Telegram Web Link
ይታሰብበት!

ምንም እንኳን ስለታሪኩ እውነተኛነት አንዳንዶች ቢጠራጠሩና እንደ አፈ-ታሪክ ቢቆጥሩትም፣ ስለጥንቱ የማሰዶኒያ (መቀዶኒያ) ገዢ እና የጦ አዛዥ አሌክሳንደረ (Alexander the Great) እንዲህ የሚል ታሪክ እንደተጻፈ ይነገራል፡፡

ይህ አለም ያወቀውና ያደነቀው ታላቅ ሰው በመጨረሻዎቹ ሰዓታት ጊዜ በሞት አፋፍ ላይ ሆኖ እንዲህ አለ ይባላል፡ “ሶስት ትእዛዞች አሉኝ፡-

1) አስከሬኔን መሸከም ያለባቸው የግል ሃኪሞቼ ብቻ ናቸው፤

2) ወደ መቃብር የምሄድበት መንገድ በወርቅ፣ በብር እና በዕንቁዎች የተሞላ መሆን አለበት፤

3) እጆቼ ከሬሳ ሣጥኑ ላይ ተንጠልጥለው መተው አለባቸው።

በአሌክሳንደር ዙሪያ የነበሩና ይህንን ትእዛዙን የሰሙ ሁሉ ግራ ሲጋቡ የቅርብ ጀረናሎቹ ቀረብ ብለው እነዚህ ሶስት ትእዛዞች ለምን ያን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ጠየቁት፡፡ መልሱ እንደሚከተለው ነበር፡፡

1. ሐኪሞች በመጨረሻ አቅመ ቢስ እንደሆኑና እኛን ከሞት መዳን እንደማይችሉ ሰዎች እንዲያውቁ እመኛለሁ።

2. ሰዎች ሀብትን ለማሳደድ ሲሉ የሚያጠፉት ጊዜ እጅግ ውድ ጊዜያቸው መሆኑን እንዲያውቁ እመኛለሁ።

3. እንዲሁም፣ ሁላችንም ባዶ እጃችንን ወደዚህ ዓለም እንደመጣን እና ሁላችንም በተመሳሳይ መንገድ ባዶ እጃችንን እንደምንሄድ ሰዎች ሁሉ እንዲያውቁ እመኛለሁ።

Ummmmm . . . ይታሰብበት!

©Dreyob
#ለምን_እናዝናለን?

በሕይወት ስንኖር ማጣትና ማግኘት ፣ ማዘንና መደሰት ... የለት ተለት የኑሮአችን አካል ናቸዉ፡፡ የሰዉ ልጅ ግን በቻለዉ መጠን ስለሀዘን ማሰብ ማየትና መስማት አይሻም ፡፡ በእርግጥ "የሀዘን" ጥልቀት ቢለያይም ሰዉ ሆኖ ግን ከሀዘን ያመለጠ የለም ፡፡ አንዳንዱ የሀዘን ስሜት ቶሎ ሲረሳ ሌላዉ ግን ልብን ሰብሮ ለዘመናት ማንነታችን ሁኖ አብሮን ይቆያል ፡፡

እና በአጠቃላይ የምናዝንባቸዉ ዋና ዋና ምክንያቶች ምንድናቸዉ ስንል?

፩. የምንወደዉን ነገር ስናጣ ፦ ይህ ዋናዉና ትልቁ ምክኒያት ነዉ ፡፡ የሰዉ ልጅ በጣም የሚያዝነዉ የሚወደዉን ሲያጣ ነዉ (ማለትም የመጀመሪያው ማጣት በሞት ሲሆን ሁለተኛዉ ደሞ በመለያየት ነዉ፡፡ ለዚህ መሰለኝ መለያየት ራሱ ሞት ነዉ ተብሎ የሚወራዉ፡፡ ስለዚህ የቅርብ ቤተሰቡን ፣ ጓደኛዉን ፣ ጎረቤቱን በሞት ሲነጠቅ ሰዉ ትልቅ ሀዘን ዉስጥ ይገባል ፡፡ በመለያየት ደግሞ ከሚወዱት ባል ወይም ሚስት ሲፋቱ ፣ ከፍቅር አጋር ሲለያዩ ብሎም ከሚኖሩበት ቀዬ ለቀዉ ወደ ሌላ ቦታ ሲከትሙ ከለመዱት በመለየትዋ ያዝናሉ ።)

#በሌላ_አገላለፅ ፡- ያለን ነገር (ጥሩ ነገር) ሲወሰድብን

፪.መጥፎ ነገር ሲገጥመን ፦ ይህ ደግሞ ከመጀመሪያዉ ጋር ተመሳሳይ ይመሰል እንጂ የራሱ አንድምታ አለዉ ግን ይሄ በተለይም የሚገናኘዉ (ስንታመም ፣ ሰዋች በተለያየ ምክንያት እኛ ላይ ጉዳት ሲያደርሱ ወይም ሊያደርሱ እንዳሉ ስናዉቅ እና በተጨማሪም ጥሩ ያልሆነ ነገር ሲገጥመን ነዉ፡፡ )

#በሌላ_አገላለፅ ፡- መጥፎ ነገር ሲጨመርብን

፫. ስለነገሮች ያሰብነዉና ነባራዊዉ ሁኔታ ሳይጣጣም ሲቀር ፦ (ይሄ የብዙዋቻችን ችግር ነዉ ፥ ብዙ ግዜ ስለ ሕይወት ፣ አዳዲስ ቦታዋች ፣ ስራና ሰዋች እንዲሆኑ የምናስበዉና ሁነዉ የምናገኛቸዉ ለየቅል ነዉ ስለዚህ ቦታዉ ደርሰን ነገሩን ስናየዉ ሌላ የሀዘን ምክንያት ይሆናል)

#በሌላ_አገላለፅ ፡- ስለ ነገሮች ያለን ጥሩ/መጥፎ አመለካከት ላይ ተቃራኒ እዉነት ሲገጥመን (expectation)

#የምናዝነዉ_በምክንያት_ነዉ !
@psychoet
ሀሙስ #4

#ሰዎች_ሁልጊዜም_የሚሉት_ነገር_አያጡም
Telegram www.tg-me.com/psychoet

አባትና ልጅ ወደ አንድ አካባቢ ረጀም ጉዞ ለማድረግ አህያቸውን ጭነው ከቤታቸው ይወጣሉ፡፡ ጉዞውን እንደጀመሩ ልጅ በአህያው ላይ ቁጭ ብሎ አባት ደግሞ የአህያዋን ልጓም ይዘው በእግራቸው ይጓዙ ጀምር፡፡ ጥቂት እንደተጓዙ ግን የልጅን በአህያ ላይ መቀመጥ የአባትን በእግር መጓዝ የተመለከቱ ሰዎች “አባቱ በእግሩ እየሄደ እንዴት ልጁ በአህያ ይሄዳል? ምን ዓይነት ስነ ምግባር የጎደለው ልጅ ነው?” በማለት ቅሬታቸውን እና ትችታቸውን ሰነዘሩ፡፡ ይህንን እንደ ሰሙ አባት እውነትም ስህተት የሰሩ መስሏቸው ልጃቸውን በእግሩ የአህያዋን ልጓም ይዞ እንዲሄድ አድርገው እሳቸው ደግሞ በአህያ ላይ ወጥተው ጉዟቸውን ቀጠሉ፡፡ ጥቂት እንደተጓዙ አሁን ደግሞ ሰዎች አባት ላይ ትችታቸውን ማዥጎድጎድ ጀመሩ;፡፡ “ምን ዓይነት ጨካኝ አባት ነው? ልጁን በእግሩ እያዳከረ እሱ በአህያ እንዴት ይሄዳል” አሉ፡፡ በዚህም አባት ይደናገጡና ከአህያዋ ላይ በመውረድ እንግዲያውስ ሁለታችንም በእግራችን እንሂድ ተባብለው በእግራቸው ጉዟቸውን ይቀጥላሉ፡፡ ወደ ሌላ መንደር ሲቃረቡ አሁንም አህያዋን ያለ ምንም ጭነት ተዝናንቶ መሄድ እና የአባትና ልጅን በእግር መጓዝ የተመለከቱ የመንደሩ ሰዎች ሌላ ትችት መሰንዘር ጀምሩ፡፡ “ድሮም ሃብት ያላቸው ሰዎች ችግራቸው ይኼ ነው! እንዴት ያላቸውን ነገር መጠቀም እንዳለባቸው አያውቁም” አሉ፡፡

አሁንም ሰውን ማስደስት እንዳልቻሉ እና ልክ እንዳልሆኑ የተሰማቸው አባት እና ልጅ የሚቀጥለው መንደር ሰው አፍ ላለመግባት ሁለቱም በአህያዋ ላይ ወጥተው መጓዛቸውን ቀጠሉ፡፡ ቀጣዩ መንደር እንደደረሱ ግን አባት እና ልጅ የገጠማቸው አሁንም ሌላ ትችት ነው፡፡ “ምን ዓይነት ጨካኝ ሰዎች ናቸው? አንደበት የላትም ብለው ነው? የእግዜር ፍጥረት ላይ ይታያችሁ እስኪ እንዴት ሁለት ሆነው ጀርባዋ ላይ ተዝናንተው ተቀምጠው ይሄዳሉ አንዳቸውን ከተሸከመች አንሶ ነው” አሉ፡፡ አባት እና ልጅ ተደናግጠው ሁለቱም ከአህያዋ ጀርባ ላይ አፍታ እንኳን ሳይቆዩ ወረዱ፡፡ በየደረሱበት ትችት የገጠማቸው አባት እና ልጅም ምን ማድረግ እንደሚገባቸው ከተመካከሩ በኋላ ቢያንስ ከዚህ በኋላ የምናገኛቸውን ሰዎች ማስደሰት ይኖርብናል ብለው በማሰብ አህያዋን ተጋግዘው ለሁለት ተሸክመው ጉዟቸውን አሁንም ይቀጥላሉ፡፡ አህያዋን በመሸከማቸው ምክንያት እጅግ ተዳክመው ወደ ሚቀጥለው መንድር ይደርሳሉ፡፡ አህያ የተሸከሙትን የከተማዋን ሰዎች የተመለከቱት ሰዎች ወገባቸውን ይዘው መሳቅ ጀመሩ፡፡ ምን ዓይነት ጅል ሰዎች ናቸው አህያዋ ላይ ተቀምጠው እንደመሄድ እንዴት አህያ ተሸክመው ይጓዛሉ በማለት ተሳለቁባቸው፡፡ አባትና ልጅም ምንም ነገር ቢያደርጉ ከሰው ትችት ማምለጥ እንደማይችሉ እና ሁልጊዜም ቢሆን ሰዎች የሚተቹት ነገር ፈልገው እንደማያጡ ተረድተው ጉዟቸውን እነሱ ባሻቸው መንገድ ቀጠሉ፡፡

እውነትም ሰዎች ምንጊዜም ቢሆን የሚሉት አንድ ነገር አያጡም፡፡ የምታደርጉትን ነገር ቢወዱትም ባይወዱትም፤ ልክ ነው ብለው ቢያስቡም ባያስቡም ፤ ቢመለከታቸውም ባይመለከታቸውም አንድ የሚሉት ነገር አያጡም፡፡ መፍትሄው የገዛ ራስን ህይወት በራስ ፍላጎት መምራት ነው፡፡ የአንተ/የአንቺ ህይወት የተባለበትም ምክንያት ይኼ ነው፤ አንተ/አንቺ በአሻችሁ መንገድ ትመሩት ዘንድ ነው፡፡

ስለዚህ የትኛውም ጥሩ ነው፣ ዋጋ አለው፣ ይበጀኛል ወዘተ ብላችሁ ከልባችሁ እስካመናችሁ ድረስ ሰዎች ምንም ይበሉ ምን ከማድረግ ወደ ኋላ አትበሉ፡፡

(በኤባ ተስፋዬ)
©zepsychologist
Telegram www.tg-me.com/psychoet
#ክፍል_4
www.tg-me.com/psychoet (በናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ)

የማስታወስና የመርሳት ችሎታ ! /Memory and Forgetting /
_________
የሰው ልጅ ካሉት ረቂቅ ነገሮች አንዱና ዋነ
ኛው ነገሮችን የማስታወስ ችሎታው ነዉ ፡፡ አስባችሁታል ነገሮችን ማስታወስ ባንችል ይቺ አለም ምን ልትሆን እንደምንትችል ? ጠቅላላውን መርሳት ትተነው ከቤታችን ስንወጣ እረስተናቸው የወጣናቸው ቁልፎች ፣ መረጃዎች ... ምን ያህል እንደሚያበሳጩን ይታወቃል ፡፡ በተማሪነት ጊዜያችንም ፈተና ላይ ስንቶቻችነን ነን ይሄንንማ አጥንቼው ነበር ብለን ከጥያቄው ጋር ለብዙ ሰአት ተፉጠን ሳንሰራው ከወጣን በኀላ መጸሐፍ ስናገላብጥ "ይህን እንዴት እረሳሁት?" ብለን የተቆጨን?! ብቻ ከመርሳት ጋር ብዙ ቡዙ ገጠመኞች ሁላችን ጋር አለ ፡፡ ብዙ ጊዜ "ልበ ቢስ !" የተባለ ሰውም የመርሳትን ውጤት ጠንቅቆ ያውቃል ፡፡

ዛሬ ታዲያ ስለዚህ ወሳኝ ነገሮች የማስታወስና የመዘንጋት ሂደት ሳይኮሎጂ ምን ይላል የሚለውን በአጭሩ እንመለከታለን ፡፡ የምታነቡትን ሳትረሱ በደንብ አንብቡት 😉
_________
አዕምሮውአችን የሚሰራው ዋነኛ ነገር ይህ መ
ረጃዎችን በተለያዩ ነርቮች አማካኝነት የመቀበል የማስቀመጥና የማስታወስ ስራ ነው ፡፡ ይህ ሁሉ ሂደት ግን ቅደም ተከተሉን ጠብቆ የሚከናወንና መረጃዎችን ከማስገባት ፣ ማስቀመጥ እስከ ማስታወስ/ አውጥቶ መጠቀም የሚደርስ ስርዓት ነው ፡፡

ስለ ማስታወስ ስናወራ #ሁለት ወሳኝ #ስርአቶችን እናነሳለን ፡፡ እነዚህም
1. የማስታወስ #ሂደት/ዘዴ (Process )
2. የማስታወስ #አወቃቀር (structure ) ናቸው ፡፡
_________

1. የመጀመሪያው ማስታወስ ሂደት/ ዘዴ (
process) መረጃዎችን የመሰብሰብ የመያዝና መልሶ የመጠቀም #ሶስት ቅደም ተከተሎች አሉት ፡፡ እነርሱም :-
1.Encoding / መረጃዎችን ማስገባት /
2.Storage / መረጃዎችን ማከማቸት /
3.Retrieval / የተከማቹ መረጃዎችን መመለስ (ማውጣት )/

1.Encoding / መረጃዎችን ማስገባት / በዚህ ሂደት ማንኛውንም የምንሰማቸው የምናያቸዉ ... ( በተለያዩ የስሜት አካሎቻን የሚገቡ መረጃዎች ) ለአጠቃቀም በሚመች ሁኔታ ወደ አዕምሮአችን የሚገቡበት ነው ፡፡

2.Storage / መረጃዎችን ማከማቸት / በዚህ ሂደት ማናቸውም የገቡ መረጃዎች የሚከማቹበት ሂደት ነው ፡፡ ለምሳሌ ኮምፒዩተር ላይ አንድ ነገር ሰርተን የሆነ ቦታ ላይ #save ካላደረግነው መልሰን አናገኘውም ፡፡ እንዲሁም መረጃዎች በአግባቡ አዕምሮአችን ውስጥ Store ካልተደረጉ ልናገኛቸው አንችልም ፡፡ አብዛኛውም "የመርሳት " ችግር የሚመጣው በዚህ የተነሳ ነው ፡፡

3.Retrieval / የተከማቹ መረጃዎችን መመለስ (ማውጣት )/ በዚህ ሂደት ደግሞ ከተለያዩ የገቡ መረጃዎች መካከል መርጠን ለተለያዩ ነገሮች የምንጠቀምበት ሁኔታ ነው ፡፡ ለምሳሌ ፦ ካጠናነው መካከል አንድ ጥያቄ ለመስራት የግድ ሁሉንም ማስታወስ አያስፈልግም አዕምሮአችን መርጦ የሚገናኘውን መረጃ ይሰጠናል ፡፡ ሰዎችን ስናገኝ ትዝ የሚለን ስለነሱ ያለን ያስቀመጥነው መረጃ እንጂ (ከነሱ ጋር የማይያያዝ ታሪክ አይደለም ) ። ይህ የማስታወስ የመጨረሻው ሂደት ነው ፡፡

_________
2. ሁለተኛው የማስታወስ
#አወቃቀር (structure ) ነው

ይቀጥላል ...

በሚቀጥለው ሳምንት ማክሰኞ (02/03/13 )ማታ 2:00 እቀጥለዋለሁ ....
#ቅዳሜ ደግሞ በተለመደው ሰአታችን በልዩ ፕሮግራም እንዴት የማስታወስ ችሎታዬን እጨምራለሁ ደግሞም መርሳትን እቀንሳለሁ በተጨማሪ መጥፎ ትዝታዎችን እንዴት አርጌ እረሳለሁ ለምትሉ በሚቀጥለው ሳምንት #ቅዳሜ በልዩ ፕሮግራም መፍትሔዎችን ይዤ እቀርባለሁ ፡፡________

❖ ❖_____❖ ❖
Source:- Different psychology text books and Addis Ababa University teaching material


ማንኛውም ጥያቄ / ተጨማሪ ሀሳቦች Comment ማረግ ይቻላል ፡፡

ይህ ፅሁፍ ለብዙ ሰው እንዲደርስ ሁላችንሞ ባለንበት የ Telegram / Facebookግሩፕ ውስጥ #ሼር እናርገው 💛

ዕውቀት ከአሉታዊ የአስተሳሰብ እስር ቤት ነፃ ያወጣል !
የሳምንት ሰው ይበለን!

THIS IS MY TELEGRAM CHANNEL :- YOU CAN Join and get BOOKS there .
🚙  www.tg-me.com/Psychoet 👍
🚕  www.tg-me.com/Psychoet 👍
🚗  www.tg-me.com/Psychoet 👍
Facebook.com/psychologyabc

ብዙ ሰዎች በዚህ ጊዜ በተለያዩ ምክንያቶች የማስታወስ አቅማቸው እየቀነሰ ስለሆነ #Share አርጉት !
ናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ 🤷‍♂ pinned «⚠️⚠️⚠️⚠️ ይሄን ሰሞን በከተማችን የተለያዩ ቦታዎች ራስን ማጥፋት በዝቷል። በተለይ በአፍላው እድሜ በሚገኙ ወጣቶች ዘንድ ራስን ማጥፋት በጣም እየጨመረ ነው። እባካችሁ ራሴን ላጠፋ ነው ወይም መሮኛል ብሎ ለፖሰተ ሰው ብታቁትም ባታውቁትም አብሮነታችሁን ድጋፋችሁን አሳዩ እንጂ ቀልድ አትቀልዱ። ለቀልድና ጨዋታ ብዙ የተሻለ ቦታ አለ። በቅርብ የምናቃቸው ሰዎች መሞታቸው ሲገለፅ የአብዛኛው ጓደኞቻቸው…»
ሀሙስ #5

#ህይወትን_በአዲስ_እይታ
www.tg-me.com/psychoet

ብዙዎቻችን ህይወትን የምንደርስበት ግብ አድርገን ፣ነገ የምናገኘው፣ ከልፋት በኋላ የምንቀዳጀው፣ ከአድማስ ባሻገር ያለ የቅርብ ሩቅ አድርገን እንስለዋለን። ይህ ግን ዛሬን እንደ መራራው ኮሶ መድኃኒት እየተጋትን ነገን በሰማይ እናዳለችው ወተቷን እንደማናየው ላም እየናፈቅን የቅዠት ኑሮ፣ በተስፋ መቁረጥ የታጨቀ፣ መፍጨርጨር የተሞላበት ግቡን ቀና ብሎ የሚያይ ግን የችግሮች እንቅፋት የሚያገላድፈው እይታችን ነው። ይህንን እይታ የኑሮ መሰረታቸው አድርገው የትዳር አጋራቸውን ያለፍቃዳቸው የራቁ፣ ልጆቻቸውን የማይንከባከቡ፣ ለእራሳቸው በቂ ጊዜ የማይሰጡ፣ ነፍሳቸው የወደደችውን ነገር ማድረግ እንደ ቅንጦት የሚቆጥሩ ሞልተዋል። ይህ ደግሞ በስተመጨረሻ ቁሳዊ የሆነ ማንነት አሳቅፎ ብቻችንን ያስቀረናል።

ግን እስኪ ደግሞ በዚህ በኩል እንመልከተው! ህይወት ግብ ሳይሆን መንገድ ነው። እራሳችንን እያወቅን የምንጓዝበት፣ በመኖራችን ለውጥ የምናመጣበት፣ በስህተታችን ተምረን የምንቀየርበት፣ በገጠመኞች የተሞላ ወደ ተሻለ ማንነት የሚደረግ ጉዞ። ይህን እይታ ከያዝን ለነገ መኖርን እናቆማለን ማለት ሳይሆን ነገን እያሰብን ዛሬን እስከነ ጭራሹ ከመዘንጋት እንላቀቃለን። ግለኝነትን ያተኮረ የራሴ ጥቅም ብቻ እያልን በሰዎች ጫንቃ ላይ በመወጣጣት እኔን ብቻ ላኑር ከሚል ርካሽ አስተሳሰብ ከላያችን ላይ አራግፈን በዛሬ ውስጥ እራሳችንን ማግኘት ያስችለናል።

ዛሬ ጊዜ ያልሰጠናቸው ቤተሰቦቻችን ነገ “እንደዛ ስለፋ የነበረው አንተ የሻለ ኑሮ እንድትኖር በማሰብ ነው” “እንዲህ እንድትንደላቀቂ ብዬ ነው ቀን ከለሊት ስለፋ የነበረው” የሚል የየዋህነት አስተሳሰብ ያሳጣናቸውን ፍቅር እና አብሮነት አይተካም። ገንዘብ ለልጆቻችን ጃኬትን እንጂ ማቀፍ የሚሰጠውን የደህነትን ስሜት አይገዛም። ገንዘብ ውድ የሆነ ስጦታን እንጂ ከትዳር አጋራችን ጋር የምናሳልፈውን ጊዜ አይገዛም፣ ገንዘብ አልጋን እንጂ እንቅልፍን አይገዛም፣ ገንዘብ ምግብን እንጂ የምግብ ፍላጎትን አይገዛም። ስለዚህ በእኛነታችን የምንሰጣቸውን፣ የገንዘብ ቁልል የማይገዛቸውን፣ የመኖር ሃብቶች፣ የህይወት ስጦታዎች የሆኑትን እኚህን የዛሬ ውጤቶችን አሳጥተናቸው ነገ ገንዘብ ብንሰጣቸው ዋጋው ምንም ነው።

ህይወታችንን ግብ አድርገን ከምንስለው በዕለት ተዕለት ኑሮዋችን ውስጥ የምናደርጋቸው ማናቸውም ቁርኝቶች ድምር መሆኑን ብናምን ይህ አዲስ እይታ የብርሃን ጮራ በህይወታችን ላይ ይፈነጥቅልናል።

(ዘመነ ቴዎድሮስ) ©psychologist
www.tg-me.com/psychoet
#ክፍል_5
www.tg-me.com/psychoet (በናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ)

ማስታወስና የመርሳት ! /Memory and Forgetting /part II
.....ከባለፈው የቀጠለ

በጣም ከሚያስቀኝ ገጠመኞቼ መካከል ስለ አንድ ደስ ስለሚል ነገር እያሰብኩ ለአፍታ ሰው ካናገርኩ / ለሰው ጥያቀቄ መልስ ከሰጠሁ በኅላ መልሼ ምን እያሰብኩ እንደነበረ የሚጠፋብኝ ነገር ነው ፡፡ ከዛ እሱን ለማስታወስ እረጅም ጊዜ ይወስድብኛል ደሞ እኮ የሚገርመኝ ሀሳቡ ምንም ይሁን ምን አዕምሮዬ በጎን "የጣም ደስ የሚል ነገር እያሰብክ ነበር እንዴት ትረሳዋለህ ? ! " እያለ የሚጎተጉተኝ ነገር ነው ።

ሌላው ደግሞ ከሰው ጋር ተቀጣጥሬ ካፌ / የሆነ ቦታ የሚገርም ወሬ ተመስጠን እያወራን በመሀል ወንበር ሲወድቅ / አስተናጋጅ መቶ ሲያዋራን / ወጣ ያለ ድምፅ ከካፌው ስንሰማ ትኩረታችን ወደዛ ሂዶ ስንመለስ ምን እያወራን እንደነበር ይጠፋናል ፡፡ ከዛ እንደዚህ እንላለን " ምን እያወራሁ ነበር .... "

በሉ መልካም ንባብ ይሁንላችሁ እኔም ስለ ምን ላስተምር እንደነበር ሳልረሳ ስለማስታወስ የጀመርኩትን ትምህርት ልቀጥል...
_________
አዕምሮውአችን የሚሰራው ዋነኛ ነገር
ይህ መረጃዎችን በተለያዩ ነርቮች አማካኝነት የመቀበል የማስቀመጥና የማስታወስ ስራ ነው ፡፡ ይህ ሁሉ ሂደት ግን ቅደም ተከተሉን ጠብቆ የሚከናወንና መረጃዎችን ከማስገባት ፣ ማስቀመጥ እስከ ማስታወስ/ አውጥቶ መጠቀም የሚደርስ ስርዓት ነው ፡፡

1. የመጀመሪያው ማስታወስ ሂደት/ ዘዴ (process) ባለፈው ክፍል ተመልክተናል ዛሬ ደግሞ ስለ ማስታወስ #አወቃቀር (structure ) እንመለከታለን ፡፡
_________
2. ሁለተኛው የማስታወስ
#አወቃቀር #ደረጃ #ቅርፅ
(structure ) ነው

በዚህ ስርአት መረጃዎች እንዴት እንደሚገለፁ ፣ እንደሚሰበሰቡና ለብዙ ጊዜ ሳይጠፉ እንደሚቆዩ ይጠናል ፡፡ማስታወስ ትልቅ ሂደትና ችሎታ ያለው ረቂቅ የአዕምሮ ስራ ነው ፡፡
Atkinson and Shiffrin የተባሉ ባለሙያዎች ያረቀቁትን ባለ #3 ደረጃ የማስታወስ አወቃቀር እንመልከት ፡፡

1.Memory /Sensory Register (በስሜት ሕዋሶቻችን የገቡ መረጃዎችን መዝጋቢ)
2.Shory-Term Memory / STM ( አጭር - ጊዜ ትዝታ )
3.Long-Term Memry / LTM (የረጅም - ጊዜ ትዝታ)
_________
1.Memory /Sensory Regi
ster (በስሜት ሕዋሶቻችን የገቡ መረጃዎችን መዝጋቢ)

በዚህ ደረጃ የገቡ መረጃዎች ተመርጠው ወደ 2ኛ ክፍል (STM) የሚገቡ ሲሆን ሌሎች የማያስፈልጉ መረጃዎች እዚሁ ይጠፉሉ ፡፡ በዚህ ጊዜ ያየናቸው በ 1 ሰከንድ የሰማናቸው ደግሞ ቢበዛ 2 ሰከንድ ይቆያሉ ፡፡

2.Shory-Term Memory / STM ( አጭር - ጊዜ ትዝታ )

ከመጀመሪያው ደረጃ ትኩረታችንን ስበዉ ተመርጠው ወደዚህ የገቡት መረጃዎች ይከማቻሉ ፡፡ ይህ ደረጃ ለማሰብ ፣ ለማንበብ ፣ ለመናገር እንዲሁም ችግሮችን ለመፍታት ወሳኝ ደረጃ ነው ፡፡ ይህ ደረጃ ሌላ በርካታ አጠራሮች አሉት እነዚህም working memory / Primary memory / Active memory ... ይህ ሁሉ አገላለፅ ምን ያህል ንቁ ትዝታ መዋቅር እንደሆነ ለማሳየት ነው ፡፡

ይህ የአጭር ጊዜ ትዝታ #4 አራት መለያዎች አሉት፡፡
1.Active / ንቁ ፦
ይህ አንድ ሰው በንቃተ አዕምሮው የሚሰራው መሆኑንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማገናዘብ ብሎም የድሮ አስፈላጊ ትውስታዎችን የሚታወስበት ነው፡፡

2.Rapid Accessibility / ፈጣን ተደራሽ ፦
በዚህ ያሉ መረጃዎች በቀላሉ /3ኛ ደረጃ LTM/ ካሉት ይልቅ ቶሎ የሚታወሱና ለጥቅም የሚውሉ ናቸው ፡፡
ለምሳሌ :- አንድ ቁም ሳጥን ውስጥ ካለ እቃና ጠረጴዛ ላይ ካለ ቶሎ በቀላሉ የምናገኘው ፊት ለፊት ጠረጴዛ ላይ የተቀመጠውን ነው ፡፡

3.Preserve the temporal sequence of information ፦
ሌላው መለያ መረጃዎች የሚቀመጡት ጊዜያዊ በሆነ መንገድ ቅደም ተከተላቸውን ጠብቀዉ ነው ፡፡

4. Limited Capacity / የተወሰነ መጠን ፦
ይህ የትውስታ ክፍል የተወሰነ መረጃ ብቻ ነው መያዝ የሚችለው ፡፡ George Miller (1956) እንዳስቀመጠው አቅሙ ( 7+- 2 ነው ) ማለትም ከ #5 እስከ #9 መረጃዎችን ብቻ ነው ሊይዝ የሚችለው ፡፡

በአጠቃላይ መረጃዎቻ በዚህ ደረጃ የሚቆዩት ቢበዛ #30 ሰከንድ ነው ፡፡

ሁላችንም እንደሚያጋጥመን ጠይቀን በቃላችን የያዝናቸውን ስልኮች ከአፍታ በኅላ ሌላ ተጨማሪ መረጃዎች ሲመጡ እንረሳቸዋለን ፡፡

3.Long-Term Memry / LTM (የረጅም - ጊዜ ትዝታ)

ይህ መዋቅር መረጃዎች በአንጻራዊነት ለረጅም ጊዜ የሚቆዩበት ሁኔታ ነው ፡፡ መጠኑም ወሰን የሌለውና አሁን እንዳሉት ኮምፒዩተሮች ይህን ያህል መረጃ ይይዛል ተብሎ የማይቀመጥ ነው ፡፡ በዚህ የተከማቸው ትውስታ / ትዝታ እኛነታችንን የሚወስን ስለ እራሳችን ያለንን አወንታዊም ሆነ አሉታዊ አስተሳሰብ የሚይዝ ፣ ስለ ከባቢያችን ስለ ሁኔታዎች ስለ ሕይወት ባጠቃላይ ማንነታችንን ሁሉ የምናስቀምጥበት መዋቅር ነው ፡፡ መረጃዎች እዚህ የሚገቡት በብዙ ሂደት ነው ፡፡ በዚህ የተከማቹ መረጃዎች ለቀናት ፣ ለሳምንታት ፣ ለወራት ላመታት እንዲሁም ለሕይወት ዘመናችን ከኛ ጋር ይቆያሉ ፡፡

የሰው አስተሳሰብና አመለካከት ከትውስታ ይገነባል ፡፡ ለዚህ ነው ከምትሰሙት / ከምታዩት ክፉ ነገር ተጠበቁ የሚባለው፡፡ ምክንያቱም ክፉ ነገር ሲሰማ ሲያይ ሲለማመድ ያደገ ሰው ትውስታው የሚሆነው ያ ወደ ውስጡ የገባው ነገር ነው ፡፡ ያ የገባው ነገር ደግሞ ....

ይቀጥላል ...
_________

#ቀጣዩን ቅዳሜ በተለመደው ሰአታችን በልዩ ፕሮግራም እንዴት የማስታወስ ችሎታዬን እጨምራለሁ ደግሞም መርሳትን እቀንሳለሁ በተጨማሪ መጥፎ ትዝታዎችን እንዴት በሂደት እረሳለሁ የሚሉትን መፍትሔዎችን አጠቃልዬ ይዤ እቀርባለሁ ፡፡___________

ሙሉውን ማንበብ ለሚፈልግ Telegram ቻናሌ post ያረኩትን PDF . www.tg-me.com/psychoet አንብቡት

❖ ❖_____❖ ❖

ይህ ፅሁፍ ለብዙ ሰው እንዲደርስ ሁላችንሞ ባለንበት የ Telegram #ሼር እናርገው 💛

ዕውቀት ከአሉታዊ የአስተሳሰብ እስር ቤት ነፃ ያወጣል !
የሳምንት ሰው ይበለን!

TELEGRAM 🚙 www.tg-me.com/Psychoet 👍
Facebook.com/psychologyabc

የሚረሳ ጓደኛ ካላችሁ ላኩለት ፡፡ 😉
ሀሙስ #6

ያዘነን ሰው ማጽናናት
#Share አርጉት
ደስታና ሃዘን የአንድ ሳንቲም ገጽታዎች ናቸው፡፡ በህይወታቸን ውስጥ ደስታ እንዳለ ሁሉ በተለያየ ምክንያት ሃዘን ሊያጋጥመን ይችላል፡፡የምንወደው ሰው መታመም ወይም ሞት፤ ያፈቀርነውን ማጣት፤ የህልማቸን አለመሳካት፤ በህይወታችን ውስጥ ትካዜን ከሚፈጥሩ ጉዳዮች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ አብዛኞቻችን በራሳችን የህይወት ልምድ ውስጥ ማዘንን ብናውቀውም  ያዘኑ ሰዎች ሲያጋጥሙን  እንዴት ማጽናናት እንዳለብንና ምን ማድረግ እንዳለብን ለማወቅ እንቸገራለን፡፡  መባል የሌለበትን ነገር በማለት ያዘኑ ሰዎችን ሃዘን ልናባብስ እንችላለን፡፡ ለምሳሌ፡-

ሃዘን ቤት ሄደን የሟች ቤተሰብን ያጽናናን መስሎን “የታመመው ምን ነበር? ህክምና ወስዳቹሁት ነበር?… ከስቃዩ ማረፉ ይሻለዋል፤ በዚህ ዕድሜው ተቀጨ…እንግዲህ ፈጣሪ ካመጣው ምን ይደረጋል….” የሚሉ ሃሳቦች በተደጋጋሚ ሲሰነዘሩ እንሰማለን፡፡ እነዚህ ነገሮች ቤተሰብን በማሰልቸትና ሟቹን እንዳይረሳ በማድረግ ሃዘንን ያባብሳሉ፡፡ ለምን ይህ ሃዘን በእኔ ላይ መጣ የሚል ስሜት በመፍጠር ሃዘንተኛውን ጸጸትና ድብርት ውስጥ ሊከቱ ይችላሉ፡፡

በጣም ደክሞ ሊሞት የሚያጣጥር ሰው ቤት ሄደን በቤተሰቡ ፊት “እንግዲህ የሚመጣውን ለመቀበል መዘጋጀት ነው… ተስፋ ያለው አይመስልም….ዛሬን የሚያድር አይመስልም” ብንል የቤተሰቡን ጭንቀት እናባብሳለን፡፡

በፍቅረኛዋ መከዳት ልቧ የቆሰለን ሴት “ቀድሞውንም ሰውየው እንደማይረባሽ ነግሬሽ ነበር….እንዴት ከዚህ ዓይነት ሰው ጋር እስካሁን ቆየሽ…” እና የመሳሰሉትን ሃሳቦች ማንሳት ለተጎጅዋ ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል

የሃዘን ደረጃዎችን መረዳት፡- ሰዎች በሃዘን ወቅት የሚያልፉባቸው 5 ደረጃዎች አሉ፡፡

ደረጃ 1፡ ሰዎች ሃዘን ሲያጋጥማቸው የመጀመሪያ ምላሻቸው ችግሩን መካድ (Denial) ነው፡፡ የቤተሰባቸው አካል መሞቱን አምኖ መቀበል ይከብዳቸዋል

ደረጃ 2፡ ከፈጣሪ ጋር መደራደር (Bargaining)፡-ሃዘን ውስጥ ያሉ ሰዎች ለምን ይህ ችግር በእኔ ላይ መጣና ጥፋቴ ምንድን ነው… የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ፈጣሪያቸውን ይሞግታሉ

ደረጃ 3- ቁጣ (Anger)፡ ያዘኑ ሰዎች በትንሹም በትልቁም ሊነጫነጩና ሊቆጡ ይችላሉ

ደረጃ 4- ድብርት (Depression)፡ ያዘኑ ሰዎች ተገቢውን ድጋፍና ዕርዳታ ካላገኙ በከፍተኛ ድብርት ውስጥ ይገባሉ

ደረጃ 5-ማጣትን መቀበል (Acceptance)፡- በጊዜ ሂደት ውስጥ ያዘኑ ሰዎች ያጡትን ነገር ለመቀበል ውስጣቸውን ያሳምናሉ

ያዘኑ ሰዎችን ለማጽናናት ማድረግ የሚገቡን ጉዳዮች፡-

ስሜትን መጋራት፡- ራሳችንን ባዘነው ሰው ቦታ ማስቀመጥና ስሜቱን እኔ ብሆንስ በሚል መንፈስ መረዳት፡፡ ለምሳሌ፡- አባትህ በሞት በመለየታቸው ሃዘን ተሰምቶኛል፤ ፍቅረኛሽ ትቶሽ በመሄዱ ምን ሊሰማሽ እንደሚችል እረዳሻለሁ፡፡

ማዳመጥ፡- ሰዎች ሃዘን ውስጥ ሲሆኑ ብዙ ማውራት፤ ብሶታቸውን ማካፈል ይወዳሉ፡፡ ስለዚህ ጥሩ አድማጭ መሆን ሃዘንን የመካፈል ሂደት ነው፡፡ ነገር ግን ማውራት የማይፈልጉትን ነገር እንዲነግሩን መወትወት አይገባም፡፡

ለዕርዳታ ዝግጁ መሆንን መግለጽ፡-“ወንድምህን እያስታመምክ እንደሆነ አውቃለሁ…እኔ ልረዳህ የምችለው በምን መልኩ ነው?” እና የመሳሰሉ ሃሳቦችን በማንሳት ሃዘንተኛው ከጎኑ መሆናችንን እንዲያውቅ ማድረግ፡፡

ማቀፍ፡-አንዳንዴ ያዘነን ሰው ምን ማለት እንዳለብን ሲቸግረን አላስፈላጊ ቃላት ከመሰንዘር ይልቅ ዝም ብሎ በማቀፍ ሃዘንን መጋራት ይቻላል፡፡

ሃዘንን ለመርሳት በቂ ጊዜ እንደሚያስፈልግ መረዳት፡- ሰዎች ከሃዘን ለመውጣት መጠኑ የተለያየ ጊዜ ያስፈልጋቸውል፡፡ አንዳንዶች በቀላሉ አገግመው ወደ ዕለት ተዕለት ተግባራቸው ሲመለሱ ሌሎች ደግሞ ረዘም ላለ ጊዜ ከሃዘን ጋር ሲታገሉ ሊቆዩ ይችላሉ፡፡ ይህ የሚወሰነው በሃዘኑ ዓይነትና በተጎጂው የስነ-ልቦና ዝግጅት ላይ ነው፡፡ ስለሆነም በተቻለ መጠን ላዘኑ ሰዎች በቂ ጊዜ እንደሚያስፈልጋቸው መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ይህ ማለት “ሃዘኑ ይበቃሃል…. ራስሽን በጣም እየጎዳሽ  ነው…በአንተ ላይ ብቻ የተከሰተ ችግር አደረግከው” እና የመሳሰሉትን ቃላት በማውጣት ሃዘንተኛውን ከመወትወት መቆጠብ ያስፈልጋል፡፡

(በሰብለወንጌል አይናለም)
©Zepsychologist
@psychoet
#Share
#ክፍል_6
(በናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ) #SHARE

ማስታወስ ! /Memory / part III
.....ከባለፈው የቀጠለ

ብዙ ጊዜ ሁላችን በተለያዩ የሕይወት መስተጋብሮች "የመርሳት" ገጠመኝ አለን ፡፡ነገሮችን ማስታወስ አለመቻል በዙሪያችን ባሉ ሰዎች መካከል እንደግዴለሽ የመታየት ፣ በስራችን አመኔታ ማሳጣት ፣ በትምህርታችን ደግሞ ያጠናነውን ያለማስታወስ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ በእርግጥ ነገሮችን መርሳት ሲበዛ እንደ ህመም ይታያል ፡፡ ለዚህም ነው በተለምዶ "የመርሳት ህመም " የሚባለዉ ፡፡ ነገሮችን አለማስታወስ ብዙ ማህበራዊ ጉዳት ካስከተለ ታዲያ እንዳንረሳ ምን እናርግ የሚለው ትልቅ ሙያዊ መልስ ያሻዋል፡፡
__________

እንዴት የማስታወስ ችሎታዬን እጨምራ
ለሁ
መርሳትን እቀንሳለሁ የሚሉትን መፍትሔዎችን፡___________
ማስታወስ / ትዝታ በብዙ መንገዶች መጨመር እንችላለን በዋነኛነት የሚመጡት ግን እነዚህ ናቸው ፡፡

Pay attention (ለነገሮች ትኩረት መስጠት ) : ከዚህ ክፍል 4 እና 5 እንዳስተማርኩት አንድ መረጃ ወደ አዕምሮአችን ገብቶ ለረጅም ጊዜ የሚቀመጠው በስነስርአቱ መረጃው ሲገባ ነው ስለዚህ ነገሮችን ለማስታወስ መጀመሪያውንም ወደ ውስጥ ስናስገባው በጥንቃቄና በአትኩሮት መሆን አለበት ፡፡ በብዛት የሚረሱ ሰዎች መጀመሪያውኑም ለፈተና ከላይ የሚያጠኑ ፣ የምንላቸውን ከላይ ከላይ / በግዴለሽነት የሚሰሙ ናቸው ፡፡

Add meaning ፦የምንሰማውን ፣ የምናየውን ነገሮች እንዳንረሳ ከዚህ ቀድም ከምናውቃቸው ጋር ማቆራኘትና ከመሸምደድ ይልቅ ትርጉሙን መረዳት ፡፡

Take your time ፦ በአንድ ጊዜ ነገሮችን ለመያዝ / ለማገባት ከመሞከር ጊዜ ወስደን እያረፍን ወደ አዕምሮአችን እናስገባ ፡፡

over learn፦ አንድን ነገር እንደምናውቀው ብናውቅም ደጋግሞ ማንበብ ፣ መስማት ፣ ማየት ለብዙ ጊዜ እንዳንረሳው ይረዳል ፡፡

Monitor your learning ፦ ያወቅነውን እንዳንረሳ ደጋግሞ በቃል ማለት በጥያቄ መፈተሽ ፡፡ በተለይሞ ተማሪ የሆናችሁ አንድን ነገር ስላነበባችሁ ብቻ በቂ አይደለም ይልቁንስ ያነበባችሁትን ወረቀት ዘግቶ ማሰብ እንዲሁም እውቀታችንን / ትውስታችንን በተለያዩ መንገዶች መመዘን ፡፡ አርቲስቶችን ብንመለከት (በቲያትር / ሙዚቃ ሙያ ያሉ ሰዎች) አንድን ገፀ ባህሪ አንብበው ያወቁ ቢመስላቸውም ከመድረክ በፊት ግን ብዙ ጊዜ ደጋግመው ይሉታል ይለማመዱታል ፡፡ ይህን የሚያረጉት የሚናገሩት ከራሳቸው ጋር እንዲዋሀድ እና እንዳይረሱት ነው፡፡

_______
እንዲሁም መርሳትን ለመቀነስ ባለፈው ትምህር
ት እንደተመለከትነው በተጨማሪ *
★የግል ምክር ነገሮችን እየረሳችሁ ላላችሁ !

በጣም ብዙ ሰዎች ሳማክር አንዱ የሚነግሩኝ ችግራቸው የመርሳት ጉዳይ ነው ፡፡ ምንም እንኳን ከእድሜ መግፋት ጋር ተያይዞ የሚመጣ የመርሳት (የአለማስታወስ) ችግር ቢኖርም በወጣቶች/ታዳጊዎች ላይም በተለያዩ ምክንያቶች መርሳት ያጋጥማል፡፡

ስለዚህ በመርሳት ለተቸገራችሁ ምክሬ እነሆ ፡- ነገሮችን መርሳት መጀመራችሁን ስትረዱ / የቅርብ ሰው ሲነግራችሁ መጀመሪያ ተረጋግታችሁ ለራሳችሁ ግዜ በመውሰድ እነዚህን አርጉ

1. በወቅቱ በብዙ ስራ / ተግባር ተወጥራችሁ ከሆነ ሀሳባችሁን በመሰብሰብ የምትሰሩትን ስራ ለመቀነስ ሞክሩ ከቻላችሁም ዋና መስራት ካለባችሁ 1/2 ስራ በስተቀር ሌሎቹን ተዋቸው ምክንያቱም መርሳት አንዱ ምክንያት በብዙ ስራ / ሃሳብ መወጠር ነው፡፡

2. ለጊዜው ለውጥ እስክታሳዩ ድረስ መስራት/ማድረግ ያለባችሁን ነገሮች በሙሉ አንድ በአንድ ወረቀት ላይ በመጻፍ ተከታተሉ ፡፡በሀገራችን "በቃል ያለ ይረሳል በፅሁፍ ያለ ይወረሳል" የሚባለውን እንደምሳሌ እንኳን ብንወስድ እንኳን ተማሪዎች የሆናችሁ ክፍል ውስጥ የምትማሩት አልቆ ስትወጡ የምታስታውሱት 50% ነው ከአንድ ቀን በኀላ ደግሞ ወደ 10% ይወርዳል ፡፡ይህም ማለት የምንማረውን ሳይቀር በአንድ ቀን 90% እንረሳለን ማለት ነው ስለዚህ ነገሮችን መጻፍ ለማስታወስ ዋነኛ መሳሪያ ነው ፡፡

3. በአንድ ጊዜ አንድ ብቻ ስራ ስሩ ይህም ማስተዋላችሁን (Concentration ) ስለሚጨምር የመርሳት ችግር ይቀንሳል ፡፡

4. (Quantity) በአንዴ ጥቂት ነገር ብቻ ይማሩ / ያጥኑ ፡ ብዙ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ለተከታታይ 5 ሰአት ከሚያጠና ሰው ይልቅ በቂ እረፍት በየመሀሉ እየወሰደ 3 ሰአት የሚያጠና ሰው የበለጠ የማስታወስ / ያለመርሳት አቅሙ ይጨምራል ፡፡

5. ለብቻችሁ በየቀኑ በቂ እረፍት ውሰዱ ፦ ይህ እረፍት ወደ አዕምሮአችን የሚገባውን መረጃ ፍሰት ለጊዜው ስለሚቀንሰው አዕምሮአችን እንዳይጨናነቅ ይረዳል፡፡

ሌላውና ዋነኛው ነገር #በጣም እየረሳችሁ ከተቸገራችሁ ከአዕምሮ ጤና ጋር ሊገናኝ ስለሚችል ወደ ህክምና ጣቢያ እንድትሄዱ እመክራለሁ ምክንያቱም የዚህ አይነች ችግር የሚታከመው በመድኃኒትም ጭምር ነው ፡፡

፠፠______፠፠
#በቀጣይ_ይህን አንገብጋቢ ጉዳይ እናያለን ፦ የቅርብ ሰውን በሞት ማጣት / አስከፊ አደጋ መመልከት /ፆታዊ ጥቃት / ከልክ ያለፈ የልጅነት ጊዜ ቅጣት ... በሕይወታችን እንዴት በሂደት እንረሳለን ፤ ደግሞስ ለተሻለ ነገ እንዴት እንነሳለን ብለን "መርሳት" በሚል ሀሳብ እንወያያለን ።


፠፠______፠፠


ይህ ፅሁፍ ለብዙ ሰው እንዲደርስ ሁላችንሞ ባለንበት የ Telegram / Facebookግሩፕ ውስጥ #ሼር እናርገው 💛

TELEGRAM 🚙 www.tg-me.com/Psychoet 👍
Facebook.com/psychologyabc
ሀሙስ #7

ሰዎች ስለእኛ በሚያስቡት ነገር ላይ መጨነቅን ለማቆም ቀላል ዘዴዎች
Telegram www.tg-me.com/psychoet

‘’የማይባል ነገር ተናገርሁ እንዴ? እንዴት እንደዚህ አደርጋለሁ? ሰዎች እኮ መሃይም :ገገማ:የሚያናድድ ሰው ነው/ነች ይሉኝ ይሆናል’’ እያልን ራሳችንን የምናስጨንቅ ስንቶቻችን ነን! ሌሎች ሰዎች ስለእኛ በሚያስቡት ነገር ላይ በመጨነቅ አእምሯችንን በጨለማ ቦታ እንዲንከራተትና ራሳችንን በመጠራጠር የስጋት ስሜት እንዲሰፍንብንና እንዳንረጋጋ እያደረግን መሆኑን ልናውቅ ይገባል:: ለነገሩ ሁላችንም ሰዎች ስለእኛ ያላቸው ሃሳብ/አስተያየት ምን ይሆን ብለን መጨነቅ እንደሌለብን እናውቃለን ወደ ተግባር ለመቀየር ግን ስንቸገር እንታያለን:: ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዘዴዎች ብንጠቀምባቸው ይረዱናል!

1. የሰዎችን አዕምሮ ማንበብ እንደማንችል መረዳት፡- እስኪ ሰዎች ስለእኛ የሚያስቡትን በእርግጠኛነት ማወቅ እንችላለን? ብዙ ጊዜ ነገራትን ሳናጣራ ይሆናል በማለት ብቻ ማወቅ እንደምንችል ነው የምናስበው ይህ አስተሳሰባችን ደግሞ ለህይወታችን ፀር ወደሆኑ ድምዳሜዎች/ዉሳኔዎች ይመራናል::ስለዚህ እነዛ ሰዎች ሃሳባቸውን የሚገልጹበትን ዕድል አግኝተው ሃሳባቸውን እስካልገለጹልን ድረስ ስለምን እንደሚያስቡ ማወቅ በፍጹም አንችልም፡፡

2. በቋሚነት ለሚጠቅመን ነገር መስራት:- ከሌሎች ሰዎች የሚሰነዘሩ የኩነኔ አስተያየቶች በእርግጥም እኛን ይጎዱናል ነገር ግን ከእነዚህ ሰዎች የሚመጣውን አሉታዊ ምላሽ በመፍራት የምናጣቸው/የምናሳልፋቸው መልካም ዕድሎች ጥለውብን ከሚያልፉት የአእምሮ ጠባሳ አይበልጥም፡፡ እነዚህ የኩነኔ/አሉታዊ አስተያየቶች የሚያደርሱብን ጉዳት ቅጽበታዊ ሲሆን ባጣናቸው/ባመለጡን መልካም ዕድሎች ምክንያት የሚደርስብን ጸጸትና ቁጭት ግን ከጊዜ ወደ ጊዜ ስር እየሰደደና እያደገ ነው የሚሄደው፡፡ ስለዚህ በቋሚነት የሚጠቅመንን ነገር ለማግኘት ጊዜያዊ የሆኑ ተቀባይነት ማጣትን ለመቀበል ፈቃደኞች እንሁን::

3. ራስን ከመኮነን/በራስ ላይ ከመፍረድ መቆጠብ:- እስኪ ሰዎች ምን ይሉን ይሆን ብለን የምንጨነቅበትን ሃሳብ ለሰከንድ ቆም ብለን እናስበው! በእርግጠኝነት እኛ ለራሳችን የምናስበውን ነገር ላይ ነው ሌሎችም እንደዚ ያስባሉ ብለን የምንሰጋ፡፡ ስለዚህ በራሳችን ላይ መፍረድን አቁመን(ራስን ከመኮነን ተቆጥበን) እኛነታችንን ከተቀብለነው ወይም ለራሳችን ጥሩ ግምት ከሰጠን ሌሎቹ ስለእኛ ለሚሰጡት/ለሚያስቡት ሃሳብ ፍርሃትና ስጋት አይኖረንም ማለት ነው፡፡

4. ሌሎች ሰዎችን መኮነንን/በሌሎች ላይ መፍረድን ማቆም፡- ሰዎችን እየገመገምን፡እየኮነንና እየፈረድንባቸው የምንኖር ከሆነ እነሱም በተመሳሳይ ሁኔታ እንደሚፈርዱብን ነው የምናስበው፤ ስለዚህ በእነሱ ላይ ከመፍረድ ይልቅ ህይወታችንን ለማሻሻልና ለማደራጀት እንደሚያግዙን ቆጥረን ብናደንቃቸውና ብናበረታታቸው የበለጠ ተጠቃሚዎች መሆን እንችላለን፡፡

5. ስለእኛ አለመሆኑን መረዳት፡- ሰዎች በራሳቸው እይታ ከደረሰባቸው ክስተት፡ ቁስል፡ ፍራቻና እንከን የተነሳ ለነገሮች የተለያዩ አሉታዊ ምላሾችን ይሰጣሉ ነገር ግን የእነሱ ምላሽ ከእኛ ጋር የሚገናኝ እንዳልሆነ ልብ ልንል ይገባናል፡፡ ለምሳሌ የሆነ ቢዝነስ ለመጀመር ብንወስንና አንድ ሰው ”እመነኝ ይህንን ስራ ከጀመርህ በሚቀጥሉት ወራት አሊያም ዓመታት ምንም ዓይነት የእረፍት ጊዜ አይኖርህም” ቢል ሰውዬው የተናገረው ቢዝነስ መጀመር ላይ ያለውን ሃሳብ/አመለካከት እንጂ እኛን በተመለከተ እንዳልሆነ ለይተን መረዳት ይጠበቅብናል::

6. በሚያስደስተን ነገር ላይ ትኩረት ማድረግ:- ይህን ባደርግ ሰዎች ይፈርዱብኛል በማለት የሚያስደስቱንን ተግባራት ከማድረግ የምንገደብ ከሆነ(የማኅበረሰቡን እሴቶች በጠበቀ መልኩ) ጊዜያችንን ምንም ዓይነት ጥቅም በሌለው ጭንቀት እያባከንነው መሆኑን እናስተውል፡፡ ስለዚህ በህይወታችን ከፍተኛ ለውጥ ማምጣት የሚችለውን ብርቅ የሆነውን አቅምና ኃይላችንን በመሸርሸር ፈንታ እኛን በሚያስደስቱን ነገራት ላይ ትኩረት ልናደርግ ይገባል፡፡

7. የሚያውኩንን ነገሮች መለየት፡– ሌሎች ሰዎች አሉታዊ በሆነ መልኩ ይገመግሙናል/ይፈርዱብናል ብለን የምንጨነቀው ምናችንን በተመለከተ ነው? በስራችን ሁኔታ: ከሌሎች ጋር ባለን ግንኙነት: ምናልባትም በክህሎታችንና ነገሮችን በመመርመር ባለን አቅም ሊሆን ይችላል:: ስለዚህ በውስጣችን መረጋጋት እንዳይኖር የሚቀሰቅሱ ነገሮችን መለየትና ማሻሻል ከቻልን ማሻሻል አሊያም እንዳሉ መቀበል ያስፈልጋል:: ምክንያቱም ከሁኔታዎች ጋር ሰላም መፍጠር ከቻልን የሰዎች አጸፋዊ ምላሽ አያስጨንቀንም ማለት ነው::

8. ራሳችንን መቀበል:– ፍጹም አለመሆናችንን፡ እንከንና ድክመቶች እንዳሉን መቀበል ነገር ግን አቻ የሌለን(ልዩ) በዓለም ላይ እኛን የሚመስል ሰብዕናና ተሰጥኦ የታደለ ሰው እንደሌለና ወደፊትም እንደማይኖር ልናስተውል ይገባል፡፡

9. አጸፋዊ ምላሾችን መጠበቅ/ተስፋ ማድረግ፡- በሰዎች ዘንድ የሚፈጠረውን አጸፋዊ መልስ በመፍራት ፈንታ ያ ምላሽ ሊፈጠር እንደሚችል አስቀድመን ተስፋ ማድረግ አለብን(የሰዎችን ስሜት ለመቀስቀስ መፍራት የለብንም) ምክንያቱም በሰዎች ዘንድ አሉታዊም ይሁን አዎንታዊ ምላሽ መፍጠር ካልቻልን ምናልባትም ራሳችንን የመሆን ድፍረቱን ልናጣ እንችላለንና፡፡

10. እየኮነኑን/እየፈረዱብን ነው ብለን ካሰብናቸው ሰዎች ጋር ማውራት፡- እንዲያው ሁኔታዎች ተመቻችተውልን ስለእኛ መጥፎነት ያስባሉ/እየፈረዱብን ነው ብለን ከምናስባቸው ሰዎቸ ጋር ተቀራርበን ብናወራ እስከምንገረም ድረስ ምንም ባለጠበቅነው ሁኔታ አዕምሯቸው በብዙ ጭንቀቶች እንደተሞላ ልናውቅ እንችላለን፡፡ ማን ያውቃል ልክ እኛ እንደምንጨነቀው እነሱም ሌሎች ሰዎች ስለእነሱ ምን ሊያስቡ/ሊሉ በሚችሉት ሃሳብ እየተጨነቁ ሊሆን ይችላል እኮ፡፡ ስለዚህ ራሳችንን ግልጽ በማድረግ ከእነዚህ ሰዎች ጋር ተቀራርበን ሃሳብ ማንሸራሸር ያስፈልጋል::

በአጠቃላይ ከላይ የተዘረዘሩትን ሃሳቦች ወደ ተግባረ ከቀየርናቸው እኛም መቀየር እንችላለን!

(በአለበል አዲስ)
©Zepsychologist
Telegram www.tg-me.com/psychoet
#ክፍል_8
(በናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ) #SHARE
#Emotional_Intelligence&Communication
#የስሜት_ብልሃትና_ተግባቦት

የስሜት ብልህነት ማለት ስሜታችንን የማወቅ ፣ የመረዳት የመምራት ችሎታ ነው ፡፡ ጥሩ የስሜት ብልሀት ያላቸው ሰዎች የተመሰገኑ ፣ በማንኛውም ሁኔታ የተረጋጉ ፣ የሩጫ ህይወት የማይመሩ ፣ የበለጠ ደስተኛና ራሳቸውንም ሆነ አካባቢያቸውን የሚመሩ ናቸው ፡፡

በህይወታቸው በጣም ደስተኛና ስኬታማ ከሆኑ ሰዎች አንዱ መገለጫቸው ያለቸው የስሜት ብልሃት ( Emotional Intelligence ) ነው ፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች ከሚሰሩበት መስሪያ ቤት ሙያውና ችሎታው እያላቸው በባህሪ ምክንያት ይሰናበታሉ ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ጥሩ ሀሳብ እያላቸው ባላቸው ባህሪ ምክኒያት ሰሚ ያጡ ፣ ተቀባይነት ያጡ ሰዎች ይኖራሉ ፡፡

#ለዛሬ እነዚህ የተግባቦትና የስሜት ብልሀት አለመኖር በሕይወታችን የሚያመጡትን ችግር እንመልከት ፡፡

እኔ አንዱን ድግሪዬን በማኔጅመንት ስሰራ የመመረቂያ ጽሑፌ (Competency development in business areas ) የሚል ነበር ፡፡ በዚህ ጥናት ያገኘሁት አንዱ ግኝት ሰዎች ለቢዝነሳቸው መውደቅ አንዱ ምክንያት ያላቸው አነስተኛ #የተግባቦትና #የስሜት_ብልሀት ነው ፡፡ በእርግጥ ተግባቦትም ሆነ የስሜት ብልህነት ሳይንሳዊ የሆኑ መንገዶችን በመጠቀም ማሳደግ ይቻላል ፡፡

#የስሜት_ብልሃትና_ጥሩ_ተግባቦት_የሌላቸው_ሰዎች_መገለጫዎች

★የራሳቸውን ስሜት አይቆጣጠሩም ( በቀላሉ ይናደዳሉ ፣ ይበሳጫሉ ፣ ከልክ ያለፈ ቁጣ ይታይባቸዋል )

★ከሰው ጋር ተግባቢ አይደሉም ፣ ፍርሀት ጭንቀት ይታይባቸዋል ፣ ስለ ራሳቸው አሉታዊ አመለካከት የላቸውም

★በትንሽ ነገር አብዝተው ያዝናሉ

★በአካባቢያቸው ያሉ ሰዎችን ባህሪ እና ስሜት ስለማይረዱ ፣ ብዙ ጊዜ ከሰዎች ጋር በሀሳብ ፣ በወሬ የመጋጨት ሁኔታ ይታይባቸዋል

★ሰው ስለነሱ ስላለው አስተሳሰብ አብዝተው ይጨነቃሉ ፣ ይረበሻሉ ፡፡

★ሃሳባቸውን በድፍረት አይገልፁም ፣ እየተጎዱ ከጉዳቱ መውጣት እየቻሉ ዝምታን ይመርጣሉ ፣

★ለውሳኔዎች ከተገቢው በላይ ይቸኩላሉ፣ በወሰኑት ነገር ለመጸጸት ደግሞ የመጀመሪያ ናቸው

ከላይ የዘረዘርኳቸው መገለጫዎች( የስሜት ብልሃትና ጥሩ ተግባቦት ክህሎት አለመኖር) የሚያመጣቸው ጉዳቶችና የባህሪ መገለጫዎች ናቸው ። በእርግጥ እነዚህ ሁሉ መገለጫዎች ሳይኮሎጂካል ህክምና አላቸው ፡፡

ስለዚህ ከላይ የጠቀስኳቸውን ችግሮች በራሳችሁ ላይ የምታዩ ሰዎች ተስፋ አትቁረጡ ፡፡ በጥቂት ጊዜ ጥሩ የሆነ ተደጋጋሚ ሳይኮሎጂካል ልምምዶችን በማረግ መዉጣት ይቻላል ፡፡
_______

፠፠______፠፠

ይህ ፅሁፍ ለብዙ
ሰው እንዲደርስ ሁላችንሞ ባለንበት የ Telegram / Facebookግሩፕ ውስጥ #ሼር እናርገው 💛

በቴሌግራም በዚህ ታገኙኛላችሁ 🚙 www.tg-me.com/Psychoet 👍


ዕውቀት ከአሉታዊ የአስተሳሰብ እስር ቤት ነፃ ያወጣል !
ቸር ሰንብቱ!
፠፠______፠፠
የሳምንት ሰው ይበለን!
ሀሙስ #8

ራስን የማወቅና የመምራት ክህሎት

የሚከተሉት ነጥቦች አንድ ራሱን የሚያውቅ ሰው ሊኖሩት የሚገባ ባህሪያትን ያሳዩናል::

*ደካማና ጠንካራ ጎኑን ለይቶ ያውቃል

*ለራሱ ህይወት ኃላፊነት ይወስዳል

*ስለራሱ ያለው አመለካከት አዎንታዊ ነው

*በራሱ ይተማመናል

*ራሱን ለማሻሻል ይጥራል (በኢኮኖሚ በማኅበራዊ…)

*የሚሄድበትን መንገድ ያውቃል/ራዕይ አለው

*ለአላማው መሳካት መስዋትነትን ይከፍላል

*ሌሎችን ለመሆን አይጥርም/በራሱ ማንነት ይተማመናል

*ራሱን ያከብራል

*የራስ ህይወት መሪ ለመሆን ደግሞ የሚከተሉት ሶስት ነጥቦች አጋዥነት ይኖራቸዋል

#ሀ. ለራስ ህይወት ኃላፊነት መውሰድ

*ስለኛነታችን ልናውቃቸው የሚገቡ እውነታዎች

*በዓለም ላይ አንተን የሚመስል ማንም እንደሌለ

*በዓለም ላይ መኖራችን ለአንድ አላማ መሆኑ

*ሃሳባችንን፤ ምኞታችንን፤ አመለካከታችንን መቆጣጠር የሚያስችል ሃይል እንዳለን

*የዛሬ አስተሳሰብ ለነገ ህይወታችን መሰረት እንደሆነ

*የራስን ማንነት ለመፈተሽ የሚረዱ ጥያቄዎች

*ጠንካራ ጎኔ ምንድን ነው?

*ደካማ ጎኔ ምንድን ነው?

*ለራሴ ያለኝ አመለካከት ምን ይመስላል?

*ለህይወት ያለኝ አመለካከት ምን ይመስላል?

#ለ. ዓላማ ያለው ህይወት መምራት

*ልንሰራውና ልንሆን የምንፈልገውን ነገር ለይተን እንድናቅ ይረዳና

*የህይወት አስቸጋሪ ሁኔታዎች በድል የምንወጣበትን ኃይል ይሰጠናል

*ጤናማና ውጤታማ ሰዎች እንድንሆን ይረዳናል

#ዓላማ_ያለው_ህይወት_ለመምራት_ምን_ማድረግ_ይጠበቅብናል?

*ዓላማ ያለው ህይወት ለመምራት ራስን ማዘጋጀት

*እየኖርን ካለነው የተሻለ ህይወት መኖር እንዳለብን ማመን

*በመጀመሪያ በቀላሉ ልንተገብረው የምንችለውን ነገር በማቀድና በመተግበር በዕቅድ መመራት/መሄድ

*ከጎጂ ልምዶችና አስተሳሰቦች ራስን ማውጣት

*ለራሳችን የምንገባውን ቃል ማክበር

*ሽንፈትን በጸጋ አለመቀበል ይልቁንም ካለፈው ስህተታችን በመማር የተሻለ ነገርን ማለም

*በዓላማ መመራት ስንጀምር ሊያጋጥሙን የሚችሉ እንቅፋቶች

*ከራሳችን/ከውስጣችን የሚመነጭ

*በአቅራቢያችን ካሉ ሰዎች የሚነሳ

*የአካባቢያዊ ሁኔታዎች አለመመቸት

(በአንቶኒዮ ሙላቱ)©zepsychologist
@Psychoet
ናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ 🤷‍♂
Photo
#ክፍል_9
(በናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ)
#SHARE አድርጉት ብዙ ሰው ያስተምራል #Like
#Frustration / #ተስፋ_መቁረጥ_ከየት_ይመጣል ?
___

ብዙ ጊዜ ሰዎች በተለያዩ ሁኔታዎች
ሁነው ተስፋ የለኝም ፣ ተስፋዬ ተሟጧል ፣ የመሳሰሉትን ቃላት በቀን ተቀን ሕይወታቸው ይጠቀማሉ ፡፡

ተስፋ መቁረጥ ወደ ግባችን / ፍላጎቶቻችን እንዳንደርስ የሚያረገን ባህሪ ነው ፡፡ በሕይወቱ ብዙ ጊዜ ተስፋ የሚቆርጥ ሰው ወደግቡ/እቅዱ የመድረሱ እድል በጣም አነስተኛ ነው ፡፡ ወደ ጠቃሚ የሕይወት ግባችን አለመድረስ ደግሞ ድብርት ፣ ጭንቀት ፣ ፍርሃት ፣ የበደለኝነት ስሜት ያመጣብናል ፡፡

ሳይኮሎጂ ችግር የመፍቻ ዋና መንገዱ የችግሩን ምክንያት መረዳት እንደሆነ ያትታል ፡፡ስለሆነም የተስፋ መቁረጥ ዋና ዋና ምክንያቶች እንመለከታለን፡፡
___
1.Environmental Factor
(አካባቢያዊ ምክንያት)

በአካባቢያችን ያሉ የተለያዩ ሁኔታዎችና ገጠመኞች ፍላጎቶቻችንንና እቅዳችንን እንዳናሳካ ይከለክሉናል ፡፡
ለምሳሌ ፦ በዙሪያችን ያሉ ሰዎች ማድረግ የምንፈልገውን ነገሮች " አትችለውም ፣ ይከብድሀል ፣ ከዚህ በፊት አልተሞከረም ፣ ሰው ምን ይልሀል" በማለት ተስፋ ሊያስቆርጡን ይችላሉ ፡፡ በተጨማሪ ደግሞ ያደግንበት ባህል ፣ የምንኖርበት አካባቢ ለማድረግ ያቀድነውን ነገር እንዳናሳካ በራሱ ሊይዘን ይችላል ፡፡ ይሄ በሕይወታችን ተስፋ መቁረጥን ያስከትላል ፡፡

2.Personal inadequency Factor (ግላዊ ብቃት/ክህሎት ማጠር )

ይህ ደግሞ ፍላጎቶቻችንን እንዳናደርግ የሚገድበን አለመሙላት (ብቃት አልባነት) ነው ፡፡ ለምሳሌ ፦ አንድን እቃ በጣም ወደነው ለመግዛት ስንፈልግ ከተወደደብንና ያለን ገንዘብ አነስተኛ ከሆነ ተስፋ ቆርጠን ላንገዛ እንችላለን ፡፡ እዚህ ጋር ነገሩን ለመግዛት በቂ ገንዘብ አለመኖር የራሳችን የሆነ ጉድለት ይሆናል፡፡ ሌላው አንድን ነገር ለመስራት አስበን የግል ችሎታ / ብቃት/ ክህሎት ሲያንሰን እሱ " በቃ አልችልም " በማለት ተስፋ ለመቁረጥ መንስኤ ይሆነናል ፡፡

3. Conflict of interest ( የፍላጎት ግጭት )
የመጨረሻው የግላዊ ፍላጎቶች/ ግቦች እርስ በእርስ ሲፃረሩ ተስፋ ሊያስቆርጠን ይችላል ፡፡ ተስፋ መቁረጡ የሚመጣዎ ሁለቱንም ግቦቻችንን ልናሳካ ባለመቻላችን ነው ፡፡ አንዱን ግብ ብናሳካ ራሱ ሌላውን ስላላሳካን የመወላወል ተስፋ የመቁረጥ ( የማዘን ) ስሜት ይሰማናል፡፡


ከነዚህ ሶስቱ ዎና ዎና ምክንያቶች እግጅ በጣም ብዙ ሰው የሚያጋጥመው የመጨረሻው (.Conflict of Motives / የፍላጎት ግጭት ) እንደሆነ ሳይኮሎጂ ይጠቁማል፡፡
__
እነዚህ Conflict of motives ( የፍላጎ
ት ግጭት ) ደግሞ በ አራት ይከፈላሉ ፡፡
__
ሀ. Approach - Approach Conflict

(ፍላጎት ፥ ፍላጎት ግጭት)

ይህ ግጭት ሁለት ነገሮችን በእኩል ፈልገን ነገር ግን መምረጥ የምንችለው አንዱን ብቻ ሲሆን ማለት ነው ፡፡ ለምሳሌ :- ተማሪዎች ዩኒቨርስቲ ከገቡ በኅላ Department ሲመርጡ ብዙ ተማሪዎች በሁለት ወይም ከዛ በላይ በሆኑ የdepartment ምርጫዎች ይወጠራሉ ነገር ግን መምረጥ የሚችሉት የወደዱትን ሁሉ ሳይሆን አንዱን ብቻ ስለሚሆን ግጭት ውስጥ ይገባሉ ፡፡ ሌላው ገበያ ሂደን ሁለት ሱሪዎች በጣም ወደናቸው ነገር ግን መግዛት የምንችለው አንዱን ብቻ ከሆነ ይህ አይነት ግጭት ከራሳችን ጋር ይገጥመናል፡፡


ለ. Avoidance - Avoidance Conflict (የማስወገድ ፥ የማስወገድ ግጭት)

ይህ ደግሞ ከሁለት የማንፈልጋቸው ነገሮች የግድ አንዱን መምረጥ ግድ ሲለን ነው ፡፡
ለምሳሌ ፦ ልጃችን በሰዎች ታግቶ ብር ካልከፈላችሁ ይገደላል ቢሉን ፤ እዚህ ጋር ልጁ እንዲሞትም አንፈልግም ለአጋቾቹ ብር መክፈልም አንፈልግም ፡፡ ግን አንዱን መምረጥ ግድ ይለናል ፡፡ ሌላ ምሳሌ ፦

ሐ. Approach - Avoidance Conflict (የፍላጎትና ማስወገድ ግጭት)

ይህ ደግሞ በአንድ ግብ ላይ የፍላጎትም የማስወገድም ስሜት ሲሰማን ነው ፡፡

መ. Multiple Approach - Avoidance Conflict (ብዙ የፍላጎት ማስወገድ ግጭት)

ይህ ሁላችንም በሕይወት ቆይታችን የሚያጋጥመን የለት ተለት ግጭት ነው ፡፡ እያንዳንዱ የሚገጥመን ነገር #ብዙ_አወንታዊና_አሉታዊ ነገሮች ይይዝና እሱን #መምረጥና #አለመምረጥ ችግር ይሆናል ፡፡
ለምሳሌ ፦ አንድ ሰው መልኩን ፣ ገቢውን ወደን ፀባዩ አመለካከቱ ካላማረን ይሆነኛል አይሆነኝም ብለን ከራሳችን እንጋጫለን ፡፡ሌላው አንድን ስራ ስንሰራ በዉስጡ ያሉ የተለያዩ ጥሩና መጥፎ ነገሮች ስገፉን ሲስቡን እንደዚህ አይነት ግጭት ውስጥ እንገባለን ፡፡



፠፠__፠፠

ይህ ፅሁፍ ለብዙ ሰው እንዲደርስ ሁላችንሞ ባለንበት የ Telegram / Facebookግሩፕ ውስጥ #ሼር እናርገው 💛

በቴሌግራም በዚህ ታገኙኛላችሁ 🚙 www.tg-me.com/Psychoet 👍


ዕውቀት ከአሉታዊ የአስተሳሰብ እስር ቤት ነፃ ያወጣል !
ቸር ሰንብቱ!
፠፠__፠፠
ሳምንት ሰው ይበለን!
ሀሙስ #9

የግጭት አፈታት ሳይኮሎጂ

#ላለንበት ችግር አንድ መፍትሄ የሆነ ጽሑፍ ስለሆነ ባላችሁበት Facebook ግሩፕ #Share አርጉት

ግጭት ጥልቅ ውስጣዊ ስሜቶች አደባባይ ላይ ወጥተው እንዲሰጡ ያደርግል፡፡ በዚህ ጊዜ በእውናችን ቀርቶ በህልማችን እንኳን አልመን የማናውቀውን ነገር ራሳችንም ሌሎችም ሲያደርጉ አስተውለን ይሆናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ለመስማት የሚከብድ ወንጀል ፈጸመው ወዳጅ ዘመዶቻቸው ስለእነዚሁ ሰዎች ጠባይ ሲጠየቁ “እሱ እኮ ሰውም ቀና ብሎ አይመለከት፣ ታላቁን አክባሪ፤ አንገት ደፊ ወዘተ ነበር” ሲሉ ይደመጣል፡፡ እንደተባለውም እነዚህ ሰዎች ሰው አክባሪ፣ ካልደረሱባቸው ሰው ላይ የማይደርሱ ይሆናሉ፡፡ መስካሪዎቹ ፊት ለፊት ያዩትን ነው የመሰከሩት፡፡ ነገር ግን እነዚህ መስካሪዎች አይተውት የማያውቁት አጥፊ ስሜት እነዚህ ሰዎች ውስጥ ይኖራል፤ ተመልካች ይቅርና ባለቤቱም ራሱ አያውቀው ይሆናል፤ ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው እንዲሉ፡፡ይህ ማለት ግን በስሜት ተገፋፍተን በፈጸምነው ድርጊት ተጠያቂ አንሆንም ማለትም አይደለም፡፡ ዞሮ ዞሮ ስሜቶቻችንም የገዛ ራሳችን ንብረት እንጂ የማንም አይደሉም፡፡

ግጭት የሚያስከትለውን ውድመት የበዛ የሚሆንበት ዋነኛ ምክንያት ከመፈጠሩ በፊት ለመከላከልም ሆነ ከተፈጠረ በኋላ በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል ዕውቀት እና ክህሎት እጦት ነው፡፡ በትንሽ በትልቁ ብስጭት የሚሉ ሰዎችን ታውቁ ይሆናል፤ ለምን ቀና ብላችሁ በሙሉ ዓይናችሁ ተመለከታችሁኝ ብለው ችግር የሚፈጥሩ እና ችግር ውስጥ የሚገቡ ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ በምዕራቡ ዓለም ለእንደዚህ ዓይነት ሰዎች ‹ንዴትን መቆጣጠር› የሚችሉበት የተለየ ስልጠና ቁጭ ብለው እንዲወስዱ ይደረጋል፡፡ ልክ እንደዚሁ ሁሉ ግጭትን መከላከልም ሆነ መፍታት በስልጠና ሊደረጅ የሚችል ችሎታ ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ ግጭትን ለመከላከል እና ለመፍታት የሚረዱ ነጥቦችን እንዳስሳለን፡፡

1. ስናዳምጥ ‹ጥቃትን› አናዳምጥ

ጥቃት እየተፈጸመብን ነው ብለን ከአሰብን አጸፋዊ መልስ ለመስጠት አናቅማማም፡፡ ክፉ ደግ መነጋገር ደግሞ ምክንያታዊ ውይይት ድራሹ እንዲጠፋ ያደርጋል፡፡ በተለይ ግጭት ከተፈጠረ በኋላ ማንኛውም ዓይነት ንግግር ሲደረግ ‹ይህ ሰው በትክክል ምን እያለ ነው?›፣ ‹ምን ዓይነት መረጃ ነው በመተላለፍ ላይ የሚገኘው?›፣ ‹ምንድነው የተከፋበት ምክንያት? ለምን ተቆጣ? ለምን ክፉ ተናገረ?› ወዘተ በማለት በስሜት ታጅበው ከሚፈሱት ቃላት ጀርባ ያለውን መልዕክት ለይቶ ማወቅ ጥሩ ነው፡፡ ይህንን ከአደረግን ራስን ለመከላከል ከፍ ሲልም መልሶ ወደ ጥቃት ወደ መሰንዘሩ ከመኬዱ በፊት መግባባት እንዲነግስ ያደርጋል፡፡

2. ደመ ነፍሳዊ ግፊት አደብ እንዲገዛ ማድረግ

የምንፈልገው እንዳልተሟላ፣ ፍትህ እንደጎደለ፣ ውሸት እንደከበረ፣ መስማት የማንፈልገው ጥያቄ እንደቀረበ ወዘተ ስናስብ እጥፍ ድርቡን መልሳችሁ አከናንቡ የሚል ውስጣዊ ደመ ነፍሳዊ ግፊት ይቀሰቀሳል፡፡ እስከ ዶቃ ማሰሪያው፣ አፍንጫው ድረስ፣ ልክ ልኩን ወዘተ ነገረው ዓይነት ፈሊጣዊ አገላለጾቻችን ‹ክፉ ነገርን ልክ የለሽ በሆነ ክፍት መመከትን› እንደምናበረታታ ፍንጭ የሚሰጡ ናቸው፡፡ አጥቂ ምክንያታዊ ይሁንም አይሁንም፣ ደግ ይሁንም አይሁንም አበጀህ የማለት፣ እንደ ጀግና ከፍ አድርጎ የመመልከት ባህል ሊወገድ ይገባል፡፡

በግጭት ወቅት ‹እንዲህ በል፣ እንዲያ በል፣ የት አባቱ ወዘተ› ዓይነት ውስጣችን የሚፈሉ የደመ ነፍስ ግፊቶችን ማቀዛቀዝ ግጭትን ለመፍታት ይረዳል፡፡ ደመ ነፍሳዊ ምሪትን ከአስቆምን በኋላ ተረጋግቶ በማሰብ መናገር የምንፈልገውን ‹እኔ› በማለት መናገርም እንዲሁ ይመከራል፡፡ ለምሳሌ፣ በቤት ውስጥ የትዳር አጋር ስራ አላግዝ ብሎ አስቸግሮ ከሆነ ‹አንተ ድሮም ሰነፍ ነህ፣ ምንትስ ነህ› ከማለት ይልቅ ‹እኔ ስራ ካላገዝከኝ/ካላገዝሽኝ ቅር ይለኛል፤ ተጋግዘን ልንሰራ ይገባል፤ ይኼ እኮ የጋራ ህይወት ነው› ማለት ግጭት ላይ አርቆ ማጠሪያ ስልት ነው፡፡ ስለዚህ በተቻለ መጠን ውስጣችን አሉታዊ ስሜት ሲጸነስ እንደመጣልን ከመናገር እንቆጠብ፡፡ ‹ከአፍ የወጣ አፋፍ› አይደል ከነአባባሉስ፡፡ ንግግር የፈሰሰ ውሃ ነው፡፡ እንደ ደራሽ ውሃ ፈሶ ያለ የሌለውን ጠራርጎ ከሄደ በኋላ ሁኔታዎችን ወደ ነበሩበት መመለስ ፈታኝ ነው፡፡ ስለሆነም ንግግር ሲያደርጉ ማመዛዘን እንዲሁም ከአንደበታችን የሚወጡ ቃላት ግጭቱ ላይ ሄደው ሲያርፍ የቤንዚን ነው ወይስ የውሃ ሚና የሚጫወቱት የሚለውን ቀድሞ ማሰብ ተገቢ ነው፡፡

3. የሰዎችን በጎ ጎን ማነጋገር

100 % አጥፊ፣ ምንም ነገር የማይገባው፤ ውስጡ እንጥፍጣፊ መልካምነት የሌለው ወዘተ ሰው አይኖርም፡፡ የትኛውም ሰው መልካም ማንነት የማንነቱ አካል ነው፡፡ እርስ በእርስ ስንነጋገር አንዳችን የአንዳችንን ይህንን መልካም ጎን ለማነጋገር ጥረት እናድርግ፡፡ ‹ጅኒ› ገለመሌ የሚል አጓጉል ፍረጃ ውስጥ ሳንገባ መልአኩን ማንነት እናወያየው፡፡የሰው የእምነቱ መነሻ ስረ መሰረት የአንድም ይሁን የብዙ የሰው ልጅ ፍቅር ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ አንድ ድፍን ያለ ‹ነጭ› አለያም ደግሞ ድፍን ያለ ‹ጥቁር› ብቻ ሊሆን አይችልም፡፡ ፈረንጆቹ እንዲህ ዓይነቱን ጠርዘኛ አመለካከት ‹‹either/or thinking›› ይሉታል፡፡ እንዲህ ዓይነቱ አስተሳሰብ ራስንም ሆነ ሌሎችን አውዳሚ ነው፡፡ ከ‹ሰይጣን› ሌላ ሙሉ ለሙሉ ‹ሰይጣን› የሆነ ፍጥረት የለም፡፡

4. ለሰዎች ስሜት ቦታ እንስጥ

ስሜቶቻችን ጠቋሚ ምልክት ናቸው፡፡ ለራሳችንም ሆነ ለሌሎች ስሜት ደንታ ቢስ መሆን ተገቢ አይደለም፡፡ የሰዎችን ስሜት መረዳት የተፈጠረው ግጭቱ መንስኤ ምን እንደሆነ ለማወቅ ይረዳል፡፡ ችግር ችግር ሆኖ የሚዘልቀው መንስኤው እስኪታወቅ ድረስ ነው፡፡ የራስንም ሆነ የሌላውን ስሜት አይቶ እንዳላዩ ማለፍ ግን ግጭትን ይወልዳል፤ ያባብሳልም፡፡ ‹ዶርማንት› የሚባል የእሳተ ገሞራ ዓይነት አለ፡፡ መገለጫው ውሎ አድሮ አንድ ይደርሳል ብለን ሳናስበው የደረስንበት ቀን ላይ መፈንዳት ነው፡፡ ያኔ ታዲያ እዚያ አካባቢ ያለን ምንም ነገር አያደርጋችሁ፡፡ የነበረውን እንዳልነበረ ይሆናል፡፡ ሰሚ ጆሮ ተነፍጎ የከረመ ስሜትም እንዲሁ ቋት ሲሞላ አንድ ቀን ያፈነውን ክዳን አሽቀንጥሮ ሲወጣ ብዙ ሳይሰባብር አይበርድም፡፡ ‹አይመጣምን ትተሸ ይመጣልን አስቢ› ትልቅ ቁም ነገር አዘል መልዕክት ነው፡፡ በእንቁላል ዕድሜ ላይ የሚገኙ ስሜቶችን ስራዬ ብሎ መስማት፣ ቦታ መስጠት እና ፍላጎታቸውን ለማሟላት ከሰማይ በታች ማድረግ የሚቻለውን ነገር ሁሉ ማድረግ ግጭትን በሩቅ ያስቀራል፤ ድንገት ቢቀሰቀስ እንኳን ያለ ብዙ ኪሰራ ይቀዘቅዛል፡፡ ሳይኮሎጂቶች ቅጣትን የማያበረታቱት ለዚህ ነው ለጊዜው ቀጪ ዱላውን ጨብጦ ዙሪያቸው ሲገኝ ልጆች ታዛዥ እንዲሆኑ ያደርጋል እንጂ ዘላቂ የሆነ የጠባይ ለውጥ ግን ጨርሶ አያመጣም፡፡ ስለዚህ በግለሰብም ሆነ በማኅበረሰብ ደረጃ ግጭትን አስቀድሞ ለመከላከልም ሆነ አንድ ጊዜ ከተፈጠረ በኋላ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ ለማረጋጋት ለሰዎች ስሜት ቦታ መስጠት፣ እንደተረዳናቸው ማስረዳት፣ ቁስላቸው እንደተሰማን መግለጽ ይመከራል፡፡
5. መስማት እና መስማማት መካከል ያለውን ልዩነት መገንዘብ

የተጋጨን ሰው ቅሬታውን መስማታችንን ማወቅ አለበት፡፡ የሰው ልጅ አለመግባባት ሲፈጠር ቀዳሚ ፍላጎቱ መሰማት ነው፡፡ መስማማት ቀጥሎ የሚመጣ ሌላ ሂደት ነው፡፡ በቂ ጊዜ ሰጥተን ሰምተናል ማለት በተባለው ሁሉ ተስማምተናል ማለት አይደለም፡፡ በሁሉ ነገርም መስማማት አይቻልም፡፡ መደማመጥ ግን ቁልፍ ሚና ሊጫወት

እና በቀላሉ ልንተገብረው የምንችለው የግጭት መፍቻ መመሪያ ነው፡፡ ከሁሉ በፊት ምንአልባትም ከሁሉ በላይም አቁሳዩ ጥይት አድማጭ ማጣት ነው፡፡ ሰውን ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ማለፍ ክብረ ነክ ድርጊት ነው፤ ንቀት ነው፤ ‹ምን ታመጣላችሁ?›፣ ‹የራሳችሁ ጉዳይ› ወዘተ ማለት ነው፡፡ እነዚህ የአመለካከከት እና ድርጊት መስመሮች በራሳቸው ግጭትን ይቀሰቅሳሉም፤ ያባብሳሉም፡፡ አንድን ሰው እህ ብሎ መስማት፣ ሃሳቡን በሚገባ እንዲገልጽ ዕድል መስጠት፣ እየተባለ ያለውን ፍሬ ነገር በገዛ ራስ ትርጉምና ፍረጃ ሳይጀቡኑ ለመረዳት ጥረት ማድረግ፣ ሳይኮሎጂስቶች ‹‹already listening›› የሚሉት አለ (የሚመልሱትን መልስ እያውጠነጠኑ መስማት ማለት ነው)፣ እንደዚህ ካለው የማይበጅ የህሊና ድምጽን ዝም አሰኝቶ የሌላውን ህሊና የቅሬታ ድምጽ መስማት ግጭትን ይቀንሳል፤ ይፈታልም፡፡ ተደማመጥን ማለት ተስማማን ማለት አይደለም፤ ሰሚ ጆሮ መስጠት መሸነፍ አይደለም፡፡ መደማመጥ እስካለ ድረስ በአልተስማሙበት ጉዳይ ላይም በልዩነት መስማማት ይቻላል፤ ‹ላለመስማማት መስማማት› እንዲሉ፡፡

6. ስናዳምጥ አስሬ ጣልቃ እየገባን አስተያየት አንስጥ

ይኼም እንዲሁ ለንግግር አድራጊው ያለንን ዝቅተኛ ክብር አስረጂ ነው፡፡ የሚከባበሩ ሰዎች ግጭት ውስጥ የሚገቡበት ዕድል አነስተኛ ነው፡፡ አይበለውና ግጭት ቢነሳ እንኳን በሰለጠነ መንገድ መፍታት አስቸጋሪ አይሆንም፡፡ አንድ ከዚህ በፊት በሌላ አንድ ጽሑፌ ላይ ያነሳሁት ገጠመኝ አለኝ፡፡ እዚህ ጋርም ቢነሳ አስተማሪነቱ የጎላ ሊሆን ስለሚችል ደግሜ ላንሳው፡፡ በነጋ በጠባ አንድንዴ አገር ጉድ እስኪል ድረስ የሚጣሉ ጥንዶች ቤት በአንድ አጋጣሚ ተገኘሁና አንድ ርዕሰ ጉዳይ ተነስቶ ሃሳብ መቀያየር ጀመርን፤ ይመስለኛል ክርክር ቢጤም ነው፡፡ ሚስት ሃሳቧን ሳትጨርስ ባል ደጋግሞ ያቋርጣል፡፡ ሚስት ታዲያ መሃል ላይ ወደ እኔ አንገቷን አዙራ በቅሬታ ድምጽ ‹ተመልከተው አያዳምጠኝም እኮ› አለችኝ፡፡ ቅሬታዋ ‹ለምን በእኔ ሃሳብ አልተስማማም› አይደለም፡፡ ቅሬታዋ ‹ለምን ስናገር አታዳምጠኝም› ነው፡፡ ስንወያይ ሃሳብ የማስጨረስ ልምድ ይኑረን፡፡ ማንም ‹ዓመት› አያወራም፡፡ የቤተሰብ ውይይት ይባልናም በመመገቢያ ጠረጴዛ ዙሪያ ተሰባስበን የወላጅን የትዕዛዝ ዝርዝር የመስማት ትዕግስት እንዲኖረን እንጂ የራሳችንን ሃሳብ እንድንገልጽ አንበረታታም፡፡ አምባገነኖችን በዚህ መልኩ ነው በየቤቱ የምንፈጥራቸው፡፡ ሳይደመጥ ያደገ ልጅ ነገ አድማጭ መሪ የሚሆንበት ዕድል ጠባብ ነው፡፡ በተቋማት ውስጥም ተመሳሳይ ችግር አለ፡፡ ውይይት ማለት በአንድ አቅጣጫ ብቻ ከአሰሪ ወደ ሰራተኛ የሚዥጎደጎድ ምክር ይመስለናል፡፡ ሃሳብን ማስጨረስ ይልቁንም ‹እንዲህ ለማለት ፈልገህ ነው ወይ?› የሚል ጥያቄ በንግግር መጨረሻ በመጠየቅ በትክክል የተባለውን ለመረዳት መጣር፣ ስንነጋገር ከተናጋሪ ጋር ቀጥታ የዓይን ግንኙነት ማድረግ፣ በየመሃሉ ‹አሃ› ማለት ወዘተ ተናጋሪ እየተደመጠ እንደሆነ ስለሚያስገነዝበው መከባበር የሰፈነበት አየር እንዲኖር ያደርጋል፤ መከባበር ወደ መስማማት የማይወስድበትም ምንም ምክንያት የለም፡፡

7. ግምታችንን ገልጸን ግምታችን ስህተት ከሆነ ለመታረም ፈቃደኛ መሆን

‹ግምቶች ብዙ ጊዜ ከእውነታ የራቁ ናቸው› ይላል አንድ ወዳጄ፡፡ ለእውነት የቆመ ሰው ‹ከአፈርኩ አይመልሰኝ› ከሚል ድርቅና የጸዳ ነው፡፡ ‹በዚህ ሰዓት ነበር አይደል ቤት የገባኸው?› ብለን ‹አይደለም፤ በዚህ ሰዓት ነው› የሚል የተለየ መልስ ከተሰጠን፣ ማረጋገጥም ከቻልን ሃሳባችንን እንቀይር፡፡ አንድ ጊዜ የተናገሩትን ላለመሻር በስህተት ላይ ስህተትን እየከመሩ የመሄድ አዚማችን ራስን እያረሙ፣ ወደ እውነት እየተቃረቡ፣ ከእውነት ጋር በእውነት እየተመሩ ከመኖር ይልቅ ሚዛን ይደፋል፡፡ በታሪክም በአመክንዮም ስህተት ስህተትን አርሞ አያውቅም፡፡ ከሰው ስህተት ከብረት ዝገት አይጠፋም፡፡ መሳሳትን ማመን የመንፈስ ከፍታ ነው፡፡ ራስን ማረም ትልቅነት ነው፡፡ ‹ይቅርታ አድርጉልኝ› ማለት ህይወት ውድድር ነው ብለን ብናምን እንኳን በልጦ መገኘት ነው፡፡ እንደ ግለሰብ ለመታረም ፈቃደኛ ያለመሆን ድርቅና ያጠቃናል፡፡ ይኼንን የስነ ልቡናችንን ጎን አፍርሶ መስራት ጠቃሚ ነው፡፡ በአንድ ወቅት አንድ አባ ወራ ከሚስቱ ጋር ተጋጭቶ ለማስማማት ጥረት በምናደርግበት ወቅት ‹እኔ ምንም ስህተት የለብኝም፤ 100 % ልክ ነኝ› የሚል መልስ ይሰጠናል፡፡ የሰው ልጅ በዚህ ደረጃ ልክ ሆኖ አያውቅም፤ ወደፊትም የሚሆን አይመስለኝም፡፡ የዚህ አባ ወራ ምላሽ ‹ስህተትን ማመን ሞት ነው› የሚል የጸና እምነት እንዳለን፣ ድርቅናችን ጥጉ የት ድረስ እንደሆነ የሚጠቁም ነው፡፡

8. ውስብስብ ነባራዊ ሁኔታዎችን ለመረዳት እንትጋ

አለማወቅ የብዙ ችግር ምንጭ ነው፡፡ ማወቅ ትዕግስትን፣ ጥረትን፣ ተነሳሽትን ወዘተ ይጠይቃል፡፡ ድምዳሜ ላይ ከመድረሳችን በፊት የግጭቱን ቀስቃሽ መንስኤዎች ለመረዳት መጓጓት ግጭትን በመፍታት ሂደት ውስጥ ገንቢ ሚና ይጫወታል፡፡

9. ‹ገንቢ ውይይት ማድረግ ይቻላል› የሚል እምነት ይኑረን

የአትሌት ኃይሌ ገ/ስላሴ የ‹ይቻላል› መርህ በግጭት አፈታት ውስጥም ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ አስቀድሞ ‹መግባባት አይቻልም› የሚል እምነት ውስጣችንን ከሞላው ለመግባባት ምንም ጥረት አናደርግም፡፡ ጥረት ብናደርግ እንኳን ለይስሙላ ይሆናል፡፡ የተዘጋ የአይቻልም አስተሳሰብ ወደ መቻል የሚወስዱንን መንገዶች ለመስራት መፈንቀል ያለብንን ድንጋይ በሙሉ እንዳንፈነቅል ጋሬጣ ይሆንብናል፡፡ ከአንጀት ካለቀሱ እንባ መቼም ቢሆን አይገድም፡፡

10. ግጭቱ እንዲባባስ እያደረግን ከሆነ ከድርጊታችን እንቆጠብ

ባልና ሚስት ፍቅራቸው ሳይጠፋ አንድ ጣሪያ ስር አብረው የሚኖሩት አንዱ እሳት ሲሆን ሌላኛው አፈር ከሆነ ብቻ ነው ፡፡ እሳትን በእሳት ማጥፋት ፈጽሞ አይቻልም፡፡

11. ጥፋቱ የማን እንደሆነ ሳይሆን መንስኤው ምን እንደሆነ ለማወቅ መሞከር

ጣት መጠቆም የረባ ለውጥ አያመጣም፡፡ ኮሽ ሲል ተወንጃይ ፍላጋ መሯሯጥ ዘላቂ ለውጥ አያመጣም፡፡ ማውገዝ ረጅም መንገድ አያስኬድም፡፡ መወነጃጀል ግጭትን መፍታት የማይችል ቀሽም ስትራቴጂ ነው፡፡ ግጭት ሲቀሰቀስ ጥፋተኛውን ሳይሆን መንስኤውን ለማወቅ መጣር ግጭቱ ዳግም እንዳይፈጠርም ሆነ አንድ ጊዜ ከተፈጠረ በኋላም እንዲበርድ ለማድረግ ያግዛል፡፡ እውነቱን ለመናገር በየትኛውም ዓይነት ግጭት ውስጥ ሁሉም ወገን የሚጫወተው ሚና ይኖራል፡፡ ስለዚህ ‹ይኼ ግጭት እንዲቀሰቀስ እንዲሁም እንዲባባስ ምን ዓይነት ሚና ተጫውቻለሁ?› ብሎ ራስን መጠየቅ እና የራስን ቤት ከሁሉ በፊት መፈተሽ ግጭትን ይከላከላል፤ ያበርዳልም፡፡
2024/09/27 00:17:19
Back to Top
HTML Embed Code: