Telegram Web Link
to whom it may concern-

Hello every one Mekelle university starts soon the reconstruction process to returned back the students to learning and teaching system,but any notification posted in telegram and facebook chanels are unchecked /uncertified then every body shoud have remain /stay till the university management notice and declared the right information .every body should have prepard with this way and with patience.

Thank You !!
But we hopefully returned soon to our university
#መቐለ_ዩኒቨርሲቲ

" ተማሪዎቻችንን እንደገና ለመቀበል ዝግጁ ስንሆን ይፋዊ መግለጫ እንሰጣለን " - ዶ/ር ፋና ሀጎስ (የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት)

ከትላንት ምሽት አንስቶ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች መቐለ ዩኒቨርሲቲን የሚመለከቱ መረጃዎች እየተሰራጩ ይገኛሉ።

እነዚህ መረጃዎች ፦
- ዩኒቨርሲቲው ወደ መማር ማስተማር ስራው እዲመለስ መወሰኑ፣
- በጦርነቱ አቋርጦ የነበረውን ስራ ከመጪው ሳምንት አንስቶ እንደሚጀምር፣
- በመንግስት በኩል አስፈላጊው #በጀት እንደተለቀቀለት፣
- 24 ሺህ ነባር ተማሪዎችን በቀጣይ 4 ወር ትምህርት እንዲያጠናቅቁ እንደሚያደርግ
- ከመስከረም 2016 ጀምሮ አዲስ ተማሪዎችን እንደሚቀበል የሚገልፁ ናቸው።

ነገር ግን ይህ የተሳሳተ መረጃ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ገልጸዋል።

መቐለ ዩኒቨርሲቲም ቢሆን በይፋዊ የፌስቡክ እና የትዊተር አካውንቱ ላይ ምንም አይነት መረጃ አልለጠፈም።

የተሰራጨውን መረጃ በተመለከተ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋና ሀጎስ ለ" ኢትዮጵያ ቼክ " መረጃ ማጣሪያ ድረገፅ በሰጡት ቃል ፥ ዩኒቨርሲቲው ስራ ለመጀመር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በቅርበት እየሰራ ቢሆንም በዩኒቨርሲቲው ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመጠገን የራሱን ጊዜና ሂደት እንደሚወስድ ተናግረዋል።

ዶ/ር ፋና " ዩኒቨርሲቲው ሥራውን ይጀምራል ነገር ግን በሚቀጥለው ሳምንት አይደለም ፤ በእርግጥ ይህን ለማድረግ ወራትን ይወስዳል " ሲሉ ተናግረዋል።

ዶ/ር ፋና እስካሁን መቐለ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች ጥሪ እንዳላደረገ ገልፀው " እኛ (ዩኒቨርሲቲው ወይም የትምህርት ሚኒስቴር) ተማሪዎቻችንን እንደገና ለመቀበል ዝግጁ ስንሆን ይፋዊ መግለጫ እንሰጣለን " ሲሉ አሳውቀዋል።

Credit : ethiopiacheck.org

@tikvahethiopia
በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ለሰራተኞቻቸው ደመወዝ መክፈል ሊጀምሩ ነው።

የገንዘብ ሚኒስቴር ለሰራተኞች ውዝፍ ደመወዝ መክፈያ እና የአንድ ወር የሥራ ማስኬጃ በጀት ባለፈው አርብ መጋቢት 01/2015 ዓ.ም እንደፈቀደላቸው ዩኒቨርሲቲዎቹ ተናግረዋል።

በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ምክንያት ላላፉት 20 ወራት በዩኒቨርሲቲዎቹ ለሚሰሩ ሰራተኞች ደመወዝ አለመከፈሉን የመቐለ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች ለ “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

የፌደራል ተቋማት ለሆኑት አራቱ ዩኒቨርስቲዎች ሰራተኞች የደመወዝ ክፍያ የሚሆን ገንዘብ መተላለፉን የገንዘብ ሚኒስቴር ምንጮች አረጋግጠዋል።

“የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ስላልተመሰረተ ለክልሉ የተላከ ገንዘብ የለም” ሲሉም የሚኒስቴሩ ምንጮች አክለዋል።  

የደመወዝ ክፍያው በ2015 በጀት ዓመት ከታህሳስ እስከ የካቲት ያሉትን ሦሥት ወራት የሚሸፍን ነው።

ውዝፍ ክፍያው የዩኒቨርሲቲዎቹ ሰራተኞች የነበሩ እና በትምህርት ሚኒስቴር ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደቡ ሰራተኞችን አይጨምርም ተብሏል።

Source -@tikvahuniversity
" ትምህርት ቤቶቹን በመጪው ሚያዝያ ወር እንደገና ለመክፈት ዕቅድ ተይዟል " - UNICEF

በትግራይ በጦርነቱ ምክንያት ከሁለት ዓመታት በላይ ተዘግተው የነበሩ ትምህርት ቤቶችን እንደገና ለመክፈት ዕቅድ መውጣቱ ተገልጿል።

በትግራይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ከመራቃቸው ባለፈ መምህራንም ለሁለት ዓመታት ደመወዝ አልተከፈላቸውም።

ትምህርት ቤቶቹን በመጪው #ሚያዝያ_ወር እንደገና ለመክፈት ዕቅድ እንደተያዘም የዩኒሴፍ (UNICEF) የትምህርት ኃላፊ ቻንስ ብሪግስ ተናግረዋል።

ይህን ያሉት ለBBC Focus on Africa ሬዲዮ ነው።

" በትግራይ ሙሉ በሙሉ የትምህርት ሥርዓቱ ፈርሷል። " ያሉት ቻንስ ብሪግስ " ካለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ጀምሮ 2.3 ሚሊዮን ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው የሚያሳይ መረጃ አለን "  ብለዋል።

በመቐለ ከባለቤታቸው እና ከአራት ልጆቻቸው ጋር ነዋሪ የሆኑት አቶ መንግሥት ገብረመድኅን የእርስ በርስ ጦርነቱ በተቀሰቀሰበት ወቅት ሁለቱ ልጆቻቸው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን ይከታተሉ ነበር።

ትምህርት ከተቋረጠም በኋላ " እነሱን ለማስተማር ሞከርኩ፣ ነገር ግን መረጋጋት እና ትኩረታቸውን መሰብሰብ አልቻሉም " ብለዋል።

" የአየር ጥቃቶች እና የድሮን ጥቃቶች ድምጽ ይሰማሉ። ህጻናቱን ጠመንጃ ይዘው የሚሄዱ ወታደሮችንም ያያሉ። እነሱንም ለማስመሰል ይሞክራሉ። " ሲሉ የነበረውን ሁኔታ ገልጸዋል።

በመቐለ ዩንቨርስቲ ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት አቶ መንግሥት ለወራት ደመወዝ ሳይከፈላቸው መቆየቱን ተናግረዋል።

" ደመወዛችን አየተሰጠን ስላልነበር ልጆቻችን ምን እንደምንመግባቸው ያስጨንቀን ነበር። ስለዚህ እነሱን በማስተማር ላይ ማተኮር ፈታኝ ነበር። ነገር ግን ትናንትና ደመወዜን ተቀበልኩ፣ አሁን ለልጆቼም ልብስ እና ምግብ መግዛት እችላለሁ " ብለዋል።

በትግራይ በነበረው ጦርነት ከዛም በፊት በነበረው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሚሊዮኖች ተማሪዎች  ከትምህርት ገበታቸው ርቀዋል ፤ መምህራን ደግሞ በጦርነት ምክንያት ደሞዝ ሳይከፈላቸው ቆይቷል።

Source-@tikvahethiopia
-BBCFocusonAfrica
To whom it concerns
#አክሱም ዩኒቨርሲቲ
The department of Crop and Horticultural Science conducted a PhD defense in Ayder Campus.
Dr. Samuel Alemayehu defended successfully his PhD dissertation on 21st March 2023 in Ayder Campus. Prof. Fetien Abay, Dr. Kiros Meles, Prof Jagger Harvey and Prof. Bhadriraju Subramanian were his promoters.
The defence signals the the restoration of our university after an over two years' challenges due to the Tigrai siege.
Mekelle University management and the community congratulates Dr. Samuel Alemayehu for his successful defense.
Condolence on the Death of Laureate Dr. Tewoldebirhan Gebregziabher

It was with great sadness that we learned today of the passing of the exceptional environmental protector Laureate Dr Tewoldebirhan Gebregziabher. Mekelle University management and the community convey their bottomiess condolences to the family, friends, colleagues and followers of the globally recognized environmental protector, notable academician and exemplary scientific researcher in the biodiversity Laureate Dr Tewoldebirhan Gebregziabher.

He made global contributions in the continuance of nature, biodiversity and the rights of communities in
developing countries over generic resources. He registered several awards from the global institutions for his outstanding leadership, negotiations and activism to the farmerss and communities right. His honors as the Right Livelihood Award in 2006; and the United Nations Environmental Program's "Champion of the Earth Award" are some among the many remarkable awards he achieved. Above all, he was behind us in the entire progress of our university Irom its establishment.Today Mother Earth has realy missed its protector, Thus, once again we, like so many otherS, miss him more than it is possible to describe and send our heartfelt condolences to his family, friends, colleagues and followers.

MEKELLLE UNIVERSITY
# Raya University had a Conference with its community about backing to the track !!!
Congratulations!
Against all odds, Mekelle University has been ranked 4th among the Ethiopian universities by the latest world university ranking portal. This certainly is an accomplishment to be applauded and inspirational.
Mekelle University - EIT-M
EIT-M handed over parabolic solar cooker technologies to SOS Children's Village.
EIT-M has been working with the Green Project Team of SOS Children's Village (CV) Mekelle Program Location (PL) on the implementation of alternative energy. The team of experts from EiT-M has successfully developed ten parabolic solar cooker technologies. Hence, the team
handed over the technologies last week. As to the Managing Director of EiT-M, Dr. Ashenafi Aregawi, the project will serve as a springboard for the EIT-M staff to take part in the revitalization of the institute. The Managing Director moreover, announced that the team will also deliver briquetting and chopping machines to the end users as a part of the project in the coming week.
" ለመምህራንና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች የመጋቢት ጨምሮ የ4 ወራት ደምወዝ ተከፍሏል " - ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ስራ ለመጀመር የሚያስችለው የዩኒቨርሲቲ ካዉንስል ስብሰባ ትላንት በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ አከናውኖ ነበር።

በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የዩኒቨርሲቲው አመራር አባላት ባካሄዱት ውይይት ስራ ለመጀመር የሚያስችል የሶስት ወራት እቅድ ስለማዘጋጀት አስፈላጊነት ስምምነት ተደርሶበታል።

በውይይቱ ወቅት በየደረጃው የተቀናጀ ጥረት በማድረግ ዩኒቨርሲቲው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተማሪዎችን መልሶ ለመቀበል ወደሚችልበት ደረጃ ማድረስ እንደሚቻል ግንዛቤ ተወስዷል።

ለዚህም ይረዳ ዘንድ ሁሉም ኮሌጆች፣ ትምህርት ክፍሎች፣ ዳይሬክተሮችና ሌሎች ፅ/ቤቶች መደበኛ ስራቸው እንዲጀምሩ መመርያ ተሰጥታል።

ዩኒቨርሲቲው ለመምህራንና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች የመጋቢት ጨምሮ የአራት ወራት ደምወዝ የከፈለ መሆኑ ለማወቅ ተችሏል።

@tikvahethiopia
Forwarded from Tikvah-University
አዲስ የስቴም ማዕከል በራያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ተመርቋል።

ማዕከሉ በ STEMpower, SmartAID እና DHL ትብብር የተቋቋመ ነው።

ማዕከሉ አነስተኛ ሰው-አልባ በራሪ ሄሊኮፕተርሮች (ኳድኮፕተሮች)፣ 3-D ፕሪንተሮች፣ ስማርት ኮምፒውተሮች እንዲሁም ኤሌክትሮኒክ ላቦራቶሪዎች ተሟልቶለታል።

በራያ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመው ማዕከል፤ በኢትዮጵያ የተከፈተ 57ኛ የስቴም ፓወር ማዕከል ነው።

@tikvahuniversity
2024/09/22 11:47:08
Back to Top
HTML Embed Code: