Telegram Web Link
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሙነሺዶች

ዘንቦል ዘንጠል ዘንፈል ዘንፈልፈል ወዝወዝ ሲሉ 🙃 አጃቢዎቹንም ተመልከቱ ፌመስ ለመሆን ጥረትና ዉጥረት...

ቆይ ግን እሽክምክም እሽክምክም እያለች ከምዘፍነዉ ዘፋኝ በምን ተለዩ🙄



የሚገርመዉ ዘንድሮ ሙነሺዶች ብዙዎቹ በረመዳን መካ ኡምራ አድርገዋል...በአዳማጩ በyoutube ብር አግኝተዉ መካ አሳለፉ...
አዳማጩ ግን ቁርአን መሸምደድ መቅራት ዚክር ማድረገዉ ትተዉ በተለይ ሴቱ ወይኔ ድምፁ ሲያምር የእሱን ድምፅ ሳልሰማ መዋል ከብዶኛል😇 ብለዉ የእነሱን ድምፅ ካልሰሙ ራሳቸዉን የሚያማቸዉ የሚያቃዣቸዉም አሉ... አንዳንድም የምታለቅስ አለች

ሀያቴን ለርሶ ብያለሁ ጀባ ይሉሀል ይሄ ጀመአ🙂
ተመልከቱ ካሜራ ማን

የሙስሊም ሴቶች ለእስልምና መስራት አለባቸዉ በሁሉም ነገር ሴት መጨቆን የለባትም ይሉሀል
ድንበር ያለፈ ለሴት ልጅ መቆርቆር መምሰል መጨረሻዉ ዉጤቱ ይሄ ነዉ......

አጂ ነብይ ጋር በዲን ስም አብሮ መሆን...
በአላህ መንገድ ሲታገል ከርሞ ወደ አንደሉስ ምድር መናገሻ ከተማ ኮርዶቫ ሲዘልቅ ዕለቱ ዒድ ጠዋት ነበር። ሰራዊቱ በፈረሶቻቸው ላይ ተፈናጠው በድካም የሚንጠፈጠፈውን ላባቸውን ከግንባራቸው ላይ እየጠራረጉ አቧራ ባጨማለቀው ልብሳቸው ኢድ ወደ ሚሰገድበት ሜዳ በማቅናት ላይ ሳሉ ነበር አንዲት እድሜዋ የገፋ አዛውንት ከሡልጣን መንሱር ፊት ቆማ የፈረሱን ልጓም ይዛ ከመንገዱ በማስተጓጎል እንዲህ ያለችው:-


"በዛሬው የዒድ ቀን ከእኔ በቀር ሁሉም ሙስሊሞች ደስተኞች ናቸው"
ሐጂብ መንሱር ንግግሯን ሲሰማ ደነገጠ "ለምን?" ሲልም ጠየቀ።
ዕንባ ባቀረረው ዓይኗ እየተመለከተችው እንዲህ አለችው "በረባህ ምሽግ ከመስቀል ጦረኞች ጋር ሲፋለም የተማረከ አንድ ፍሬ ሙጃሂድ ልጅ አለኝ እሱ በጠላት እስር ቤት ውስጥ ሆኖ እንዴት መደሰት ይቻለኛል?"

ዘመኑ 380 ዓመተ ሂጅራ ግዛቶች በሐጂብ አል መንሱር ይተዳደሩ ነበር። የአንደሉስ ኢስላማዊ መንግስት በጥንካሬና በከፍታ ማማ ላይ የደረሰበት ወርቃማ ዘመን! የፉቱሐትና የዘመቻ የፍትህና የእኩልነት ጊዜ!

   ሐጂብ ንግግሯን ሲሰማ በፍጥነት ፊቱን ወደሠራዊቱ አዞረ። የፈረሱን ልጓም አጥብቆ ያዘና በጂሃድ ሜዳ የአፈር ትቢያውን ገና ላላራገፈው ሙጃሂድ፣ ከድካም ጀርባውን ላላሳረፈው ሠራዊት እንዲህ ሲል ትዕዛዙን አስተላለፈ "ከፈረሳችሁ ጀርባ እንዳትወርዱ" አለ።

   የፈረሱን ልጓም እየጎተተ ጀርባው ላይ እንደተፈናጠጠ ወደ ረባህ ምሽግ ሰራዊቱን ይዞ ገሰገሰ። የአሮጊቷን ልጅ ጨምሮ ሙስሊም እስረኞችን አስፈትቶ ከተማዋን በድል ከፍቶ ወደ አንደሉስ ምድር ተመለሰ።

ይህ ስለኢስላም መስራት በማንደክምበት ዕለት የተከሰተ የጀግንነት ታሪካችን ነው።


ለሁላችሁም ኢድ ሙባረክ ብያለሁ
ረመዷን እስኪወጣ ሣይሆን ሩሕ እስኪወጣ ጌታችንን የምንታዘዝ ያድርገን....ከረመዷን በፊት ወደነበርንበት አመፅና ወንጀል የማንመለስ ያርገን
....ረመዷን እስኪወጣ ሣይሆን  ሩሀችን   እስኪወጣ ጌታችንን የምንታዘዝ ያድርገን ያረብ

የቻናል ቤተሰቦች መልካም በአል ተመኘሁ❤️
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ልብሽን ምክንያት እየሰጠሽ አታድክሚዉ
ዩምና ሙሀመድ

እራስሽን ልክ እንደ ሙሳ ቀይ ባህር መሀል ላይ አኑሪው ከጀርባሽ ፊርአውንን እሚያክል ጠላት ወይ ችግር አለብሽ ከበላይሽ የተሰነጠቀ ባህር እሚያክል አንቺ ላይ ሊደርስ እሚችል ችግሮች ተከምረው ታይተውሻል ወደ ጎን አትይም መካከል ላይ ነሽ ብቻሽን አይደለሽም በአንቺ ስር ያሉ የብዙዎችን ህይወት ከአላህ በታች ይዘሻል ....ልክ ሙሳ ተከታዮቹን እንደያዘው ነፍሴን ብቻ አይልም ነፍሳችንን እንጂ ከእራሱ ሩህ በላይ እሚያስጨንቀው የተከታዮቹን ነገር ነው ምናልባትም አንቺ የብዙ ሀላፊነት ባለቤት ሆነሽ ይሆናል፡፡

ታዲያ ሙሳ ከባህሩ አልወጡምን? በየትኛው መንገድ? ከፊት ለፊታቸው በምትታያቸው አንድ መንገድ ያቺን መንገድ እስኪያገኟት ድረስ ወደ ሗላ አልዞሩም ወደ ሗላ ችግራቸው ነው ያለው ፊት ለፊታቸው ግን ነፃነት ከብዙ የነፍሶች ሀላፊነት ማረፍ ሀቀኝነትን ብቻ ቡዙ ተአምሮችን ይዟል ያቺ የታየቻቸውን መንገድ በጀሊሉ ፍቃድ ደረሱባት ዞር ብለው ወደ ችግሮቻቸው ሲያዩ ግን ቢወርድ ሊያጠፋቸው እሚችለው ባህር ሲከተላቸው የነበረውን ችግር ድምጥማጡን አጠፋላቸው

አንቺም ያሉብሽን ችግር እስክታልፊያቸው ዞረሽ አትመልከቻቸው ይደርሱብኛል እምትያቸው ችግሮችሽ ምናልባት የደረሱብሽን ችግሮች ማጥፊያ ናቸው ፡፡ መውጫሽን ተመልከቺ ግን ስለሁሉም ጌታሽን አጥብቀሽ ያዢው በእሱ ያለሽ እምነት ከልብሽ አድርጊው የተፃፈልሽ ሙሲባ በሙሉ ሊስትሽ አልነበረም የሳተሽ በሙሉ ሊያገኝሽ አልነበረም ልብሽን ምክኒያት እየሰጠሽ አታድክሚው

☞ አንቺ ማለት ሳትጠይቂው ለእሱ ባሪያው እንድትሆኚ የፈጠረሽ ባሪያው ነሽ
☞አንቺ ማለት ከስንት ሚሊዮን እህት እና ወንድሞችሽ ተመርጠሽ የተፈጠርሽ ፍጡር ነሽ
☞አንቺ ማለት በዱንያው እሳት ፈትኖሽ እንደ ወርቅ ሊያስከብርሽ ሊያስወድድሽ እሚያደርግ ጌታ ነው ያለሽ

>>> እናም ያኡኽታ ረህማኑን አጥብቂው የተጣበቀብሽ ይለቅሻል
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አሁንስ አትገረሚም???
ዩምና ሙሀመድ

ምን ያስገርመኛል መሰለሽ ሁሌ የረህማኑን አዛኝነት እኔ የእሱ ባሪያው እንድሆን የመሻቱ ስፋት በእኔ  መታወስ የፍላጎቱን ጥግ አስተውለሽው ይሁን?
እኔ ባላስታውሰው እኮ ሚጎድልበት ነገር የለም እሱ እኮ ስንት እሚዋደቁለት ባሪያዎች አሉት እሱ እኮ ምድር ላይ ያለች ትንሿ ጠጠር ሳትቀር የፈጠረ ጌታ እኔን ማስታወሱ አይገርምሽም?

^ ቢተወኝስ ቆይ ሲጀመር ባይፈጥረኝስ ስንት እህት እና ወንድሞቼን እናቴ ሆድ ውስጥ ባክነው እኔ መፈጠሬ ስለወደደኝም አይደለምን?
ታዲያ አይደለም የወደደኝ ጌታ የወደደኝ ሰው እኔ ላይ መብት የለውም እንዴ?
ምሳሌ ላንሳልሽ ምድር ላይ በጣም በጣም ከሚሳሱልኝ ሰዎች ውስጥ ከእናቴ ወይ ከአባቴ በላይ ፍጥረት የለም እኮ አይደል!! 
እስኪ ልጅኘታችንን ዞረሽ እይው ልጅ ናቸው በሚል ሀላፊነት የሚባል አልነበረብንም ሀላፊነት መውሰድን በትንሽ በትንሹ እንድንማር አደረጉን
አላሄዋም እስከ 15 አመት ወይም እራሳችንን እስክናውቅ ነፃነት ሰጠን ምንም ቅጣት እንደሌለብን አሳወቀን ለቤተሰቦቻችን ግን የኛን የመኮትኮት ሀላፊነት ሰጣቸው  አትገረሚም!!


.....ቡሗላ እንዳንደክም ግራ እንዳንጋባ እኮ ነው ከዛማ ልክ ስናድግ ቤተሰቦቻችን ለማስደሰት ውለታቸውን ለመመለስ እያልን ሀላፊነት እንዳለብን ሁላ ከእልጅነት እስከእውቀት  የለፉብንን  ለመመለስ ስንል እኛ ላይ መብት አላቸው እያልን እነሱን ለማስደሰት መብታቸውን ለመጠበቅ ደፋ ቀና እንላለን ታዲያ ያኡኽታ ይሄንን ሁላ ነገር አንቺ ካለነበርሽበት አስገኝቶ ጭራሽ እማያውቁሽ እማታውቂያቸውን ፍጡሮች እናት እና አባት ያውም ከእዝነት ጋር የለገሰሽ ጌታ አንቺ ላይ መብት የለውምን?

>>>>> ብርጭቆ ስትሰብሪ ሁላ እኮ እናትሽ ወይ ትቆጣሻለች ወይ ትመታሻለች እና ስለምን ሲባል የፈጠረሽ ጌታ በነገሮች ሲቆነጥጥሽ ቢጠላኝ ነው አስባለሽ?ምን ባደርገው ነው እያልሽ ከእሱ ጋር ግብግብ አስፈጠረሽ?

^^ደሞ እኮ በተከበረው ቃሉ ሲፈትንሽ እያላቀሽ  ስለመሆኑ አማኝ ስለመሆንሽ እንዲህ እያለ ነግሮሻል "አሊፍ ላም ሚም አሀሲበናሱ አዩትረኩ አመና ፈሁም ላዩፍተኑን"
^የሰው ልጆች አምነናል ካሉ ቡሗላ እንፈተናለን ብለው አላሰቡንም አልገመቱምን^ ይለናል አየሽልኝ ኡኽታ በእሱ ስለማመኔ ማመልከቻው ወይ ደሞ መለያው በሚያመጣልኝ ነገር መታገሴ ነው::
* ለትምህርት ፈተና ስል ስንቴ አነባለው ለሊት አዳር እያነጋሁኝ  እየተጨነኩኝ ካለፋሁኝ እንደምወድቅ አውቃለዋ ከወደኩኝ ደሞ ያኔ ለቤተሰቦቼ ተገቢውን ምላሽ አልሰጠሁም ማለት ነው የት ት ፈተናውን ማለፌ
ከእኔ በላይ ቤተሰቦቼ ያስደስታቸዋል አላሄዋም ሲሞክረኝ ወደእሱ እንድቀርብ አጥብቆ ይሻብኛል::

>>>>>አስተውዪማ የሆነ መስሪያ ቤት እራስሽን አስቀጥረሽ ሳዩው ከዛማ አሰሪሽ አንቺን ይወድሻል ሊያጣሽ አይፈልግም እንድትቀርቢው ይፈልጋል ምን እሚያደርግሽ ይመስልሻል?
በጣም ከምትፈልጊው እሱ ጋር ካለ ነገር ይቀንስብሻል ወይም ያስቀርብሻል ለምሳሌ ደሞዝሽን ግማሹን ወይም እሩቡን እሱ ጋር አስቀርቶ ቀሪውን ቢሰጥሽ እመኚኝ ቀሪውን ደሞዝሽ ፍለጋ አሰሪሽ ቢሮ ትመላለሻለሽ አሰሪሽም እሱ እሚፈልጋትን ሴት እስክትሆኚለት በመመላለስሽ እርካታን አግኝቶ ይቀመጣል::
____አላሄዋም ከአሰሪሽ በላይ ላንቺ እሚያስፈልግሽን ነገር ሲነጥቅሽ መርጦሽ ነው ወደእሱ እራስሽን እንድታዞሪ እየጠየቀሽ ነው ግን እኛ መመረጥን እምናውቀው ሁላ አይመስለኝም::
*ደሞ እኮ አያቆምም በቃ ተስፋ ቆርጫለው የፈጠረኝንም አስከፍቻለው ብለን ስናስብ እንዲህም አይደል የሚለን
"ቁል ያኢባዲየለዚነ አስረፋ አላ አንፉሲሂም ላተቅነጡ ሚን ራህመቲላህ ኢነላሀ ገፉሩን ረሂም"
(እናንተ በነፍሶቻቹ ላይ ድንበር ያለፋቹ ባሪያዎቼ ሆይ በአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡ አላህኮ አዛኝና ማሀሪ ነው)
  ይለናል እሺ አሁንስ አትገረሚም?



አምፀነውም ወዶን በሞከረን ነገር ላይም እንዴት ብለን የእሱን መብት ለእራሳችን ሰጥተንበትም አሁንም ኑኑኑኑ ቅረቡኝ እያለን እኮ ነው::  ከእዝነቱ እንዳንሸሽ ይነግረናል ምን ያክል ለእኛ ቅርብ እንደሆነ ያሳውቀናል የእሱ እዝነት ትልቅ ስለመሆኑ ከእዝነቱ ያሻንን እንደምንወስድ እየወስድንም እንደሆነ
"ወኢን ተኡዱ ኒእመላሂ ፈላቱአዱሀ"
(የአላህን ፀጋ ብትቆጥሩት አትዘልቁትም)እያለ ያበስረናል በሰፊው እዝነቱ እንደምንኖር ስለምን በእዝነቱ እና በፀጋው ተከበን ተስፋን እንቆርጣለን አንቺዬ?
^መለስ አድርጎ ደሞ ፈተናዎቹ ብቻቸውን እንዳልመጡ ነገራቶች ሁላ መሞከሪያዎች ከእዛም ብርሀናዊ ፀጋዎች ስለመሆናተው እንዲህ ይለናል አይደል "ፈኢነማአል ኡስሪ ዩስራ" (በእርግጥም ከችግር ቡሓላ ምቾት አለ)
ብሎ ከፀጋዎቹ ውስጥ የሆነኛውን ይገልፅልናል እናም ኡኽታ ጨንቆሻል ከፍቶሻል ወይ የሆነ ይሳካልኛል ያልሽው ነገር አለመሳካቱ አዘንብሎብሻል ተሳሰቢውማ ተነሺና ውዱእ አድርገሽ መስገጃሽ ላይ ተደፍተሽ ማድረግ እየፈለግሽ ይቺን ትልቋን ነፍሲያሽን አሸንፈሽ ለአላሄዋ ብለሽ በተወሽው ነገር ተሳሰቢው ያኔ ግን ለእሱ ብለሽ የተወሽው ነገር ካጣሽ ቀድመሽ ነፍስሽን ተሳሰቢያት
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አሰላሙ አለይኩም ፉአድ ሙና ኢፋዳ የሚል መፅሀፍ አዘጋጅቶ ገበያ ላይ ከኢድ ጀምሮ ለአንባቢዎች አድርሷል፡፡ ሙስሊም ፀሀፊዎችን ማበረታታት ለወደፊት ለሚሰሩት ስራ ሞራል መስጠት ነዉ፡፡ እኔ ይሄን መፅሀፍ የገዛሁት ገበያ ላይ እንደዋላ order ሲደረግ በኢዱ ቀን ነበር...ይሄዉ ትናንት ደሴ መጥቶ ተረከብኩ፡፡
ማንበብ ጀምሪያለሁ፡፡
እናም ፉአድ ሙናን ማጠናከር ማበረታታት አለብን፡፡ አዲስ አበባም በክልል ከተሞችም
ስለተሰራጨ መፅሀፉን በመግዛት ከጎንህ ነን ልንለበዉ ይገባል

ክፍለ ሀገሮች ኢፋዳን በተጠቀሱት አድራሻዎች ማግኘት ትችላላችሁ።

ኢፋዳን በክልል ከተሞች!
.
★ወራቤ
ወራቤ ከቴሌ ጎን(ፓርክ ሆቴል ፊትለፊት) አቅሷ የኪታብ መሸጫ መደብር

★ሀዋሳ
ሀዋሳ ፒያሳ ኬርአውድ ሆቴል ፊትለፊት ሁሴን ሞል ሳኒ ሞባይል አክሰሰሪ ሱቅ ቁ.29

★ጅማ
ጅማ +251944842429 በመደወል ማግኘት ትችላላችሁ።

★ደሴ
ደሴ +251982674095 በመደወል ማግኘት ትችላላችሁ።

★አዳማ
ፖስታ ቤት ወደ ፒኮክ በሚወስደው አስፓልት በኩል አቢሲኒያ ባንክ አጠገብ አሰብ አዳማ የገበያ ማዕከል መግቢያ ላይ በሚገኘው ፖስታ ስቴሽነሪ

★ድሬዳዋ
ድሬዳዋ አሸዋ በሚገኘው ሲትራ ሱፐርማርኬት
ቦታው ከጠፋችሁ+251929065110 ደውሉ

★ሀረር
ሀረር ሲጋፋ ተራ kim Cafe ፊትለፊት መካ ኤሌክትሮኒክስ
ቦታው ከጠፋችሁ +251968209420 ይደውሉ።
.
#Ifadasales

.
በመሆኑም ቀድማችሁ @ifadasales ላይ ክፍያ የፈፀማችሁ የተላከላችሁን ቁጥር በማሳየት መረከብ የምትችሉ ይሆናል።
በሞባይል ባንኪንግ @ifadasales ላይ መክፈል የማትችሉ በካሽ እየከፈላችሁ መግዛት ትችላላችሁ።
አዲስ አበባ ያላችሁ


አዲስ አበባ ላይ ኢፋዳን ምስሉ ላይ በተጠቀሱት ቦታዎች በመሄድ ይግዙ። በቴሌግራም @ifadasales ላይ ቀድመው ኦርደር ማድረግና ክፍያ መፈፀምም ይችላሉ። ከዚያም ከዚያ የሚሰጥዎትን ቁጥር በማሳየት ብቻ መፅሀፉን ከሚቀርብዎ ቦታ መውሰድ ይችላሉ።

ቀዳሚ አንባቢ ይሁኑ!
.
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ውርጭ ያዘለ ልቤን❤️❤️❤️
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔴ታላቅ የምስራች ተጅዊድን መማር ለምትፈልጉ ተማሪዎች🟡

#ዚክራ_ኦንላይን_የቁርአን_ማእከል_የሁለተኛ #ዙር_ምዝገባ_መጀመራችንን_ስናበስር_በደስታ_ነው
#የሁለት_ወር_ጥቅል_የተጅዊድ_ትምሀርት

🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘
    
            #የትምህርቱ_አሰጣጥ📘📕

1,በዙም አፕልኪሼን
2,በቴሌግራም አፕልኬሽን
🟠🟠🟠🟠🟠
    
        #የቆይታ_ጊዜ 🕙
በሳምንት 3 ቀን
⚫️⚫️⚫️⚫️⚫️⚫️

#ትምህርቱን_ለመከታተል_የሚያስፈልጉ
🔹ዋይፋይ(ፈጣን ኔትወርክ)
🔸ስማርት ስልክ📱💻
🔳🔳🔳🔳🔳🔳🔳🔳🔳

        #ያሉን_ቦታዎች⛺️🛖

##በጀመአ (በግሩፕ)
##vip🏠 (በ ግል)

ከተሟላ በሰርተፍኬት ጋር🔖

በግል ለመመዝገብ
👇👇👇
@redwan6910

ዋትስ አፕ https://chat.whatsapp.com/I6YyupqN1TW8Nzf6DgVZXz

ወደ ተጅዊድ ትምህርት መስጫ ግሩፕ👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/+V3lxqKjWQHxiYzFk

ወደ public group
👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/+-zHkXQeSZdc4MjY0

#zikra_Qur'anic_academy
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በፈረንጆቹ በ1950ዎቹና በ1960ዎቹ አካባቢ የሴት ፍላጎት፣ መብትና ነፃነት አይደለም ሊከበር ቀርቶ አልታሰበም ነበር፡፡ ሴት ልጅ ያገባች ከሆነ የባሏ አገልጋይ፤ ለትዳር ካልደረሰች ደግሞ የእናቷ ረዳት፤  ወግ ሳይደርሳትና ዕድል ሳይገጥማት ሳታገባ ከቆየች ወይም ፈት ከሆነች ደግሞ በማህበረሰቡ የስድብ ናዳ ይወርድባታል፣ ትናቃለች፣ ትገለላች፡፡ ሴት ሆኖ መፈጠር ምን ያህል ከባድ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው፡፡ በአሜሪካ እንኳን እ.ኤ.አ. በ1950 ዓ.ም. የነበረው ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተዘጋጀውን የኑሮ በዘዴ መማሪያ መፅሐፍ (Home Economics text book) ብናይ ያገባች ሴት የባሏን ፍላጎት እንዴት ማሟላት እንዳለባት የሚያስተምርና የሚተነትን ነበር፡፡ ሴት ግዴታዋና ሃላፊነቷ የበዛ ነገር ግን መብትና ነጻነቷ ያነሰ፤ ምንም ምርጫ ያልነበራት እንደነበረች እናቶቻችንን ማየት በቂ ነው፡፡

ያም ሆነ ይህ በዘመናችን ያለችው ሴት በእናቶቻችን ዘመን ከነበሩት ሴት በብዙ መልኩ ትለያለች፡፡ ትናንት ፍላጎቷ የማይከበርላት፤ ዛሬ በአንድም በሌላም መንገድ ፍላጎቷ ይከበርላት ዘንድ አቅምና ጊዜ አግኝታለች፡፡ የዘመናችን አንገብጋቢውና አሳሳቢው ጉዳይ ግን ሴቶቹ ራሳችን የምንፈልገውን ነገር አለማወቃችን ነው፡፡ ራሳችንን አለማወቃችን የወንዶች ብያኔ ተጠቂ እንድንሆን አድርጎናል፡፡ ለጉብዝናችን ወይም ለቁንጅናችን የምስክር ወረቀት የምናገኘው ከወንዶቹ ነው፡፡ በዛም አለ በዚህ የወንዶች ስነልቦና ተጠቂ ሆነናል፡፡ በኢኮኖሚ ራሳችንን እየቻልን ብንመጣም በአስተሳሰብ ግን አሁንም የወንዶች ጥገኛ ነን፡፡ ራሳችንን በምግብ ብቻ ሳይሆን በሃሳብም ካልቻልን ከወንዶች ጭቆና አንተርፍም፡፡

መቼስ ሴትን እንደ እንደስነልቦና ምሁሩ ሲግመንድ ፍሮይድ ያጠናት የለም፡፡ ሰውየው ሴት ልጅ ገና ከልጅነቷ ጀምሮ ምን ዓይነት አስተሳሰብና ባህሪ ሊኖራት እንደሚችል፤ እንዲሁም ትክክለኛ ፍላጎቷ ምን እንደሆነ ለማወቅ የተመራመረ ነው፡፡ ለዚህ ነው ‹‹ሴት የምትፈልገው ምንድነው? What do women want›› በሚለው ጥያቄው የሚታወቀው፡፡

ሴት በሴት መቀናናት ያለ ነው፡፡ የማታስቀናም የማትቀናም ሴት የለችም፡፡ ሴት በወንድ ስትቀና ግን ሊያስገርም ይችላል፡፡ ፍሮይድ ይሄን በተመለከተ አንድ ጥናት ነበረዉ፡፡ ይሄ ጥናት ሴት ገና ከአፍላ እድሜዋ ጀምሮ አጎጠጎጤዎች ስታወጣ፣ የመራቢያ አካሏ እየዳበረ ሲመጣ፣ ለአቅመ ሔዋን ስትደርስና እንደ ወንድ አለመሆኗን ስታውቅ በወንዱ መቅናት ትጀምራለች ይለናል፡፡ መቅናት ከሴት ተፈጥሮ ጋር የተዋሃደ ይመስላል፡፡ ይሄ የስነልቦና ተመራማሪ ስለሴቶች ባህሪ ለማወቅ ብዙ ጥናቶችን ቢያከናውንም ሴቶች ግን እንቆቅልሽ እንደሆኑበት ነው ህይወቱ ያለፈው፡፡ የሚገርመው ሴት ልጅ አይደለም ለወንዱ ለገዛ ራሷ ግራ አጋቢ ፍጥረት መሆኗ ነው፡፡ ኤቭሊን ሌት (Evelyn Leite) የተባለች ታዋቂ የስነልቦና አማካሪ “Women” በተባለ መፅሐፏ ‹‹ፍሮይድ -- ሴት ምንድነው የምትፈልገው? -- የሚለው ጥያቄው ወንዱን ብቻ ሳይሆን ሴቷ ራሷ መልስ ያጣችለት ነው፡፡ (Freud’s question – What do women want – frustrates men, It also frustrates women)›› በማለት ትገልጻለች፡፡

ብዙዎቻችን ሴቶች ባላችን ወይም ምን እንዲያደርግልን ከመፈለጋችን በፊት እኛ የምንፈልገውን ቀድመን ማወቅ ይጠበቅብናል፡፡ ሚስቶች ከባሎቻችን የምንፈልገው ነገር ብዙ ነው፡፡ ነገር ግን የምንፈልገውን ነገር በግልጽ አናውቀውም፡፡ ባሎችም ሚስቶቻቸው ምን እንደሚፈልጉ አለማወቅ ብቻ ሳይሆን የሚስቶቻቸው ፍላጎት በየጊዜው የሚለዋወጥ በመሆኑ ግራ ተጋብተዋል፡፡ ሴት የራሷን አካላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ስሜታዊ እና ሌላም ፍላጎቷን ለይታ ካላወቀች እንዴት ብሎ ነው ባሏ ፍላጎቷን ሊያሟላ የሚችለው? ብዙዎቻችን ሴቶች ለይተን ባላወቅነው ፍላጎታችን ወንዶችን ተጠያቂ እናደርጋለን፡፡

ግራ የሚያጋባ ነዉ.....
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ለአንዲት ሴት በተለይ “ቆንጆ ሴት” ነን ብለን ለምናስብ ሴቶች ፣ አቅማችንን እንዳንጠቀም እስር ቤት የሚሆንብን የራሳችን ቁንጅና ነው፡፡ የራሳችን ቆዳ የራሳችን እስር ቤት ነው፡፡
በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ  ‘ሴትነት እና ቁንጅና’ የሚባል እስር ቤት ፍርግርጋችንን እያስዋብን ተሟሙቀን የወንዶችን ጭብጨባና አድናቆት እየጠበቅን እንድንኖር ሆነናል፡፡ ሁሉም እስር ሰንሰለቱ ፈጦ አይታይም….. እንደውም አንዳንዱ እስራት ለታሳሪው ለራሱ ጭምር አይታይም፡፡ ማኅበረሰቡ አንዲትን ሴት “የብረት መዝጊያ የሚሆን አማች የምታመጣ እንጂ፣ የብረት መዝጊያ መሆን የምትችል አድርጎ አያስብም፡፡ ስለዚህ የእነሱን የምኞት በር የሚዘጋ የብረት መዝጊያ ለማምጣት፣ አንዲት ሴት ዓይኗንም አእምሯዋንም ሳይሆን እግሯን እንድትከፍት ከሕፃንነቷ  ጀምሮ ሲያዘጋጃት ይኖራል ”
”እግር የተፈጠረበት የመጀመሪያ ዓላማው መራመድ ነው፤ ለሴት ልጅ ግን ከመራመድ በላይ እግር ውበት እንደሆነ እንድታስብ በሥነጽሑፉ፣ በፊለሙ አእምሮዋ ውስጥ ሲታጨቅባት ኖሯል፡፡ ከመራመዷ በላይ የአረማመዷን እና የእግሯን ውበት እንድታስብ ስትሰበክ ኖራልች፡፡ ለዚያም ነው ከፊታቸው የተነጠፈውን እሾህም ይሁን ጠጠር ረግጠውና ዋጋ ከፍለው ወዳሰቡበት ከሚራመዱ ሴቶች ይልቅ፤ ከየትም ባገኙአት ሳንቲም በየውበት ሳሎኑ ተጎልተው፣ እግራቸውን የጥፍር ቀለም ሲያስቀቡና ተረከዛቸውን ሲያስፈገፍጉ የሚውሉ ዘመነኞች የሚበዙት፡፡ እግራቸውን ከለሰለሰ በኃላ፣ አዝሎ የሚያሻግር ወንድ ሲጠብቁ ቁጭ ብለው ይኖራሉ፡፡
እጅ የተፈጠረበት የመጀመሪያ ዓላማው መሥራት ነው፡፡ ብዙ የፋሽን እና ዘመናዊውን የውበት ሚዛን የሚደፉ ’ዘመናዊ’ ሴቶች፣ እጃቸው ከሚበላሽ ስማቸውም ሕይወታቸውም ቢበላሽ እና እጃቸው እንደለሰለሰ ቢኖር ይመርጣሉ፡፡ በልስላሴ ሳይሆን በንጽሕናና ራስን ችሎ በመቆም እንጨባበጥ ከተባለ ማን ናት ደፍራ እጇን የምትዘረጋ?! ለብዙኃኑ ወንዶች ጠንካራ የሴት እጅ ሀገርን ያቆመ ሳይሆን፣ ሴትነትን የገፋ መስሎ ነው የሚታያቸው፡፡ ለዚያ ነው በሥራ ስለደደረ የሴት መዳፍ፣ ዘፋኙም መዝፈን፣ ገጣሚውም መግጠመ የማይወደው፡፡ ድንጋይ ፈልፍሎ እና እምነበረድ ጠርቦ ውብ የእጅ ጣት ያላት ሴት ሐውልት የሚያቆመውን ቀራጺ እጅ ግን ተመልከተው፣ በሥራ የጎለደፈ ሆኖ ታገኘዋለህ፡፡ ከግማሽ በላይ የሚሆነው ሕዝብ ሴት በሆነበት አገር፣ ሴቶች እጃቸውን አስውበው መደርደሪያ ላይ እንዲያስቀምጡ በማድረግ፣ ለውጥ ጠብ አይልም፤ እንዲሰሩ….. ማደፋፈር….እጅ ወደተፈጠረበት የመጀመሪያ ዓላማ እንዲመለስ መሰበክ አለበት፡፡
                                                                                                                                                                                            
ከእለታት ግማሽ ቀን; ገጽ 182-183
2024/10/02 20:40:29
Back to Top
HTML Embed Code: