ሆኖ እንደሚውል አስታውቋል።

ኤምባሲው ፥ ሰኞ ግንቦት 19/2016 ' ሚሞሪያል ዴይ 'ን ወይም በግዳጅ ላይ የተሰዉ የአሜሪካ አርበኞች መታሰቢያ በዓልን ምክንያት በማድረግ እንደሚዘጋ አመልክቷል።

በነጋተው ማክሰኞ ግንቦት 20 የ #ደረግ_መንግሥት የወደቀበትን ቀን ምክንያት በማድረግ ሙሉ ቀን ተዘግቶ እንደሚውል ገልጿል።

ኤምባሲው ዳግም የሚከፈተው #ረቡዕ_ግንቦት_21 መሆኑን አሳውቋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#Tecno #Camon30Pro5G

Tecno Camon 30 pro 5G እያንዳንዱ ፎቶ እና ቪድዮ ከፍተኛ ጥራት እንዲላበሱ የSony IMX890 ካሜራ ሴንሰር ገጥሞ ቀርቧል!

#Camon30Et #Camon30Pro5GEt #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt
#ሰከላ

" ባለፈው ሳምንት ውስጥ ብቻ 47 ሰዎች ናቸው የተገደሉት " - ነዋሪዎች

" በተጨባጭ የሞተ አንድም ሲቪል የለም። ይህ ነው ትክክለኛው እውነት " - የኮማንድ ፖስት ምክትል ሰብሰቢ

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ላይ ግንቦት 4 ቀን 2016 ዓ/ም በ " ፋኖ " እና በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች መካከል የተኩስ ልውውጥ እንደነበር ፣ ከዚያ በኋላ ባሉት ቀናት " በጸጥታ ኃይሎች " ንጹሐን መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ቃላቸውም የሰጡ ነዋሪዎች ምን አሉ ?

° #ሰርገኞች ሳይቀሩ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ተገድለዋል። ሰርግ ላይ የነበሩ የሙሽራው ወንድም፣ አጃቢዎች ሰኞ ግንቦት 5 ቀን 2016 ዓ/ም መንገድ ላይ ተረሽነዋል።

° ሴቶች ተገድለዋል።

° 3 ካህናት ከቤተክርስቲያን እየተመለሱ በነበረበት ወቅት ተገድለዋል።

° ባለፈው ሳምንት ብቻ 47 ሰዎች ናቸው የተገደሉት።

° እውነት የተናገሩ ሰዎች ተጨፍጭፈዋል።

° ግንቦት 15/2016 ዓ/ም ከሰከላ 4 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ቦታ 6 ሰዓት የተጀመረ ተኩስ እስከ ምሽቱ 12 ቆይቷል።

° ተራው ህዝብ ወደ ገጠራማው አካባቢ፣ ባለሃብቶች ወደ ባሕር ዳር ከተማ ለመፈናቀል  ተገደዋል።

አንድ አሽከርካሪ አባትም ልጃቸው ሱቅ ብሎ እንደወጣ እንደተገደለባቸው በሀዘን ስሜት ሆነው ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ተኩስ ያለው ሰሞኑን ብቻ ነው ከዚህ በፊትም ነበር ?  ተብሎ ጥያቄ የቀረበላቸው ነዋሪዎች ፣  የካቲት 20 ቀን 2016 ዓ/ም ነበር። ከየካቲት 2016 ዓ/ም ጀምሮ በሰከላ ብቻ 107 ሰዎች ተገድለዋል " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ሰላም እንዲያሰፍንላቸው የጠየቁ ሲሆን  " ሰላም ይውረድልን ግጭት በመጣ ቁጥር እየሞተ ያለው ንጹሃን እንጂ የታጠቀ ኃይል አይደለም " ብለዋል።

የምዕራብ ጎጃም ኮማንድ ፖስት ምክትል ሰብሳቢ እና የዞን ዋና አስተዳዳሪ እድሜአለም አንተነህ ከሰሞኑን ለ ' አሻም ቴሌቪዥን ' በሰጡት ቃል ፥ " አንድም ንጹሃን አልተገደለም " ብለዋል።

ዋና አስተዳዳሪው ምን አሉ ?

- ከሳምንት በፊት ሰከላ ላይ ሌሎች ቦታዎች አልፎ አልፎ እንደሚደረገው ግጭት ነበር። ግጭት የነበረው ከከተማው 18 ኪሎ ሜትር ቦታ ላይ ነበር። ግጭቱ የነበረው በታጠቁ ኃይሎች እና በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች መካከል ነው። ሁለቱም መሳሪያ የያዙ ናቸው።

- እዛ የነበረውን ክፍተት መነሻ አድርጎ ሌላው የታጠቀ ኃይል እኛ ' ፅንፈኛው ኃይል ' የምንለው  ሾልኮ ገብቶ ባንኮችን እና የግለሰብ ድርጅቶች ላይ ከፍተኛ ዝርፊያ ነው የፈጸመው። በቦታው ላይ በሁኔታው ላይ የተሳተፈ በተጨባጭ የሞተ አንድም ሲቪል የለም።

- በተጨባጭ የሞተ አንድም ሲቪል የለም። ይህ ነው ትክክለኛው እውነት።

- ሲቪሊያን ሰዎች የሚኖሩበት አካባቢ ላይ ግጭት መተንኮስ አግባብ አይደለም። የተፈናቀለ ሰው የለም፣ የወጣ ሲቪልም የለም። በግጭቱ የተሳተፈ ሲቪል የለም። ከተማው ላይ ያችግር ሲፈጠር ሰዎች ቤታቸው ውስጥ ነበሩ።

- አሁን የገጠሩ ህዝብ ዘር እየዘራ ነው። የአካባቢው ኑሮም መደበኛው ነው። የተፈናቀለም የለም፤ እንደዛ የሚባል ስጋት የለም።

በሰከላ ተፈጸሟል የተባለውን ግድያ ሰምቶ እንደሆን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበለት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ፣ ሰሞኑን በአማራ ክልል ስላለው ጥቃት ሪፓርት ይፋ እንደሚያደርግ፣ የሰከላውም በዚሁ ሪፖርት ውስጥ ተካቶ ሊሆን እንደሚችል ገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#Tigray

" በአላማጣ ዙሪያ የነበረው ኃይል አከባቢውን ለቆ ወጥቷል " - የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ትላንትና ከምሸቱ 4:00 ባወጣው መግለጫ ፥ " በአላማጣ በቅሎ ማነቂያና ገርጃለ የነበረው #የተወስነ የትግራይ ተዋጊ ኃይል አከባቢውን ለቆ ወጥቷል " ብሏል።

የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነትን በማስመልከት በአዲስ አበባ በወጣው የአተገባበር ኦፕሬሽን ፕላን መሰረት በማድረግ ተዋጊ ኃይሉ አከባቢውን እንዲለቅ መደረጉን ገልጿል።

ለአላማጣ ህዝብ ደህንነት ተብሎ የተወሰነ ተዋጊ ኃይሉ ከቦታው ለቆ ቀድሞ ወደ ነበረበት ቦታ መመለሱን አመልክቷል።

የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንትም አቶ ጌታቸው ረዳም ይህኑን አረጋግጠዋል።

አቶ ጌታቸው ራዳ ፤ " የፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት ትግበራ አካል ሆኖ የትግራይ ተፈናቃዮች በቀላሉ ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ ከፌዴራል መንግስት እና ከአማራ አስተዳደር ጋር ያለውን መግባባት ለማክበር በአላማጣ አቅራቢያ ከሚገኙት ገርጀለ እና በቅሎማናቂያ አካባቢዎች የትግራይ ሃይሎች እንዲወጡ ተወስኗል " ብለዋል።

ተጨማሪ የትግራይ ተፈናቃዮችን ለመመለስ ተመሳሳይ አይነት እርምጃ ለመውሰድ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

የጊዚያዊ አስተዳደሩ ም/ፕሬዝዳንት ሌ/ ጀነራል ታደሰ ወረደ ባለፈው እሁድ በሰጡት መግለጫ የትግራይ አስተዳደር ወደ አላማጣ እንደሚገባና በአከባቢው  የሚገኘው የትግራይ ታጣቂ ኃይል ይወጣል በማለት ተናግረው ነበር።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
                                       
@tikvahethiopia            
2024/09/26 22:10:32
Back to Top
HTML Embed Code: