Telegram Web Link
ንጉስ ፈይሰል አሸዋ ላይ በተዘረጋው ምንጣፍ ላይ ተቀምጦ የአሜሪካ ቴፕላይን ካምፓኒ ሃላፊን አስጠራ
"አንዲት የነዳጅ ጠብታ ወደ እስራኤል እንዳይላክ" ሲልም አዘዘ።

አሜሪካ ትዕዛዙን ጥሳ ለእስራኤል እርዳታ እንደላከች ሲሰማ ከአሜሪካ ጋር የነበረውን የነዳጅ ሽያጭ ውሉን አቋረጠ።
በሀገረ አሜሪካ ሰላማዊ ሰልፍ ነገሰ
ሰዎች በነዳጅ ማደያዎች ፊት ተሰልፈው
ነዳጅ እንጂ እስራኤልን አንፈልግም የሚለውን መፈክር አስተጋቡ።
በዚህ ጊዜ ንጉስ ፋይሰል ታዋቂ ንግግሩን አደረገ
"ነዳጅ ከቁድስ ክብር አይበልጥብንም። አያቶቻችን በተምርና በወተት ኖረዋል እኛም ወደዛው ህይወት እንመለሳለን"
አላህ ይዘንልህ

ዛሬስ አረቦች
ዛሬስ የአለም ሙስለሞች??
በቀን ይሄን ያህል ንፁሀን ሞቱ ቆጣሪ ሁነናል
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከመፅሀፍ ገፅ ➊

#የነብዩ ሰዐወ መቃብር ቁፈራ የተጋለጠበት!!
አዘጋጅ ☞አሚር ሰይድ
የታሪክ መጻሕፍት በ557 ዓ.ሂ የተከሰተን አንድ አስገራሚ ጉዳይ ሳይጠቅሱ አያልፉም፡፡ ያ ዘመን የዐብባሳውያን ሥርወ-መንግሥት በመንኮታኮት ላይ የነበረበት ዘመን ነበር፡፡ ይህን አጋጣሚ በመጠቀም በአጐራባች አገራት ይኖሩ የነበሩ ክርስቲያን መንግሥታት አንድ ከባድ ሴራ ጠነሰሱ። ሴራቸው የሙስሊሞችን መዳከም ተገን አድርገው የነቢዩን አስከሬን ከነበረበት በመስረቅ ወደ ራሳቸው ግዛት መውሰድ ነበር፡፡ ይህን በማድረግም በሙስሊሞች ላይ ከፍተኛ ሞራላዊ ጉዳት ለማድረስ
አሰቡ::

ስለዚህ ይህን ረቂቅ ተንኮል ለማስፈፀም ሁለት የተመረጡ ሰላዮችን የሞሮኮ ኢስላማዊ አለባበስ በማልበስ ወደ መዲና ከተማ ሰደዱ ሰዎቹም ለነዋሪዎቿ ለፀሎት ወደ ቅድስቲቷ ከተማ የመጡ ሐጃጆች መሆናቸውን እንዲናገሩ ጥብቅ ማሳሰቢያ ተሰጣቸው፡፡ ሁለቱ ሰዎች ተልዕኮኣቸውን ለመወጣት እንዲችሉ መስጂደል ነበዊ (የነቢዩ መስጂድ) አጠገብ ባለ ቤት ውስጥ መኖር ጀመሩ፡፡ በጐረቤቶቻቸውም ዘንድ ለመታመን ሲሉ መስጂድ ማዘውተርና የዒባዳ ተግባራትን በጥልቀት ማከናወን የዕለት ተዕለት ተግባራቸው ሆነ፡፡ ዋናው ጉዳያቸው ግን የተላኩበትን ዓላማ ማስፈፀም እንደሆነ ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡ ይህን ተልዕኮ ለማከናወን የመጀመሪያ ሥራቸውንም ከነበሩበት ቤት አንስተው ወደ ነቢዩ መቃብር ለመድረስ ውስጥ ለውስጥ በመቆፈር መሿለኪያ ለማበጀት ቁፋሮ ጀመሩ፡፡ እንዳይነቃባቸውም በየቀኑ ትንሽ ትንሽ ብቻ እየቆፈሩ የሚያወጡትን አፈር በትናንሽ መያዣዎች አድርገው ጀለቢያቸው ሥር በማንጠልጠል አል-በቂፅ ወደሚባለው የመዲና
   የቀብር ስፍራ እየወሰዱ ይደፉ ነበር። ሌሎቹ ነዋሪዎች ሰዎቹ በየዕለቱ ወደ ቀብር ሥፍራ የሚሄዱት የሞቱትን በመዘየር ሞትና አኼራን ለማሰብ ነው የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል፡፡ ሰዎቹ አንዳንዴ ሲደክማቸው መሿለኪያ ለማበጀት የሚቆፍሩትን አፈር ከሚኖሩበት ቤት አጠገብ ወዳለ ጉድጓድም ይደፉ ነበር። እንዲህ እያደረጉ በመጨረሻ መሿለኪያውን ከነቢዩ ሰዐወ ቀብር ጋር ሊያገናኙ ደረሱ፡፡ እዚህ ደረጃ ሲደርሱ ተልዕኮኣቸው ለመሳካቱ እርግጠኛ ስለነበሩ የትኩረት አቅጣጫቸው የነቢዩን አስከሬን ካወጡ በኋላ በምን መንገድ ወደ መጡበት ግዛት እንደሚያጓጉዙ ማቀድ ነበር፡ የተለያዩ ዘዴዎችን አውጥተው አወረዱ፡፡ በዚያው ወቅት አላህ የራሱን ሴራ እያሴረባቸው እንደሆነ ግን አላወቁም፡፡

የዘመኑ የሙስሊሞች መሪ የነበሩትና ከመዲና ብዙ ርቀው የሚኖሩት ኑረዲን ሙሐመድ ኢብኑ ዘንጂ በዚያው ሰሞን አንድ ለየት ያለ ሕልም እዩ፡፡ በሕልማቸው ውስጥ ነቢዩ ሰዐወ ነበር የታዩዋቸው፡ ነቢዩ ወደ ሁለት ቀያይ ፀጉረ ልውጥ ሰዎች እያመለከቱ ከእነርሱ እንዲያድኗቸው ኑረዲንን ይማፀናሉ ይህን ከባድ ሕልም ሲመለከቱ ኑረዲን በድንጋጤ እየተንቀጠቀጡ ከእንቅልፋቸው ነቁ። ራሳቸውንም ለማረጋጋት ሶላት ከሰገዱ በኋላ ተመልሰው ወደ መኝታቸው ቢሄዳም አሁንም ያው ሕልም ተመልሶ መጣባቸው:: ሕልሙ ለሦስተኛ ጊዜ ሊመጣባቸው ከእንቅልፋቸው በመነሣት ከሚንስትሮቻቸው መካከል ሷሊሕና ብልህ የነበረውን ጀማሉዲን አል ሙሲሊ የተባለውን አስጠሩ፡፡ ያዩትን ሕልም ለጀማሉዲን ሲነግሩት ሕልማቸው በመዲና ውስጥ የሆነ እንግዳ ነገር እየተከናወነ መሆኑን እንደሚጠቁም አስረዳቸው፡፡ በአስቸኳይም ወደ ነቢዩ ከተማ በመሄድ ስለ ሕልሙ ለማንም ሳይናገሩ ሁኔታዎችን እንዲከታተሉ አሳሰባቸው፡፡ ኑረዲን ከለሊቱ የቀረውን ክፍል ለጉዞው ዝግጅት ሲያደርጉ አደሩ፡፡ ጀማሉዲንን ጨምሮ ሃያ ጭነት ከሃያ ሰዎች ጋር እንዲዘጋጅ አዘዙ፡ ከሻም(ሶሪያ) ተነስተው መዲና ለመድረስ የፈጀባቸው ዐሥራ ስድስት ቀናት ብቻ ነበር። መዲና ሲደርሱ በፍጥነት የሄዱት በመስጂደል ነበዊ ውስጥ ወደሚገኘው አልረውዳ ልዩ የሶላት ስፍራ ነበር፡፡ እዚያ በመሄድም ዱዓ አደረጉ:: ይሁን እንጂ ሕልሙን በተመለከተ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ሊያውቁ አልቻሉም፡፡ አማካሪያቸው ጃማሉዲን በሕልማቸው ውስጥ ያዩዋቸው ሁለት ሰዎች ምን ዓይነት እንደሆኑ እንዲነግሩት ሲጠይቃቸው ኑረዲን የሰዎቹን መልክና አለባበስ እንደሚያስታውሱና ቢያገኙዋቸው መለየት እንደሚችሉ ነገሩት፡፡ ጀማሉዲን ሰዎቹን ለመያዝና ሴራቸውን ለማክሸፍ ቆርጠው በመነሳታቸው ፈጣን እርምጃዎችን መውሰድ ጀመሩ፡፡ የመዲና ነዋሪዎች በመስጂዱ ውስጥ ሲሰበሰቡም እንዲህ የሚል ማስታወቂያ አስነገሩ፡፡ 'መሪያችን በሶደቃ ለመስጠት ነይተው ያመጡት ብዙ ሃብት አለ፡፡ ሶደቃውን ለማከፋፈል እንዲመቸን በችግር ውስጥ ያላችሁ ሰዎች ሁሉ እየመጣችሁ ስሞቻችሁን እንድታስመዘግቡ እንጠይቃለን የሚል፡፡ ይህን ማሳሰቢያ እንዳስነገሩ ሰዎች ሶደቃውን ፍለጋ ተንጋግተው መምጣት ሲጀምሩ ኑረዲን በሕልማቸው ውስጥ ያዩዋቸውን ሰዎች ለመለየት ዳር ቆመው እያንዳንዱን ሰው ይቃኙ ነበር። ብዙ ሰዎች መጥተው የድርሻቸውን እያነሱ ቢሄዱም ኑረዲን ተፈላጊዎቹን ሁለት ሰዎች ሊያገኙ አልቻሉም፡፡

በመጨረሻም ከሶደቃው ድርሻውን ያልወሰደ ሰው እንዳለ ሲጠይቁ የሆነ ሰው ·ከሞሮኮ የመጡ ሁለት ሰዎች አሉ፡፡ ሰዎቹ በጣም ሷሊሕ ሰዎች ስለሆኑ ሶደቃውን ለመቀበል አልፈለጉም አላቸው፡፡ ኑረዲን ይህን እንደሰሙ ሁለቱን ሰዎች በአስቸኳይ እንዲያመጧቸው አዘዙ፡፡ ኑረዲን ሁለቱ ሰዎች እፊታቸው እንደቀረቡ ሰዎቹ ነቢዩ ሰዐወ በሕልማቸው ያመለከቷቸው ሰዎች መሆናቸውን በቀላሉ አወቁ። ሰዎቹንም “ለመሆኑ ከየት ነው የመጣችሁት? በማለት ጠየቁ፡፡ እነርሱም የመጣነው ከመግሪብ ነው፣ አመጣጣችን ለሐጅ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ይህን ዓመት እዚሁ ለማሳለፍ ወስነናል' አሏቸው:: ኑረዲን ሰዎቹ የሆነ ያቀዱት ሴራ መኖሩን ቢጠረጥሩም ምን እንደሆነ በእርግጠኝነት ለመለየት ስላልቻሉ ድብቅ ሴራቸውን ይፋ እንዲያወጡ በማሰብ የተለያዩ ጥያቄዎችን አከታትለው ቢጠይቁም ምንም ፍንጭ ሳያገኙ ቀሩ፡፡ በዚህም የተነሣ ምንም እርምጃ ሊወስዱባቸው አልተቻላቸውም:: ኑረዲን ቀጥለው ያዘዙት ቤታቸው ይፈተሽ የሚል ነበር፡፡ ቤታቸው ሲፈተሽም በቤቱ ውስጥ ካስቀመጡት በርካታ ገንዘብ ውጭ ሊያስጠረጥራቸውና ሊያስወነጅላቸው የሚችል ምንም ነገር ሳይገኝ ቀረ፡፡ ለፍተሻ ወደ ቤታቸው የገባ ሰው አንድ በአንድ መውጣት ሲጀምር ኑረዲንም ምንም ምልክት በማጣታቸው ቤቱን ለቀው ሊወጡ ሆነ: በዚያች ቅፅበት ነበር አላህ የሙስሊሞቹ መሪ አንዳች ነገር አትኩረው እንዲመለከቱ ያደረገው ኑረዲን ወለሉን ሲቃኙ በወለሉ ላይ ከተነጠፉት ጣውላዎች ው አጥብቆ እንዳልያዘ አስተዋሉ፡፡ ይህን እንዳዩ ጐንበስ በማለት ጣውላውን ሲያነሱ የመዲናን ነዋሪዎች ጉድ ያሰኘ ክስተት ተስተዋለ። በወለሉ መሿለኪያ መቆፈሩን ነዋሪዎቹ ግን ይበልጥ የተደናገጡት መሿለኪያው ወዴት እንደሚያመራ ሲረዱ ነበር፨ መሿለኪያውን የቆፈሩት በከተማይቷ ውስጥ በሷሊሕነታቸው ይታወቁ የነበሩት ሁለቱ የሩቅ አገር እንግዶች መሆናቸው ሌላው ግርምታ የፈጠረ ጉዳይ ሆነ፡ እስከዚያን ጊዜ ድረስ ሁለቱ ሞሮኮኣውያን የሚታወቁት በጥልቅ ዒባዳቸውና በላቀ ኢስላማዊ ሥነ-ምግባራቸው ነበር፡፡ እጅግ የተናደዱት መሪ ኑረዲን ሁለቱን ሰዎች መግረፍ ሲጀምሩ ሰዎቹ በርግጥ ከመግሪብ (ሞሮኮ) አንዳልመጡና በመሪያቸው ከፍተኛ ገንዘብ ተከፍሏቸው የተላኩ ክርስቲያኖች መሆናቸውን የመጡትም የነቢዩን አጽም ቆፍረው በማውጣት በድብቅ ወደ አገራቸው ለመውሰድ መሆኑን አመኑ፡፡ ኑረዲን ሁለቱ ሰዎች በሞት እንዲቀጡ አዝዘው የተቆፈረው መተላለፈያም በአስተማማኝ መልኩ በአለት እንዲደፈን አደረጉ፡፡ ሴራውንም እንዳከሸፉ ወደ ሻም (ሶሪያ) ተመለሱ፡፡
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከመፅሀፍ ገፅ ➋

#ነፍስያውን_ያሸነፈው_ወጣት
አሚር ሰይድ

ኢብን ሐዝም በጣም ይዋደዱ ስለነበሩ ሁለት ጓደኛሞች ታሪክ አስተላልፈውልናል፡፡ ሁለቱ ጓደኛሞች ከመዋደዳቸው የተነሣ በመካከላቸው ምንም ገደብ አልነበራቸውም። ከዕለታት አንድ ቀን ጓደኛሞቹ በአንደኛው ቤት ተቀምጠው ሳለ መሸ። ከጓደኛው ጋር ሲጫወት የነበረውና የቤቱ ባለቤት የሆነው በድንገት ለአስቸኳይ ሥራ ወጥቶ ለመመለስ ባለመቻሉ በቤቱ የቀረው ጓደኛው እዚያው የማደሩ ነገር እርግጥ ሆነ። በቤቱ ውስጥ እሱና የጓደኛው ሚስት ብቻ ቀሩ፡፡የሁለቱን ጥብቅ ጓደኝነት የማታውቀው ሚስት እኩለ ለሊት ሲደርስ ከባሏ ጓደኛ ጋር የመተኛት ፍላጐት ስላየለባት እሱ ወደተኛበት ክፍል ዘልቃ በመግባት እንዲገናኛት ወተወተችው፡ በመጀመሪያ ላይ የጠየቀችውን ለማድረግ ልቡ ቢነሣሣም የጓደኛው አመኔታ ሲታወሰው ስሜቱን ለመግታት ያልተለመደ እርምጃ ለመውሰድ ተነሣ፡፡ የጓደኛው ሚስት ስታስቸግረውና የእሱም ስሜት ሲነሣሣ አንደኛውን የእጁን ጣት አጠገቡ በነበረው ኩራዝ ላይ እያስቀመጠ “ከጀሃነም እሳት ይህ ይሻልሃል' ይል ጀመር፡፡ ሴትየዋ ይህንንም እያየች ወጣቱን ለወሲብ መፈለጓን አልተወችም፡፡ እሱም እሷ ባስቸገረችውና ስሜቱ በተቀሰቀሰበት ቅፅበት የእጆቹን ጣቶች በኩራዝ መለብለቡን ቀጠለ። ሲነጋ ከእጆቹ ጣቶች አንደኛው ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጭ ሆኖ ነበር፡፡

ጓደኝነት ይህ ነው


join👇👇👇

www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከመፅሀፍ ገፅ ➌
#የዱዓ_ዕምቅ_ኃይል
  አሚር ሰይድ

ከብዙ መቶ ዓመታት በፊት አንዲት ሴት የኢማም ማሊክ ደረሳ የነበሩ ኢስማዒል የሚባሉ ዓሊም ታገባለች የዚህ የተቀደሰ ጋብቻ ትሩፋት ሙሐመድ የሚባል ልጅ ማግኘታቸው ነበር ኢስማዒል ብዙም ሳይቆዩ አረፉ። ከበስተኋላቸው ግን ለሚስታቸውና ለሕፃን ልጃቸው ማሳደጊያ የሚሆን ብዙ ሃብት ትተው ነበር፨ እናት ልጇን ሙሐመድን በጥሩ ኢስላማዊ ሥነ-ምግባር ኮትኩታ አሳደገች በቂ የዲን ዕውቀትም እንዲቀስም አደረገችው ልጃ, አድጐና በዕውቀት ፋፍቶ ታላቅ ዓሊም እንዲሆንላት ምኞት ቢኖራትም ይህ ልጅ አንድ ችግር ነበረበት ዓይነስውርነት። በዘመኑ ደግሞ ለዓይነስውር ታዳጊ በዕዉቀት ለመግፋት ምቹ ሁኔታ አልነበረም፨ የዲን ዕውቀት የሚፈልጉ ሰዎች ከአገር አገር፣ ከዓሊም ዓሊም መሄድ የግድ ስለነበር ይህ ልጅ ይህን ለማድረግ ዕድል አልነበረውም፡፡እናቱ ግን ተስፋ አልቆረጠችም በየዕለቱ ዱዓ ማድረግ ጀመረች በዚህ ሁኔታ እያለች ከዕለታት አንድ ቀን በእንቅልፋ ለየት ያለ ህልም አየች። በህልሙ ውስጥ ነቢዩላህ ኢብራሂም  ወደ እሷ መጥተው “ከዱዓዎችሽ ብዛት የተነሣ አላህ ሰምቶሽ ለልጅሽ የአይኑን ብርሀን መልሶለታል አሏት

እናት እስኪነጋ ለመጠበቅ አልቻለችም፨ ተነስታ ልጁ, ወደተኛበት ክፍል ገብታ ከእንቅልፉ ስትቀሰቅሰው የሙሐመድ ዓይኖቹ በርግጥም በርተዋል አላህ የሚሳነው ነገር የለም፡፡

በታላቅ ጭንቀት ላይ ያሉና ለእርዳታ ወደርሱ የተመለሱትን ባሮች ከመርዳት ወደኋላ አይልምና አላህ የልጇን ዓይነስውርነት በመፈወሱ እጅግ የተደሰተችው እናት ልጇ ለትምህርት ያለውን ጉጉት ያብልጥ እንዲገፋበት በርትታ አዝዘችው በዚህ የዒልም ዘርፍ ከፍተኛ የተባለ ዕውቀቶችንም እንዲቀስም ረዳችው፡፡ በሕይወት ዘመኑ አጋማሽ ላይ ይህ ልጅ ከቁርኣን ቀጥሉ ታላቅ ተቀባይነት ያለውን መጽሐፍ ለማዘጋጀት የበቃው የሶሒሕ ቡኻሪ አጠናቃሪ –በሙሉ ስማቸው ሙሐመድ ኢብኑ ኢስማኢል አል- ቡኻሪ ናቸው፡፡

ቡኻሪ አላህ በዲናዊ ዕውቀት ያበለፀጋቸው እጅግ ብሩህ አስተዋይና አስታዋሽ አዕምሮ የሰጣቸው ታላቅ ዓሊም ነበሩ።

join👇👇👇

www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከመፅሀፍ ገፅ ➍
#አላህ_እንዲህም_ያድናል!
አሚር ሰይድ

ከምዕተ ዓመታት በፊት የኖረው መሪ ሱልጣን ሱቀይላ እንቅልፍ ቶሎ የሚጥለው ሰው ነበር። ከምሽቶቹ በአንዱ ግን እንቅልፍ ሸሸው፡፡ ቢገላበጥ ሊወስደው አልቻለም። እንቅልፍ እንደሸሸው የተረዳው ሱቀይላህ 'መንቃቴ ካልቀረ ሥራ ልሥራ በማለት የባሕር ኃይሉን ጀነራል በመቀስቀስ “ከመርከቦቻችን አንዱን ወደ አፍሪካ ላክ፡፡ ምን እየተከናወነ እንደሆነም መልዕክት እንዲልኩ አድርግ የሚል ትዕዛዝ ሰጠው፡፡ ጄነራሱም እንደታዘዘው አደረገ፡ እንቅልፍ በማጣቱ በለሊት የሚንሸራሸረው ሱልጣን ቆየት ብሎ ወደ ባሕር ዳርቻው ወርዶ መርከቦቹን ሲቃኝ ወደብ የለቀቀ አንድም መርከብ አለመኖሩን ስላየ ጀነራሉን ተቆጣዉ:: ጀነራሉ የታዘዘዉን መፈፀሙን እሱ በማያቀዉ ምክንያት ተመልሶ መልህቅ መጣሉን ነገረዉ፡፡

መርከቡ ከጉዞው ለምን እንደተመለሰ የመርከቡን ካፒቴን ለመጠየቅ ተያይዘው ወደ ካፒቴኑ ሄዱ፡፡ ካፒቴኑም ለምን ከጉዞው እንደተገታ እንዲህ ሲል ነገራቸው፡፡ 'የባሕር ጉዞውን ስንጀምር ድቅድቅ ጨለማ ስለነበር ምንም ነገር ለመመልከት አልቻልንም፡፡ ትንሽ እንደተጓዝን ግን ከጭለማው ውስጥ ከባሕር ላይ “አላህ ሆይ አንተ ለእርዳታ ሲጠሩት ለጠሪው የምትደርስለት አምላክ እርዳኝ" የሚል የሰው ድምፅ ስለሰማን ድምፁን ወደሰማንበት አቅጣጫ አመራን፡፡ ስንደርስ የሆነ ሰው ከመስመጥ ለመዳን የሞት ሽረት ትግል ላይ ነበር፡፡ ከባሕሩ ውስጥ ጐትተን ካወጣነው በኋላ የገጠመውን ስንጠይቀው ይቀዝፍበት የነበረው ጀልባ እንደሰጠመችበትና እኛ እስከደረስንለት ጊዜ ድረስ እርዳታ ፍለጋ ሲጮህ ውሉ እንዳመሸ ነገረን

ከዚህ ታሪክ አላህ የአንድ ግለሰብ ሕይወት ለማዳን ሲል የአገሩን መሪ እንቅልፍ መንሳቱን እንገነዘባለን፡፡ አላህ ሱወ ጥበቡ የላቀ አሠራሩ የረቀቀ እርዳታው ከማይጠበቅበት አቅጣጫ የሚደርስ አምላክ ነው፡፡


join👇👇👇

www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከመፅሀፍ ገፅ ➎
#ሙእሚን_ከአንድ_ጉድጓድ_ሁለቴ_አይነደፍም
አሚር ሰይድ


የበድር ጦርነት ወቅት አቡ ዐዝዛህ አል-ጁመሂ የተባለ ባለቅኔ በምርኮነት ሙስሊሞች እጅ ወደቀ፡፡ አቡ ዐዝዛህ የግጥም ተሰጥኦውን ተጠቅሞ በሙስሊሞች ላይ ቁረይሾችን ሲያነሣሣ የነበረ ሰው ነበር። ከተማረክ በኋላ ወደ ነቢዩ ሙሐመድ ሰዐወ ዘንድ ቀርቦ “እኔ ብዙ የቤተሰብ አባላትን የማስተዳድር ደሃ ስለሆንኩ ምሕረት አድርገውልኝ ይልቀቁኝ, ይዘኑልኝ• በማለት ተማፀናቸው፡፡

ነቢዩም ሰዐወ አዝነውለት እንዲለቀቅ አዘዙ፡፡ ሌላ ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ግን ከቁረይሽ መሪዎች አንዱ የሆኑት ሶፍዋን ኢብኑ ኡመያህ ለአቡ ዐዝዛህ 'ያ አቡ ዐዝዛህ አንተ ትልቅ የግጥም ችሎታ አለህ  ይህን ችሎታህን ተጠቅመህ ተከታዮቻችን ሙስሊሞችን በመውጋት ላይ ጽናት እንዲኖራቸው ቀስቅስልን∶ በማለት ተማፀነው፡፡ አቡ ዐዝዛህ ነቢዩ ሰዐወ እሱን በመልቀቅ የዋሉለት ውለታ ስላለ ውለታቸውን ውድቅ በማድረግ የሚጐዳቸው ነገር ላይ ለመሳተፍ እንደማይፈልግ ቢነግረውም ሶፍዋን ኢብኑ ኡመያህ አቡ ዐዝዛህ በቅስቀሣው ዘመቻ የሚረዳቸው ከሆነ- “ከጦርነቱ በሰላም ከተመለስክ ከሃብቴ አካፍዬህ ሃብታም አደርገሃለሁ፡፡ በጦርነቱ ላይ ከተገደልክ ሴቶች ልጆችህን ከእኔ ሴቶች ልጆች ጋር የተቀማጠለ ኑሮ እንደማኖራቸው ቃል እገባልሃለሁ ብሎት አሳመነው፡ በተገባለት ቃል የጓጓው አቡ ዐዝዛህ ወደተባለው ጦርነት ሄደ። ለሁለተኛ ጊዜም የሙስሊሞች ምርኮ ሆነ፡፡ እንደ በፊቱም ነቢዩ ሰዐወ ፊት ቀርቦ ምሕረት እንዲያደርጉለት ጠየቃቸው፡፡ ነቢዩ  ግን “በአላህ ይሁንብኝ ከእንግዲህ ጉንጮችህ ዳግም መካን አይነኩም። በርግጥ ሙሐመድን ሁለቴ አታለሃል፡፡ አንድ ሙእሚን ደግሞ ከአንድ ጉድጓድ ሁለቴ አይነደፍም፡ ካሉት በኋላ ወደ ዙበይር ዞር ብለው ዝብይር ሆይ! ይህን ሰው ሰይፈው አሉት፡፡ ሁለቴ ለማታለል የሞከረው አቡ ዐዝዛህ በገዛ ቅጥፈቱ ምክንያት ሕይወቱን አጣ፡፡


http://www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከመፅሀፍ ገፅ ➏
#ስግብግብነት_ሲበዛ
አሚር ሰይድ

ሙሐመድ አደ-ዳሪ የሚከተለውን አስተላልፈዋል- “ከእኛ መሃከል አንድ ስግብግብ ሰው ነበር። ይህ ሰው ያለውን ዐሥር አህዮች እየነዳ የዳር ከተማን ለቅቆ ወጣ፡ በመጓዝ ላይ እያለም አንደኛይቷን አህያ ተቀመጠባት፡፡ አህያዋ ላይ ተቀምጦ እያለ የተቀሩትን አህዮች ሲቆጥር ዘጠኝ አህዮች ብቻ ሆኑበት፨ አህዮቹን ደጋግሞ ቢቆጥርም ቁጥራቸው ያው ዘጠኝ ሆነ። ከዚያ ከተቀመጠው አህያ በመውረድ ·ተቀምጨያት ከማገኘው ጥቅም ከአንዲት አህያ ቁጥር የማገኘው ትርፍ እመርጣለሁ🙄 በማለት በእግር መጓዙን መረጠ። መኖሪያ ቀየው ሲደርስ ረጅም ርቀት በእግሩ ተጉዞ ስለነበር ተዝለፍልፎ ሊወድቅ ደርሶ ነበር፡፡

join👇👇👇

www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከመፅሀፍ ገፅ ➐
#ሙእሚኑ_ሲፈተን!
አሚር ሰይድ

አንድ ካፊር ለሙእሚን እንዲህ አለው፡፡ “አላህ ከከተበብኝ (ከጻፈብኝ) በስተቀር ሌላ ጉዳት አይነካኝም ብለህ አልነበረም? ሙእሚኑም “አዎ ብያለሁ አለው፡፡ ካፊሩ መልሶ “እንደሱ ከሆነ በል አሁን ከዚህ ተራራ ጫፍ ላይ ዝለል። አላህ ሊያድንህ ወስኖ ከሆነ ያድንሃል” አለው፡፡ ሙእሚኑም “ይህን ያልከኝን እፈጽም ነበር። ግን ደግሞ አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር ባሮቹን የሚፈትነው አላህ ነው እንጅ ባሮች አላህን አይፈትኑትም በማለት የካፊሩን ተንኮል ውድቅ አደረገበት፡፡

join👇👇👇

www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከመፅሀፍ ገፅ ➑
#የኢብን_ቀይም_ወርቃማ_አባባሎች
አሚር ሰይድ

ኢብን ቀይም እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል- “አንድ የአላህ ባሪያ ከእንቅልፉ ሲነቃ ብቸኛው ምኞቱ አላህን ለማስደሰትና እርሱን ለመገዛት ከሆነ አላህ ወዲያው የዚህን ሰው ፍላጐቶች ሊያሟላለትና የሚያበሳጩትን ነገሮች ሊያስወግድለት ይወስናል። ይህ ብቻ አይደለም፨ አላህ የዚህ ሰው ልብ እርሱን ብቻ እንዲያፈቅር፣ ምላሱ እርሱን ብቻ እንዲዘክር፣ ሰውነቱ እርሱን ብቻ እንዲገዛ ያደርጋል፡

ባሪያው ሲነጋ ጭንቀቱ ሁሉ የዚህ ዓለም ጉዳይ ከሆነ አላህ የሰውየውን ጭንቀቶችና ሸክሞች ለራሱ (ለሰውየው) ይተወዋል። ልቡን በጭንቀት፣ ውሎውን በመከራና በብስጭት ይሞላል፡፡ ፍቅሩን ከዚህ ዓይነት ሰው ስለሚያርቀው የሰውየው ፍቅር ለምድራዊ ነገሮች ብቻ ይሆናል። ምላሱ ስለሌሎች ሰዎችና ሌሎች ነገሮች በማውራት ይገደባል። ሰውነቱ ያምጻል፡ ለተለያዩ ስሜቶችና ፍላጐቶች ተገዢ ይሆናል። ልፋቱ የአህያ ዓይነት ልፋት ይሆናል፡፡ ፊቱን ከአላህ ፍቅር፡ ዒባዳና
ታዛዥነት ያዞረ ሰው ደግሞ ሕይወቱ በምድራዊ ደስታዎችና ፈንጠዚያዎች፣ ለፍጡራን በመገዛትና በማጐብደድ የተሞላች ትሆናለች- አላህ ﷽ “አር-ረሕማንን ከማውሳት ራሱን ያገለለ ሰይጣንን የቅርብ ወዳጁ ይሆን ዘንድ እናዘጋጅለታለን" (ቁርኣን 43:36) ብሏልና፡፡

ኢብን ቀይም ይህ እንዳይከሰት የሚከተለውን እንድናደርግ ይመክሩናል- “በሦስት ሁኔታዎች ውስጥ ስትሆኑ ልቦቻችሁን ፈልጉ
➊ ቁርኣንን ስታደምጡ፣
➋ ዚክር ከሚያደርጉ ሰዎች መካከል ስትቀመጡና
➌ ለብቻችሁ ስትሆኑ˚ በእነዚህ ሦስት ሁኔታዎች ውስጥ ሆናችሁ ልባችሁን ለመግዛት (ለመሰብሰብ) ካልቻላችሁ አላህ ልብ ይስጣችሁ*

join👇👇👇

www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከመፅሀፍ ገፅ ➒
#የተበደለ_ሰው_ዱዓ_መሬት_ጠብ_አይልም
አሚር ሰይድ

ነቢዩ ሰዐወ በእርሱና በአላህ መሃከል ምንም ዓይነት ግርዶ የለምና የተበደለን ሰው ዱዓ ፍሩ” ማለታቸውን ኢብኑ ዐብባስ አውርተዋል፡፡ ስለዚህ ሰዎች ሲበድሉን መፍትሔው መበሳጨት ወይም ለሌሎች ሰዎች መናገር ሳይሆን የአላህን እገዛ በነርሱ ላይ መሻት ነዉ፡፡

አርዋ ቢንት ዑወይስ ከእርሻ መሬቷ የተወሰነው በሰዒድ ኢብኑ ዓምር ኢብኑ ኑፈይል ተወስዶብኛል በማለት ለአሚር ሙሐመድ ኢብኑ ዐምር ኢብኑ ሐዝም አቤቱታ አቀረበች፡በአላህ ይሁንብኝ የነጠቀኝን መሬት በአስቸኳይ የማይመልስልኝ ከሆነ በነቢዩ ሰዐወ መስጂድ ውስጥ ጀመዓው ፊት አዋርደዋለው በማለትም ዛተች፡፡ ሙሐመድ ግን- "እባክሽን የአላህ መልዕክተኛ ባልደረባ የሆኑትን (ሰዒድ ኢብኑ ዐምር) አትጉጂኣቸው፡፡ ሰዒድ የሚበድልሽ ወይም መብትሽንም የሚነካ ሰው አይደለም የሚል ምክር ሰጧት፡፡ አርዋ በዚህ ምላሽ ባለመርካቷ ወደ ዑመይራህ እና ዐብደላህ ኢብኑ ሰላማህ በመሄድ ተመሣሣይ አቤቱታና ዛቻ ሰነዘረች: ዑመይራና ዐብደላህ ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ሰዒድ ዘንድ ሄዱ፡፡ ሰዒድ በእርሻ ቦታው ላይ ሆነው ወደሳቸው የመጡትን ሁለት ሰዎች ሲመለከቱ- 'ምን ጉዳይ ገጥሞኣችሁ ነው ወደኔ ልትመጡ የቻላችሁት?" በማለት ሲጠይቁ
....አርዋ ስለሳቸው የምታቀርበውን ክስ ለማጣራት መሆኑን ነገሯቸው፡፡ ሰዒድ ኢብኑ ዓምር በሰሙት ነገር በማዘን “የአላህ መልዕክተኛ ሰዐወ የሌላ ሰው ሐቅ የሆነችን የእጅ መዳፍ የምታክል መሬት እንኳን ብትሆን በሕገ-ወጥ መንገድ የወሰደ ሰው በቂያማ ቀን ከሰባቱ መሬቶች የዚያችን ቦታ የሚያክል ሸክም ይንጠለጠልበታል ማለታቸውን ስለሰማሁ ትምጣና የኔ ሐቅ ነው የምትለውን መሬት ትውሰድ” ካሉ በኋላ " #አላህ_ሆይ! ይህች ሴት በሐሰት ወንጅላኝ ከሆነ ሳትሞት የዓይኗን ብርሃን ነስተሃት የሞቷንም መንስዔ ዓይነስውርነቷ እንድታደርግ እጠይቅሃለሁ የሚል ዱዓ አደረጉ፡፡ ለሰዎቹም ያደረጉትን ዱዓ ለሴትየዋ እንዲነግሯት ጠየቁ።
.... አርዋ ያሸነፈች መስሏት ሰዒድ በመሬቱ ላይ የነበረን ጎጆ በማፍረስ በምትኩ የራሷን ቤት ሠራች። ይሁን እንጂ ይህን እንዳደረገች ብዙም ሳትቆይ ዓይኖቿ ጠፉ፡፡ የምትንቀሣቀሰውም በአገልጋይዋ ድጋፍ ሆነ፡፡


አንድ ቀን ውኃ ለመቅዳት ወደ ጥልቅ ጉድጓድ ብቻዋን በመሄዷ ጉድጓዱ ውስጥ ገብታ ሕይወቷ አለፈ፡ የተበደለ ሰው ዱዓ በአላህ ዘንድ ይህን ያህል ተቀባይነት አለው፡፡

ሰዉን ከበደል አደራ አደራ እንጠንቀቅ!!!


join👇👇👇

www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
2024/10/02 12:28:43
Back to Top
HTML Embed Code: