Telegram Web Link
# ለ አክሱም ዩኒቨርሲቲ
የገንዘብ ና የማተርያል ድጋፍ ጥሪ
#AxumUniversity

አክሱም ዩኒቨርስቲ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሳቢያ የደረሰበት ጉዳት 15 ቢሊዮን ብር እንደሚገመት ማስታወቁን " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ዘግቧል።

ላለፉት 19 ወራት ትምህርት መስጠት አቁሞ የቆየው ዩኒቨርስቲው፤  ሊያከናውነው ላቀደው ዳግም ግንባታ የድጋፍ ጥሪ አቅርቧል።

የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ገብረእየሱስ ብርሃነ የሰጡት ቃል ፦

- ዩኒቨርስቲው በጦርነቱ ሳቢያ በደረሰበት #ውድመት እና #ዘረፋ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር የሚያስችሉት ቁሳቁሶች እና መሳሪያዎች አጥቷል።

- ሙሉ ለሙሉ የተዘረፉ እና ከወደሙ የዩኒቨርስቲው ንብረቶች ውስጥ ኮምፒውተሮች፣ የላብራቶሪ መሳሪያዎች፣ ሰርቨሮች እና የቢሮ በሮች ይገኙበታል።

- ዩኒቨርስቲው ከጦርነቱ በፊት የነበሩት 60 ገደማ ተሽከርካሪዎች ተዘርፈው እና ተቃጥለው አሁን በስራ ላይ የሚገኘው #አንድ_መኪና ብቻ ነው።

- በጥር ወር ላይ በተደረገ ዳሰሳ የደረሰው ውድመት 15 ቢሊዮን ብር ይደርሳል።

- ጉዳት የደረሰባቸውን ንብረቶች በተወሰነ መልኩ በመተካት ወደ ስራ ለመግባት ታቅዷል።

- ለሚያከናውነው ዳግም ግንባታ እና ጥገና ስራ የገንዘብ እና የማቴሪያል ድጋፍ እንዲደረግልን  ጠይቀናል። የድጋፍ ጥሪው ለዓለም አቀፍ እና ለሀገር በቀል አጋር ድርጅቶች፣ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ነው።

- ዩኒቨርስቲው የሚያገኘውን ድጋፍ በፌደራል መንግስት ከሚመደበለት በጀት ጋር በማጣመር በአጭር ጊዜ ውስጥ የመማር ማስተማር አገልግሎቱን ለመስጠት ታቅዷል። 

- ቁሳቁሶችን በተወሰነ መልክ ቅድሚያ እየሰጠን ካስገባን፤ የግዢ ሂደቱ ፈጣን ከሆነ፤ ተማሪዎችን #በሶስት_ወር ውስጥ ማስገባት እንችላለን። በትግራይ ክልል የሚኖሩ እና ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ትምህርት ያቋረጡ የዩኒቨርስቲው ተማሪዎችን ትምህርት ማስጨረስ ላይ ትኩረት ይደረጋል።

አክሱም ዩኒቨርሲቲ እስካሁን ከፌደራል መንግስት በጀት ባይለቀቅለትም፤ በስሩ ለሚገኘው የጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 43 መምህራንን ለመቅጠር ከ2 ሳምንት በፊት ማስታወቂያ አውጥቷል።

የቅጥር ሂደቱ የሚፈጸመው በትምህርት ሚኒስቴር ተፈቅዶ፣ በጀት ሲለቀቅ መሆኑ ተገልጿል።

ከፌደራል መንግስት የሚለቀቀው በጀት፤ ለዩኒቨርስቲው ሰራተኞች ደመወዝ ለመክፈል እና ትምህርት ለማስጀመር ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

#አራት_ሺህ ገደማ የሚሆኑት የዩኒቨርስቲው መምህራን እና ሰራተኞች ከሐምሌ 2013  ዓ.ም. ወር ጀምሮ #ደመወዝ_አለማግኘታቸውን ዩኒቨርስቲው አስታውቋል።

Credit : www.ethiopianInsider.com

Via - @tikvahethiopia
#Aksum University
Subiect: Disclosing Bank Account Number
Recently, we have invited all concerned bodies to support Aksum University in cash and/or in kind for the reconstruction and rehabilitation endeavor of the University. At the moment, our supporters are requesting for bank account number of Aksum University to support
in cash. Hence, we are kindly disclosing that Aksum University bank account number is 1000022445956 (Commercial Bank of Ethiopia,Aksum Branch).

We respectfully inform you that we will issue a receipt and certificate of appreciation for the support to be given to the University in kind and/or cash. We thank you so much in advance for your financial and material support.


Aksum University

For additional information, use the following address.

Mobile no. +251910593109
+251962212100

Email: [email protected]
to whom it may concern-

Hello every one Mekelle university starts soon the reconstruction process to returned back the students to learning and teaching system,but any notification posted in telegram and facebook chanels are unchecked /uncertified then every body shoud have remain /stay till the university management notice and declared the right information .every body should have prepard with this way and with patience.

Thank You !!
But we hopefully returned soon to our university
#መቐለ_ዩኒቨርሲቲ

" ተማሪዎቻችንን እንደገና ለመቀበል ዝግጁ ስንሆን ይፋዊ መግለጫ እንሰጣለን " - ዶ/ር ፋና ሀጎስ (የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት)

ከትላንት ምሽት አንስቶ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች መቐለ ዩኒቨርሲቲን የሚመለከቱ መረጃዎች እየተሰራጩ ይገኛሉ።

እነዚህ መረጃዎች ፦
- ዩኒቨርሲቲው ወደ መማር ማስተማር ስራው እዲመለስ መወሰኑ፣
- በጦርነቱ አቋርጦ የነበረውን ስራ ከመጪው ሳምንት አንስቶ እንደሚጀምር፣
- በመንግስት በኩል አስፈላጊው #በጀት እንደተለቀቀለት፣
- 24 ሺህ ነባር ተማሪዎችን በቀጣይ 4 ወር ትምህርት እንዲያጠናቅቁ እንደሚያደርግ
- ከመስከረም 2016 ጀምሮ አዲስ ተማሪዎችን እንደሚቀበል የሚገልፁ ናቸው።

ነገር ግን ይህ የተሳሳተ መረጃ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ገልጸዋል።

መቐለ ዩኒቨርሲቲም ቢሆን በይፋዊ የፌስቡክ እና የትዊተር አካውንቱ ላይ ምንም አይነት መረጃ አልለጠፈም።

የተሰራጨውን መረጃ በተመለከተ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋና ሀጎስ ለ" ኢትዮጵያ ቼክ " መረጃ ማጣሪያ ድረገፅ በሰጡት ቃል ፥ ዩኒቨርሲቲው ስራ ለመጀመር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በቅርበት እየሰራ ቢሆንም በዩኒቨርሲቲው ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመጠገን የራሱን ጊዜና ሂደት እንደሚወስድ ተናግረዋል።

ዶ/ር ፋና " ዩኒቨርሲቲው ሥራውን ይጀምራል ነገር ግን በሚቀጥለው ሳምንት አይደለም ፤ በእርግጥ ይህን ለማድረግ ወራትን ይወስዳል " ሲሉ ተናግረዋል።

ዶ/ር ፋና እስካሁን መቐለ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች ጥሪ እንዳላደረገ ገልፀው " እኛ (ዩኒቨርሲቲው ወይም የትምህርት ሚኒስቴር) ተማሪዎቻችንን እንደገና ለመቀበል ዝግጁ ስንሆን ይፋዊ መግለጫ እንሰጣለን " ሲሉ አሳውቀዋል።

Credit : ethiopiacheck.org

@tikvahethiopia
በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ለሰራተኞቻቸው ደመወዝ መክፈል ሊጀምሩ ነው።

የገንዘብ ሚኒስቴር ለሰራተኞች ውዝፍ ደመወዝ መክፈያ እና የአንድ ወር የሥራ ማስኬጃ በጀት ባለፈው አርብ መጋቢት 01/2015 ዓ.ም እንደፈቀደላቸው ዩኒቨርሲቲዎቹ ተናግረዋል።

በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ምክንያት ላላፉት 20 ወራት በዩኒቨርሲቲዎቹ ለሚሰሩ ሰራተኞች ደመወዝ አለመከፈሉን የመቐለ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች ለ “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

የፌደራል ተቋማት ለሆኑት አራቱ ዩኒቨርስቲዎች ሰራተኞች የደመወዝ ክፍያ የሚሆን ገንዘብ መተላለፉን የገንዘብ ሚኒስቴር ምንጮች አረጋግጠዋል።

“የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ስላልተመሰረተ ለክልሉ የተላከ ገንዘብ የለም” ሲሉም የሚኒስቴሩ ምንጮች አክለዋል።  

የደመወዝ ክፍያው በ2015 በጀት ዓመት ከታህሳስ እስከ የካቲት ያሉትን ሦሥት ወራት የሚሸፍን ነው።

ውዝፍ ክፍያው የዩኒቨርሲቲዎቹ ሰራተኞች የነበሩ እና በትምህርት ሚኒስቴር ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደቡ ሰራተኞችን አይጨምርም ተብሏል።

Source -@tikvahuniversity
" ትምህርት ቤቶቹን በመጪው ሚያዝያ ወር እንደገና ለመክፈት ዕቅድ ተይዟል " - UNICEF

በትግራይ በጦርነቱ ምክንያት ከሁለት ዓመታት በላይ ተዘግተው የነበሩ ትምህርት ቤቶችን እንደገና ለመክፈት ዕቅድ መውጣቱ ተገልጿል።

በትግራይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ከመራቃቸው ባለፈ መምህራንም ለሁለት ዓመታት ደመወዝ አልተከፈላቸውም።

ትምህርት ቤቶቹን በመጪው #ሚያዝያ_ወር እንደገና ለመክፈት ዕቅድ እንደተያዘም የዩኒሴፍ (UNICEF) የትምህርት ኃላፊ ቻንስ ብሪግስ ተናግረዋል።

ይህን ያሉት ለBBC Focus on Africa ሬዲዮ ነው።

" በትግራይ ሙሉ በሙሉ የትምህርት ሥርዓቱ ፈርሷል። " ያሉት ቻንስ ብሪግስ " ካለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ጀምሮ 2.3 ሚሊዮን ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው የሚያሳይ መረጃ አለን "  ብለዋል።

በመቐለ ከባለቤታቸው እና ከአራት ልጆቻቸው ጋር ነዋሪ የሆኑት አቶ መንግሥት ገብረመድኅን የእርስ በርስ ጦርነቱ በተቀሰቀሰበት ወቅት ሁለቱ ልጆቻቸው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን ይከታተሉ ነበር።

ትምህርት ከተቋረጠም በኋላ " እነሱን ለማስተማር ሞከርኩ፣ ነገር ግን መረጋጋት እና ትኩረታቸውን መሰብሰብ አልቻሉም " ብለዋል።

" የአየር ጥቃቶች እና የድሮን ጥቃቶች ድምጽ ይሰማሉ። ህጻናቱን ጠመንጃ ይዘው የሚሄዱ ወታደሮችንም ያያሉ። እነሱንም ለማስመሰል ይሞክራሉ። " ሲሉ የነበረውን ሁኔታ ገልጸዋል።

በመቐለ ዩንቨርስቲ ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት አቶ መንግሥት ለወራት ደመወዝ ሳይከፈላቸው መቆየቱን ተናግረዋል።

" ደመወዛችን አየተሰጠን ስላልነበር ልጆቻችን ምን እንደምንመግባቸው ያስጨንቀን ነበር። ስለዚህ እነሱን በማስተማር ላይ ማተኮር ፈታኝ ነበር። ነገር ግን ትናንትና ደመወዜን ተቀበልኩ፣ አሁን ለልጆቼም ልብስ እና ምግብ መግዛት እችላለሁ " ብለዋል።

በትግራይ በነበረው ጦርነት ከዛም በፊት በነበረው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሚሊዮኖች ተማሪዎች  ከትምህርት ገበታቸው ርቀዋል ፤ መምህራን ደግሞ በጦርነት ምክንያት ደሞዝ ሳይከፈላቸው ቆይቷል።

Source-@tikvahethiopia
-BBCFocusonAfrica
To whom it concerns
#አክሱም ዩኒቨርሲቲ
The department of Crop and Horticultural Science conducted a PhD defense in Ayder Campus.
Dr. Samuel Alemayehu defended successfully his PhD dissertation on 21st March 2023 in Ayder Campus. Prof. Fetien Abay, Dr. Kiros Meles, Prof Jagger Harvey and Prof. Bhadriraju Subramanian were his promoters.
The defence signals the the restoration of our university after an over two years' challenges due to the Tigrai siege.
Mekelle University management and the community congratulates Dr. Samuel Alemayehu for his successful defense.
Condolence on the Death of Laureate Dr. Tewoldebirhan Gebregziabher

It was with great sadness that we learned today of the passing of the exceptional environmental protector Laureate Dr Tewoldebirhan Gebregziabher. Mekelle University management and the community convey their bottomiess condolences to the family, friends, colleagues and followers of the globally recognized environmental protector, notable academician and exemplary scientific researcher in the biodiversity Laureate Dr Tewoldebirhan Gebregziabher.

He made global contributions in the continuance of nature, biodiversity and the rights of communities in
developing countries over generic resources. He registered several awards from the global institutions for his outstanding leadership, negotiations and activism to the farmerss and communities right. His honors as the Right Livelihood Award in 2006; and the United Nations Environmental Program's "Champion of the Earth Award" are some among the many remarkable awards he achieved. Above all, he was behind us in the entire progress of our university Irom its establishment.Today Mother Earth has realy missed its protector, Thus, once again we, like so many otherS, miss him more than it is possible to describe and send our heartfelt condolences to his family, friends, colleagues and followers.

MEKELLLE UNIVERSITY
# Raya University had a Conference with its community about backing to the track !!!
Congratulations!
Against all odds, Mekelle University has been ranked 4th among the Ethiopian universities by the latest world university ranking portal. This certainly is an accomplishment to be applauded and inspirational.
2024/09/23 03:22:08
Back to Top
HTML Embed Code: