Telegram Web Link
ትምህርት ጀመርን እኔም መማር ጀመርኩኝ...አባቴም ዩኑፎርም የለም እኮ ልብስ ጫማ እና ፓርሳ መቀያየሪያ መግዣ ብር እያለ በጣም ብዙ ብር ይሰጠኛል......በዚህም ብር በጣም የሚያማምሩ ጫማዎች ልብሶች ፓርሳዎች ስለገዛሁኝ እቀያይራለሁ፡፡ በኔ ዉበት የተነሳ የትምህርት ቤት ወንዶች እኔን አይቶ ምራቁን የማይዉጥ ወንድ የለም ..
የሚገርማችሁ ኮሌጅ ለራሱ ገብቼ የአእምሮ ዲፕሬሽን አለቀቀኝም ከሰዉ ጋር አልቀላቀልም ብቸኝነት ምርጫየ ነዉ ከክላስ ዉጭ ላይብረሪ ነዉ የማሳልፈዉ...በዚህ ፊልድ ጥሩ ዉጤት ለማምጣት ቸክየ እየተማርኩ ነዉ

ወንድም ሴትም እኔ ጋር ጓደኛ መሆን ይፈልጋሉ ለምን በትምህርቴም ጎበዝ ስለሆንኩ ብዙ ሰዉ ጓደኛ እንሁን ይሉኛል ..ግን እኔ 10ክፍል ላይ መጥፎ ጓደኞች ሒወቴን ስላበላሹት ..አሁን ያሉት የሴትም የወንድም ጓደኞች እኔ በራሴ መፈተኛ ስፈተናቸዉ አይመጥኑኝም፡፡ ሴቶቹ ወሬያቸዉ አመለካከታቸዉ..ለትምህርት ያላቸዉ አመለካከት እንደ ጊዜ ማሳለፊያ ስለያዙት እነዚህ የክላስ ልጆች ጋር አብሮ ጓደኛ መሆን ልቤ አልፈቀደልኝም፡፡ትምህርቴ ላይ ጎበዝ ሆንኩኝ ስለማጠና የሚያስተሞሩን መምህሩ ጋር በጣም ተግባባን ፡፡


             አንድ ቀን እኛ ክላስ አንዲት ጅልባብ የምለብስ ልጅ ስሟ መፍቱሀ ትባላለች ደግሞ አንዲት ክርስቲያን ልጅ አለችኝ ስሟም ብሩክታይት ትባላለች ሁለቱ አንድ ላይ መጥተዉ ከአንቺ መተዋወቅ እንፈልጋለን ብለዉ እጃቸዉን ዘረጉ....

ብሩክቲን አንግባባም እንጂ አቃታለሁኝ የእኔ እናት እና የእሷ እናት ጓደኛ ናቸዉ፡፡ ክላስ ዉስጥ ሁለታችን እንፎካከራለን ....መፍቱሀ ግን ሰነፍም ጎበዝም አትባልም መካከለኛ ናት ፡፡
......እኔም እሺ እልኩኝ
..... መፍቱሀም:- ሁሌም አንቺ ጋር መተዋወቅ እንፈልጋለን ዛሬ ደፍረን ለመተዋወቅ እኛዉ መጣን በጣም አድናቂሽ ነን ለትምህርትሽ ያለሽ ትኩረት በጣም አስደሳች ነዉ ለአላህ ብየ እወድሻለሁ ከአሁን ቡሀላ አንቺም ለአላህ ብለሽ ዉደጅኝ አለችኝ መፍቱሀ
......እኔም 10Q ችግር የለም ከአሁን ቡሀላ ጓደኞች እንሆናለን አልኳቸዉ
.....መፍቱሀም ስልክ ቁጥር እንለዋወጥ አንዳንዴ እንደዋወላለን አለችኝ....
ስልክ ቁጥሬን ሰጠሆት የሷንም Save አረኩት..አብሬም ለብሩክቲ ስልኬን ሰጠሆት
     ስልኬን ልስጣቸዉ እንጂ ብዙም ትኩረት አላረኩም ለምን እስከ 10 በምማርበት ጊዜ ለኔ ሒወት መንገድ መሳት መጥፎ የሙስሊምም የክርስቲያንም ጓደኞች ነበሩኝ እነ መፍቱሀም ከዚህ ዉጭ ምንም አስቤ አላቅም

መፍቱሀ በቀን ሁለቴ ሶስቴ ትደዉልልኛለች የምናወራዉ ስለትምህርት በተጨማሪም ስለ ቂርአት እሷ የተለያዩ ኪታቦች እንደቀራች እና እኔም ቂርአት እንድቀራ ትመክረኛለች....,መፍቱሀ ሁሌም አብሽሪ ኪታብ መቅራት እኮ ቀላል ነዉ እኔ ስቀራ ብዙ አመት አልፈጀብኝም እያለች ...እየቀለደች እየሳቀች ሒወቷን ታጫዉተኛለች

አንድ ቀን መፍቱሀ ወደ አሱር አካባቢ ደወለችልኝና ነዋል ዛሬ ይዤሽ የምሄድበት ቦታ አለኝ እንገናኝ አለችኝ
.....እኔም እሺ አልኳት
....አሱርን ሰግደን ተገናኘን .... የት ነዉ የምንሄደዉ ብየ ሳልጠይቅ ወደ ምትሄድበት አብሬ ሄድኩኝ
....ጅማ ሪፈራል ሆስፒታል ሂደን የታመሙ ሰዎችን ዘይረን፡፡ ከሆስፒታል ስንመለስ በሌላ አካባቢ ወስዳኝ  አቅማቸዉ የደከሙ ትላልቅ ሰዎች በስራ አግዘን እና ትንሽ ብር ሰጥተን እነሱም መርቀዉን ተመለስን፡፡ መፍቱሀ ከትምህርት ሰአት ዉጭ ዛሬ የምንሄድበት አለ እያለች ኸይር መስራት የቲሞችንን ጧሪ ቀባሪ የሌላቸዉን አዛዉንት የሆኑትን መዘየር ሁኗል ስራችን ...

የእኔ ቤተሰቦች ሀብታም ስለሆን ድህነትን አላቀዉም የተቸገሩ መኖራቸዉን ድህነት እንዴት ሰዉ እንደሚጎዳ ዘያራ በምንሄድበት ጊዜ አስተዋልኩኝ ...እኔም ልብስ ግዢ ጫማ ግዢ ተብሎ ከሚሰጠኝ ብር ላይ ለተቸገረ መስጠቱ ለኔ ደስታ ሆነኝ፡፡

መፍቱሀ የሴቶች ጀመአ አሚር ናት  በወር በወር በመዋጮ የተቸገሩትን መርጠዉ ቋሚ የብር ወይም የአስቤዛ እርዳታ ይሰጣሉ .....እስኪ ሂደን አይተናቸዉ እንምጣ ትለኛለች...አብረን ሂደን ዘይረን እነሱ ጋር ተጫዉተን ብርም ከያዝኩኝ ለአንዳንድ ነገር ይሁናችሁ እያልኩ ብር ሰጥቼ እመጣለሁ.....

እኔም መፍቱሀ ጋር በዚህ የተቸገሩትን ዘያራ በምናደርግ ሰአት እራሴን እንድፈትሽ ከኔ የባሱ ብዙ መኖራቸዉን አስተዋልኩኝ..አልሀምዱሊላህ አልኩኝ..ከኔ ጀምሬ የበታችንን ብናይ አመስግነን ባልጠገብን ነበር ግን ምነ ይደረጋል የሰዉ ልጅ ዘንጊ ነዉ እንጂ በየእለት ተግባራችን ሰንት የማንሰማዉ የማናየዉ የለም ግን ስናመሰግን አይስተዋልም፡፡
ለመሆኑ ስንቶቻችን ነን በምንመለከታቸዉ የለያዪ ትዕይንቶች ልባችን ተነክቶ የአላህን ዉለታ አስታዉሰን የምናመሰግነዉ??? ወይም የምስጋና ሱጁድ የምናደርገዉ? ጥያቄዉ ለሁላችንም ይቆይ ራሳችን መልሰን እኛዉ እንረመዉ....


መፍቱሀ ለኔ ኸይር እንስራ  እያለች የምታበረታታኝ ነች፡፡ አንዳንዴም ብሩክቲም አብራን ትመጣለች...ብሩክቲ ክርስቲያን ትሁን እንጂ አለባበሷ አስተሳሰባ እንደሙስሊሞች ነዉ፡፡ ክሪም ለብሰን ፀጉራችን ከታየ ሸፍኑ ፀጉራችሁ እየታየ ነዉ ትለናለች... የቱርክ የዱባይ ጠባብ ልብስ ለብሰን ስንሄድ ይሄ እኮ ሰዉነት ያሳያል ሒጃብ ልበሱ የምትል ...,አንዳንዴ የሶላት ሰአት ደርሶ እሺ እንሰግዳለን እያልን ወሬ ስናወራ መጀመሪያ ስገዱ እያለች ትገስፀናለች፡፡ ይገርማል የብሩክታያት ቅርብ ጓደኛዋ መፍቱሀ ብቻ ናት .ብሩክቲን የኢስላምን አደብ አስተምራታለች ፡፡
 
መፍቱሀም እኔን እኛ ጀመአ መግባት አለብሽ የምንገናኛዉ በሳምንት አንዴ ነዉ እያለች ብዙ ጊዜ ነገረችኝ..
...,,እኔ ሰዉ ጋር መቀላቀሉ ሌላ ጓደኛ መፍራቱን አልፈለኩም ግን መፍቱሀ ግድ እኛ ጀመአ ገብተሽ የዲን እህቶሽን ተዋዉቀሽ ኪታብ መጀመር አለብሽ እያለች ሁሌ ስለምትናገረኝ.....እሺ ቅዳሜ እንሄዳለን አልኳት
.......ቅዳሜ ደረሰ መፍቱሀ ጋር አብሬ ሬፍት ቫሊ ኮሌጅ በቅርብ ርቀት የሚገኘዉ ዓሊይ መስጊድ ጀመአቸዉ የሚገናኙበት ሄድኩኝ.....



በፊት አስረኛ ክፍል ስማር በመጥፎ ጓደኞች ተተብትቦ አላማየን እንዳልሳትኩኝ ዛሬ ኮሌጅ ላይ ደግሞ እንደ መፍቱሀ እና ብሩክቲ አይነት ምርጥ እህቶች እና ጓደኛ ሰጥቶኝ ...ትክክለኛ መስመር የያዝኩ ሁኛለሁ ኢስቲቃማዉን ይስጥሽ በሉኝ....

#ክፍል 1⃣3⃣
ይ......ቀ.......
......ጥ......ላ........ል


JOIN
´ www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ አስራ ሶስት 1⃣3⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ




ቅዳሜ ደረሰ መፍቱሀ ጋር አብሬ ሬፍት ቫሊ ኮሌጅ በቅርብ ርቀት የሚገኘዉ ዓሊይ መስጊድ ጀመአቸዉ የሚገናኙበት ሄድኩኝ.....

ዓሊይ መስጊድ ደረስን የሴቱ ጀመአ በጣም ብዙ ናቸዉ
.....መፍቱሀም አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካትሁ ዉድ የኢስላም እህቶቼ ዛሬ አንድ እህታችን መጥታለች ስሟም ነዋል ትባላለች ብላ ከሁሉም ጋር በአንዴ አስተዋወቀችኝ፡፡ ደስ የሚሉ ጀመአዎች ነበሩ ሲጀመር እኔም በባህሪየ ሰዉ ጋር መቀራረብ ሰዉ ጋር መላመድ ችግር የለብኝም ..ሁሉም ጋር ብዙም ቀን ሳይፈጅብኝ ተግባባን፡፡


መፍቱሀም፡- ሁሌ ቅዳሜ መቅረት አይቻልም የጀመአዉ አባል ተብለሽ ተመዝግበሻል አለችኝ፡፡
.....እኔም እሺ እመጣለሁ አልኩኝ..
    መፍቱሀ ጋር ወደ ቤት እየተመለስን ግን የወደፊት አላማሽ ምንድን ነዉ ?? ለወንድ ልጅ ያለሽ አመለካከትስ እንዴት ነዉ ?? አለችኝ
.....እኔም ወንድ ልጅን በፍቅር አልቀርብም አላህ ባለቀን boyfrind ሳልይዝ እኔን ከማንነቴ ተቀብሎኝ ቀጥታ ቤተሰብ የሚጠይቅ ነዉ የምፈልገዉ ..እኔ በዘንድሮ ፍቅር አላምንም አልኳት
...መፍቱሀም ማሻ አላህ ወላሂ የኔም ሀሳብ እንደዚሁ ነዉ የኔ ሀላል ባሌ የምፈልገዉ እኔን በቻት በተለያዩ መህበራዊ ሚዲያ ሳይጀነጅነኝ በመስኮት ሳይሆን በበር የሚገባ ለቤተሰቦቼ የሚያሳዉቅ ነዉ የምፈልገዉ አለችኝ ፡፡ሁሌ ተገናኝተን ስለፍቅር ስለትዳር ካወራን አስተሳሰባችን አንድ አይነት ነዉ፡፡

መፍቱሀ ጋር ከምነግራችሁ በላይ በጣም እንዋዳደላለን ከጓደኛ በላይ እንደ እህት ነዉ የማያት ...ጓደኝነታችን በጣም ቅርርብ ስላለን ብቻየን እኔ ከሄድኩ ወይ መፍቱሀ ብቻዋን ከሄደች ምነዉ ጓደኛሽ ዛሬ የለችም ወይ?..ወይ እሷን ነዋል ዛሬ የለችም ወይ ?ብለዉ ይጠይቁናል.. ብዙ ጊዜ በጀመአም በስብሰባም በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች የሆነ ጥያቄ ሀሳብ ካስፈለገ የእኔና የእሷ ሀሳብ ሁሌም አንድ ነዉ፡፡ እኔ የሆነ ነገር ሳስብ እሷም አስባዉ አገኛታለሁ..የሆነ ኸይር ስራ ለመስራት ሳስብ ላማክራት ስል ወይ እሷ ትቀድመኛለች ወይ ስነግራት እሷም እንደ አሰበችዉ ትነግረኛለች ..እሷም የሆነ ሀሳብ ስታማክረኝ እኔም የአሰብኩት ሀሳብ ሁኖ አገኘዋለሁ....ከአካል አልፎ ልባችን ለራሱ ጓደኝነት ፈጥሯል..ሰዉ ብዙ ጓደኛ አለዉ  ..በጣት የሚቆጠር የልብ ጓደኛ የሚለዉ አለ ነገር ግን ጭራሽ ልብ ለልብ አይገናኙም ጭራሽ የሆድህን ለማስረዳት ጓደኛም ለመረዳት ሳይቻል ይስተዋላል..ይሄ ገና ጓደኝነቱ ብዙ ይቀረዋል ማለት ነዉ፡፡ ለምን ጓደኝነት በሀሳብ ገና ፊትህን አንብቦ የልብህን የሚያቅ ሲሆን ነዉ፡፡ የሚገርማችሁ አመናችሁም አላመናችሁም ያዉ በአላህ ፍቃዴ እኔና መፍቱሀ የወር አበባ ለራሱ የምናይበት ቀን ድረስ የተመሳሰለ ነበር...ብዙ ቀናቶች እኔ ታምሜ ሀኪም ቤት ስሄድ እሷም ትታመም ነበር...አንድ ሀኪም ሙድ ይይዝብን ነበር ዛሬ ጓደኛሽ አልታመመችም ወይ እስከ ማለት ደርሰዉ ነበር..ይሄን ያህል ድረስ ነበር የኔና የመፍቱሀ ልብ ለልብ ጓደኝነታችን


አንድ ቀን መፍቱሀ በስጦታ መሸፈኛ የተጠቀለለ ነገር ሰጠችኝ
...የተጠቀለለዉን ስከፍተዉ ኪታብ ነበር ...እኔም ደስ ብሎኝ አብረን ኪታብ መቅራት ጀመርኩኝ ..ለሒወቴ ትልቅ ለዉጥ እያመጣችልኝ ነዉ፡፡

ደግሞ በሌላ ቀን መፍቱሀ በስጦታ የተጠቀለለ ነገር ሰጠችኝ
...መፍቱሀ የተጠቀለለ ነገር ከሰጠችኝ ለኔ አስፈላጊ በጣም የሚጠቅም ነገር እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለዉም
....እኔም ምንድን ነዉ ?? አልኳት
.......እሷም የዛሬዉ ስጦታ እቤትሽ ሒደሽ አይተሽዉ ከዛ ትደዉይልኛለሽ አለችኝ
.....እኔም የሰጠችኝን ስጦታ እስከማየዉ እየቸኮልኩኝ እቤቴ ደረስኩኝ
........የስጦታ ወረቀቱን ስፈታዉ ጥቁር ጅልባብ ነዉ፡፡
እኔም ወደ መፍቱሀ ደዉየ ጅልባቡን ወድጀዋለሁ አላህ ይስጥልኝ አልኳት
.......እሷም ነዋል ......ልበሽዉ እና በመስታወት አንቺ ጋር እንዴት እንደሚያምር ተመልከቺዉ ከዛም ዛሬ የዙሁርን ሶላት ስገጂበት...ሰግደሽበት በጣም ትወጅዋለሽ እርግጠኛ ነኝ ትሞህርት ቤት ለብሼዉ እመጣለሁ ነዉ የምትይዉ አለችኝ

እኔም መፍቱሀ እንዳለችኝ ጅልባቡን ለብሼ በመስታወት ሳየዉ በጣም ነዉ ያማረብኝ ....መፍቱሀ እንዳለችኝ ጅልባቡን ለብሼ ዙሁሩን ሰግጄ ጨርሼ ሳሰላምት አባቴ ከሆላየ ቁማል

...አባቴም ዛሬ በሰላም ነዉ እቤት የመጠሀዉ?? አልኩት
አባቴም የምፈልገዉ እቃ ነበር ጠዋት እረስቼዉ አሁን ልወስድ ነዉ .....ነዋል ጅልባቡን መቼ ገዝተሽዉ ነዉ ??? ነዋልየ የኔ ልጅ ወላሂ እንደዚህ አምሮብሽ አይቸሽ አላቅም ወደ ቤት ስገባ ጅልባብ ለብሰሽ ስሰግጂ እንዴት ደስ እንዳለኝ ከምነግርሽ በላይ ነዉ ደስታየን መቆጣጠር አቅቶኝ የደስታ እምባ አነባሁ፡፡ ነዋል አምሮብሻል አታዉልቂዉ አለኝ፡፡
....እኔም ጓደኛየ ስጦታ ሰጥታኝ ነዉ አባቢ አልኩት
.......አባቴም ጥሩ ጓደኛሽ ናት፡፡ ለወደፊትም እሷን ጓደኛ አርገሽ ያዢ ብሎ ከአንጀቱ እጆቹን ወደ ላይ ዘርግቶ ዱአ አደረገላት...ነዋል ሲመቸኝ ጓደኛሽን ታስተዋዉቂኛለሽ አለኝ አባቴ
...,,,እኔም እሺ አስተዋዉቅሀለሁ አልኩት ...አባቴም የረሳዉን እቃ ይዞ፡ከቤት ወጥቶ ሄደ
  

እኔም አምሮብኛል ማለት ነዉ ??ብየ መልሼ መልኬ እስከሚገፍ መስተዋት ላይ አፈጠጥኩኝ፡፡

ዛሬ  ከሰአት ክላስ አለን ጅልባቡን ለብሼዉ ልሂድ ወይስ አልሄድ ??ጅልባብ ስለብስ የመጀመሪያየ ነዉ ሰዉ ምን ይለኛል ??? እያልኩ ብቻየን እያሰብኩ መልበሱን ፈራሁ

★★★ በዲነል ኢስላም ሀይማኖት ዉስጥ እምነት የሚለዉ ቃል በአረበኛ ትርጉሙ ሲፈታ አንድን ነገር እዉነት ብሎ መቀበል ሲሆን ኢስላማዊ ትርጉሙና ትንታኔ ግን ሰፊ ቢሆንም የኢስላም ሊቃዉንቶች በአጭሩ ሲያስቀምጡት እንዲህ ይላሉ ..አል አሚኑ ማወቀረ ፊል ቀልብ ወሰደቀሁል አመል ..ትርጉሙም፡-እምነት ማለት በልብ ወስጥ ተደላድሎ የተቀመጠ እና ስራ ወይም ተግባር ያረጋገጠዉ ነዉ በማለት ይገልፁታል፡፡ ሌሎች የኢስላም ሙሁራን እምነትን ሲገልፁ በልባችን (በቀልባችን)እዉነት ነዉ ብለን የምንቀበለዉ..በምላሳችን ሙሉ ፍቃደኝነት የምንናገረዉ እና በሰዉነት አካላችን የምንተገብረዉ ነገር ነዉ...በማለት ይገልፁታል ፡፡እኔም ታዳ ጅልባብ መልበስ ሰዉ ምን ይለኛል ብየ ከፈራሁ እምነቴ ላይ ችግር አለ ሀይማኖቴ ከልቤ ሳይገባ ተደላድሎ አልተቀመጠም ማለት ነዉ::

ለኔ ጅልባብ መሸፈኛየ መከበሪያየ ነዉ፡፡
ምን ያህል ስለ ሒጃብ ጥቅሞች እናዉቃለን???

★★★ ሒጃብ ለአላህና ለመልዕክተኛው መታዘዝ እንጂ የሆነ ሀገር ባህል ተከታይነት አይደለም።

⇘ሒጃብ ጥብቅነትና ንፅህና ነው። ሒጃብን የማትለብስና
ከሂጃብ የተራቆተች እንስት ሁለት ነገሩዋ ቆሽሿል ፡፡ አንዱ ንፁህ ቢሆን እንኳን አንዱ ንፁህ አይሆንም አንደኛ ልቧ ቆሽሿል ፡፡ ሁለተኛ ሸይጧን አሳስቷት ሰውነቷን በተለያየ ወንጀል አቆሸዋለች በዝሙትና በተለያየ ነገር ሰውነቷን አጨማልቃው ሊሆን ይመቻል የሚፀዳው ሒጃቧን ለብሳ ክብሩዋን ጠብቃ ጥንቁቅ ሆና ወደ ጌታዋ ቁሩጥ ያለን መመለስ ስትመለስ ብቻ ነው!!!👇👇👇
ልቧ ባይቆሽሽ አትራቆትም ነበር ከሂጃብ መራቆቷ ራሱ የወንጀል መብዛት አንዱ ምልክት ነው ሸይጧን ሴትን ልጅ ወንጀል እንድታበዛና እንድትሰራ ይገፋፋታል ከዛ በኋላ ግን ከሂጃቧ እንድትገፈፍና ክብር እንዳይኖራትና በባለጌዎች እንድትደፈርና እንደ ቀላል እንድትታይ ያደርጋል፡፡ ሒጃቧን በአግባቡ የምትለብስ ሴት ግን ሁሉም ዘንድ ክብር አላት ባለጌዎች ዘንድም ክብር አላት እሷን ቀና ብለው እንኳን አያዩዋትም መልካም ሰዎች ዘንድም ልዩ ክብር አላት።

⇘ሒጃብ ኢማን ነው ኢማን ማለት:– በልብ ማመን በምላስ መናገር በአካል መተግበር ነውና።
አንዳንዶች ካሉበት ሸሪዓን የሚቃረን ተግባር እንዲመለሱ ሲነገራቸው ኢማን በልብ ነው ልቤን ከፍተህ አይተሀል? እያሉ የውሸት ቅንብራቸውን ስያቀናብሩ ይስተዋላሉ። ጥያቄ አለኝ ልባችሁ ካመነበት ተግባራችሁ ሊመሰክር ምን ከለከላችሁ? ለአላህ ግን መዋሸት አይቻልም! ለማነኛውም ኢማን ሶስት ክፍሎች አሉት ከነዛ ውስጥ ምንም ማጉደል አይቻል ታዲያ 3ኛው በአካል መተግበር ነውና ተግብሪ ሒጃብሽን ጠብቂ አንቺ ሒጃብ ብለሽ የምትጠሪው በወገብሽ ልክ አጣብቀሽ የሰዉነት ክፍልሽን የሚያሳይ አድርገሽ ከሴቶች ሱሪ ከሚለብሱት የማይሻል አድርገሽ የምታሰሪዉ ሳይሆን ኢስላም/ሸሪዓ ሒጃብ ብሎ ያስቀመጠልሽን ሒጃብ ነው የምልሽ።

⇘ሒጃብ የህፍረተ–ገላ መደበቂያ ነው። ሴት ልጅ ደግሞ መላ ሰውነቷ ህፍረተ–ገላ ነውና መላ ሰውነቷን ልትሸፍነው ይገባታል!! አንዳንድ (ፈቂህ መስለው ሙተፈቂሆች) ስለ ዲኑ ሳይገነዘቡ የተገነዘቡ የሚመስሉ ሰዎች እና ሴትን ልጅ ልቅ እንድትሆን ከአጂ ነብይ ጋር እንደፈለገች እንድትተራመስ ኢስላምን ታኮ የመጣ ኢስላም መስሎ ኢስላምን የሚያዳክም ሊያጠፋ የመጣ የአህባሽ አስተምሮን ይመስል አይ እጅና ፊት እንኳን ሱና ነው ኪላፍ አለበት ምናምን… የሚሉትን ተረታቸውን ትተሽ አንቺ ለአላህ ብለሽ ተቃራኒ ፆታዎችን ላለ መወስወስ ብለሽ መላ ሰውነትሽን ልትሸፋፈኚ ይገባል።

⇘ሒጃብ የሼመኝነት ምልክት ነው። የሴት ልጅ ተፈጥሮ ሼመኝነት ነውና ተፈጥሮን ጥለሽ ሌላን ለመሆን መሞከር አደጋው የከፋ ነው።
ተወዳጁ የአላህ መልዕክተኛ ነብዩ ሙሀመድ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- ሴት ሁና በወንድ የምትመሳሰልና ወንድ ሁኖ በሴት የመመሳሰልን አላህ ረግሟቸዋል ብለዋል። ልብ በይ እህቴ የአላህ እርግማን ነው ያለበት!

⇘ሒጃብ መልካም የሆነች አማኝ ሴት በህሪ ነው። አላህ ይጠብቅሽና እህቴ የዚህ ተቃራኒ መሆንሽ ምንኛ የከፋ ነው? መልሱን ቆም ብለሽ እንድትመልሺው ለአንቺው ተውኩት


       አንድ ኡስታዝ ደአዋ እያደረገ.. የተለያዩ ሀይማኖቶች ስብከታቸዉን እያካሄዱ ሙስሊሙ ተዳክሟል ምን ይሻላል? ተብሎ ተጠይቆ እንዲህ ብሎ መልሷል ፡-እኔ ግን የሚያሳስበኝ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በሌሎች ስብከት ሌላን ሀይማኖት ይከተላል የሚለው ጉዳይ ሳይሆን በስሜት ተከታይነት ይጠፋል የሚለው ጉዳይ ነው የሚያሳስበኝ ብሏል፡፡
⇘አዎን! በትክክል ተጨባጩም የሚያስገነዝበው ይህን ነው
በአሁኑ ሰዓት ስለ ዲኑ ጠንቅቆ የሚያውቀው በጣም አናሳ ነው በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ አብዘሀኛው ማለት በሚያስችል መልኩ ትንሽ ያውቃል ተብሎ ተስፋ የሚደረግበትም አላህ ያዘነለት ሲቀር የስሜቱ ተከታይ ነው በስሜት ተከታይነት ሀራሙ እንደ ሀላል ተቆጥሮዋል በስሜት ተከታይነት ሱና ቢድዓ ይደረጋል ቢድዓ ደግሞ በተቃራኒው እንደ ሱና ይታያል በስሜት ተከታይነት ሽርክ እንደ ተውሂድ የሚቆጠርበት ቦታም አለ… ሌላም ሌላም
ይህንኑ የሚያበረታቱና ባለ በሌለ ሀይላቸው የሚያስፋፉ የሸይጧን ወዳጆች ደግሞ በዛው ልክ በዝተዋሉ!

ልብ በይ እህቴ!!!!! አንቺ የህብረተሰቡ መሰረት ነሽ አንቺ ከተበላሸሽ ይህ ህብረተሰብ ይበላሻል አንቺ ከተስተካከልሽና ከለማሽ ህበረተሰቡም ይስተካከላል አንቺን ለማጥመምና ከተፈጥሮሽ ለማውጣት ከሂጃብሽ ለማላቀቅ ከአላህና ከመልዕክተኛውﷺ ተከታይነት አስወጥተው የሸይጧንና የስሜትሽ ተከታይ ሆነሽ የጀሀነምን ገደል ገብተሽ ህብረተሰቡንም ወደ ጀሀነም ገደል እንድታስገቢ ሸይጧንና የሸይጧን ወዳጆች የሚያደርጉትን ጥረት አውቀሽ ለእነሱ አላማ የሚመቻቸውን አካሂድ እርግፍ አድርሽ ትተሽ ወደ አላህ ተመልሰሽ ሒጃብሽን ጠብቀሽ ስለ ዲንሽ ተምረሽ አውቀሽ ተግብረሽ ምርጥ ትውልዶችን የጀነት ሙሹሮችን አፍሪ
ይህቺ አለም እያየሻት ነው አጭርናትና ለዘላለማዊ አለም ጥሩ ስንቅ ሰንቂ።



       እኔም ጅልባቡን ልልበስ አልልበስ እያልኩ ለብቻየ ሳመነታ ዉሳኔየ ሲምታታብኝ ለመፍቱሀ ደዉየ ጅልባቡን ለብሼ ልመጣ ነበር የሰዉ አይን ማየት እና ሰዉ ምን ይሉኛል ብየ ፈራሁ ምን ይሻለኛል?? አልኳት
......መፍቱሀም ነዋልየ አንቺ የምፈሪዉ አላህን ከሆነ ጅልባቡን እንደለበሽ ሳታወልቂ ነይ ... አንቺንም እኔንም እነሱንም የፈጠረንን አላህን ብቻ ፍሪ አላህን ካልፈራሽ ማንን ትፈሪያለሽ ??...ግን ሰዉ ከሆነ የምፈሪዉ ቀይረሽዉ ትመጫለሽ ማለት ነዉ..ለሰዉ በጭራሽ እንዳትጨነቂ ....ማንንም እንዳፈሪ ጅልባቡን ሳታወልቂ ለብሰሽዉ ነይ አለችኝ........

ነዋል ጅልባቡን ትለብሰዉ ይሆን???

#ክፍል 1⃣4⃣

ይ........ቀ ......
.....ጥ.........ላ........ል


JOIN
´´´´´´´ :¨·.·¨: ❀ share
           `·. www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ አስራ አራት 1⃣4⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ




ማንንም እንዳፈሪ ጅልባቡን ሳታወልቂ ለብሰሽዉ ነይ አለችኝ........
የመፍቱሀ ንግግር ልቤ ዉስጥ ገባ ..ሰዉ ምን ይለኛል የሚል ፍርሀትን አስወግጄ ወኔ ፈጠረብኝ ....ማንንም አልፈራም ደግሞ ለዘንድሮ ሰዉ ብየ ጅልባቡን እንደለበስኩኝ ከቤቴ ወደ ሬፍት ቫሊ ኮሌጅ መሔድ ጀመርኩኝ....ግን እደሄድኩ የመጀመሪያየ ስለሆነ እየተንቀጠቀጥኩ እየፈራሁኝ ነዉ፡፡ ሰዉ ሁሉ በመንገድ ስሄድ ሲያየኝ ምን ሁና ነዉ የሚለኝ ይመስለኛል.... በጣም ነበር የማያስፈራዉ፡፡ እንደ ምንም ብየ ኮሌጅ ደረስኩኝ...

ትምህርት ቤት ያሉ ተማሪዎች ሁሉም እየተጠቋቆሙ እኔን ነዉ የሚያዩት ...በጣም ነዉ የገረማቸዉ ያልጠበቁት ተአምር ነዉ የሆነባቸዉ፡፡ ከትምህርት ቤታችን ቁጥር አንድ በፋሽን ልብስ ዘናጭ የተባልኩኝ ተማሪ ዛሬ ጅልባብ ለብሼ ከች ስል ሁሉም ገርሞት መልኬ እስከሚገፍ ተመለከቱኝ ግን እኔን ደፍሮ ለመናገር የሞከረ የለም ዝም አሉኝ

  መፍቱሀ ከሩቁ አየችኝ ፊቷ በደስታ የሚያበራ ይመስላል ..ከተቀመጠችበት ቁማ ጠበቀችኝ እሷ ጋር ስደርስ ነዋልየ ወላሂ ለአላህ ብየ እወድሻለሁ ዛሬ ደግሞ በጣም አስደሰትሽኝ ብላ በደስታ እቅፍ አድርጋ ሳመችኝ....ደስታዋን የምገልፅበት ቃላት አጠራት የደስታ እምባ እያነባች በለበሰችዉ ክሪም እምባዋን ትጠርግና አይን አይኔን ታየኛለች መልሳ እቅፏ ዉስጥ ታስገባኝ እና ትስመኛለች፡፡ ነዋልየ አኮራሽኝ ወላሂ እንዴት እንዳስደሰትሽኝ ...አላህ ሁሌም ያስደስትሽ ነዋልየ ወላሂ እንዴት እንዳማረብሽ ልነግርሽ አልችልም፡፡ ደስታየን አንድ ቀን ብቻ እንዳታደርጊዉ ነገም ለብሰሽ እንድመጪ አንድ ቀን ብቻ ለብሰሽ እንዳታወልቂዉ አለችኝ
......እኔም እሺ መፍቱሀ ኢንሻ አላህ አለብሳለሁ አልኳት፡፡ ክላስ ገብተን ተምረን ወደ ቤታችን ተለያየን፡፡

እድሜ ለሰጠዉ ሰዉ ወደ ሞት እየተጓዝን ቢሆንም ከቀናችን አንድ ቀን ለመቀነስ መንጋቱ አይቀርም..ይሄዉ ዛሬም ነጋ ..እንደትናቱ ጅልባቤን ለብሼ ወደ ኮሌጅ አመራሁኝ ...እዛም እንደ ደረስኩ የትምህርት ቤት ልጆች እንደትናትናዉ ለመናገር አልፈሩም ..የብዙ ሰዉ አስተያየት ተቀበልኩ፡፡ የሚገርማችሁ ክርስቲያን የሆኑ የኛ ክላስ ልጆችና ትምህርት ቤት የምግባባቸዉም የማልግባባቸዉም ነዋል ይሄ አለባብስ አምሮብሻል አታዉልቂዉ .....ትናንት ለብሰሽዉ ስናይሽ ለአንድ ቀን ብቻ የለበሽዉ መስሎን ነበር የሁሌም ልብስሽ ብታደርጊዉ ያምርብሻል አሉኝ፡፡
ብዝዎቹ ክርስቲያን የክላስ ልጆችም ነዋል አንቺ ቀይ ስለሆንሽ በጥቁር ጅልባብ ከሁሉም ሴቶች አንቺ ላይ አምሮብሻል አሉኝ ፡

አስተያየት ከሰጡኝ ሁሉም ክርስቲያኖች 100% እንደአማረብኝ አታዉልቂዉ አምሮብሻል ብለዉ መሰከሩልኝ ፡፡ እዉነታቸዉን ነዉ አልተሳሳቱም መልኬ በጣም ቀይ ነኝ ጥቁር ጅልባቡ ሲጨመርበት ምንም የማይሳነዉ ጀሊሉ አምጥቶ ዉበቱን ደፋብኝ....

ብሩክታይትም ደስ ብሏት ማርያምን አምሮብሻል እንዳታወልቂ አለችኝ፡፡ አንዳንድ ሙስሊም እህቶቼም ማሻ አላህ አሉኝ በጣም ደስታ ተሰማኝ፡፡

ደግሞ በተዘዋዋሪ ሙስሊም ሁነዉ ፋሽን ተከታይ ሴቶች  ደግሞ ምን ሁነሽ ጅልባብ ለበሽ?? አንቺ ገና ነሽ ወጣት ነሽ እንደ በፊቱ ብዘንጪ ነዉ የሚያምርብሽ እያሉ በለበስኩት ጅልባብ አንቋሸሹብኝ ወላሂል አዚም በጣም ተአጀብኩኝ ሙስሊሞቹ ከሰጡኝ አስተያየት 35% መልበሴን የተቃወሙ ናቸዉ፡፡ ይሄ ሁሉ የሚያመለክተዉ ዲነል ኢስላም ላይ ገና አለመሰራቱ እና ሙስሊም ናቸዉ እንጂ ኢስላም ሀይማኖት ምን እንደሆነ ገና የሚቀረን ማህበረሰቦች ነን ያለነዉ ማለት ነዉ...አሁን ላይ በእንደዚህ ያሉ የሀይማኖት ተከታዮች ተተብትቦ ዲነል ኢስላም የምናሰድበዉ ፡፡ ዲነል ኢስላም መመዘን ያለበት በሀይማኖቱ ዉብነት ለሰዉ ልጅ ፍትህ እንደሆነ እንጂ በዲነል ኢስላም አንዳንድ ተከታዮቹ ኢስላም ቢፈተሽ አንድም ሰዉ ወደ ኢስላም ባልገባ ነበር..ግን ምን ይደረጋል ዲነል ኢስላም በአንተም በአንቺም በእሱም በእሷም በእነሱም በእነዛም የሚመዘን አይደለም ሀቅ በያዙ ደጋግ አቢድ ሷሊህ በሆኑ ባርያዎቹ እንጂ፡፡

ክርሰቲያኖች በመንገድ የሚያገኙኝ አድንቀዉኝ ሙስሊሞቹ እንደዚህ ሲያንቋሽሹኝ በእኔ ሳይሆን ሙስሊም ሁነዉ እንደዚህ በማሰባቸዉ አፈርኩባቸዉ፡፡
      የቱርክ የቻይና የዱባይ ፋሽን ተብየ ልብስ መልበስ ትቼ ጅልባብ ብቻ መልበስ
ጀመርኩኝ....,ልብስም ከገዛሁ የምገዛዉ የተለያዩ ጅልባቦች በተለያዩ ከለሮች እና የጅልባብ ማላበሻ ክሪም ብቻ ሆነ፡፡

አንድ ቀን እኔና ብሩክቲ አንድ ላይ ቁመን
አንድ ወንድ ክርስቲያን የክፍላችን ልጅ እኔ እና ብሩክቲን መጥቶ ሰላም አለን.... ወንድ ልጅ ጋር መጨባበጥ ሀራም እንደሆነ አቃለሁኝ ግን እሱን እንዳይደብረዉ ብየ ነበር ሰላም ያልኩት
...... ብሩክቲም እንዴት ወንድ ሰላም ትያለሽ ?? መፍቱሀ የአጂ ነብይን እጅ የጨበጠ ጀሀነም እሳትን እንደጨበጠ ነዉ ስትል ሰምቻታለሁ እንዴት ትጨብጫለሽ ? ደግም ከአሁን ቡሀላ ጅልባብ ለብሰሻል ወንድ ልጅ መጨበጥም አቁሚ አለችኝ ክርስቲያን ጓደኛየ ብሩክቲ
....እኔም እሺ ልክ ነሽ ብሩክቲ አልኳት ፡፡ በጣም አፈርኩኝ ብሩክቲ ክርስቲያን ሁና ስለ ኢስላም አዉቃ እኔ እንዴት እያወኩኝ መተግበር አቃተኝ ?? እንዴት አጂ ነብይ መጨበጥ ሀራም መሆኑን እያወኩ እንዴት ሰላም እላለሁ ?? ከአሁን ቡሀላ ወንድን ልጅ ማንም ይሁን ማንም ሰላም ላልል ለራሴ ቃል ገባሁ

   መፍቱሀ ከትምህርት ሰአት ዉጭ መርከዝ ገብተሽ ተማሪ አለችኝ...
... እኔም መርሀባ በማለት ጅሬን ሰፈር የሚገኘዉ አባጅፋር መርከዝ ተመዘገብኩኝ ቁርአኔን ሙራጅአ ማድረግ ጀመሬ ብዙም ሳልቆይ ጨረስኩኝ ኪታብ መቅራትም ጀመርኩኝ በኡስሉሰላሳ ጀመርኩኝ በሉገል መራም ሌላ ኪታቦች እዛዉ ቀራሁኝ ....ሰአት እያመቻቸሁ ሌላ ቦታ ሪያደሷሊህን መቅራት ጀመርኩኝ.....እኛ ሰፈር ያለዉ አጂፕ መስጊድ ሰአት እያመቻቸሁ ቁርአን ተፍሲር መቅራት ተያይዠዋለሁ፡፡
የመፍቱሀ ግፊት ለኔ በሒወቴ መስመር የያዝኩበት ኪታብ የቀራሁበት ዲነል ኢስላምን ያወኩበት ነዉ ...መፍቱሀ ለኔ ሁለ ነገሬ ናት
#የትአሉ_ለአላህ_ብለዉ_የተዋደዱ!!!!!"
መፍቱሀን አላህ የሰጠኝ ለሂድያ ስበብ የሆነችኝ የጨለመዉን ሒወቴን መብራት ያበራችልኝ ናት

★★★★ባልደረባክን ጓደኛክን ምረጥ ……
ተወዳጁ ነብያችን ﷺ በሀዲሳቸው እንዲህ ይላሉ:-
ሰውየው ሀይማኖት በጓደኛው ላይ ነው አንድኛችሁ ባልደረባ አድርጎ ወደያዘው ሰውዬ ይመልከት

>>>አሏህ ይዘንላቸውና ኢብን ኡሰይሚን እንዲህ ይላሉ:- የኸይር ባልተቤቶች የሆኑትን ሰዎች ጓደኛ አድርገክ በመያዝ ጓጓ ትኩረት አድርግ መልካም ጓደኞች በጠመምክ ጊዜ ይመሩካል፣ በተሳሳትክ ጊዜ ያቀኑካል፣ አሏህን በረሳክ ጊዜ ያስታውሱካል፣ ጃሂል ( መሀይም) በሆንክ ጊዜ ያስተምሩካል።ብለዋል👇👇👇
        መፍቱሀ ዓሊይ መስጂድ የሚገኘዉ የሴቶች ጀመአዉ ላይ አሚር ስለሆነች እኔ በተለለያዩ ነገር እንድሳተፍ አደረገችኝ፡፡በሳምንት ቅዳሜ የኛ የሴቶች ጀመአ ዝግጅት አለን.... እናም እሳተፋለሁ.., ሁሌም መፍቱሀ አንቺ ተሰጥኦ ታለንት አለሽ ትለኛለች፡፡ መፍቱሀ ግጥም ትፅፍ እና እኔ ነኝ የማቀርበዉ....መነባነብ ለራሱ እንደ እኔ የሚሆን የለም .....እናም በመሀል ቀልድም ሲያስፈልግ እኔ ነበርኩ ፈታ የማረጋቸዉ፡፡
በሂደት እኔዉ የተለያዩ ግጥሞች ታሪኮች ፅፌ ለሷ አነብላታለሁ እሷም ይሄ ጀመአ ላይ መቅረብ አለበት እያለች የተለያዩ ኢስላማዊ ይዘት ያላቸዉ ዝግጅቶች አቅራቢ ሆንኩኝ፡፡

ድፍረቴን ተስጦኦየን አይተዉ ዝግጅት ሲኖር የጀመአዉ መድረክ መሪ አስተዋዋቂ እኔዉ ሆንኩኝ፡፡ ፕሮግራም መሪ..ፕሮግራም ያላቸዉ...እናም የሚቀርቡትን ነገሮች ይመጥናል አይመጥንም እያልኩ እኔዉ እገመግማለሁ፡፡
ዝግጅት ሲኖር ሀሳባቸዉን ሁሉም ለኔ ትተዋል፡፡ እኔም በዚህ መድረክ መምራት ማንንም አልፈራም

መፍቱሀን ዛሬም ነገም ለወደፊትም ብሆን ዉለታዉን መመለስ ባልችልም ሁሌም ሳመሰግናት እና በልቤ ዉስጥ አስቀምጫታለሁ
★★★ነብዩ ሙሀመድ ሰ.ዐ.ወ እንዲህ ብለዋል በጎ ነገር ላደረገላችሁ ሰዉ ወረታዉን መልሱ ..ካልቻላችሁ ጀዛኩሙሏሁ ኸይረን በማለት ዱዐ አርጉለት ብለዋል ፡፡
በሌላ ሀዲሳቸዉ ነብዩ ሰ.ዐ.ወ እንዲህ ብለዋል ሰዉ ላደረገለት በጎ ተግባር ሰዉን ያላመሰገነ አላህንም አያመሰግንም ..ብለዋል፡፡ ሁሌም ቢሆንም ለእኔም ዱአ ሳደርግ ለመፍቱሀም አብሬ ዱአ አደርጋለሁ

ይሄ ጀመአ የሴት ብቻ አይደለም ወንዶችም እራሳቸዉን ችለዉ አላቸዉ የጀመአችን ስም አንድ ነዉ Telegram ..Whatsap..Youtube አድራሻዎች አሉን በጂማ ታዋቂ ነዉ፡፡ ፋዉንዴሽንም አለዉ የቲሞችን የተቸገሩን ጧሪ ቀባሪ የሌሊቸዉን ወረሀዊ መዋጮ አለ በተጨማሪም ከባለሀብቶች በማስተባበር እየሰበሰብን በወር ብዙ ችግረኞችን የቲሞችን እንደጉማለን

   ጅልባብ ለባሽ ከሆንኩ ቡሀላ ከጀመአም ልጆች መስጊድ ከሌላም ቦታ የምንገናኝ ሙስሊም እህቶቼ በጣም ይቀርቡኛል ፡፡ አንድ አባባል አለ አንተ ጥሩ ቦታ ከሆንክ የሚቀርቡህ ጥሩ ነገር ነዉ፡፡ መጥፎ ቦታ ከሆንክ የሚጠጋህ መጥፎ ባለጌ ሰዉ ነዉ...አላህ ከወደደህ ሁሉ ሰዉ ይወደሀል አይደል የተባለዉ ሀቅ ነዉ ፡፡ እኔ ለዲኔ ጠንካራ ሆንኩኝ ለሊት እየተነሳሁ መስገድ ሱና ሶላቶች እና ሱና ፆሞችን መፆም ከጀመርኩ ቆየሁ ፡፡

ግን ሁሌ በመደጋገም ዱአ ማደርገዉ አለ ...አላህ ሆይ ከማንነቴ የሚወደኝ እኔን የሚረዳኝ የትዳር አጋር ስጠኝ እያልኩ ዱአ አደርጋለሁ

በጀመአ ዝግጅት መድረክ መሪ በሆንከበት ጊዜ ብዙ ሰዉ አይን ዉስጥ መግባት እና ለኔ ጥሩ ጥሩ ሲለሚወራ ለሰሚ ጆሮ አገኘሁ፡፡ እኔ ዝግጅት መሪ ስሆን አዳራሽ ተከራይተን ዝግጅት ስናዘጋጅ ወንዶች በመጋረጃ ተከልለዉ ይታደማሉ ፡፡ እኔ መድረክ መሪ በመሆኔ ከተለያዩ ወንዶች አድናቆት እየጎረፈ ነዉ..........፡


#ክፍል 1⃣5⃣

ይ.........ቀ.............
.......ጥ...........ላ.................ል

JOIN
           `·. www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ አስራ አምስት 1⃣5⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ





አብራኝ መድረክ የምትመራ ሰልዋ የምትባል ጓደኛ ነበረችኝ ...እሷም ብዙ ሰዉ አንቺ እንድመሪ ይፈልጋሉ ..አንቺ አቅርቢ አስተያየት ላይ ነዋል መድረክ ትምራ እየተባለ ስለሆነ አንቺ ነሽ መምራት ያለብሽ ትለኛለች፡፡ ሰልዋ አግብታለች ሁሌ አብረን ስንሆን ትዳር እንዳገባ ትመክረኛለች ..ነዋል አንቺን ብዙ ሰዉ ዳሪኝ አስተዋዉቂኝ እያሉኝ ነዉ፡፡ ትዳር ምን ያህል ደስታ እንዳለዉ ትነግረኛለች፡፡ እኔ ያገባሁት ቤተሰብ ያመጡልኝን ነዉ እንጂ ከትዳር በፊት Boy frind ብየ የያዝኩት ማንም ወንድ የለም ..ቤተሰብ ለኔ ይሆናል ብለዉ መርጠዉ ያመጡልኝ ጋር ተጋብተን በጣም ተዋደን ተፋቅረን ልጅም ወልደን እየኖርን ነዉ፡፡ ለምን ብትይ ከትዳር በፊት እንጠናና እየተባባልን ስላልተሰላቸን ይሄዉ ፍቅር ሰጥቶኝ እኔም ሰጥቸዉ እየኖርን ነዉ ትለኛለች ሰልዋ የዘወትር ምክሯ ነዉ፡፡
ሰልዋ በምትመክረኝ ምክር ምነዉ በአገባሁ እያልኩ ጥሩ ትዳር መመኘት ጀመርኩኝ...

★★★★ ከኒካህ በፊት ስለማንነታችን በደንብ እንተዋወቅ። ለትዳር ሂወታችን ጠቃሚ ስለሆነ እየተጠናና እንቆይ የሚባለው አባባል ከሸሪአ አንፃር እንዴት ይታያል?
የሴት ልጅ ክብሯ እና ውበቷ እራሷን የህዝብ ሃብት ከማድረግ መቆጠብ መቻሏ ነው፡፡ ይህን ደግሞ ሂጃብ ከማደረግ እራሷን ከመሸፈን አንስቶ ከማንኛውም አይነት አጂ ነብይ ወንድ ጋር ከኒካህ በፊት ግንኙነት ሳታደርግ መቆየት መቻሏ ነው፡፡

ወጣቱም፣አዋቂውም፣ጃሂሉም ባጠቃላይ ማገናዘብ የጀመረ ሙስሊም በሙሉ ከኒካህ በፊት ምንም አይነት ግንኙነት ማድረግ በኢስላም ክልክል መሆኑን ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ ይህን የአላህን ክልከላ አውቆ የሚርቀው ግን በጣም ጥቂቱ ነው፡፡

በኢስላም ጋብቻ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ሲሆን መልካም የሆኑ ባል እና ሚስቶችን የሚጣመሩበት ይሆን ዘንድ ያዛል፡፡ ባለጌ ባለጌን እንጂ ጨዋን እንድታገባ በኢስላም አይፈቀደም፡፡ በዝሙት የተጨማለቀ ወንድም የሱ ቢጤውን እንጂ ጥብቅ የሆነችን ሴት እንዲያገባ አይፈቀደም፡፡ ታዲያ ከጋብቻ በፊት ዝሙት እስካልፈፀምን ድረስ ይህ ክልከላ አይመለከተንም ይባል ይሆናል፡፡

መረጃውም አላህ በተከበረ ቅዱስ ቁርአኑ እንዲህ ይለናል፡-
ጥብቆች ኾነው ዝሙተኞች ያልኾኑ የስርቆሽ ወዳጆችንም ያልያዙ ሲኾኑ አግቧቸው፡(ሱራ አል ኒሳዕ፡25) ብሎ አስቀምጦልናል፡፡

ኢብኑ ከሲር በተፍሲራቸው ይህን አንቀፅ  ሲፈስሩት ጥብቆች የሆኑ ማለቱ ምንም አይነት ዚና ያልፈፀሙ እና የብልግና ተግባር ከማንም ጋር ለመፈፀም እሺ የማይሉ እና ፍቅረኛ ያልያዙትን ማለት እንደሆነ አስቀምጠዋል፡፡

ተመሳሳይ መልዕክትም በሱረቱል ማዒዳ ላይ የሚከተለውን እናገኛለን

ከምእመናት ጥብቆቹም ከእነዚያ ከእናንተ በፊት መጽሐፍን ከተሰጡት ሴቶች ጥብቆቹም፤ ዘማዊዎችና (ዝሙተኞች) የምስጢር ወዳጅ ያዢዎች ሳትኾኑ ጥብቆች ኾናችሁ መህሮቻቸውን በሰጣችኋቸው ጊዜ ልታገቡዋቸው የተፈቀዱ ናቸው፡፡(አል ማዒዳ፡5)

ይህንንም አንቀፅ አስመልክቶ ኢብኑ ከሲር(አላህ ይዘንላቸው) ሲያብራሩ ጥብቅ የሆነችን ሴት የሚለውን ከዝሙት የራቀች ፣የወንድ እጮኛ ያልየዘች መሆኑን በመግለፅ ይህ ድንጋጌ ወንዱም ጥብቅ፣ዝሙተኛ ያልሆነ፣የሴት እጮኛ ያልያዘ መሆን እንዳለበት ገልፀዋል፡፡ በዚሁ ማብራሪያቸው ላይ ብዙ እጮኛ ያለውም ሆነ አንዲት እጮኛ ተመሳሳይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በዚህ ማብራሪያ ላይ ኢማሙ አህመድ(አላህ ይዘንላቸው) ከላይ በተገለፀው አንቀፅ መሰረት ጥብቅ ያልሆነ ወንድ ወይም እጮኛ የያዘ እንደሆነ ጥብቅ የሆነችን ሴት ተውበት አድርጎ ከድርጊቱ ሳይመለስ ማግባት ለሱ የተከለከለ መሆኑን ፡፡ እንዲሁም ጥብቅ ያልሆነች ሴት፣ ወይም ወንድ እጮኛ ይዛ የነበረች ሴት ከድርጊቷ ተውበት አድርጋ እስካልተመለሰች ድረስ ጥብቅ ወይም ጨዋ ወንድን ማግባት ክልክል ነው ማለታቸውን ኢብኑ ከሲር በተፍሲራቸው ላይ ገልፀዋል፡፡

እንግዲህ ከላይ እንደተመለከትነው ሴት እጮኛም ሆነ የወንድ እጮኛ መያዝ ምን ያህል የተከለከለ መሆኑን በግልፅ ተቀምጦልናል፡፡

አብዛኞቻችን በዚህ ጉዳይ ላይ እራሳችንን የምንሸውድባቸው መገለጫዎች አሉ፡፡ ከነዚህም መካከል ይህን ሃራም የሆነ ፆታዊ ግንኙነት ሃላል ለማስመለስ ከምንጠቀማቸው ምክንያቶች መካከል. ፡- እኛ አላህ ለሚወደው የትዳር ሂወት ተሳሰብን እንጂ ለሀራም አልተፈላለግንም፣ በቅርቡ ኒካህ ለማሰር አስበናል፣ ትምህርቴን እስክጨርስ እንጂ ኒካህ ቶሎ እናስራለን፣ አንዳንድ ነገሮችን እስካስተካክል ድረስ እንጂ ሽማግሌ እልካለው፣ ቤተሰቦቼ ልጅ ነሽ ስለሚሉኝ ላይፈቅዱ ስለሚችሉ እነሱን እስካሳምናቸው ትንሽ ታገሰኝ፣ ለትዳራችን የሚሆን መኖሪያ ቤት እና ቁሳቁስ እስካሟላ ጠብቂኝ፣ በአካል እስካልተገናኘን እኮ ሀራም ላይ አንወድቅም፣ ሰው ባለበት አካባቢ ብቻ አብረን ስለምንሆን ችግር የለውም፣ ከኒካህ በፊት ስለማንነታችን በደንብ ማወቅ ለትዳር ሂወታችን ጠቃሚ በመሆኑ እየተጠናናን ነው፣ ወዘተ..የሚሉ እራስን መሸወጃ ምክንያቶችን በመስጠት በሀራም ግንኙነት ውስጥ መዘፈቁን ይቀጥላሉ..ስለሆነም በሀራም የተጀመረ ነገር በረካ ስለሌለዉ .ሁሉም ለአቅማ አዳም የደረሰ ሰዉ ትዳርና እንቅልፍ በራሱ ጊዜ ይመጣል ብሎ መሶበር ከሀራም መራቅ እና ለሌት እየተነሱ ቁርአን እየቀሩ ከሶላትም በፊትም ቡሀላም በዱአ መበረታታት አለበት፡፡ ትዳር ከፈጣሪ የሚሰጥ ፀጋ ነዉ እንጂ ከፈጣሪ ባይሆንማ በየመንገዱ ያላገባ ወንድም ሴትም መንገዱን ይመላለስበታል..ስንቱን ለትዳር እንመኛለን??ግን ብዙ ተመኘን የምናገባዉ ግን ፈጣሪ የመረጠልንን አንዱን(አንዷን) መሆኑን የማይካድ ሀቅ ነዉ፡፡


ወንድ ለብቻ ሴት ለብቻ በመጋረጃ ተጋርዶ ስንሆን እኛ ሴቶቹ ዝግጅት ስናዘጋጅ ዳቦ ተቆርሶ ወይም ዉሀ ለመስጠት ወደ ወንዶቹ ወደሚቀመጡበት ከመጋረጃ ጀርባ ላላዉ ስጪ ሒጂ አድርሺ ትለኛለች
.....እኔም አልወስድም ሌላ ሰዉ ላኪ እላታለሁ
.....ከዛም እንደዚህ ትለኛለች ነብዩ ሙሀመድ ሰ.ዐ.ወ አሚሩን የተኻለፈ የረሱልን ትእዛዝ ኺላፍ ያደረገ ነዉ ደግሞ የረሱልን ኺላፍ ያደረገ ደግሞ አላህን ኺላፍ ያደረገ ነዉ ትለኛለች፡፡ እኔም ሳልወድ በግዴ ወደ ወንዶቹ መቀመጫ ሂጄ የላከችኝን የሚበላ የሚጠጣ ነገር ሰጥቼ ወዳዉ እወጣለሁ
ሰልዋ ማታ ትደዉልልኝ እና ስትገቢ እንደዚህ የለበሰዉ አንደዚህ ያለሽ ልጅ ብዙ ምልክት ትነግረኝ እና ልጁን ሳወቀዉ እሱ ልጅ ዳሪኝ እያለ ጠይቆኛል ትለኛለች...

ሰልዋም ምን ይሻለኛል?? ለየትኛዉ እንደምድርሽ የትኛዉን እንደምመርጥልሽ ግራ ገባኝ ዳሪኝ እያሉ ብዙ ሰዉ ጠየቀኝ ተቸገርኩኝ......ትለኛለች፡፡
..እኔም ቆይ እስኪ ልሰብበት ሰልዋ እላታለሁ

  .....እኔ የምፈልገዉ ከነማንነቴ የሚቀበለኝ ..በልጅነት መደፈሬን አዉቆ ሞራሌን የሚጠብቅልኝ ነዉ .... ደግሞ እሺ ተቀራረብኩኝ የኔን ማንነት እንዴት አድርጌ ነዉ የምነግረዉ ??? እንዴት ብየ ወንዶችን እቀርባለሁ??? እያልኩ ብቻየን በሀሳብ ጭልጥ ብየ ሀሳብ ወስዶ ይመልሰኛል

አንድ ቀን ሴት ተማሪዎች ቁርአን ሀፍዘዉ ስለጨረሱ ትልቅ ዝግጅት ተዘጋጅቷል ፡፡ አንድ ወጣት ጋር ስለዝግጅቱ ሰልዋ ጋር ያወራል... እኔ ስመጣ እንተዋወቅ አለኝ
.....እኔም እሺ አልኩት
.... ካሊድ እባላለሁ አለኝ
...እኔም ነዋል እባላለሁ አልኩት
በዛዉ ተዋዉቀን እናም አብረን እሷ ጋር ሄድን👇👇👇
ካሊድ ለሰልዋ እኔን እንደሚወደኝ ለወሬ ለጅንጀና ሳይሆን ቀጥታ ሽማግሌ ልኬ ማግባት ነዉ የምፈልገዉ ብሎ ነግሯታል
....ሰልዋ እኔን ስጠይቀኝ እኔ አሁን ማግባት አልፈልግም ቤተሰብም እንድማር ነዉ የሚፈልጉት አልኳት
........ከአሁን በፊት ካሊድ ብዙ ቀን ለሰልዋ እና ለመፍቱሀ እኔን እንደሚወደኝ ነግሯቸዋል፡፡ ካሊድ እኔን ለማዉራት በጣም ይፈራኛል ..ስለእኔ ጉዳይ የሚጠይቃቸዉ ሰልዋን እና መፍቱሀን ነዉ፡፡ለትዳር ዝግጁ ከሆነች እኔን ማግባት ምርጫዋ ከሆነ ዛሬ ነገ ሳልል ሽማግሌ ልኬ ለማግባት ነዉ አላማየ እያለ ሁሌ ይነግራቸዋል፡፡

ካሊድን ባንግባባም አቀዋለሁ ባጃጅ አለዉ በኛ አካባቢ መስመር ነዉ የሚሰራዉ ፡፡ ግን በእሱ ባጃጅ ስሄድ ትኩር ብሎ ያየኛል
......ሰልዋ ቀን በቀን ካሊድን ምን አሰብሽ?? አግቢዉ እያለች ስትጠይቀኝ ካሊድ ከኔ ተስፋ እንዲቆርጥ ብየ.....ማግባት አልፈልግም ስለዚህ ጉዳይ ሁለተኛ እንዳታነሺ አልኳት

እሺ ነዋል ግን ስልክ ቁጥሯን ስጭኝ ብሎኛል እሰጠዋለሁኝ አለችኝ
....እኔም እሺ ስጭዉ የተለየ ነገር ግን አይፈጠርም አልኳት

ካሊድ ጋር የምናወራዉ በTelegram ነዉ በስልክ እኔን ለማዉራት ድምፄን ለመስማት ይፈራል
በTelegram እያወራን እኔን ማግባት እንደሚፈልግ በግልፅ ነገረኝ
........እኔም ካሊድ ተረዳኝ አሁን ማግባት አልፈልግም ትምህርቴን መማር ነዉ የምፈልገዉ ከአሁን ቡሀላ ስለትዳር እንዳታነሳብኝ ብየ ተቆጣሁት
.....ነዋል ትምህርት እኮ ከትዳር አይከለክልም አለኝ
....,ከዛ በቃ አልፈልግም ተወኝ ብየ ከtelegram ወጣሁኝ፡፡ ተነስቼ ዉዱእ አድርጌ ሶላተል ኢስቲሀራ ሰገድኩኝ ..ልክ እንደሰገድኩኝ ልቤን እፍን አደረገኝ መረጋጋት አልቻልኩም...,ወዳዉ ለካሊድ በmessage መልዕክት ላኩለት

መልዕክቱም እንዲህ ብየ ነበር የላኩለት
"""""ካሊድ ሶላተል ኢስቲሀራ ስሰግድ ልቤን አፈነኝ የሰላም ስሜት አልተሰማኝም  ስለዚህ ተረዳኝ እኔ በጭሬሽ አንተን ላገባህ አልቾልም የትዳር ምርጫየም አይደለህም አልፈልግህም""""" አልኩት
......ካሊድም የላኩለትን message አይቶት---- መልሶ እንደዚህ ብሎ ላከልኝ-------ነዋል አብሽሪ አንቺን እየጀነጀንኩሽ አይደለም ደግሞም በኔ የተነሳ እንድትጨናነቂ እንድታስቢ አልፈልግም  ፡፡ ባይሆን አንድ ነገር ብቻ ፍቀጅልኝ በሳምንት አንድ ቀን ለሰላምታ ስደዉልልሽ አንስተሽ ፈታ ብለሽ አዉሪኝ መንገድም ላይ ስንገናኝ ሰላምታ ሳቀርብልሽ ፊት እንዳነሽኝ አናግሪኝ አለኝ
....,,እኔም እሺ በዚህ እስማማለሁ አልኩት

ከካሊድ ጋር በTelegram ማዉራት ቀነስን ሁሌ በሳምንት ጁምአ ጁምአ 8:00 ሰአት ሲል ሁሌ ይደዉልልኛል ፡...ከዛም እንዴት ነሽ ቤተሰብ ሰላምናቸዉ ??ጁምአ እንዴት ነበር ?? ትምህርት እንዴት ነዉ ?? ሳምንቱ እንዴት አለፈ ብሎ ይጠይቀኛል...
....,አጠር አጠር አድርጌ እመልስለታለሁ ከ10ደቂቃ የበለጠ ሳናወራ በአጭሩ ቶሎ ወሬያችንን እንጨርሳለን ፡፡ ሁሌ ጁምአ Alarm የቀጠረ ይመስለኛል 8:00 ሲል ይደዉልልኛል ከዚህ ዉጭ ከካሊድ ጋር ሌላ በስልክ ቅርርብ የለንም

  አንድ ቀን ክላስ በነበርኩበት  ቲወሪ የተማርነዉን ፕራክቲክ የምንሰራበት የምናይበት ክፍል(Dimonstration class) ሁኜ በፕራክቲክ እየተማርን .....የማለቀዉ ስልክ ቁጥር ተደወለ
.....,እኔም ማንሳት ስላልተመቸኝ ማንሳቱን ተዉኩት
..........አሁንም በድጋሜ ተደወለልኝ ፡፡ አሁን ድረስ የሚገርመኝ ስልኩ ሲደወል ጭንቅ ጥብብ አለኝ ሳየዉ ስልኩ አስፈራኝ....ይሄ የማላቀዉ ቁጥር ማን ይሆን ????
.... እየተደወለ ሲደጋገም መምህሬን አስፈቅጄ ወደ ዉጭ ወጥቼ ስልኩን አነሳሁት........



ነዋል አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካትሁ አለኝ
...እኔም ወአለይኩም ሰላም ወራህመቷሏሂ ወበረካትሁ አልኩት
....ሰላም ነሽ እንዴት ነሽ ነዋል?? አለኝ
........አልሀምዱሊላህ
......አወቅሽኝ ??? አለኝ
....እኔም አረ አላወኩህም ማን ልበል ??
......እሱም እርግጠኛ ነሽ አላወቅሽኝም ??ይሄን ድምፄን አስታዉሺ አለኝ
......እኔም በጭራሽ ይሄን ድምፅ ላስታዉሰዉ አልቻልኩም
.....እሱም እርግጠኛ ነሽ ??
..........እኔም አዎ እርግጠኛ ነኝ
.....ማስታወስ ባለመቻልሽ ገርመሽኛል ለማንኛዉም ሚፍታህ እባላለሁ አለኝ
..... አሁንም ላስታዉስህ አልቻልኩም አልኩት
....እሱም እንዴት ???
........ብዙ ሚፍታህ የሚባሉ ሰዎችን ስለማወቅ ልለይህ አልቻልኩም
............እሺ ከእነዚህ ብዙ ሚፍታህ ስሞች ዉስጥ የማትረሺዉ የትኛዉን ነዉ ???
.....በጣም አናደደኝ ሰማሀኝ ወንድም ለጅንጀና ጊዜም ሰአትም የለኝም ተወት አድርገኝ ብየ ተቆጣሁት
.....,አትቆጪ ሲርየስ አትሁኝ ሲርየስ መሆን ለወታደር ነዉ ለዛዉም ግድ ሁኖበት ነዉ...ለማንኛዉም አሁን ክላስ ነሽ መሰለኝ ቡሀላ ደዉየ ማንነቴን በደንብ እነግርሻለሁ አለኝ
...... እሺ ብየ ስልኩን ዘጋሁት
     
ስልኩን አዉርቼ እንደጨረስኩ የሆነ ደስ የሚል ስሜት ከየት እንደመጣ የማላቀዉ ተሰማኝ ..ገና ማንነቱን ሳላዉቀዉ ደዉሎ ለስለስ ባሉ በሚያምር ድምፆቹ ስላወራኝ ብቻ ደስተኛ ሁኛለሁ ...አላህ ለኸይር ያርግልኝ ....ከዛም ወደ ፕራክቲክ ክላስ ገባሁኝ፡፡

    ከትምህርት ቤት እንደወጣሁ አሁንም ቅድም በተደወለበት ስልክ ቁጥር ተደወለልኝ ....እኔም አነሳሁት ፡፡ እንደቅድሙ ሰላምታ ከተለዋወጥን ቡሀላ
.....,አሁንስ አስታወሽኝ ??? አለኝ
......... አላስታወስኩህም አልኩት
......እሺ ካላስታወሽኝ አላህ ቀልቡን እስኪ ሰጥሽ ማንነቴን ልንገርሽ ... አንቺን ኪታብ የሚያቀሩሽ የኡስታዝ ልጅ ነኝ አሁንስ አወቅሽኝ ???አለኝ
ሚፍታህን አሁን አወኩት የተለያየ ኪታብ ያቀሩን የኡስታዛችን ልጅ ነዉ
......... አዎ አዉቄሀለሁ አልኩት
......የተለያየ ወሬ ካወራን ቡሀላ ነዋል ከአሁን ቡሀላ እደዉልልሻለሁ ከአንቺ ትልቅ ሀጃ አለኝ ...ብሎ በአፉ ተነፈሰ
......እኔም እሺ ብየ ቻዉ ተባብለን የስልክ ወሬያችንን ጨረስን
.......ሚፍታህ የኡስታዛችን ልጅ ነዉ፡፡ በፊት ኪታብ ስቀራ ይቆጣጠረኛል፡፡ .... ወንድ ጋር ካወራሁ ይመክረኛል ...የሴት መጥፎ ጓደኞች ስይዝ ተይ እነዚህ ዱርየ ናቸዉ አይጠቅሙሽም ይለኛል፡፡ ኪታብ እየሰጠኝ ቅሪ እያለ ያበረታታኝ ነበር፡፡
ከዛ ወደ ዉጭ ሀገር ለስራ እንደሄደ ሰምቻለሁ ከአየሁት ብዙ አመታት አልፈዋል ....ዛሬ መደወሉ ገርሞኛል ደግም ከአንቺ ትልቅ ሀጃ አለኝ ብሎኛል እያልኩ ብቻየን እንደ እብድ አወራ ይዣለሁ፡፡ ገና በመጀመሪያ በደወለልኝ ቀን የሆነ መግለፅ የማልችለዉ ብዥታ አእምሮየን አናወዘዉ...ይገርማል


#ክፍል 1⃣6⃣
ይ........ቀ.............
......ጥ........ላ................ል


JOIN
´´´´´´´ :¨·.·¨: ❀ share
           `·. www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ አስራ ስድስት 1⃣6⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ




ገና በመጀመሪያ በደወለልኝ ቀን የሆነ መግለፅ የማልችለዉ ብዥታ አእምሮየን አናወዘዉ...ይገርማል


ማታም ልተኛ ስል ደወለልኝ እያወራን ነዉ........ቀን በቀን ቀን ማታም መደዋወሉን ከሚፍታህ ጋር ተያይዘንዋል ለምን በፊት ስለምንግባባ ለማዉራት እሱም እኔም አንፈራራም ፡፡ በቀላሉ እንደ ሴት ጓደኛ እንደምናወራዉ ያህል የእኔ እና የሚፍታህ ቅርርብ ወሬ እንደዛ ሆነ.........

አንዴ በስልክ እያወራን ነዋል ትልቅ ሰዉ ሁነሻል አሉ ፎቶሽን አሳይተዉኝ እኔ የማቅሽ ልጅ እንደነበርሽ ስለሆነ ነዋል አይደለችም እስከማለት ደርሼ ነበር በግድ አመንኩኝ... የሇላዉ መጣ እና የፊቱን ቀደመዉ እኛ እናሳድጋለን በቃ እናንተ ግን ያሳደጋችሁን ትረሳላችሁ ብሎ አሳቀኝ
...,ኪታብ ምን እንደምቀራ ጠየቀኝ ነገርኩት
....,እሱን ስጠይቀዉ አዲስ አበባ ነዉ የምኖረዉ ፡፡
ትምህርትም የተማርኩት አዲስ አበባ አዉልያ ኢስላማዊ ትምህርት ቤት እና ቁርአን የሀፈዝኩትም አዲስ አበባ ነዉ፡፡ አሁን የምሰራዉ ከቻይና ከዱባይ እቃ እያመጣሁ አዲስ አበባ ማከፋፈል ነዉ አስመጭ እና ላኪ ሁኜልሻለሁ አለኝ፡፡ ...አልሀምዱሊላህ ሒወት መስመር ይዛልኛለች ግን አንድ ነገር ብቻ ጎዶሎ ሁኖብኝ ያለኝ ብር ንብረት ደስታ አልሰጠኝም ጎዶሎ እንደሆንኩ ይሰማኛል አለኝ
.......እኔም ምንድን ነዉ የጎደለህ?? አልኩት
.........,እሱም ትዳር የለኝም ማግባት እፈልጋለሁ ...ደግሞ የማገባዉ.አንቺ የመረጥሽልኝ ከጀመአ ልጆች  ነዉ የምፈልገዉ ፈልጊልኝ  አለኝ
.....እኔም አብሽር ጣጣ የለም አንድ ላይ ሁነን እንፈልጋለን አልኩት፡፡
ግን ትዳር በፍለጋ ይገኝ ሁን ?ትዳር ቀልድ ነዉን?በኔ ፍለጋና በሚፍታህ ሀሳብ ይሳካ ይሆን?ለምን ትዳር በባህሪዉ መረጋጋት ትዕግስት ቆም ብሎ ማሰብ ያስፈልጋል፡፡
★★★ትዳር በባህሪው ትግዕስትን ይፈልጋል ኢማንና ፍቅርን አላማቸው አድርገው ባንድላይ ለመሆን የወሰኑ ሰዎች መደማመጥን ሀሳብን መቀባበል ካልቻሉ በዘመናችን ከእሾህ እንደተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅሱና ሲያማርሩ እንዲሁም ደስታና ሰላም የሸሸው ህይወትን ሲገፉ ይኖራሉ።

   ዛሬ ዛሬ አያሌ የዘመኑ ወጣቶች ትዳርን አስበውበትና ወስነው ሳይሆን በዘፈቀደ ለጊዜያዊ ስሜት ብለው የሚገቡበት መሆኑ በጉልህ የሚታይ ነው ጋብቻ እርቆ ማሰብና ማሰላሰልን ብሎም መወሰንን ይጠይቃል።

ይሁንና ጋብቻ ሲጀመር ብዙ ውጣ ውረድ እንዳለው የሚዘነጉ ቀደም ብሎው ያላሰቡበት አንዳንዶች ገና ከጅምሩ በጋብቻቸው የተደላደለ ኑሮን ለመኖር ይፈልጋሉ፡፡ የትዳርን ትክክለኛ ገፅታ ማየት ተስኗቸው ትዳርን በየዋህነት የሚጀምሩ ሰዎች ትዳር እንዳሰቡት ሳይሆን ሲቀር ያለው አማራጭ የያዘውን ትቶ ሌላ ለመሞከር እንድ ሁለት ማለት ይሆናል ፡፡በመሆኑም ፍቅርንና ኢማንን አላማቸው አድርገው በትዳር ተሳስረው ለመኖር የወሰኑ ሰዎች በሰርጋቸው ማግስት ወይም በቀጣዩ የትዳር ህይወታቸው ውስጥ ግራ የሚያጋቡና ተስፋ የሚያስቆርጡ የስሜት አለመጣጣም የፋላጉት አለመርካት የአመለካከትና የልምድ ማነስ ልዩነቶች የሚታይበት ሊሆን ይችላል።

#ይሁን_እንጂ ትዳራቸውን እንደ አላህ ፍላጎትና ትዕዛዝ የጀመሩ ከመሆናቸው የተነሳ ለጊዜያዊ ችግር ብለው ወደ ፍቺ (ትዳርማፍረስ) አይሮጡም፡፡ ከዚህ ይልቅ ለገጠማቸው ችግር አላህ ሱበሀን ወተአላ ከልብ እየተማፀኑና የተፈጠረውን ችግር ለመቅረፍ አብረው ይሞክራሉ .... አንዱ የሌላውን ሃሳብ ለመቀበልና የታየውን ድክመት በይቅርታ ለማለፍ ፍቃደኞች ይሆናሉ። ይህም ትዳራቸው አስደሳች ህይወትና ረጅም ዕድሜ እንዲኖረው ለማድረግ ከማንም የተሻለ ዕድል ይሰጣቸዋል። ጋብቻ የተከበረ የህብረተሰብ የመጀመሪያ ተቋም እንደመሆኑ መጠን

ይህ ተቋም ያማረና የተስተካከለ እንዲሆን የአላህ
እዳርታ የግድ ስለሚሆን አላህ ሱበሀን ወተዓላ መለመንና መማፀን ያፈልጋል።አላህም በቁርአኑ ይህን አስመልክቶ እንዲህ ይላል

«ጌታችን ሆይ! ከሚስቶቻችንና ከዘሮቻችን ለዓይኖች መርጊያን ለእኛ ስጠን፡፡ አላህን ለሚፈሩትም መሪ አድርገን» የሚሉት ናቸው፡፡

በዚህ መልኩ የትዳር ህይወትን ከጀመሩ በኋላ ስለአንድነታቸውና ፍቅራቸው በጋራ ዱዓ በማድረግ መትጋት ይኖርባቸዋል ስለትዳራቸው በግልፅና በታማኝነት አብሮ መወያየትና መነጋገር ከቻሉ ዓላማቸው የሚሰምር መሆኑን ተስፋ እናደርጋለን የሚያጋጥሟቸው ችግሮችም በአላህ ሱበሀን ወተዓላ ፊቃድ ይወገዳሉ። ፈጣሪ ሚፍታህ ያሰበዉን አይነት ትዳር ለኔም የተፃፈልኝን አሳካልን ብየ በዱአ ተያይዣለሁ ፈጣሪ ይገዝሽ በሉኝ


      ሚፍታህ ከበፊቱ በበለጠ እያወራን ነዉ ማርሽ መጨመር እንጂ መቀነስ አይታሰብም ፡፡
ሚፍታህን ዲነኛ አዋቂ አድርጌ ነዉ የማስበዉ..ለምን ቁርአን ሀፊዝ ነዉ በተጨማሪም አዉልያ ኢስላማዊ ትምህርት ቤት ነዉ የተማረዉ በቂርአቱም በዲኑም በትምህርቱም ጎበዝ ስለሆነ ምነዉ ለኔ በሆነ ብየ ተመኘሁ፡፡፡

አንድ ቀን ሚፍታህ እንደዚህ አለኝ የአንቺን ስልክ ቁጥር የሰጠኝ የሱፍ ነዉ ነዋልን አዉራልኝ ብሎኝ ነዉ አለኝ...
.....እንዴ የሱፍ ጋር ትግባባላችሁ እንዴ ??? አልኩት
......,እሱም አዎ አንድ ነገር ልንገርሽ እኔ አንቺን የማወራሽ የሱፍን በfb አላወራዉ ስላልሽዉ ነዉ በጣም ነዉ የሚወድሽ ሁሌም ስንደዋወል ነዋል እወዳታለሁ እባክህ አንተ የኡስታዝ ልጅ ስለሆንክ፡በፊት ትግባባላችሁ ....አሁንም አንተ የምትላትን ስለምትሰማ በዛ በዚህ ብለህ አሳምንልኝ ብሎ ስልክሽን ሰጥቶኝ ነዉ አለኝ......
.......ጉድ ነዉ በጣም አጀበኝ ...የሱፍ ማለት እዚሁ ጂማ የሚኖር ጎረቤታችን ነዉ፡፡ የሱፍ ብዙ ጊዜ Facebook ላይ ያወራኛል እኔ ግን ከ10ክፍል ቡሀላ fb ላይ ማዉራት አይመቸኝም.... እሱ ቢያወራኝም ለማዉራት ቢፈልግም እኔ ግን አላወራዉም ፡፡

የሱፍ የሰራዉ ስራ በጣም አናደደደኝ እኔን ከፈለገኝ እኔን ከወደደኝ እኔን ማግባት ከፈለገ ፍቅር እና ትዳር ሰዉ የሚገባበት ወይ እኔ እምቢ ስል ነዉ እንጂ የሱፍ እኔን ማግባት እየፈለገ እንዴት ለሚፍታህ ነዋልን የወደፊት ሚስቴ እንድትሆን አመቻችልኝ ይላል ???? በጭራሽ የማይደረግ ነዉ የሰዉ ልጅ መጀመሪያ ግልፁን መናገር ነዉ እንጂ በታዋቂ ሰዉ ወይም በታዋቂ ሰዉ ልጅ እንደዚህ አይነት ስራ መስራቱ በእኔ አስተሳሰብ የወረደ እና በጣም የሚያሳፍር አስተሳሰብ ነዉ፡፡
እኔም ያወራኝ ለራሱ አለመሆኑን ሳዉቅ ከሚፍታህ ተስፋ ቆረኩ ....እኔም አሁን ላይ አላገባም መማር ነዉ የምፈልገዉ....  እናም አደራ የሱፍን እንደማልፈልገዉ መቼም እንደማላገባዉ ከኔ ተስፋ እንዲቆርጥ ንገረዉ አልኩት፡፡
....ሚፍታህም እሺ ካልፈለግሽ እምቢ ብላለች አልተሳካም ብየ እነግረዋለሁ አለኝ፡፡

ሚፍታህ ለሌላ ልዳርሽ ከሚለኝ እኔ ላግባሽ ቢለኝ በጣም ደስ ይለኝ ነበር....ምን ይደረጋል ነበር ሁኖ ቀረ፡፡ አንድ ነገር ይገርመኛል ሴት ልጅ የምትወደዉን ስትከተል የሚወዳትን ታጣለች ይባላል ካሊድ ላግባሽ ብሎ ስንት እንዳለመነኝ እኔም እምቢ እንዳላልኩኝ ..ግን ሚፍታህ ገና ለወደፊቱ ላግባሽ ቢለኝ ደስታየ ነዉ ምንም ሳላቅማማ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ👇👇👇
ሚፍታህ አላማዉ እኔን ማዉራት የጀመረዉ ለየሱፍ እኔን ድሮኝ ...እኔ ደግሞ ብዙ ጓደኞች ስላሉኝ ከእነሱ መካከል አንዷን እኔዉ መርጬ እንድድረዉ ይመስለኛል ......ወይም አይታወቅም የሰዉ አስተሳሰቡ በየሱፍ አሳቦ እኔን የሱ ማረግ ፈልጎም ሊሆን ይችላል.....
  በመነገታዉ ሚፍታህ ደዉሎልኝ ለየሱፍ ነዋል አልተስማማችም ከአቅሜ በላይ ነዉ ብየ በስልክ ነግሬዋለሁ አለኝ.... ነገር ግን እኔና ሚፍታህ አሁንም ማዉራት አላቆምንም...እንደዉም ከበፊቱ በባሰ መልኩ እያወራን ነዉ፡፡

   ደግሞ በተዘዋዋሪ ካሊድ  ከኔ ተስፋ አልቆረጠም ሁሌም ጅንጀና አይሆንለትም....ካሊድ ግልፁን እንደሚወደኝ እና ለወደፊት እኔን ማግባት እንደሚፈልግ ይነግረኛል....ሁሌም ጁምአ እየደወለ ነዋል ተረጂኝ እኔ ጅንጀና አይሆንልኝም  .... ነዋል አንድ ጥያቄ መልሽልኝ ምን አይነት ባል ነዉ የምፈልገዉ ??? አለኝ

.......እኔም ብዙ ሴቶች ሲጠየቁ የሚመልሱትን መልስ መለስኩለት_እኔ የምፈልገዉማ የተማረ ዲን ያለዉ ኪታብ የቀራ ከምንም በላይ  የሚወደኝ የምወደዉ የሚሳሳልኝ ልጅ ወልደን በፍቅር አብረን መኖር የምንችል እና ""እስከ ማንነቴ የሚቀበለኝ"" አልኩት....
.....ካሊድም:- ነዋል አንድ ነገር ልታዉቂ እፈልጋለሁ >>>>>አንቺ የሆንሽዉን ብትሆኝ ሁለት ጊዜ ባል አግብተሽ ብፈቺ አምስት ልጅ ቢኖርሽ ለኔ ምንም አይደል...እኔ የምፈልገዉ አንቺ የኔ እንድትሆኝ ብቻ ነዉ የምፈልገዉ<<<<<< አለኝ
....ካሊድ እኔን ከማንነቴ የሚቀበለኝ ይመስለኛል...ነገር ግን በጭራሽ ዉስጤ ሊቀበለዉ አልቻለም .....ከካሊድ ጋር ከብዙ ንትርክ ቡሀላ  ከእኔ ተስፋ አልቆርጥ ሲል በዉሸት እኔ የዉጭ ሀገር ፕሮሰስ ጀምሪያለሁ አሁን ማግባት አልችልም ብየ በዉሸት ተስፋ አስቆረጥኩት....
....ካሊድም ሳይወድ በግዱ እሺ አለኝ ግን ያዉ ስለትዳር ባናወራም ጁምአ ጁምአ ይደዉልልኛል

በተዘዋዋሪ ደግሞ ሚፍታህ ጋር ሳወራ ደስታየ ነዉ ምነዉ እወድሻለሁ ላግባሽ ባለኝ እያልኩ እነዚህን ቃላቶች ቢነግረኝ ምኞቴ ነዉ
እንደዚህ እያለ የኮሌጅ አንደኛ አመት እና ክረምቱም በዚሁ  አለፈ ....ሁለተኛ አመት የኮሌጅ ትምህርት ጀመርን አሁንም ከአህመድ ጋር እያወራን ነዉ፡፡

አንድ ቀን እንዲህ አለኝ...>>>>ነዋል ማግባት እፈልጋለሁ የአሁኑ አመት ላይ የመጀመሪያ እቅዴ ማግባት ነዉ ለኔ የምትሆነዉን ምረጭልኝ<<<<አለኝ
......እኔም ምን አይነት ሴት ነዉ የምፈልገዉ ?? ከጓደኞቼ በመስፈርትህ መሰረት መርጬ ፎቶ እና ስልኳን ልኬልህ ከተግባባችሁ ትጋባላችሁ ግን መስፈርትህ ምንድን ነዉ?? አልኩት

.....እሱም እሺ መስፈርቴ ቁመቷ ልክ እንደ አንቺ.. መልኳ ልክ እንደ አንቺ.. የትምህርት ደረጃዋ. ዲኗ እድሜዋ..ልክ እንደ አንቺ ሁሉ ነገሯ ልክ እንደ አንቺ አለኝ፡፡
ግን ልክ እንደ አንቺ ማለቱ ምን ማለቱ ነዉ <?<<? እያልኩኝ ግን የእኔን ጓደኛ መፍቱሀን ለምን አልድረዉም?? ምክንያቱም የኔ ሒወት መስመር እንዲይዝ ያረገችኝ.....ከኔም የተሻ የዲን እዉቀት አላት ብየ አሰብኩኝ
.......,,እኔም ሚፍታህን እየወደድኩት እሱን ማጣት ሳልፈልግ ሂጄ መፍቱሀን ለሚፍታህ ልዳርሽ አልኳት
......መፍቱሀም እኔ አልፈልግም አለችኝ...እሷም እኔ እንደምወደዉ ከአነጋገሬ ከሁኔታየ ተረድታኛለች ግን ነዋል ለምን ሚስት ፈልጊልኝ ከሚልሽ ለምን አንቺን አያገባሽም ??? እንዲህ የሚልሽ አንቺ አግባኝ እንድትይዉ...የአንቺን  ቃልሽን እየጠበቀ ይሆናል አለችኝ....
ወደዳችሁም ጠላችሁም ሚፍታህ በስልክ በተደጋጋሚም ስለምናወራ ልቤ ተሰርቋል አጉል መቀራረብ ፍቅር የሚባል ጦስ ይዞ ይመጣል..

የበፊት ያለፉት ምርጥ ትዉልዶች ፍቅርን እንዴት ነበር የገለፁት እስኪ ከዚህ የንጉስ የፍቅር አገላለፅ እንመልከት
★★★ ሕንድን የከፈተዉ ሱልጣን ጋዛሊን ማህሙድ በጣም ተወዳጅ የሆነ አገልጋይ ነበረዉ...ስሙ ሙሀሙድ ይባላል ሱልጣን ማህሙድ አገልጋዩን የሚጠራዉ ሙሀመድ በሚለዉ መጠሪያዉ ሲሆን አንድ ቀን ግን በአባቱ ስም ጠራዉ
..በዚህ የሱልጣኑ ድርጊት ልቡ የተሰበረዉ አገልጋዩ ሱልጣኑ ለምን በአባቱ ስም እንደጠራዉ ሲጠይቀዉ
>>>>>>>>የምወድህ ልጄ!! ሁልጊዜም በስምህ ስጠራህ ነዉ የኖርኩት .. #በእነዚህ_ጊዚያት_ሁሉ_ዉዱዕ_እያለኝ_ነበር የጠራሁህ...ሆኖም ግን አሁን በአባትህ ስም በጠራሁህ ቅፅበት ዉዱዕ አልነበረኝም..ዉዱዕ ሳላደርግ ይሄን የተባረከ ስም ሙሀመድን መጥራት ስላሳፈረኝ ነዉ በአባትህ ስም የጠራሁህ በማለት ይቅርታ ጠየቀዉ፡፡


ይሄን ያህል ለተወዳጁ ነብዩ ሙሀመድ ሰ.ዐ.ወ ፍቅር ነበራቸዉ ዉዱእ ሳይኖራቸዉ የተከበረ ስማቸዉን ለመጥራት ለራሱ ይሄን ያህል ፍቅራቸዉ በልባቸዉ ገብቶ ያከብራቸዉ ይወዳቸዉ ነበር...ዛሬ ግን ስማቸዉን በቀላሉ አንስተን ከልብ ባልመነጨ ፍቅር በነሽዳ በተራ ሙነሺዶች ...በተራ የሰርግ ነሽዳ አድማቂ ተብየ ወጣቶች በዱአዉ በነሽዳዉ ሙሀመድ ነብየ ስንል እንዉላለን ሁሉም ከአንገት በላይ ነዉ..እስኪ እራሳችንን እንፈትሽ የነብዩን ልጆች ሁሉንም በቃላችን ሸምድደናል??ነብዩ በስንት አመታቸዉ ነዉ ነብይ የሆኑት??የነብዩ ሚስቶች ጥቀሱ ብትባሉ ስንቱን መጥቀስ እንችላለን?? ከነብዩ ምርጥ ሱሀቦች ስንት እናዉቃለን?? በስንት አመተ ሂጅራ ተወለዱ ?? ወዘተ የተለያዩ ጥያቄዎችን እራሳችንን እንፈትሽ፡፡ አሁን ላይ ገና እንቦቅላ ወጣት ተነስቶ ነሽዳ አወጣሁ ብሎ ሙሀመድ ነብየ ሲል ይስታወላል..ሰዉ በተዉሂድ መተናፅ ሲገበረዉ ሙነሺድ ተብየዎች ሰዉን ለማዘናጋት በቃል ብቻ የቀረ ከሆድ ያልገባ ዉዴታ ነቢይ ነቢይ እወድወታለሁ እያሉ ነሽዳ ሲያወጡ አብረዉ ሽርካ ሽርኩን ጨምረዉ ህዝቡን በጭፍን ሲመሩት እያየን ነዉ ...ግን የነብዩ ዉዴታ ይሄ ነዉ?? በፊት የነበሩ ምርጥ ትዉልዶች ግን ሙሀመድ የሚለዉን ስም ዉዱዕ ሳይኖራቸዉ ለመጥራት ይከብዳቸዉ ነበር እኛ ግን አብሮ ቂጣ እንደበላ ጓደኛ ስማቸዉን ስናነሳ እንደ ጩጫን እንኳ ክብደት አልቆጠርንም ...??እኛ ዉዴታን የምንገልፀዉ የማይጠቅም ግን ብዙ የሚጎዳ ነሽዳ እያዳመጡ አብሮ ሙሀመድ ነብየ ማለት ነዉ ?? ዉዴታ በነሽዳ ነዉ የሚገለፀዉ ??
ነብዩ ሙሀመድ ሰዐወ እኔን የሚወደኝ የሰራሁትን ስራ ይከተል ብለዋል...ዉዴታ የሚገለፀዉ እሳቸዉ የሰሩትን ስራ በመስራት ነዉ... መቼ ነዉ ሁላችንም ከኔ ጀምሮ ተዉሂድ ለመማር ፍቃደኛ የምንሆነዉ??ተዉሂድን ተምረን ትክክለኛ የእሳቸዉን መንገድ ተከትለን የእሳቸዉን መዉደዳችን የምናረጋግጠዉ?? ሁሉም መልሱን በልቡ ይመልስ....
   

ሚፍታህ ጋር  ማዉራቱን ተያይዘንዋል.... ረመዷን ደርሷል ፡፡ በዛዉም coc ፈተና ስለነበረኝ እየተዘጋጀሁ ነዉ፡፡

በጊዜ ሒደት አንድ ቀን እንዲህ አለኝ ነዋል ለየሱፍ ቢያወራሽ በጭራሽ እንዳነግሪዉ አደራ :-እኔ ለየሱፍ ልድርሽ ነበር ያሰብኩት .... ምርጫሽ እሱ ካልሆነ ካልፈለግሽዉ እኔ ላገባሽ እፈልጋለሁ ነዋል ወላሂ ከምሬ ነዉ አንቺን ማዉራት ከጀምርኩ ቡሀላ ወላሂ በልቤ ገብተሻል እወድሻለሁ አለኝ.....

 
#ክፍል 1⃣7⃣
ይ...........ቀ............
.......ጥ...........ላ..........ል

Join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ አስራ ሰባት 1⃣7⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ





ነዋል ከምሬ ነዉ አንቺን ማዉራት ከጀምርኩ ቡሀላ ወላሂ በልቤ ገብተሻል እወድሻለሁ አለኝ.....

 
እኔም የሰማሁትን ማመን አቃተኝ ... ተክዞ የተኛዉ ጆሮየ ቀጥ አለ....በጣም ደስ አለኝ የምሆነዉን አሳጣኝ...አቁነጠነጠኝ...መቼም በስልኩ ድምፅ ነዉ እንጂ የዛን ጊዜ ሚፍታህ ቢያየኝ ተገርሞም ስቆም አያበቃም ነበር ...ይሄን ደስታየን በግድ መዋጥ አለብኝ ሴት ነኝ እና ደስታየን መቆጣጠር አለብኝ
.....አረ ሚፍታህ አቀልድ አልኩት
...........ወላሂ ከምሬ ነዉ ነዋል ደግሞ ጊዜ መስጠት አልፈልግም ቶሎ ሀላሌ እንድትሆኝ ነዉ የምፈልገዉ፡፡ Coc ከተፈተንሽ ቡሀላ ቤተሰቦቼን ነግሬ ሽማግሌ እልካለሁ አለኝ፡፡
...........እኔም እሺ ልሰብበት ጊዜ ስጠኝ አልኩት..ብዙ ሴቶች እየወደድን ቶሎ እሺ ማለት ሴትን ልጅ ያስንቃል ብለን እናስባለን እየወደድኩም ቢሆን መግደርደር የሴትነት ወጉ ስለሆነ እኔም ልቤ እየፈለገ አፌ ልሰብበት የሚለዉን አስቀደምኩኝ ፡፡

ከ ከ3ቀን ቡሀላ ሚፍታህ ደዉሎልኝ የጠየኩሽን ጥያቄ ምን ወሰንሽ ??? ብሎ ጠየቀኝ
......እኔም እሺ ተስማማቻለሁ አልኩት
ሚፍታህ በጣምምም ተደሰተ በስልክ ደስታዉን ሊቆጣጠረዉ አልቻለም....የእኔም ደስታ ከሱ ቢበልጥ እንጂ አያንስም ...ይገርመኛል የኔዉ ሞኙ ልቤ ከካሊድና ከየሱፍ አስበልጦ ለሚፍታህ ትኩረት ሰጥቷል፡፡

ሚፍታህ ረመዷን ሲያበቃ ኢንሻ አላህ ለኢድ ጅማ መጥቼ በአካል እንገናኛለን አለኝ፡፡
.....እኔም ለሚፍታህ ለጠየቀኝ ጥያቄ መልሴ እሺ ብቻ ሁናል፡፡ ረመዷን ደረሰ ሚፍታህ ጋር ሁሌ ማታ ማታ እናወራለን ፡፡ ከማዉራታችን ብዛት አንዳንዴ ተራዊህ የማልሄድባቸዉ ቀናቶች ነበሩ...

ረመዷን አልቆ ኢድ ላይ ደርሰናል....ሚፍታህም ኢድን ቤተሰብ ጋር ለማክበር ከአዲስ አበባ ጅማ ተከስቷል.... ጅማ የኢድ ሶላት የምንሰግደዉ ጅማ ስታዲየም ነዉ.... ሰግደን ስንወጣ በስልክ ተደዋዉለን ለመጀመሪያ ጊዜ ሚፍታህ ጋር ተገናኘን . . እኔ እና ሚፍታህ ስንገናኝ ሁለት እህቶቹ ጋር አብሮ ነበር....አንዷ እህቱ የወንድሜ ሚስት ነዋል እንዴት ነሽ ብላ ሳመችኝ
.....እኔም ሚፍታህን እያየሁ በእህቱ ሁኔታ ተግባብተን ሳቅን
....ከመስገጃ ቦታዉ እየተመለስን ስለ አንዳንድ ነገሮች እያወራን ነዉ....ሚፍታህም እንዲህ አለኝ ፡- ነዋል ሁሉንም ቤተሰቦቼን እናቴም አባቴም እህቶቼም አንቺን እንደማገባ እቤት አሳዉቂያለሁ አለኝ ...
....ግን እናቴ አንቺን እንዳገባ አልተስማማችም አለኝ
.......እንዴት ላትስማማ ቻለች ??አልኩት
...........ነዋል እኮ ከ10ኛ ክፍል ቡሀላ አድጋ ነዉ እንጂ ገና ልጅ ናት ...አለችኝ አለኝ
...... እና ምን አልካት ??? አልኩት
............ነዋል ነዉ ማግባት የምፈልገዉ አሁን ትልቅ ሰዉ ሁናለች ቁመት ብጨምርም አብራ አስተሳሰብ ጨምራለች የትናንቷ ልጅ አይደለችም ብየ አሳኳት አለኝ
.......እናቴም፡- እሺ አንተ የወደድከዉን እኔም እወዳለሁ ብላ በኔ ሀሳብ ተስማማች አለኝ
እንደዚህ እየተጨዋወትን በደስታ ሁለታችንም በወሬ ፍንክንክ ብለን እኔን እቤቴ ሸኝቶኝ እሱም ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
 
በዚሁ በኢድ ቀን የሚፍታህ እናት እና አባት የኔን ቤተሰቦች ሊዘይሩ እኛ ቤት መጡ፡፡
ከበፊትም ጀምሮ የእኔ ቤተሰቦች እና የሚፍታህ ቤተሰቦች በጣም ይግባባሉ፡፡ በተለይ ደግሞ የኔ አባት እና ኡስታዝ(የሚፍታህ አባት)በጣም ይቀራረቡ  ይዋደዳሉ፡፡ አባቴ የሆነ ሀሳብ ሲይዘዉ..ግራ የሚያጋባ ጉዳዮች ሲገጥሙት የሚፍታህን አባት ብዙ ጊዜ ሲያማክር አስታዉሳለሁ፡፡

ሚፍታህ ቀን በቀን በደወለ ቁጥር ይቼ ቃላት ምላሱ ላይ አብራ የተሰፋች ነዉ የሚመስለዉ ... #እወድሻለሁ_አፈቅርሻለሁ ሳይለኝ ዉሎ አድሮ አያቅም ...እኔም ይሄን ቃል ስሰማ ደስታኛ እንደሆንኩ ይሰማኛል... አሁን ዘመን ላይ ፍቅርን በአፋችን ስንገለፀዉ ለምላስ የብናኝ ያህል ክብደት አይኖረዉም ..እዉነተኛ ፍቅር ግን ማን ነዉ መግለፅ የሚችለዉ?? ስለፍቅር ምን በአንተ አስተሳሰብ ግለፅ ብላችሁ መቶ ሰዉ ብትጠይቅ የመቶዉም ሰዉ ስለፍቅር ያለዉ አመለካከት የተለያየ ነዉ ...ግን ለምን ይሆን በብዙ ሰዉ ልብ ያለን ፍቅር ቃላት ለመግለፅ የማይችለዉና ..ቃላቱ ሶስት ቃላት ናቸዉ #ፍቅር ግን ስለፍቅር ምን ትላለህ ሲባል ፍቅርን በቃላት መግለፅ አልችልም ሲሉ ይደመጣሉ..አንዳንድ ሙሁር ተብየዎች..ገጣሚዎች..ዘፋኞች ..ፍቅርን በማይታይ ህልም ሲስሉት እናስተዉላለን..ግማሹ የሰዉነቷን ክፍል ቆራርጠዉ አይኗ ከዋክብት..ጥርሷ ነጭ በረዶ ..ሷቋ የፀሀይ ጮራ ቁመቷን ተራራ..አፍንጫዋን ጥሩ መአዛ ብቻ የሚቀበል መጥፎ ሽታን የሚያስወግድ ..ችቧ አይሞላም ወገቧ ማር እሸት ነዉ ቀለቧ እየተባለ ..ወዘተ ብለዉ ሲጠቆሱት እያየን ነዉ...ግን ይሄ አገላለፅ ፍቅርን ይገልፀዋል ወይ??

★★★አንዳንድ ሠዉ ስለ ሌላ ሰዉ በዚህ ፍቅር ተብየዉ እየተጨነቀ ያስብና እየተቆጨ ይኖራል..በእርግጥም ሌላ ሠዉ መልካምን ለማድርግና ችግሩን ለማቅለል መጨነቅ ማሰብና መቆጨት መልካም ነዉ.
.
.
ማፍቅር መልካም ነገር ነዉ* አላህ በሰዎች መካከል የሚስቀምጠዉ ደስታን፣እርካታን የሚያጣጥሙት የሂወት ቅመም ነዉ ይህ ፍቅር ግን ያለቦታዉ ገብቶ የማይዋልበት ቦታ ሲገባ ስቃይና መከራ ይሆናል.
..
ከመፍትሄ ይልቅ ችግር ከእረፍት፣ ይልቅ ስቃይ ፣ከደስታ ይልቅ ሀዘንን ያበዛል .በተለይ በልጅነት ሂወት ላይ ሲከሰት መካራዉ ይደራረባል ሂወት አጭር ናት ከትደሰትክባት በሚል የተሳሳተ ተስፋ አጭሯን ሂወት ለስቃይና ለመከራ የሚያደርግ ስስት ዉስጥ ይገባል .
"
"
በጓደኛም ይሁን በአይን ስህተት* በጅንጀናም ይሁን በዉሸት ፍቅር የያዛቸዉ ይህንን ፍቅር የሚሉትን ስሜት ለማስታገስና ለማከም የማይገባዉ ጉድጓድ ዉስጥ ይገባሉ .ለመዉጣት ደግሞ መዉጫ ቀዳዳ ይጠፋል ..

:
ለማናዉቃቸዉና ለማንተማመንባቸዉ ጊዜ አዊይ ስሜቶች የማናዉቀዉን የማንተማመንበት ጣፋጭ ሂወት እናበላሻለን ከሸይጧን ግፊት ለሚደረግበት ስህተት ፍቅር በሚል ሽንገላ ከአላህ ሽልማት የሚጠበቀዉን እድል እናፈርሳለን...ግን ለዚህ ሁሉ መፍትሄዉ ፍቅርን በሰዎች ሁሉ ለሰጠዉ ፈጣሪ አመስግኖ መጀመሪያ ፍቅርን ለሰጠን ፈጣሪ ፍቅሩን ለፈጣሪ ከሰጠነዉ ሁላችንም አሸናፊዎች ነን፡፡ ፍቅርን ሳናባክን መጀመሪያ የሰጠንን ፈጣሪ አንርሳ ለምን የሰጠንን ነገር ሁሉም የሚቀመጠዉ በሂደት ነዉ...
መጀመሪያ ማስቀመጥ ያለብን ለፈጣሪ መሆን ሲገባዉ ነገር ግን ይሄን የመጀመሪያ እድል ለፍጡር ከተደረገ የፈጠረህን ፈጣሪ ሀቅ አጉድልሀል ..ባለቤቱ አምጥቶ አደራ ብሎ አስቀምጦ የሄደዉን ለሌላ ለማያገባዉ ከሰጠን ጥፋቱ አደራዉን የካደዉ ነዉ ...አደራችንን የሰጠንን ፈጣሪ እያስታወስን እናስቀምጥ፡፡ የዛን ጊዜ እኛ በፈጣሪ እገዛ አሸናፊዎች ነን፡፡

      ከኢድ ቀን ቢያነስ ከ15 ቀናት ቡሀላ የሚፍታህ አባት እንደ ሽምግልና ባይሆንም የአባቴን ሀሳቡን መረዳት ያክል እሳቸዉ እና የሚፍታህ አጎት ሁነዉ አባቴ እቤት ባለበት ሰአት መጡ....

ለአባቴ -------እኔና ሚፍታህ በአንድ ጎጆ ለመኖር መጨረሳችንን ሁሉንም ነግረዉት ግን የአንተ ፍቃደኝነት ያስፈልጋል .... ሚፍታህ ልጅህን ነዋልን ማግባት ይፈልጋል ፍቃደኛ ነህ ወይ ??? ብለዉ ጠየቁት👇👇👇
አባቴም:- ኡስታዝ እናንተ መጥታችሁ እንዴት እምቢ እላለሁ ??? እሺ ተስማማቻለሁ ነገር ግን ነዋል የሁለተኛ አመት ተማሪ ናት ዘንድሮን ትማር ከዛም ሶስተኛ አመቷ ላይ ኒካህ ያስራሉ ከዛም ትምህርት ስጨርስ ቀጥታ ይጋባሉ ብሎ አባቴ አስተያየት አቀረበ .
...የሚፍታህ አባትም መርሀባ ተስማምተናል ብለዉ የኔ እና የሚፍታህን ወደ ትዳር የምንገባበት ፈትል መፈተል ተጀመረ፡፡

ሰዉ ሁሉ ጆሮ ደረሰ ሚፍታህ እና ነዋል ሊጋቡ ነዉ ተብሎ በእኛ ሰፈር በአንዴ ተናፈሰ፡፡ ካሊድም ይሄዉ ወሬ ጆሮዉ ደረሰ
ካሊድም በtelegram እንዲህ ብሎ ላከልኝ
""' ወሬዉን ሰምቻለሁ አንቺ ደስተኛ ከሆንሽ ጥሩ ነዉ ..ግን አንድ ነገር እወቄ ልታገቢ ነዉ ተብሏል ነገር ግን መቼም ቢሆን እኔ ከአንቺ ተስፋ አልቆርጥም.. #ከአሏህ_ጋር_የኔ_እንደምትሆኝ_ተስፋ_አልቆርጥም አለኝ """"
   የሚፍታህ ጓደኛ የሱፍ ይሄን ወሬ ሲሰማ ከባድ ፀብ ተፈጠረ ....ሚፍታህን እገለሀለሁ አንተ ከሀዲ ጓደኛየ ነህ አምንሀለሁ ነዋልን እወዳታለሁ አንተ ጠይቅልኝ ብልህ እኔን አብሮ አደግ ጓደኛህን አሞኝተህ ሸዉደህ ለራስህ ልታገባት ነዉ አይደል ...አማናሀን በላህ ቃልህን በላህ አንተ ከሀዲ መቼም ቢሆን አንተን አለቅህም ብሎ ዝቶበት ከቤተሰብ ድረስ የደረሰ ከባድ ፀብ ተጣሉ፡፡
   
ከአሁን በፊትም እኔ ሚፍታህ በስልክ በምናወራበት  ጊዜ የሱፍ መረጃዉ ደርሶት ብዙ ጊዜ ተጣልተዋል፡፡ ጂማ ሲመጣ እና በአካል ሲገናኙ ደግሞም የትዳር ወሬዉን ሲሰማ የሱፍ መቋቋም አልቻለም፡፡ 

   እኔና ሚፍታህ የየሱፍ ፉከራ ድንፋታና እገልሀለሁ ቢልም በስልክ ማዉራታችን ተያይዘንዋል...እንደዉም ከበፊቱ በበለጠ መልኩ ስለወደፊቱ የትዳር ሒወታችን እያወራን ነዉ ...በስልክ ስንደዋወል ነዋል ስንት ልጅ ከኔ መዉለድ ትፈልጊያለሽ???ይለኛል
...እኔም አንተን ደስ የሚልህን ያህል እወልድልሀለሁ እለዋለሁ
..እኔም በተራየ ሚፍታህ ስንት ልጅ መዉለድ ትፈልጋለህ??? እለዋለሁ...
...እሱም አንቺ መዉለድ እስከምታቆሚ እወልዳለሁ ይሄን ያህል ማለት አልፈልግም ይለኛል ..

    የብዙ ቀን የደስታ ህይወት በሰከንዶች ወደ ሀዘን የሚቀይረዉን ጌታ ኩን በሚለዉ ቃሉ ዱንያ የደስታ ህይወት መኖሪያ ስላልሆነ የሀዘን ማቅ ያኮናንባል .. በቀናት በሰከንድ በደቂቃ ምን እንደሚፈጠር አናቅም ..በሀያሉ አሏህ ትዕዛዝ በአንድ ሰከንድ የስንት አመት ደስታን ማደብዘዝ ሲችል. በተዘዋዋሪ ደግሞ በአንድ ሰከንድ የብዙ አመታት ስቃይ ለቅሶን ወደ ደስታ መቀየር አይሳነዉም ..ታዳ በጊዜ ብዛት ሚፍታህ የሚያወራዉ ወሬ የማይሆን ለጆሮ የሚቀፍ ሆነብኝ ..ይህን አዲስ ባህሪ ከየት አመጣዉ እስከምል ድረስ ፀባዩ ተቀያየረብኝ ..... ስልክ ስንደዋወል እንዲህ ማለት ጀመረ>>>>>>

#ነዋል_ሚስቴ_ድንግል_ካልሆነች_መቼም_አፍርባታለሁ፡፡ የእኔ ሚስት ሁሌም ምኞቴ ድልግል እንድትሆን ነዉ..ባለፈዉ  ጓደኛየ አግብቶ  ሚስቱ ቢክራ ባለመሆና በጣም ተናዷል....እኔ ሚስቴ ቢክራ ባትሆን ሳልዉል ሳላድር ቀጥታ ለቤተሰቦቿ ነዉ የምመልሳት....
.....ጓደኛዉን ስሙን እየጠቀሰ እንትና ጓደኛየ ሚስት ቨርጅን ናት .. እንዴት ደስ እንዳለዉ ልነግርሽ አልችልም ጓደኛየ አሁን ድረስ ወሬዉ ሚስቴ እኮ ቢክራ አገኘሁባት እናንተ የምታገቡትን ሚስት አይቼ እያለን ነዉ ይለኛል.... በስልክ በተከታታይ ቀናት በደወለ ቁጥር የጓደኞቹን የትዳር ገጠመኝ ይነግረኝ ይዟል...

ስለጓደኞቹ ታሪክ ይተርክልኝ ይዟል .. ሚስቶቻቸዉ ጋር የተጣሉበት ምክንያት ምን እንደሆነ ...ከጓደኞቹ ሚስቶክ ቢክራ የሆኑት ማን እንደሆኑ እና ቢክራ ያልሆኑት ማን እንደሆኑ ታሪካቸዉን ይተርክልኛል ፡፡
....እኔም ሁሌም ታወራላችሁ ማለት ነዉ ስለዚህ ጉዳይ ??ብየ ጠየኩት
....እሱም አዎ ግድ ነዉ ጓደኞቼ ሚስጥር አይደብቁኝም እኔም አልደብቃቸዉም አለኝ

ሚፍታህ እንደዚህ ሲለኝ የኔ እጣ ፈንታ ምንድን ነዉ ???ነገ እኔም ስንጋባ ቨርጅን አይደለሁም አይቤን ለጓደኞቹ ሊያወጣብኝ ነዉ ማለት ነዉ፡፡ ሚፍታህ እኔን እስከማንነቴ አይቀበለኝም ብየ እራሴን አሳመንኩት፡፡ እየወደድኩት እያፈቀርኩት በልጅነቴ ስለተደፈርኩ ድንግል አይደለሁም ብየ ራሴን አሳምኜ ሚፍታህን ልለየዉ ወሰንኩኝ...



በልጅነቴ የደፈረኝን ቶፊቅን በመጥፎ ጎኑ እያሰብኩ ስሙን በመጥፎ እያነሳሁ ብቻየን መኝታ ክፍሌ ቁጭ ብየ አይኔ ቀይ ሸክላ አፈር እስኪመስል ድረስ አለቅስ ይዣለሁ😢😢.....ምን ይደረጋል ማንነት በእምባ አይመለስም...ፈሶ አያልቅ ወይ ከዚህ ጭንቀት አይገላግለኝ ..ይሄን ሁሉ የዘረገፍኩት እምባ አላህን ፈርቼ አንድ ቀን ባለቅስበት ስንት ሀጃየን ያሳካልኝ ነበር??ብየ አስባለሁ
ከአሁን ቡሀላ በአላህ ተወኩል ማድረግ አለብኝ አላህ ያለዉ ይሆናል ካልሆነ ይቀራል ብየ እራሴን አሳመንኩ...አላህ ያለዉ ሚፍታህ ለኔ ካለዉ ከነማንነቴ ከተቀበለኝ በሩ ክፍት ነዉ ካልሆነም አላህ የተሻለ ይሰጠኛል ብየ ሙሉ በሙሉ ሁሉ ነገሬን ለአሏህ ሰጠሁኝ...ይሄ የድንግልና ጉዳይ ሲነሳ ጉልበቴ የሚፍረከረከዉ እምባየ የሚፈሰዉ ለምንድን ነዉ?? ሰነፍ ደካማ መሆን የለብኝም እምነቴን ሙሉ በሙሉ ለአላህ መስጠት እንዳለብኝ እራሴን አሳመንኩኝ

    ሁሉን ነገር አየሁት ደስተኛ የምወደዉን አግብቼ ደስተኛ  ለመሆን ሞከርኩ አልተሳካም የብስ ስቃይ ይዞብኝ መጣ... ለሊት ቀን በቀን በመነሳት አልቅሼ ዱአየን አድርጌ ሁሉንም ሀጃየን ለአላህ ሰጠሁኝ

.....የእኔም የሚፍታህም ቤተሰቦች ሁለታችን እንድንጋባ ተጠይቆ እሺ ስለተባለ ..እኔ ደግሞ ሚፍታህ ከትዳር በፊት
እኔ በልጅነቴ ስለተደፈርኩ የዛ ጠባሳ ሳያንሰኝ በሚናገራቸዉ ቃላቶች  ልቤን እያደማዉ እያቆሰለዉ  ስለሆነ ...የጓደኞቼ ሚስቶች ቢክራ ናቸዉ ሚስቴ ቢክራ ካልሆነች በምላሹ እናቷ ቤት ነዉ የምልካት እያለ በተደጋጋሚ ስለነገረኝ ...ሚስት ብሎ እኔን ምርጫዉ አርጎኛል የእሱን መስፈርት ስለማላሟላ
ሚፍታህን አሳማኝም ሆነ የማያሳምን የተለያዩ ለፀብ ለቁርሾ የሚሆን ስበብ ፈልጌ አንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ልርቀዉ ወሰንኩኝ .........


#ክፍል 1⃣8⃣
ይ.............ቀ............
.........ጥ............ላ..............ል


JOIN
´´´´´´´www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ አስራ ስምንት 1⃣8⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ



ሚፍታህን አሳማኝም በሆነ የማያሳምን የተለያዩ ለፀብ ለቁርሾ የሚሆን ስበብ ፈልጌ አንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ልርቀዉ ወሰንኩኝ .........
በተለያዩ ዘዴዎች አዉቄ ሁለታችንን ሊያጣላን የሚችል ጥፋት እያጠፋሁ ነገር እየፈለኩት በራሴ ጥፋት ሚፍታህን መጣላት ጀመርኩኝ....ግን በተጣላን ማግስት ሚፍታህ ከቤቴ ስወጣ መንገድ ላይ እየጠበቀ በራሴ ጥፋት ይቅርታ አርጊልኝ  ይለኛል

በተለያዩ ዘዴዎች የዉሸት ምክንያቶች እየደረደርኩ ብዙ ጊዜ አስቀየምኩት ግን ሚፍታህ ይቅርታ አርጊልኝ እያለ ሊርቀኝ ከኔ ተስፋ ሊቆርጥ በጭራሽ አልቻለም.....

ከትንሽ ቀን ቡሀላ ሚፍታህ ለስራ ጉዳይ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ ፡፡ አሁን ሚፍታህን በአካል አላገኘዉም በስልክ ብቻ ነዉ የምንገናኘዉ...ለመለያየት ከኔ ተስፋ ለመቁረጥ ጥሩ ጊዜ ነዉ ብየ አሰብኩኝ ...ለእኔም ለሚፍታህም የሚጎዳ ከባድ ዉሳኔ ወሰንኩኝ....

ሚፍታህ ከልቡ ቆርጦ እንዲጠላኝ ስልኩን block አረኩት ... ምክንያቱም እሱን ባወራሁት ድምፁን በሰማሁት ቁጥር የበለጠ እየወደድኩት እያፈቀርኩት መሀባዉ እየጨመረብኝ ሄደ ፡፡ ደግሞ በዚህ ሁኔታ ሁኜ መለየት አቅቶኝ እያለቅሱኩኝ ከዚህ በላይ ደግሞ ብወደዉ አብጄ ልብሴን መቅደዴ አልቀረም.
ፍቅር ግን ምንድን ነዉ የበፊት ምርጥ ትወልዶች፡ፍቅርን እንዴት ነበር የገለፁት??? መጀመሪያ የፍጡራን ፈጣሪ የሆነዉን የአለማት ጌታ ለአላህ ነበር ፍቅራቸዉ..እስኪ የዚችን ንፁህ ልብ ያላት ወጣት የፍቅር ታሪክ ልጋብዛችሁ

★★★ ኡመር(ረ.ዐ)በመዲና ጎዳናዎች ላይ በጨለማ ሲዘዋወሩ አንድ ቤት አጠገብ ሲደርሱ እናት እና ልጅ ሲከራከሩ ይሰማሉ
እናት፡-ልጄ ሆይ ነገ ከምንሸጠዉ ወተት ላይ ጥቂት ዉሀ ጨምሪበት
ልጅ፡-እማዬ ኸሊፋዉ ኡመር ወተት ላይ ዉሀ እንዳንጨምር ከልክለዉናል ትላታለች እናቷን
እናትም፡-ኸሊፋዉ እኮ አሁን የምንሰራዉን አያየንም አለቻት
ልጅም፡ አላህን በመፍራት ለእርሱ ባላት ፍቅር ልቧ የተሳበዉ ወጣት እንዲህ አለቻት ..እናቴ ሆይ!!!ይህን ድርጊታችንን ኸሊፋዉ ባይመለከተንም ከአላህ ግን ልንደብቀዉ አንችልም አለቻት፡፡
ልጅቱ ለእናቷ የሰጠቻት መልስ ኡመርን በቆሙበት ቦታ በሲቃ ናጣቸዉ፡፡ ከዛም ሲነጋ ቤቱ የማን ቤት እንደሆነ አረጋግጠዉ ያቺን ልጃገረድ ልጃቸዉ እንዲያገባ ሁኔታዉን አመቻቹለት፡፡ ምክንያቱም ልጅቱ ለአላህ የነበራት ፍራቻ ከርሷ የሚጠበቅ አልነበረምና፡፡ ከእነዚህ ጥንዶች የተወለደዉ በኢስላም አምስተኛዉ በትክክል የመራ ኸሊፋ እንደሆነ የተመሰከረለት ኡመር ኢብኑ አብደል አዚዝ የተገኘዉ፡፡ እናቱ አላህን ፈሪ ስለሆነች በዛ ተርብያ ስላሳደገችዉ ለዲነል ኢስላም መሪ የሆነ ልጅ አበርክታለች....እንደዚህ ለአላህ የነበራቸዉ ፍቅር ላይ ያለፉ ትዉልዶች ስንት ስቃይ አሳልፈዉ እኔ ግን በሚፍታህ ፍቅር እርብሽብሽ ለቅሶ በለቅሶ ሁኛለሁ

... እኔም እንዲህ ብየ አሰብኩኝ
>>>> #ትዳር_ለኔ_አልተፈጠረም_ቢክራ_ስላልሆንክ_የወደድኩትን_ሰዉ_ማግባት_አልችልም<<<<<<<ብየ ከሰዉ በታች እንደሆንኩ ሁሌ ይሰማኛል፡፡

 
.....ሚፍታህ በጭራሽ ከኔ ተስፋ ሊቆርጥ አልቻለም ፡፡ በተለያዩ የተለያዩ ሰልክ ቁጥር ቢደዉል ቢደዉል እኔ አላነሳ ስለዉ በእናቴ ስልክ ይደዉላል ፡፡
እናቴም፡- ሚፍታህ ነዉ ነዋልን ፈልጊያት ነዉ አገናኚኝ እያለ ነዉ በስልክ አግኝዉ ስትለኝ
እኔም፡- አሁን ማናገር አልፈልግም እላታለሁ......

በሌላ ስልክ ሲደዉል እንደ አጋጣሚ ካነሳሁት የእሱ ድምፅ መሆኑን ስሰማ አላናግረዉም......እንዲዚህ እያልን 3ወር ያህል የሚፍታህን ድምፅ ሳልሰማ block እንዳደረኩበት ጨከንኩበት፡፡


አንድ ቀን አባቴ ብር አሰግቢ ብሎኝ ብር ላስገባ ባንክ ቤት ሄድኩ.. የአላህ ነገር ሁኖ ሚፍታህ ጋር ባንክ ቤት ተገናኘን
.....ነዋል አሰላሙ አለይኩም አለኝ
....እኔም ያልጠበኩት ነገር ነዉ ደንግጬ ወአለይኩም ሰላም አልኩት
.........የሚገርም ነዉ ገና ትናንት ከአዲስ አበባ መጥቼ ነዉ .ከአዲስ አበባ የመጣሁበትም ምክንያት ለአንቺ ብየ ነዉ ምን ሁነሽ ነዉ ስልኬን block ያረክሽዉ ??
አሁኑኑ ስልኩን ከblock አንሺዉ አለኝ
....እኔም ዉሳኔየ ነዉ አሁን አላነሳዉም አልኩት
.......ሚፍታህም ባንክ ቤት ተገልጋዮች ባሉበት ሰዉ ፊት ነዋል ምን አድርጌሽ ነዉ Block ያረግሽኝ??ምን አርጌሽ ነዉ ??? ጥፋት ካለኝ እዚሁ ሰዉ በተሰበሰበበት ጥፋቴን ንገሪኝ ፡፡ እኔ ወላሂ በጣም ነዉ የዎወድሽ አንቺን አጥቼ መኖር አልፈልግም አንቺን ተለይቶ መኖር ልቤ መቼም አይፈቅድልኝም.. ለምንድን ነዉ ብሎክ ያረግሽኝ??? እያለ ሲጮህ
በጣም ደነገጥኩኝ
....ሚፍታህም ጥፋት የለብኝም ሰዉ ፊት ነዉ ጥፋቴን የጠየኩሽ አሁኑኑ አይኔ እያየ block አንሺዉ አለኝ
...እኔ ደንግጫለሁ ብሎኩን አንስቼለት ቶሎ ብየ ከባንክ ቤቱ ወጣሁ፡፡

ከዚህ ቀን ቡሀላ የሚፍታህ ፀባይ አስተሳሰብ የተቀየረ መሰለኝ..በጣም የሚወደኝ ያለኔ መኖር የማይችልም መሰለኝ.....እንደበፊቱ በስልክ ማዉራት ጀመርን ፡፡ እቤት አባቴ በትምህርትሽ እንዳትሳነፊ  ብዙ ስልክ ማዉራት ቀንሱ ተብሎ ተከልክለናል...የማወራዉ ተደብቄ ነዉ ፡፡ እንደበፊቱ ብዙ ነገሮች ማዉራት ጀመርን ያዉ በወሬ በወሬ እኔ የምሸማቀቅበት አንገቴን የምደፋበት ስለትዳር እና ስለ ድንግልና እኔን በቀጥታ መጠየቅ ቢፈራኝም ግን በተዘዋዋሪ እንደበፊቱ የጓደኞቹን ታሪክ እያነሳ ያወራኛል
....እኔም ይሄ ወሬ መደጋገም ሲበዛብኝ ..ምራቄን ዉጬ እንዲህ አልኩት
ሚፍታህ እኔ እንደምጠብቀኝ አይነት ልጅ አይደለሁም ከኔ የተሻሉ ብዙ ሴቶች አሉ ሌላ ሴት አግባ ...እኔ አንተ ላቀረብካቸዉ የትዳር መስፈርትህ ማሟላት አልችልም አልኩት...
...እሱም ነዋል እንደዚህ አትበይ ከአንቺ የተሻለ ሴት መቼም አላገኝም እወድሻለሁ እኮ ..አንቺ የኔን የትዳር ዉሳኔ አሁን መወሰን አትችይም እኔ አንቺን መርጫለሁ ወደ ሆላ አትመልሽኝ ፡፡ በፀባይ በዲን በአስተሳሰብ ከአንቺ የተሻለ አላገኝም ይለኛል፡፡

እኔ በልጅነቴ ልደፈር አልደፈር ይወቅ አይወቅ የማቀዉ ነገር የለኝም፡፡ ግን የሱፍ ያቃል ..የሱፍ ታስታዉሱ እንደሆነ ገና ታሪኩ እንደጀመረ ልጅ ሁኜ ተራዊህ ልንሰግድ ገብተን እናቴ ነዋል በልጅነቷ ተደፍራለች ብላ ነግራኛለች ብላ የተጣላሇት ልጅ እህቱ ናት( part ➎ላይ ያለችዉ ልጅ) ፡፡
የሱፍ የኔን ታሪክ ያዉቃል..ግን ለሚፍታህ ይንገረዉ አይንገረዉ የማቀዉ ነገር የለኝም...

ግን ሚፍታህ ጋር በአወራን ቁጥር የእኔ ባለቤት ድንግል ካልሆነች ቀልድ የለም ይለኛል ..እንደዚህ ሲል መደፈሬን አልሰማም ማለት ነዉ ብየ አሰብኩኝ... ግን አሁን ድረስ ግራ የሚገባኝ ለኔም ያልተመለሰልኝ መልስ ሚፍታህ ስለኔ ያቃል አያቅም??የሚለዉ የተወዛገባ ሀሳብ በጭራሽ መልስ ላገኝለት አልቻልኩም....ብቻየን በሀሳብ ማዕበል እጓዛለሁ ..ግን ምን ዉሳኔ እንደምወስን ይጨንቀኛል ..ደግሞም ልንገረዉ ብየ እወስንና እንዴት ብየ ልንገረዉ??እያልኩ ደግሞ ሀሳብ ይሆንብኛል ግን ያለኝ አንድና አንድ ብቻ ነዉ ...ካልደፈረሰ አይጠራም በልጅነቴ መደፈሬን ለመንገር ወሰንኩኝ

ሚፍታህ ሲደዉልልኝ ከዛሬ ነገ ልንገረዉ?? መቼ አልንገረዉ ???እያልኩ እኔዉ ለራሴ ሀሳብ ሆነኝ እንዴት ብየ ልንገረዉ???...ዉይ ሒወት የስቃይ ማዕበል👇👇👇
የሒወቴ ከባዱ ፈተና ይህ አመት ነዉ

ልጅ ሁኜ ትምህርት ቤት ያለዉ ተፅእኖ ያሳለፍኩት አሁን ካለሁበት ሳነፃፅረዉ በልጅነቴ ሲሰድቡኝ ሲጠቋቆሙብኝ የነበረዉ ቀላል ነዉ ...የኔን ማንነት ለማያቅ ሰዉ ነገ አብሬዉ ለምኖረዉ ለትዳር አጋሬ እንዴት ብየ ነዉ ድንግል አለመሆኔን የምነግረዉ ??
እኔ እወደዋለሁ እሱም ይወደኛል ለመጋባት በመሀከላችን ምንም የሚያጣላን የሚያለያየን ነገር የለም ..ነገር ግን የኔን ማንነት ይቀበለኛል ወይ ? ?? አግብቼ ከሚፍታህ ጋር በዚሁ ምክንያት ከትዳር መለያየት ቢመጣ ነዋል አግብታ ፈታች እየተባለ የቡና መጠጫ ወሬ እሆናለሁ ...

ደግሞ እኔን የሚያቁኝ ሰዎች ከሌሎች ሴቶች ለኔ ቦታ አላቸዉ በትምህርቷ ጎበዝ ናት፡ ዲን አላት ፡ጥሩ ፀባይ አላት ፡ ጅልባብ ለባሽ ናት ብሎ ማንኛዉም ሰዉ ይመሰክርልኛል....ነገር ግን ዉስጤ ያለዉ ቁስል ነዶ የማያልቅ የፉም እሷት ጨብጬ ይዣለሁ ...እንዴት አርጌ ልንገረዉ ??? እያልኩ ብቻየን መጨነቅ መኝታ ክፍል ሁኜ ማልቀስ ሁኗል ስራየ

ሚፍታህ ተወኝ ብለዉ አይተወኝም...,,ደግሞ ካልተወኝ ለወደፊት ግንኙነታችን ለመጋባት ስለጨረስን ይሄን ነገር ማወቅ አለበት ...ከተጋባን ቡሀላ ድንግል አለመሆኔን ያዉቃል ከዛ ምን ይፈጠር ይሆን ???እላለሁ 

ለሊት እየተነሳሁ ረከአተይን ሰግጄ ዱአ አደርጋለሁ ... ደግሞም በማንኛዉም ሰአት እና ከሶላት ቡሀላ ዱአ አደርጋለሁ...የሚገርማችሁ ነገር ይሄን ዱአ በመደጋገም አደርግ ነበር >>>

#አላህዋ_መርየመን_ያለድንግል_ማንም_ሳይነካት እንድትወልድ ያረካት ጌታ ሆይ የመርየምን ድንግል ለኔ ስጠኝ<<<<<<<< ብየ ብዙ ጊዜ አልቅሼ😢😢😢 ዱአ አድርጌያለሁ በሒወቴ ከባዱ ገጠመኝ በማንነቴ ያለቀስኩበት የተጎዳሁበት አመት ይሄ አመት ነዉ ፡፡

ኮሌጅ የሁለተኛ አመትን እንደዚህ ነበር ያሳለፍኩት....እናም አመት ዙሮ ረመዷን ቢደርስም የዚህ አመት ረመዷንን በመጨናነቅ በማሰብ አሰለፍኩኝ.....አስከትሎም ኢድም አልፎ ዛሬ ልንገረዉ አልንገረዉ እያልኩኝ ስወዛገብ ሳለቅስ ኑሬ ...... ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለመንገር ተዘጋጀሁ...ለመንገር ለሚፍታህ ልደዉል ስልኬ ከተቀመጠበት ሳነሳ በእጄ እንዳለ ስልኬ ጠራ ..የደወለዉም ሚፍታህ ነዉ፡፡

ስልኩን አንስቼ ሰላምታ ከተለዋወጥን ቡሀላ
.....ነዋል ልሄድ ነዉ አለኝ
.........,,እኔም ልቤ እየደነገጠ የት ነዉ የምትሄደዉ ??አልኩት
...እሱም አረፋን የምዉለዉ ሀጃጆች ጋር ነዉ.. በዚህ አስር ቀን ዉስጥ ሳዉዲ አረቢያ ሀጅ ልሄድ ነዉ ከሀጅ ስመለሰ እናወራለን እዛ ሁኜ በimo እና telegram እንገናኛለን አለኝ......
...እኔም እሄዳለሁ ሲለኝ ደንጋጤም ጥርጣሬም አስቤ ነበር ..ተረጋግቼ መርሀባ አላህ ያሳካልህ ሀጅህንም ይቀበልህ እኔም ብዙ ሀጃ አለኝ በዱአህ አትርሳኝ አልኩት
....እሱም አልረሳሽም አለኝ

ሚፍታህ ለሀጅ ወደ ሳዉዲ አረብያ ሄደ ..ሳዉዲ ከገባበት ሰአት ጀምሮ እኔ እዛ የሄድኩ እስኪመስለኝ ሳዉዲን በየሄደበት በtelegram እና በimo video እየቀረፀ እየላከ ያሳየኛል፡፡ ጠዋፍ ሲያደርግ..ሶፋ እና መርዋ ላይ ሲወጣ..አረፋ ተራራ ..ስንቱን ላዉራዉ ሀጅ በሚያደርገበት ቀን በቀን ያለዉን ሁኔታ እስከሚመለስ ድረስ በimo እየላከ ያሳየኛል፡፡ አሁን ላይ ሁኜ ሳስበዉ ሀጅ የሚሰራዉ ሀጅ አደረገ ለመባል ነዉ ወይስ ግዴታ አላህ እንደአዘዘዉ ሰርቶ ወንጀሉን እንዲማር ነዉ ??
እስኪ እንደዚህ አድርጎ ያረገዉ ሀጅ ከአላህ ጋር ተቀባይነት ያገኝ ይሆን ??? እላለሁ፡፡ ታዳ ይሄ አይነት አላህን ይፈራል ብሎ መገመት ይቻላልን??


ታዳ እንደሚፍታህ ያሉ ሀጃጆች ስንት ስራቸዉን አበላሽተዋል??? ቤት ይቁጠረዉ ..አላህ ሆይ አንተ ያዘዝከንን ስንሰራ ከሰዉ ምስጋናን ሳይሆን የአንተን ሀቅ አሟልተን ከአንተ ሽልማት የምናገኝ አድርገን

ሚፍታህ ሀጅ አድርጎ ሲመጣ ጂማ የሚገኘዉ መርካቶ ሰፈር ኤሌክትሮኒስ ሱቅ ከፈተ ...ታላቅ ወንድሙ ከዉጭ ሀገር እቃ ይልካል አንድ ወንድሙ አዲስ አበባ ይሸጣል ለሚፍታህ ደግም ወደ ጅማ ይላክለታል.....ሚፍታህ ኑሮዉንም አዚሁ ጅማ አደረገ ፡፡ ለኔ በጣም ደስ አለኝ በስልክ ሳይሆን ሲናፍቀኝ አይኑን ማየት እችላለሁ ብየ አሰብኩ፡፡


አንድ ቀን እለቱ ቅዳሜ ቀን ነዉ የኔን ማንነት በልጅነቴ መደፈሬን ልንግረዉ ብየ እራሴን አሳምኜ ደወልኩለት
....... ስልኩን አነሳዉ
............ሰላምታ ከተለዋወጥን ቡሀላ ሚፍታህ ዛሬ ትልቅ ሚስጥር ነዉ የምነግርህ ..አደራህን የምነግርህን ተረዳኝ በነገርኩህ ነገር ተቀይመህ ወይም እኔን እንደአሰብከኝ አለመሆኔን ስታቅ ከአንተ አፍ የሚወጣዉ ቃላት እኔን አንተን የሚወደዉን ልቤን እንዳያደማዉ ተጠንቀቅ ..እኔ ለአንተ ያልነገርኩህ ብዙ የሚያስጨንቁ በሆዴ የታፈኑ ማንነቶች አሉኝ..አንተ እኔን እንደምታስበኝ ሴት አይደለሁም.. የአንተ የትዳር መስፈርትህ እኔ ካለኝ ማንነት ጋር በጣም ሰፊ ልዩነት አለ አልሆንህም .....እያልኩ ወደ ዋናዉ ቁም ነገር መደፈሬን ልነግረዉ ከአፌ ላወጣዉ ስል...,ሚፍታህ ወሬየን አስቆመኝ
.....ነዋል ወሬዉን አቁሚዉ እና አሁኑኑ በአካል እፈልግሻለሁ እቤት ነይ አለኝ.....
.....እኔም እሺ ብየ ከጠየቀኝ አንድ ባንድ እነግረዋለሁ ብየ ወደ ቤቱ ሄድኩኝ

... እቤቱ እንደደረስኩ ያየሁት ነገር አይኔን ማመን አቃተኝ...እኔ ያሰብኩት ሌላ የሚሆነዉ ሌላ ነዉ
.......ሚፍታህ ቢያንስ ከ6 የሚበልጡ ጓደኞች ባሉበት ነዋል እወድሻለሁ አፈቅርሻለሁ አንቺን አጥቼ መኖር አልፈልግም  ይሄዉ በጓደኞቼ ፊት እመሰክርልሻለሁ ...,በተጨማሪም አንድ የማረሳዉ ንግግር እንዲህ አለኝ
>>>>>>እኔ ዲንጋይ እመስልሻለሁ እንዴ ???እንደፈለኩ እወድሻለሁ አፈቅርሻለሁ ስል ቆይቼ ተወኝ ስትይኝ የምተወዉ አንስተሽ የምትወረዉሪኝ ዲንጋይ እመስልሻለሁ እንዴ ???እኔ የፍቅር የመዉደድ ስሜት የለኝም እንዴ??" ...እኔ አልሆንህም ስትይኝ እኮ ልቤ እየደማ ነዉ ነዋል እባክሽ ሌላ ፈልግ አትበይኝ እንደዚህ ስትይኝ ፍቅርሽ ያሳደረብኝ ዉጋት እየጨመረብኝ ነዉ <<<<<<አለኝ፡፡

እኔም እንደዚህ ሲለኝ ሆዴ ባባ አሳዘነኝ እሺ ከአሁን ቡሀላ እንዲህ አልልህም አልኩት

ወደ ቤቴ ተመለስኩ ... ማታ ተኝቼ ዛሬ ሚፍታህ እቤቱ ሂጄ በነገረኝ ቃላቶች አስተነተንኩኝ እንደሚወደኝ እርግጠኛ ሆንኩ በጓደኞቼ ፊት ነዉ ቃል የገባልኝ... ሚፍታህ እንደዚህ ቢለኝም ግን ይሄ ማንነቴን መናገር አለብኝኝ ግዴታየ ነዉ ....በልጅነቴ መደፈሬን ተገናኝተን ሻይ ቡና እያልን ከአንድ ሳምንት ቡሀላ ልነግረዉ ወሰንኩኝ ፡፡ከአንድ ሳምንት ቡሀላ ልነግረዉ የወሰንኩት ዛሬ በተናገሩኝ ቃላቶች እኔ አልሆንህም ሁለተኛ እንዳትይኝ ስላለኝ ደስታዉን በዚህ ሳምንት ላለማደፍረስ በማሰብ ነዉ፡፡

  ከአንድ ሳምንት ቡሀላ ይሄን ጉዳይ ለመንገር ... ስደዉልለት ስልኬን block አድርጎታል.....በጣም ግራ ገባኝ በጓደኞቼ እና በሌላ ሰዎች ስልክ ስደዉልም የኔ ድምፅ መሆኑን ሲሰማ ጆሮየ ላይ ይዘጋብኛል.. ስልክ ማንሳቱንም አቆመ ..
ምክንያቱን በማላቀዉ መልኩ ሚፍታህ የእኔን ስልክ block አረገዉ የጓደኞቼንም አያነሳም...በጣም ግራ ገባኝ ምን ይሆን ምክንያቱ ????

#ክፍል 1⃣9⃣
ይ..........ቀ.......
....ጥ..........ላ............ል

    www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
2024/10/03 04:36:53
Back to Top
HTML Embed Code: