Telegram Web Link
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ልብሽን ምክንያት እየሰጠሽ አታድክሚዉ
ዩምና ሙሀመድ

እራስሽን ልክ እንደ ሙሳ ቀይ ባህር መሀል ላይ አኑሪው ከጀርባሽ ፊርአውንን እሚያክል ጠላት ወይ ችግር አለብሽ ከበላይሽ የተሰነጠቀ ባህር እሚያክል አንቺ ላይ ሊደርስ እሚችል ችግሮች ተከምረው ታይተውሻል ወደ ጎን አትይም መካከል ላይ ነሽ ብቻሽን አይደለሽም በአንቺ ስር ያሉ የብዙዎችን ህይወት ከአላህ በታች ይዘሻል ....ልክ ሙሳ ተከታዮቹን እንደያዘው ነፍሴን ብቻ አይልም ነፍሳችንን እንጂ ከእራሱ ሩህ በላይ እሚያስጨንቀው የተከታዮቹን ነገር ነው ምናልባትም አንቺ የብዙ ሀላፊነት ባለቤት ሆነሽ ይሆናል፡፡

ታዲያ ሙሳ ከባህሩ አልወጡምን? በየትኛው መንገድ? ከፊት ለፊታቸው በምትታያቸው አንድ መንገድ ያቺን መንገድ እስኪያገኟት ድረስ ወደ ሗላ አልዞሩም ወደ ሗላ ችግራቸው ነው ያለው ፊት ለፊታቸው ግን ነፃነት ከብዙ የነፍሶች ሀላፊነት ማረፍ ሀቀኝነትን ብቻ ቡዙ ተአምሮችን ይዟል ያቺ የታየቻቸውን መንገድ በጀሊሉ ፍቃድ ደረሱባት ዞር ብለው ወደ ችግሮቻቸው ሲያዩ ግን ቢወርድ ሊያጠፋቸው እሚችለው ባህር ሲከተላቸው የነበረውን ችግር ድምጥማጡን አጠፋላቸው

አንቺም ያሉብሽን ችግር እስክታልፊያቸው ዞረሽ አትመልከቻቸው ይደርሱብኛል እምትያቸው ችግሮችሽ ምናልባት የደረሱብሽን ችግሮች ማጥፊያ ናቸው ፡፡ መውጫሽን ተመልከቺ ግን ስለሁሉም ጌታሽን አጥብቀሽ ያዢው በእሱ ያለሽ እምነት ከልብሽ አድርጊው የተፃፈልሽ ሙሲባ በሙሉ ሊስትሽ አልነበረም የሳተሽ በሙሉ ሊያገኝሽ አልነበረም ልብሽን ምክኒያት እየሰጠሽ አታድክሚው

☞ አንቺ ማለት ሳትጠይቂው ለእሱ ባሪያው እንድትሆኚ የፈጠረሽ ባሪያው ነሽ
☞አንቺ ማለት ከስንት ሚሊዮን እህት እና ወንድሞችሽ ተመርጠሽ የተፈጠርሽ ፍጡር ነሽ
☞አንቺ ማለት በዱንያው እሳት ፈትኖሽ እንደ ወርቅ ሊያስከብርሽ ሊያስወድድሽ እሚያደርግ ጌታ ነው ያለሽ

>>> እናም ያኡኽታ ረህማኑን አጥብቂው የተጣበቀብሽ ይለቅሻል
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አሁንስ አትገረሚም???
ዩምና ሙሀመድ

ምን ያስገርመኛል መሰለሽ ሁሌ የረህማኑን አዛኝነት እኔ የእሱ ባሪያው እንድሆን የመሻቱ ስፋት በእኔ  መታወስ የፍላጎቱን ጥግ አስተውለሽው ይሁን?
እኔ ባላስታውሰው እኮ ሚጎድልበት ነገር የለም እሱ እኮ ስንት እሚዋደቁለት ባሪያዎች አሉት እሱ እኮ ምድር ላይ ያለች ትንሿ ጠጠር ሳትቀር የፈጠረ ጌታ እኔን ማስታወሱ አይገርምሽም?

^ ቢተወኝስ ቆይ ሲጀመር ባይፈጥረኝስ ስንት እህት እና ወንድሞቼን እናቴ ሆድ ውስጥ ባክነው እኔ መፈጠሬ ስለወደደኝም አይደለምን?
ታዲያ አይደለም የወደደኝ ጌታ የወደደኝ ሰው እኔ ላይ መብት የለውም እንዴ?
ምሳሌ ላንሳልሽ ምድር ላይ በጣም በጣም ከሚሳሱልኝ ሰዎች ውስጥ ከእናቴ ወይ ከአባቴ በላይ ፍጥረት የለም እኮ አይደል!! 
እስኪ ልጅኘታችንን ዞረሽ እይው ልጅ ናቸው በሚል ሀላፊነት የሚባል አልነበረብንም ሀላፊነት መውሰድን በትንሽ በትንሹ እንድንማር አደረጉን
አላሄዋም እስከ 15 አመት ወይም እራሳችንን እስክናውቅ ነፃነት ሰጠን ምንም ቅጣት እንደሌለብን አሳወቀን ለቤተሰቦቻችን ግን የኛን የመኮትኮት ሀላፊነት ሰጣቸው  አትገረሚም!!


.....ቡሗላ እንዳንደክም ግራ እንዳንጋባ እኮ ነው ከዛማ ልክ ስናድግ ቤተሰቦቻችን ለማስደሰት ውለታቸውን ለመመለስ እያልን ሀላፊነት እንዳለብን ሁላ ከእልጅነት እስከእውቀት  የለፉብንን  ለመመለስ ስንል እኛ ላይ መብት አላቸው እያልን እነሱን ለማስደሰት መብታቸውን ለመጠበቅ ደፋ ቀና እንላለን ታዲያ ያኡኽታ ይሄንን ሁላ ነገር አንቺ ካለነበርሽበት አስገኝቶ ጭራሽ እማያውቁሽ እማታውቂያቸውን ፍጡሮች እናት እና አባት ያውም ከእዝነት ጋር የለገሰሽ ጌታ አንቺ ላይ መብት የለውምን?

>>>>> ብርጭቆ ስትሰብሪ ሁላ እኮ እናትሽ ወይ ትቆጣሻለች ወይ ትመታሻለች እና ስለምን ሲባል የፈጠረሽ ጌታ በነገሮች ሲቆነጥጥሽ ቢጠላኝ ነው አስባለሽ?ምን ባደርገው ነው እያልሽ ከእሱ ጋር ግብግብ አስፈጠረሽ?

^^ደሞ እኮ በተከበረው ቃሉ ሲፈትንሽ እያላቀሽ  ስለመሆኑ አማኝ ስለመሆንሽ እንዲህ እያለ ነግሮሻል "አሊፍ ላም ሚም አሀሲበናሱ አዩትረኩ አመና ፈሁም ላዩፍተኑን"
^የሰው ልጆች አምነናል ካሉ ቡሗላ እንፈተናለን ብለው አላሰቡንም አልገመቱምን^ ይለናል አየሽልኝ ኡኽታ በእሱ ስለማመኔ ማመልከቻው ወይ ደሞ መለያው በሚያመጣልኝ ነገር መታገሴ ነው::
* ለትምህርት ፈተና ስል ስንቴ አነባለው ለሊት አዳር እያነጋሁኝ  እየተጨነኩኝ ካለፋሁኝ እንደምወድቅ አውቃለዋ ከወደኩኝ ደሞ ያኔ ለቤተሰቦቼ ተገቢውን ምላሽ አልሰጠሁም ማለት ነው የት ት ፈተናውን ማለፌ
ከእኔ በላይ ቤተሰቦቼ ያስደስታቸዋል አላሄዋም ሲሞክረኝ ወደእሱ እንድቀርብ አጥብቆ ይሻብኛል::

>>>>>አስተውዪማ የሆነ መስሪያ ቤት እራስሽን አስቀጥረሽ ሳዩው ከዛማ አሰሪሽ አንቺን ይወድሻል ሊያጣሽ አይፈልግም እንድትቀርቢው ይፈልጋል ምን እሚያደርግሽ ይመስልሻል?
በጣም ከምትፈልጊው እሱ ጋር ካለ ነገር ይቀንስብሻል ወይም ያስቀርብሻል ለምሳሌ ደሞዝሽን ግማሹን ወይም እሩቡን እሱ ጋር አስቀርቶ ቀሪውን ቢሰጥሽ እመኚኝ ቀሪውን ደሞዝሽ ፍለጋ አሰሪሽ ቢሮ ትመላለሻለሽ አሰሪሽም እሱ እሚፈልጋትን ሴት እስክትሆኚለት በመመላለስሽ እርካታን አግኝቶ ይቀመጣል::
____አላሄዋም ከአሰሪሽ በላይ ላንቺ እሚያስፈልግሽን ነገር ሲነጥቅሽ መርጦሽ ነው ወደእሱ እራስሽን እንድታዞሪ እየጠየቀሽ ነው ግን እኛ መመረጥን እምናውቀው ሁላ አይመስለኝም::
*ደሞ እኮ አያቆምም በቃ ተስፋ ቆርጫለው የፈጠረኝንም አስከፍቻለው ብለን ስናስብ እንዲህም አይደል የሚለን
"ቁል ያኢባዲየለዚነ አስረፋ አላ አንፉሲሂም ላተቅነጡ ሚን ራህመቲላህ ኢነላሀ ገፉሩን ረሂም"
(እናንተ በነፍሶቻቹ ላይ ድንበር ያለፋቹ ባሪያዎቼ ሆይ በአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡ አላህኮ አዛኝና ማሀሪ ነው)
  ይለናል እሺ አሁንስ አትገረሚም?



አምፀነውም ወዶን በሞከረን ነገር ላይም እንዴት ብለን የእሱን መብት ለእራሳችን ሰጥተንበትም አሁንም ኑኑኑኑ ቅረቡኝ እያለን እኮ ነው::  ከእዝነቱ እንዳንሸሽ ይነግረናል ምን ያክል ለእኛ ቅርብ እንደሆነ ያሳውቀናል የእሱ እዝነት ትልቅ ስለመሆኑ ከእዝነቱ ያሻንን እንደምንወስድ እየወስድንም እንደሆነ
"ወኢን ተኡዱ ኒእመላሂ ፈላቱአዱሀ"
(የአላህን ፀጋ ብትቆጥሩት አትዘልቁትም)እያለ ያበስረናል በሰፊው እዝነቱ እንደምንኖር ስለምን በእዝነቱ እና በፀጋው ተከበን ተስፋን እንቆርጣለን አንቺዬ?
^መለስ አድርጎ ደሞ ፈተናዎቹ ብቻቸውን እንዳልመጡ ነገራቶች ሁላ መሞከሪያዎች ከእዛም ብርሀናዊ ፀጋዎች ስለመሆናተው እንዲህ ይለናል አይደል "ፈኢነማአል ኡስሪ ዩስራ" (በእርግጥም ከችግር ቡሓላ ምቾት አለ)
ብሎ ከፀጋዎቹ ውስጥ የሆነኛውን ይገልፅልናል እናም ኡኽታ ጨንቆሻል ከፍቶሻል ወይ የሆነ ይሳካልኛል ያልሽው ነገር አለመሳካቱ አዘንብሎብሻል ተሳሰቢውማ ተነሺና ውዱእ አድርገሽ መስገጃሽ ላይ ተደፍተሽ ማድረግ እየፈለግሽ ይቺን ትልቋን ነፍሲያሽን አሸንፈሽ ለአላሄዋ ብለሽ በተወሽው ነገር ተሳሰቢው ያኔ ግን ለእሱ ብለሽ የተወሽው ነገር ካጣሽ ቀድመሽ ነፍስሽን ተሳሰቢያት
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አሰላሙ አለይኩም ፉአድ ሙና ኢፋዳ የሚል መፅሀፍ አዘጋጅቶ ገበያ ላይ ከኢድ ጀምሮ ለአንባቢዎች አድርሷል፡፡ ሙስሊም ፀሀፊዎችን ማበረታታት ለወደፊት ለሚሰሩት ስራ ሞራል መስጠት ነዉ፡፡ እኔ ይሄን መፅሀፍ የገዛሁት ገበያ ላይ እንደዋላ order ሲደረግ በኢዱ ቀን ነበር...ይሄዉ ትናንት ደሴ መጥቶ ተረከብኩ፡፡
ማንበብ ጀምሪያለሁ፡፡
እናም ፉአድ ሙናን ማጠናከር ማበረታታት አለብን፡፡ አዲስ አበባም በክልል ከተሞችም
ስለተሰራጨ መፅሀፉን በመግዛት ከጎንህ ነን ልንለበዉ ይገባል

ክፍለ ሀገሮች ኢፋዳን በተጠቀሱት አድራሻዎች ማግኘት ትችላላችሁ።

ኢፋዳን በክልል ከተሞች!
.
★ወራቤ
ወራቤ ከቴሌ ጎን(ፓርክ ሆቴል ፊትለፊት) አቅሷ የኪታብ መሸጫ መደብር

★ሀዋሳ
ሀዋሳ ፒያሳ ኬርአውድ ሆቴል ፊትለፊት ሁሴን ሞል ሳኒ ሞባይል አክሰሰሪ ሱቅ ቁ.29

★ጅማ
ጅማ +251944842429 በመደወል ማግኘት ትችላላችሁ።

★ደሴ
ደሴ +251982674095 በመደወል ማግኘት ትችላላችሁ።

★አዳማ
ፖስታ ቤት ወደ ፒኮክ በሚወስደው አስፓልት በኩል አቢሲኒያ ባንክ አጠገብ አሰብ አዳማ የገበያ ማዕከል መግቢያ ላይ በሚገኘው ፖስታ ስቴሽነሪ

★ድሬዳዋ
ድሬዳዋ አሸዋ በሚገኘው ሲትራ ሱፐርማርኬት
ቦታው ከጠፋችሁ+251929065110 ደውሉ

★ሀረር
ሀረር ሲጋፋ ተራ kim Cafe ፊትለፊት መካ ኤሌክትሮኒክስ
ቦታው ከጠፋችሁ +251968209420 ይደውሉ።
.
#Ifadasales

.
በመሆኑም ቀድማችሁ @ifadasales ላይ ክፍያ የፈፀማችሁ የተላከላችሁን ቁጥር በማሳየት መረከብ የምትችሉ ይሆናል።
በሞባይል ባንኪንግ @ifadasales ላይ መክፈል የማትችሉ በካሽ እየከፈላችሁ መግዛት ትችላላችሁ።
አዲስ አበባ ያላችሁ


አዲስ አበባ ላይ ኢፋዳን ምስሉ ላይ በተጠቀሱት ቦታዎች በመሄድ ይግዙ። በቴሌግራም @ifadasales ላይ ቀድመው ኦርደር ማድረግና ክፍያ መፈፀምም ይችላሉ። ከዚያም ከዚያ የሚሰጥዎትን ቁጥር በማሳየት ብቻ መፅሀፉን ከሚቀርብዎ ቦታ መውሰድ ይችላሉ።

ቀዳሚ አንባቢ ይሁኑ!
.
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ውርጭ ያዘለ ልቤን❤️❤️❤️
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔴ታላቅ የምስራች ተጅዊድን መማር ለምትፈልጉ ተማሪዎች🟡

#ዚክራ_ኦንላይን_የቁርአን_ማእከል_የሁለተኛ #ዙር_ምዝገባ_መጀመራችንን_ስናበስር_በደስታ_ነው
#የሁለት_ወር_ጥቅል_የተጅዊድ_ትምሀርት

🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘
    
            #የትምህርቱ_አሰጣጥ📘📕

1,በዙም አፕልኪሼን
2,በቴሌግራም አፕልኬሽን
🟠🟠🟠🟠🟠
    
        #የቆይታ_ጊዜ 🕙
በሳምንት 3 ቀን
⚫️⚫️⚫️⚫️⚫️⚫️

#ትምህርቱን_ለመከታተል_የሚያስፈልጉ
🔹ዋይፋይ(ፈጣን ኔትወርክ)
🔸ስማርት ስልክ📱💻
🔳🔳🔳🔳🔳🔳🔳🔳🔳

        #ያሉን_ቦታዎች⛺️🛖

##በጀመአ (በግሩፕ)
##vip🏠 (በ ግል)

ከተሟላ በሰርተፍኬት ጋር🔖

በግል ለመመዝገብ
👇👇👇
@redwan6910

ዋትስ አፕ https://chat.whatsapp.com/I6YyupqN1TW8Nzf6DgVZXz

ወደ ተጅዊድ ትምህርት መስጫ ግሩፕ👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/+V3lxqKjWQHxiYzFk

ወደ public group
👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/+-zHkXQeSZdc4MjY0

#zikra_Qur'anic_academy
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በፈረንጆቹ በ1950ዎቹና በ1960ዎቹ አካባቢ የሴት ፍላጎት፣ መብትና ነፃነት አይደለም ሊከበር ቀርቶ አልታሰበም ነበር፡፡ ሴት ልጅ ያገባች ከሆነ የባሏ አገልጋይ፤ ለትዳር ካልደረሰች ደግሞ የእናቷ ረዳት፤  ወግ ሳይደርሳትና ዕድል ሳይገጥማት ሳታገባ ከቆየች ወይም ፈት ከሆነች ደግሞ በማህበረሰቡ የስድብ ናዳ ይወርድባታል፣ ትናቃለች፣ ትገለላች፡፡ ሴት ሆኖ መፈጠር ምን ያህል ከባድ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው፡፡ በአሜሪካ እንኳን እ.ኤ.አ. በ1950 ዓ.ም. የነበረው ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተዘጋጀውን የኑሮ በዘዴ መማሪያ መፅሐፍ (Home Economics text book) ብናይ ያገባች ሴት የባሏን ፍላጎት እንዴት ማሟላት እንዳለባት የሚያስተምርና የሚተነትን ነበር፡፡ ሴት ግዴታዋና ሃላፊነቷ የበዛ ነገር ግን መብትና ነጻነቷ ያነሰ፤ ምንም ምርጫ ያልነበራት እንደነበረች እናቶቻችንን ማየት በቂ ነው፡፡

ያም ሆነ ይህ በዘመናችን ያለችው ሴት በእናቶቻችን ዘመን ከነበሩት ሴት በብዙ መልኩ ትለያለች፡፡ ትናንት ፍላጎቷ የማይከበርላት፤ ዛሬ በአንድም በሌላም መንገድ ፍላጎቷ ይከበርላት ዘንድ አቅምና ጊዜ አግኝታለች፡፡ የዘመናችን አንገብጋቢውና አሳሳቢው ጉዳይ ግን ሴቶቹ ራሳችን የምንፈልገውን ነገር አለማወቃችን ነው፡፡ ራሳችንን አለማወቃችን የወንዶች ብያኔ ተጠቂ እንድንሆን አድርጎናል፡፡ ለጉብዝናችን ወይም ለቁንጅናችን የምስክር ወረቀት የምናገኘው ከወንዶቹ ነው፡፡ በዛም አለ በዚህ የወንዶች ስነልቦና ተጠቂ ሆነናል፡፡ በኢኮኖሚ ራሳችንን እየቻልን ብንመጣም በአስተሳሰብ ግን አሁንም የወንዶች ጥገኛ ነን፡፡ ራሳችንን በምግብ ብቻ ሳይሆን በሃሳብም ካልቻልን ከወንዶች ጭቆና አንተርፍም፡፡

መቼስ ሴትን እንደ እንደስነልቦና ምሁሩ ሲግመንድ ፍሮይድ ያጠናት የለም፡፡ ሰውየው ሴት ልጅ ገና ከልጅነቷ ጀምሮ ምን ዓይነት አስተሳሰብና ባህሪ ሊኖራት እንደሚችል፤ እንዲሁም ትክክለኛ ፍላጎቷ ምን እንደሆነ ለማወቅ የተመራመረ ነው፡፡ ለዚህ ነው ‹‹ሴት የምትፈልገው ምንድነው? What do women want›› በሚለው ጥያቄው የሚታወቀው፡፡

ሴት በሴት መቀናናት ያለ ነው፡፡ የማታስቀናም የማትቀናም ሴት የለችም፡፡ ሴት በወንድ ስትቀና ግን ሊያስገርም ይችላል፡፡ ፍሮይድ ይሄን በተመለከተ አንድ ጥናት ነበረዉ፡፡ ይሄ ጥናት ሴት ገና ከአፍላ እድሜዋ ጀምሮ አጎጠጎጤዎች ስታወጣ፣ የመራቢያ አካሏ እየዳበረ ሲመጣ፣ ለአቅመ ሔዋን ስትደርስና እንደ ወንድ አለመሆኗን ስታውቅ በወንዱ መቅናት ትጀምራለች ይለናል፡፡ መቅናት ከሴት ተፈጥሮ ጋር የተዋሃደ ይመስላል፡፡ ይሄ የስነልቦና ተመራማሪ ስለሴቶች ባህሪ ለማወቅ ብዙ ጥናቶችን ቢያከናውንም ሴቶች ግን እንቆቅልሽ እንደሆኑበት ነው ህይወቱ ያለፈው፡፡ የሚገርመው ሴት ልጅ አይደለም ለወንዱ ለገዛ ራሷ ግራ አጋቢ ፍጥረት መሆኗ ነው፡፡ ኤቭሊን ሌት (Evelyn Leite) የተባለች ታዋቂ የስነልቦና አማካሪ “Women” በተባለ መፅሐፏ ‹‹ፍሮይድ -- ሴት ምንድነው የምትፈልገው? -- የሚለው ጥያቄው ወንዱን ብቻ ሳይሆን ሴቷ ራሷ መልስ ያጣችለት ነው፡፡ (Freud’s question – What do women want – frustrates men, It also frustrates women)›› በማለት ትገልጻለች፡፡

ብዙዎቻችን ሴቶች ባላችን ወይም ምን እንዲያደርግልን ከመፈለጋችን በፊት እኛ የምንፈልገውን ቀድመን ማወቅ ይጠበቅብናል፡፡ ሚስቶች ከባሎቻችን የምንፈልገው ነገር ብዙ ነው፡፡ ነገር ግን የምንፈልገውን ነገር በግልጽ አናውቀውም፡፡ ባሎችም ሚስቶቻቸው ምን እንደሚፈልጉ አለማወቅ ብቻ ሳይሆን የሚስቶቻቸው ፍላጎት በየጊዜው የሚለዋወጥ በመሆኑ ግራ ተጋብተዋል፡፡ ሴት የራሷን አካላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ስሜታዊ እና ሌላም ፍላጎቷን ለይታ ካላወቀች እንዴት ብሎ ነው ባሏ ፍላጎቷን ሊያሟላ የሚችለው? ብዙዎቻችን ሴቶች ለይተን ባላወቅነው ፍላጎታችን ወንዶችን ተጠያቂ እናደርጋለን፡፡

ግራ የሚያጋባ ነዉ.....
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ለአንዲት ሴት በተለይ “ቆንጆ ሴት” ነን ብለን ለምናስብ ሴቶች ፣ አቅማችንን እንዳንጠቀም እስር ቤት የሚሆንብን የራሳችን ቁንጅና ነው፡፡ የራሳችን ቆዳ የራሳችን እስር ቤት ነው፡፡
በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ  ‘ሴትነት እና ቁንጅና’ የሚባል እስር ቤት ፍርግርጋችንን እያስዋብን ተሟሙቀን የወንዶችን ጭብጨባና አድናቆት እየጠበቅን እንድንኖር ሆነናል፡፡ ሁሉም እስር ሰንሰለቱ ፈጦ አይታይም….. እንደውም አንዳንዱ እስራት ለታሳሪው ለራሱ ጭምር አይታይም፡፡ ማኅበረሰቡ አንዲትን ሴት “የብረት መዝጊያ የሚሆን አማች የምታመጣ እንጂ፣ የብረት መዝጊያ መሆን የምትችል አድርጎ አያስብም፡፡ ስለዚህ የእነሱን የምኞት በር የሚዘጋ የብረት መዝጊያ ለማምጣት፣ አንዲት ሴት ዓይኗንም አእምሯዋንም ሳይሆን እግሯን እንድትከፍት ከሕፃንነቷ  ጀምሮ ሲያዘጋጃት ይኖራል ”
”እግር የተፈጠረበት የመጀመሪያ ዓላማው መራመድ ነው፤ ለሴት ልጅ ግን ከመራመድ በላይ እግር ውበት እንደሆነ እንድታስብ በሥነጽሑፉ፣ በፊለሙ አእምሮዋ ውስጥ ሲታጨቅባት ኖሯል፡፡ ከመራመዷ በላይ የአረማመዷን እና የእግሯን ውበት እንድታስብ ስትሰበክ ኖራልች፡፡ ለዚያም ነው ከፊታቸው የተነጠፈውን እሾህም ይሁን ጠጠር ረግጠውና ዋጋ ከፍለው ወዳሰቡበት ከሚራመዱ ሴቶች ይልቅ፤ ከየትም ባገኙአት ሳንቲም በየውበት ሳሎኑ ተጎልተው፣ እግራቸውን የጥፍር ቀለም ሲያስቀቡና ተረከዛቸውን ሲያስፈገፍጉ የሚውሉ ዘመነኞች የሚበዙት፡፡ እግራቸውን ከለሰለሰ በኃላ፣ አዝሎ የሚያሻግር ወንድ ሲጠብቁ ቁጭ ብለው ይኖራሉ፡፡
እጅ የተፈጠረበት የመጀመሪያ ዓላማው መሥራት ነው፡፡ ብዙ የፋሽን እና ዘመናዊውን የውበት ሚዛን የሚደፉ ’ዘመናዊ’ ሴቶች፣ እጃቸው ከሚበላሽ ስማቸውም ሕይወታቸውም ቢበላሽ እና እጃቸው እንደለሰለሰ ቢኖር ይመርጣሉ፡፡ በልስላሴ ሳይሆን በንጽሕናና ራስን ችሎ በመቆም እንጨባበጥ ከተባለ ማን ናት ደፍራ እጇን የምትዘረጋ?! ለብዙኃኑ ወንዶች ጠንካራ የሴት እጅ ሀገርን ያቆመ ሳይሆን፣ ሴትነትን የገፋ መስሎ ነው የሚታያቸው፡፡ ለዚያ ነው በሥራ ስለደደረ የሴት መዳፍ፣ ዘፋኙም መዝፈን፣ ገጣሚውም መግጠመ የማይወደው፡፡ ድንጋይ ፈልፍሎ እና እምነበረድ ጠርቦ ውብ የእጅ ጣት ያላት ሴት ሐውልት የሚያቆመውን ቀራጺ እጅ ግን ተመልከተው፣ በሥራ የጎለደፈ ሆኖ ታገኘዋለህ፡፡ ከግማሽ በላይ የሚሆነው ሕዝብ ሴት በሆነበት አገር፣ ሴቶች እጃቸውን አስውበው መደርደሪያ ላይ እንዲያስቀምጡ በማድረግ፣ ለውጥ ጠብ አይልም፤ እንዲሰሩ….. ማደፋፈር….እጅ ወደተፈጠረበት የመጀመሪያ ዓላማ እንዲመለስ መሰበክ አለበት፡፡
                                                                                                                                                                                            
ከእለታት ግማሽ ቀን; ገጽ 182-183
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አዎ ! እሱ ጋ ያመኛል መጽሐፍን ዉስጥ አንዳንድ ሀሳቦች ፦
___

➫ ሁልጊዜ እሮሮ የሚዘበዝቡ፣ ሁልጊዜ ሰው ማጣጣል ላይ የተመሰጡ ሰዎች፣ ሁልጊዜም አልተሳካልን ዓይነት ደረት የሚመቱ፤ ለውድቀታቸው ሰው የሚወቅሱ ሰዎች፣ ለመውደቃቸው ኃላፊነት ከማይወስዱ ጋ አትወዳጅ ” ( ገጽ 17 )

➫ ደካማነት ምቹ ስፍራ ሲያገኝ እና ጊዜ ሲደላደልለት የሚያብብ ደዌ ነው። ( ገጽ 25 )

➫ መልካም አድራጎት የሚገዝፈው መልካም አድራጊው በየሰበቡ ካልፎከረበት ነው። ( ገጽ 28 )

➫ ወደ በጎ መለወጥ ብዙ ጠመዝማዛ መንገድ አለው። እንደ መበላሸት ቀላል አይደለም። ( 31 )

➫ አንዳንድ ትናንት ትናንት ላይ ብቻ አይቆምም። ዛሬያችንን የፈለገ ከትናንት አርቀን ሰቅለነዋል ብንል ፣ ጥለነው ብዙ መጥተናል ያልነው ትንናት ነጋችን ላይ በሁለት እግሩ ቆሞ እናገኘዋለን። ( ገጽ 49 )

ፍቅር ማለት ለሚያፈቅሩት ሲሉ ከማይችሉት ጋ መታገል እንጂ የሚያሸንፉትን ማሸማቀቅ አይደለም። ( ገጽ 59 )

➫ ከአማኝ ጥቅማጥቅማችን አንደኛው ከአቅማችን በላይ የሆነ ሁነት ሲጋረጥብን ፈጣሪ ላይ ሙጥኝ ማለት አይደል ?” ( ገጽ 65 )


➫ ለራስ ሰው አለመድረስን ያህል አርፋጅነት የለም። ( ገጽ 70 )

➫ ሴት ልጅ ትታለልልሃለች እንጂ አታታልላትም። ( 72 )


➫ ፍቅራችን ለምናፈቅራቸው እንድንጠነቀቅ ካላደረገን ፍቅራችን የእውነት ላለመሆኑ ምስክር ነው። ( 95 )

➫ ሰው በዕድሜ ብዛት ማስተዋል ከቻለ የሚማረው ነገር አለመፍረድን ነው። ( 96 )

➫ የበዳይን ምክንያት ሳንጠይቅ በደልን ከምንጩ ማድረቅ እንዴት ይቻላል ?” ( 99 )

➫ ችግራችንን የምናይበት መንገድ የገዘፈ ስለሆነ ነው ከችግራችን በታች የምንሆነው። ( 104 )

➫ በአለም ላይ ስሜቱን እንደሚከተል ሰነፍ የለም፤ ስሜቱን ብቻ መከተል የሰው ባሕሪ አይደለም፡፡ ከስሜት እውነት ይበልጣል ፣ እውነት ነው በጊዜ ብዛት የማይደበዝዘው ፣ ስሜት ዘለቄታዊ ደስታን አይፈጥርም። ማደግ ማለት ደግሞ እውነትን እየመረረንም ቢሆን የመዋጥ ክህሎትን የማዳበር ሂደት ነው። ( 118 )

➫ አሸናፊነት የሚመጣው ተጋጣሚ የሚፈልገውን ባለመስጠት ነው። የምንፈልገውን የምናገኘው እራሳችንን ከምንፈልገው ነገር ባለማሳነስ ነው። ( ገጽ 130 )

➫ ራስን የመሆን እና ራስን የማወቅ ጥግ ራስን መቀበል ነው። በዙሪያችን ያሉ ሰዎች እንዲቀበሉን እኛ ቀድመን ራሳችን መቀበል አለብን። ደካማ ሰው ነው ድክመት ላይ የሚመሰጠው ፣ በራሱ የማይተማመን ፣ እንከኑ የሚያሳቅቀው ነው ጉድለት የሚያስሰው። የማይለወጥ ነገርን መቀበል ከራስ ጋ ያዋሕዳል። ያየነውን ጥሩ ነገር በትክክለኛው ሰዓት ማንፀባረቅ በራስ መተማመን ይባላል። በራሳቸው የማይተማመኑ ሰው ማሳነስ ላይ ሲረማመዱ የሚውሉ ናቸው። ( ገጽ 130 )

➫ ማደጋችን የሚለካው የምንፈልገውን ሁሉ ባለማድረግ ነው። ( ገጽ 155 )

➫ ሕመማችን የሚባባሰው የበሽታችን ምክንያቶች እናክምህ ሲሉን አይደል ?” ወዳጃችን ሲያቆስለን ሕመማችን የሚበረታው እንደሚያስብልን ማስመሰሉ ስለማይቀር ነው። ( 155 )

➫ ባልተሳተፍንበት ነገር መስዋዕት የመሆን ያህል ከንቱነት የለም !! ( ገጽ 157 )

➫ ተገማች አለመሆን ዓላማን ለማሳካት ምቹ ነው። ( 162 )

➫ ከተበደለ የበለጠ ፣ መበደሉ የገባው በዳይ ኑሮው ሲኦል ነው !! ( 165 )
_



⚡️ሁሉ
ም አሪፎች ናቸዉ ይቺ ግን ከሁሉም ትለያለች 👇

➫ ሕመማ
ችን የሚባባሰው የበሽታችን ምክንያቶች እናክምህ ሲሉን አይደል ?” ወዳጃችን ሲያቆስለን ሕመማችን የሚበረታው እንደሚያስብልን ማስመሰሉ ስለማይቀር ነው። ( 155 )

ለእናንተስ???
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቆይ ግን ምንድን ነዉ ነገሩ??🙄
       አሚር ሰይድ

   በቃ መፃፍ መናገር አስጠልቶኝ ሰልችቶኝ ነገሮችን እያየሁ ከአቅም በላይ ሁነዉ ዉስጤ እየተቃጠለ ብዙ ነገሮችን እያለፍኩ እና በቻልኩት አቅም ከሚዲያ ርቄ በተቻለኝ  አቅም በቻልኩት ብቻየን እየሰራሁ ነዉ ግን አንድ እጅ አያጨበጭብም ግን አሁን ዘመን ካለ ሙስሊሞች ጋር የኢንሻ አላህና የአላሁ አክበር ከማለት ዉጭ ወደ ተግባር የማይሄዱ ጋር ከመስራት ብቻ መስራት ይሻላል፡፡

በቃ ለሴት የተጣመመ መጥፎ አመለካከት አለህ ምናምን ስድብ ወቀሳ ሲበዛ ከሚዲያ ራሴን አራኩ ግን በቃ ነገሮች አያስችሉም

ዛሬ ወረረኝ በቃ አለ አይደል በጣም ልቤን የነካኝ በጣም ያሳዘነኝ ነገር ገጠመኝና ለመፃፍ ተገደድኩ፡፡
በጂልባብና በኒቃብ ዙሪያ ከምር ከባድ ነዉ ..ጅልባብ ኒቃብ የሸፈናቸዉ ነገሮች እየከበዱ ትክክለኛ ለባሾችን በኛም በሙስሊሙ ለሌላም ሀይማኖት አያጋለጥናቸዉ ነዉ  እያዮቸዉም ነዉ ፡፡

!!!ሴቶች ሆይ እባካችሁ ከአረብ ሀገር ስትመጡ አትልበሱ በቃ ኢትዮ ኤርፓርት ስደርሱ አዉልቁትና ስታምኑበት ልበሱ...ሴቶች ሆይ ኢማን ይጨምራል ይቀንሳል ኢማናችሁ ሲጨምር ወይም አንድ ሁለት ኪታብ ስትቀሩ ዲኑ የገባችሁ መስሏችሁ ኒቃብ ጅልባብ ለብሳችሁ አላህን የማይፈራ ሴት ጓደኛ ይዛችሁ ወይም የቱርክ ልብስ ወይም በራሳችሁ ሳይዝ አሰፍታችሁ መልበስ ስትፈልጉ ኒቃብን ጅልባብን አታሰድቡ እባካችሁ፡፡ ከለበሱ ቡሀላ ኢስላም ከሚሰደብ እባካችሁ በቃ አዉልቁትና እንደገና የጂልባብ የኒቃብ ትርጉሙ ጥቅሙ ሲገባችሁ ልበሱት፡፡
..,አላህን ፍሩ ማለቱ ከቃላት ማባከን ዉጭ ለዉጥ አላመጣም በቃ አላህን አታስቆጡ ዲነል ኢስላምን አታሰድቡ...ኢስላምን መጥቀም  ባንችል በኛ እንዲሰደብ ለምን እናደርጋለን???

ዛሬ ጁምአ የገጠመኝን ልንገራችሁ
እኔ የምኖርበት ሰፈር ቤተክርስቲያን በቅርብ አለ ጠዋት ስወጣ ብዙ ሙስሊም ሴቶች ፀበል ሲያስጠቅሙ ሲገቡ እኔ ለስራ በጠዋት ነዉ ከቤት የምወጣዉ መቼም መንገድ የማያሳየዉ የለም አያቸዋለሁ፡፡ ጠዋት ጠዋት እየመጡ ሳገኛቸዉ እኔ አረ አላህን ፍሩ በቁርአን መጀመሪያ ሞክሩ የሚሰማ የለም ኢንሻ አላህ ብሎ ከማለፍ ዉጭ.. ግዴታ ማድረስ ስላለብኝ አይቶ ማለፍ ወንጀል ነዉ በቻልነዉ አቅም እናገራለሁ...

ዛሬ ያየሁት ግን በቃ ለአቅል ከበደኝ ሁለት ኒቃብ የለበሱ ሴቶች እኛ ሰፈር ያለ ቤተክርስቲያን እናታቸዉ ወይ ዘመዷን ይሆናል ይዘዉ ሲገቡ አየሁ ደነገጥኩ😧😧...ግን ወደ ቤተክርስቲያኑ ሲገቡ እዛ የነበሩ ሰዎች ስልካቸዉን አዉጥተዉ ፎቶ ሲያነሷቸዉ አየሁ   .. ወደ ቤተክርስቲያኑ አልገባ ጁምአ ነበር ጀለብያ ለብሻለሁ ጀለብያ ለብሼ ብገባ የነዛ ሰዎች ካሜራ ዉስጥ እገባለሁ ምን እንደሚያደርጉ ስለማይታወቅ...እስከምትወጣ ወደ 1 ሰአት ያክል ጠበኩ አልወጡም እኔም ከዛ አካባቢ ተንቀሳቀስኩ ... ዛሬ በአይኔ አየሁ ግን ከአሁን በፊትም ይገባሉ አላገጠምኝ ማለት ነዉ፡፡

እና ምንድን ነዉ ነገሩ???ሊታወቅልኝ የሚገባዉ ጅልባብ ኒቃብን ተቃዉሜ አይደለም ግን በጅልባብና በኒቃብ ጀርባ ብዙ ከኢስላም ያፈነገጡ ነገሮች አሉ... ትክክለኛ ኒቃብ ጅልባብ ለባሽ በነዚህ ፎርጅድ ለባሾች አብረዉ እየተወቀሱ አንገታቸዉን እየደፉ ነዉ፡፡


ከምር ጊዜዉ ከባድ ነዉ ብዙ የማቃቸዉ ወንዶች ኒቃቢስት ጅልባቢስት ነች ብየ አግብቻት እንዲህ እንዲህ ሆን እያሉ ብዙ ነገሮች እየሰማን አሁን ዘመን ላይም እያየን ነው...ያኒቃምን የጅልባብን  ትርጉሙን ሳያቁት የሚለብሱትም ግራ እየተጋባን ነዉ፡፡

አሁን ላይ እሷ ሷሊህ ነች ኢማን አላት ወይም ኢማን አለዉ ማለት ይከብዳል .. አፍ ሞልቶ የኔ ልጅ ወይ የኔ እህት እተማመንባታለሁ ማለት ከባድ ነዉ....እኔ እንደሚመስለኝ
ኢማን የሴት ልጅ..ሷሊህ የወንድ ስም ነዉ ወዳጄ🙄..እከሌ ኢማነኛ እሱ ሷሊህ ነዉ ማለት የማይቻልበት ዘመን ላይ ነን ..
ሷሊሀ ነች ሳይሆን በግልባጩ ጧሊሀ የሆነበት ተጨባጭ እያየን ነዉ፡፡


አሁን ሴቱ እሁድ ተጋብቶ ከወር ቡሀላ ብትፈታ ችግር የለባትም
ሀሳባቸዉ ብራይድ ሰርግ እንጂ ነገን ከነገ ወዳስ ትዳር ላይ እንዴት ነዉ ብለዉ ብዙዎች አያስቡም በተለይ ከ22 አመት በታች የሆነች ሴት፡፡
የሴት ኢማኗ የሚለካዉ ሰርጓ አካባቢ ነዉ በፊት ጅልባብ ለባሽ ኒቃብ ናቸዉ የተባሉት ለሰርጋቸዉ ኢማናቸዉ እንደ ወራጅ ወንዝ ወደ ታች ይፈሳል ልባቸዉ ላይ አይረጋም፡፡

የአማረኛ የቱርክ ፊልም እያዩ  በኑሮ ዉድነት እዳዉን ያየ ወንድ ሰርፕራይዝ ምናምን ነዉ ሀሳባቸዉ እንጂ ትዳሬ የምትል ሴት እንጃ እየጠፋች ነዉ፡፡ ወንዱም በሴቱ ባህሪ ማግባት ባለመቻሉ ዝሙት ላይ እየወደቀ ነዉ

⚡️ አንድ ነገር ሴቶች ላስታዉሳችሁ ነገሮች አሁን ወንድን ልትረዱ አልቻላችሁም  የኑሮ ዉድነት
የክርስቲያን ወንድ በ6000 ደመወዙ ማግባት ይችላል፡፡ የሙስሊም ወንድ ግን ከሴቱ ፍላጎት አንፃር 12,000 ደመወዝ ይዞ ማግባት አይችልም፡፡
በነገራችን ላይ ፍቅር ወንድም ሴትም እወዳታለሁ እወደዋለሁ እንጂ ይወደኛል ትወደኛለች ማለት ራስን ማሞኘት ነዉ፡፡ብዙ ያፈቀረ ሰዉ በህይወትህ ምን ተሳስተሀል ቢባል ማፍቀሬ ነዉ የሚለዉ ፍቅር እወዳታለሁ እወደዋለሁ በሉ እንጂ ይወደኛል ትወደኛለች ብላችሁ ራሳችሁን አታሳምኑ በራሳችሁ ብቻ እርግጠኛ ሁኑ....

⚡️⚡️ በተጨማሪ በዚህ 3ወር ዉስጥ Hiv positive የሆኑትን ትዳር ለማገናኘት በሚል ከእነሱ ጋር እየሰራሁ ወላሂ ከባድ ጊዜ ላይ ነዉ ያለነዉ...
አዲስ አበባ,ደሴ,ባህርዳር,ጎንደር,ጅማ,ድሬድዋ,አፋር ክልል,ኦሮሚያ ክልል
ወዘተ ከተማ ላይ ከተለያዩ ሙስሊሞች ነርሶች ጋር ለማገናኘት ጥረን ነበር፡፡
ከባድ ነዉ የሰማሁት ለአቅል የሚከብድ ነዉ
አዲስ አበባ ሆስፒታሎች ደሴ የተለያዩ ከተሞች ላይ ያሉት በብዛት ከወንድ ብዙ እጥፍ ሴቶች ናቸዉ፡፡

አዲስ አበባ የሚያገናኝ ጀመአ ነበሩ እነሱን ስጠይቅ እንኳን Hiv pos ወንድ ኖርማል ወንድ ሴቶችን ለማገናኘት ጀምረን ለትዳር ዝግጁ የሆነ ወንድ አጣን ነዉ ያሉኝ...አሁን አቋም ያለዉ ወንድ የለም የሚያጮልቅ የሚያደባ እንጂ ሴቱ በምላስ ፍቅር ተተብትቧል ግን መቼ ድረስ???

አሁን በተለይ ሴቶች hiv pos የሆኑ እኔ እንኳ አሁን ለማገናኘት የማቃቸዉ ብዛትና ከተለያዩ ሆስፒታሎች ያገኘሁት መረጃ አለቅል ስለሚከብድ ዝምታ ይሻላል..አሏህ ለነዚህ ሴት እህቶች ይድረስላቸዉ፡፡ የሚገርመዉ ብዙ hiv pos ወንድ ወጣት ገና ከ16-25 እድሜ ያለዉ ይበዛል እነሱ የሚሉት አቅም የለንም ነዉ፡፡ ደግሞ አቅም አለን የሚሉት ስናገናኝ 1ሳምንት አዉርተዉ  ስልካቸዉን ጥፍት በቃ ለምን በሴት ልብ እንጫወታለን???
Hiv pos የሆኖት ብቻ ሳይሆን ወንድ ሆይ!!! የትዳር process አገባሻለሁ እያልክ እድሜ ህልሟን ተስፋዋን አታጨልምባት ተስፋ አትስጥ ቶሎ ወስኑ ቀልብ አንስበር

ነገሮችን ስናጠና ወንዶች hiv ሲገኝባቸዉ ራሳቸዉን እየደበቁ በዚና ሴቶችን እያስያዙ እያገቡ እንደሆነ 90% እርግጥ ሁኗል፡፡👇👇
2024/09/21 07:28:20
Back to Top
HTML Embed Code: