Telegram Web Link
ከወደ አርባምንጭ ሜሎሪና-ቴሎስ እየተነበበ ነው

‹‹ልጄ ያሬድ፣ የሰው ልጆችን መከራ ማሸነፊያ መሣሪያ ስለኾነው ነገር ልንገርህ፡፡ ችግሮችን ሁሉ የምናሸንፍበትና ከገባንበት አረንቋ የምንወጣበት አንድ ትልቅ መሰላል አለ፤ እሱም መልካም ተስፋ ነው፡፡ ተስፋ፣ ከምንኖርበት ቦታና ካለንበት አካባቢ አልፈንና ተሻግረን አርቀን እንድናስብ የሚረዳን ነው። ተስፋ አሳብ ነው፤ ተስፋ ምኞት ነው። ዛሬያችንን፣ ከተወረሰበት ጨለማ አራግፈን የምናወጣበት ነው፡፡ ይቺ ዓለምም ብትኾን ለተስፈኞች የተለየ ቦታ ያላት ትመስላለች፡፡ ምክንያቱም ምንም ነገር ሳይታይ፣ ሳይሰማ፣ ሳይዳሰስና ሳይጨበጥ በፊት በአሳብ ደረጃ እያለ የማይታየውን እንዲታይ፣ ያልተጨበጠውን እንዲጨበጥ የሚያደርጉት ትላልቅ ተስፈኞች
ናቸው፡፡ ተስፋ በርግጥ የወደቀውን ያነሣል፤ የተሰበረውን ይጠግናል፡፡

‹‹ስለዚህ ዛሬን በደስታ እየኖርህ ነገ የተሻለ ቦታ መድረስ እንደምትችል በፈጣሪ መልካም ተስፋ አድርግ፡፡ ኹኔታዎች ምቹ ባይመስሉም ተስፋህን ግን አታርቀው፤ ሁሌ ለችግርህና ለሐዘንህ ተስፋን አሳያቸው፡፡ ሕይወትህ መከራ፣ ችግር፣ ሐዘን ውስጥ ቢገባም በቅርቡ ወደ በለጠ ደስታ፣ ድልና ስኬት እንደምትሸጋገር እመን፡፡ በምታልፍበት የሕይወት ችግር ውስጥ የምትኖረው ለጥቂት ጊዜ ብቻ እንደኾነ ለችግርህ ንገረው፡፡ በነገ መልካም ተስፋ ዛሬን በደንብ ጠንክረህ ሥራ በደስታም ኑር፡፡››

የናንተንም ፎቶ ከወደዳችሁት ከመጽሐፉ የወጣ አባባል ጋር ላኩልን
📸 Kibre-ab Elias ĸébå
ወዳጆቼ ኾይ፣ ከጠቀማችሁ ትንሽ ነገር ልበላችሁ

ኹላችንንም ወደዚህች ምድር የላከን ፈጣሪ ነው፡፡ አንዳችንም ወደን ፈቅደንና አስበንበት የመጣን የለንም፡፡ ታዲያ ለምን ይኾን ፈጣሪ ወደዚህች ምድር የላከን? በቃ በልተን ጠጥተን፣ ተምረን ሰርተን ፣ አግብተን ወልደን እንድንሞት ብቻ ነው? ወይስ ሌላ ምክኒያት ኖሮት ይኾን? ቆይ የሕይወት ሩጫችን የት ለመድረስ ነው? ከደረስንስ በኀላ? የሕይወትስ ትልቁ ነገር ምንድነው?
#ራሳችንን_እንጠይቅ
@Psychoet
በዛው መጠን የኛ የሆኑ ሰዎችንም እናውቅበታለን 😍 @psychoet
ሰው ነህ !
💧በሰጡህ ቦታ አትቅር ፣ ሰው እንጂ ድመት አይደለህምና።
💧ማንም ወደ ፈለገው አይቀይስህ፣ ሰው እንጂ የመስኖ ውኃ አይደለህምና።
💧በቁጣ የሠራኸውን አታፍርስ ፣ ሰው እንጂ ጎርፍ አይደለህምና።
💧በወደቅህበት አትቅር፣ ሰው እንጂ ዛፍ አይደለህምና።
🙏ሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን::
የተባለው ከተስማማህ ሼር አድርግ

@Psychoet
እውነት ከሚናገር ሰው በላይ የሚጠላ የለም፡፡
@psychoet
🔥👉 ጭንቀትን_ድብርትንና_አሉታዊ ስሜቶችን_ለመከላከል የሚረዱ_ዘዴዎች🔥👈

🎈ባለፈ ጥፋት ወይም ውድቀት ላይ በማተኮር #ፀፀት# ውስጥ አለመግባት። ከባለፈው ስህተት በመማርና አሁን/ዛሬ ላይ ማተኮር።

🎈 ማህበራዊ ተሳትፎዎችን ማድረግ።

🎈 ከተለያዩ እፆችና አልኮል #ሱሰኝነት# መቆጠብ።

🎈 ግጭቶችን፣ ቅራኔዎችንና አለመግባባቶችን በአግባቡ መፍታት።

🎈 ውጥረትንና ጭንቀትን የሚፈጥሩብዎትን ነገሮችና ሁኔታዎችን መለየትና ከእነሱ መራቅ።

🎈 በጎ ማድረግና ምላሹን ከሰዎች አለመጠበቅ።

🎈ጭንቀትና ድብርት ሲሰማዎ ለቅርብ ወዳጅ፣ ጓደኛ ወይም ቤተሰብ ማጋራት።

🎈ድንገተኛ ችግር ሲያጋጥምዎ፤ ራስን ማረጋጋት።

🎈ሌሎች ሰዎች ስለእርስዎ በሚሰጡት ትችት እና አስተያየት አለመረበሽ።

🎈 የህይወትን ጥሩ ገፅታ ማየት።

🎈በአላማና በእቅድ መኖር ፤ ጊዜን በስራ ማሳለፍ።

🎈የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፤ ንፅህናን መጠበቅ እና ጤናማ የአመጋገብ ስርአትን መከተል።

🎈ለራስ ጊዜን መስጠትና እረፍት ማድረግ።

🎈ከሁሉም በላይ በፈጣሪ መታመንና እኛ ልንፈታ የማንችላቸውን ነገሮች ለእርሱ መተው።

መልእክቱ ለብዙዎች እንዲደርስ Share & Like አይርሱ።

© Psych ጤና Fb ፔጅ
👉በመአዛ መንክር -ክሊኒካል ሳይኮሎጂስት

ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
www.tg-me.com/psychoet
በዓሉን ለምታከብሩ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን አደረሳችሁ 🙏
ሰው መሆን በቂ ነው!

አንድ ቀን አንድ ሰው በድንገት በአንድ ጉድጓድ ውስጥ ወደቀና መውጣትም አልቻለም፡፡ ከብዙ ጥረት በኋላ ደክሞት በጉድጓዱ መካከል ቁጭ እንዳለ …

• ከንፈር መጣጭ ሰው አየውና - “ሁኔታህን ሳስበው በጣም በሃዘን እሞላለሁ” ብሎት ሄደ፡፡

• ተመራማሪ ሰው አየውና - “ይህ ጉድጓድ ከተማ መሃል ሆኖ ሰው መውደቁ አያስደንቅም” ብሎት ሄደ፡፡

• ፈራጅ ሰው አየውና- “ክፉ ሰዎች ብቻ ናቸው እንደዚህ ሊወድቁ የሚችሉት” ብሎት ሄደ፡፡

• ነጭናጫና አጉረምራሚ ሰው አየውና- “እኔ ወድቄ የነበረበትን ጉድጓድ አላየህ” ብሎት ሄደ፡፡

• አነቃቂ ንግግር አስተማሪው አየውና- “በራስህ ብታምን ከዚህ ትወጣለህ” ብሎት ሄደ፡፡

• ዘረኛ ሰው አየውና - “የምን ሃገር ሰው ነህ?” በማለት ከጠየቀው በኋላ የእርሱን ቋንቋ ስላልተናገረ ጥሎት ሄደ፡፡

•ውሸተኛ የሀይማኖት ሰው አየውና - " የኔ እምነት ተከታይ ብትሆን አወጣህ ነበር " ብሎት ሂደ፡፡

• በመጨረሻ ይህንን ሁሉ ድራማ ሲመለከት የነበረ አንድ ጨዋ ጎልማሳ ሰው ከብዙ ጥረት በኋላ እየሳበ አወጣው ፡፡

ከዚህ ታሪክ ምን እንማራለን? በእርግጥ ሰውነት ከሁሉ ይበልጣል ፡፡

ምንጭ :- ከዚሁ ማህበራዊ ሚዲያ የተገኘ

በቅንነት ሼር ያድርጉ👇
http://www.tg-me.com/psychoet
#መልካም_የጥር_ወር_ይኹንላችሁ!

ይህ ወር የአእምሮ ደስታ ፣ ሰላም ፣ እረፍት የምታገኙበት ፤ ካሳሰባችሁና ካስጨነቃችሁ የማያልቅ የሕይወት ውጣ ውረድ እፎይ የምትሉበት ፣ ሕይወታችሁ የሚለወጥበት ፣ አስተሳሰባችሁ መልካምና ቀና የሚሆንበት ፣ ያላቀዳችሁ የምታቅዱበት ፣ ያቀዳችሁ ያቀዳችሁትን የምታሳኩበት ወር ይሁንላችሁ ፡፡

ለሀገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ በኹሉም አካባቢዎች ሰላምን የምንሰማበት ፣ ፍትህን የምናይበት ይሁንልን ፡፡

የሳይኮሎጂና የሕይወት ክህሎት የማሕበራዊ ሚዲያ ትምህርታችን በዚህ ወርም ተጠናክሮ ይቀጥላል ፡፡

ሁሌም የማያልቅ ተስፋ አለ።
ናሁሰናይ ፀዳሉ አበራ
Telegram : www.tg-me.com/psychoet
Facebook : fb.com/psychologyabc

መልዕክቱን #Share #Like በማረግ ለሌሎችም እናጋራ
💪በራስ መተማመንን ማጎልበት💪
Developing Self Confidence

በራስ መተማመን ማለት ሰው ባለው ችሎታ፣ አካላዊ ውበትና ሁለንተናዊ ማንነት አለመፍራት እና ሚዛናዊ በሆነ መልኩ ራስን መቀበል ማለት ነው፡፡ ትእቢት ፣ ትምክህት፣ ያልተገባ አውቃለሁ ባይነት እና ከመጠን ያለፈ ድፍረት በራስ መተማመን አይደለም።

በራስ መተማመንን የሚያጎለብቱ ብልሀቶች

🔥 ራስዎን ከሌሎች ጋር አለማነፃፀር።

🔥 ያለዎትን ክህሎት እና ድክመት መለየት።

🔥 የአካላዊ ገፅታ ውበትን መጠበቅ ደግሞም የሰውን ትኩረት ከልክ ባለፈ ሁኔታ የሚስቡ ጌጣጌጦችንና ሜካፖችን አለመጠቀም።

🔥 ጥሩ እና ምቹ አለባበስ መልበስ።

🔥 ነቃና ቀልጠፍ ብሎ መራመድ ።

🔥 በሰው ፊት ሀሳብዎን መግለፅ ሲኖርብዎ ቀድመው በቂ ዝግጅት ማድረግ።

🔥 መልካም በሆነ የህይወት እንቅስቃሴ የበኩልዎን አስተዋፅዖ ማድርግ።

🔥 ጥሩ የሚሰሩ ሰዎችን ማድነቅ/ ማበረታታት።

🔥 ሰዎች የተቃወሙዎት ወይም የናቁዎት ሲመስልዎ በእርጋታ ምላሽ መስጠት።

🔥 ሰዎች ስህተትዎን ሲነግሩዎ በቀና ማየት(ስለሚጠሉኝ ነው አለማለት)።

🔥 እርዳታ ሲያስፈልግዎ ያለፍርሀት መጠይቅ።

🔥 ሰአት ማክበር።

©በመአዛ መንክር - ክሊኒካል ሳይኮሎጂስት
YouTube: Dink Mikir

#Like #Share በማረግ ለሌሎችም እናስተምር

ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@psychoet
#መጀመር
ማንኛውም ነገር ካልጀመርነው ይከብዳል ስንጀምረው ተግዳሮት አለዉ ደጋግመን ስናደርገዉ ቀላል ነዉ።
ሳንጀምር ይከብዳል አንበል እንደሚከብድ በምን አወቅን?
1. እንጀምረው
2. እንቀጥለው
3. እንጨርሰው ።
#ሁሌ ከሁዋላ የሚሰበረው እስክንለምድ ነው!!!
©ሁንዴ

ይህን መልዕክት ለምትወዱአቸው #5 ታታሪ ጓደኞቻችሁ Forward አርጉልኝ !
#Join #Share
@psychoet
@psychoet
@psychoet
፩. ትናንትን የምታርመውም ኾነ የምታድሰው ዛሬ ላይ ኾነህ ነው፡፡
፪. ነገ ውብ የምትኾነው ዛሬን ስትንከባከባት ነው፡፡
፫. ነገ ከተስፋነቷ በስተቀር ያንተ አይደለችም፡፡

ተስፋህ እውን ኾኖ የምታገኛት ግን ዛሬን በተጠቀምክባት ልክ ነው፡፡ ስለዚህ፣ ትዝታህ ላይ ተቀምጠህ በተስፋ ጋሪ ተሳፍረህ ዛሬን በደንብ ኑር።

ሜሎሪና❤️
በአሉን ለምታከብሩ ለመላ ኦርቶዶክስና ካቶሊክ ቤተሰቦች፣ እንኳን አደረሳችሁ!
@psychoet
ምን ታስባላችሁ?
ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ በተለያዪ የሥነ ጽሑፍ ዘርፎች የላቀ አስተዋጽዖ ያበረከተውን የወንድዬ ዓሊን ልዩ የምስጋናና የዕውቅና መረሐ ግብር ኹላችሁም ተጋብዛችኋል፡፡

በዕለቱ የደራሲው የበኩር ሥራ የኾነችው "ወፌ ቆመች" በዳግም ኅትመት ተመርቃ ለአንባቢ ትቀርባለች፡፡

መግቢያ: በነፃ - ኹላችሁም ተጋብዛችኋል
ቦታ - በአገር ፍቅር ቲአትር
🗓ቅዳሜ ጥር 27 ከጠዋቱ 3:00 - 6:00
በሕይወቴ ከገጠሙኝ መልካም ሰዎች አንዱ ነው፥ ወንድዬ ዓሊ

ነገ ቅዳሜ ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ በተለያዪ የሥነ ጽሑፍ ዘርፎች ላበረከተው የላቀ አስተዋጽዖ ልዩ የምስጋናና የዕውቅና መረሐ ግብር ይካሄዳል፡፡ በተጨማሪም የበኩር ሥራው "ወፌ ቆመች" በዳግም ኅትመት ተመርቃ ለአንባቢ ትቀረርባለች። ኹላችሁም ተጋብዛችኋል፡፡
መግቢያ - በነፃ ቦታ - በአገር ፍቅር ቲአትር
🗓ቅዳሜ ጥር 27 ከጠዋቱ 3:00 - 6:00
2024/09/27 17:23:10
Back to Top
HTML Embed Code: