Telegram Web Link
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በዉብ ቃሪዕ የቁርአን ግብዣ
ያዳምጡት ...ሼር አይዘንጉ

https://www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
#እኔ_ሆይ_ተይ_በቃ 🤦‍♀
#የቆራጧ_ሴት_ማስታወሻ_በግጥም

እኔ ሆይ ተይ በቃ እራስሽን አትደልይ
ገብቶሽ እንዳልገባው እውነትን አትከልይ
••• ትናንት •••
ለማይሆንሽ ፍቅር
ይሆናል በማለት ደክመሻል ታመሻል
የራስሽን ትተሽ ስለሰው ኑረሻል
መሳቅ ሲኖርብሽ ተክዘሽ በማልቀስ
እድልሽን ስትረግሚ ወዲህም በመውቀስ
ከደስታ ተጣልተሽ ተላምደሽ ከብሶት
መከረኛ ጎንሽ ናፍቆ ድሎት ምቾት
ከሰው በመገለል በብቸኝነት ጎን
አንገትሽን ደፍተሽ ገፍተሻል ብዙ ቀን
አሁን ያ ቀን አልፏል
አንቺ ግን ቁመሻል
ለምን? ለምን ? ለምን ? 🤔
እንዴትስ በዚህ ልክ እኔነትሽን ጣልሽ
ነቅተሽ እንዳልነቃ ካላንቀላፋሁ አልሽ
•••• ትናንት ••••
መሄድ ቻልኩ ብለሽ መድረሻሽን ሳትለይ
እንዲሁ ስትጓዥ በግምት መንገድ ላይ
ሳደርሽ ሲመሽብሽ ድካም ስታተርፊ
በዋዛ ፈዛዛ እድሜንሽን ስትገፊ
ድሮን አባክነሻል ፈቅደሽም ጥለሻል
አዎን ሀቁ ይህ ነው ልቦናሽም ያውቃል
••• ትናንት ••••
ያለቦታሽ ሁነሽ ከማይሆንሽ ስፍራ
ቅን የዋህነትሽ ተቆጥሮ እንደተራ
እንደ ሞኝ ተስለሽ በጅላጅል ቀለም
ወርደሽ ከደረጃሽ ቁመሽ ከሰው አለም
ሲያወሩሽ እያመንሽ
ሲያዙሽ እያደረግሽ
እንዳሉሽ እየሆንሽ
ያንቺን ሂዎት ጉዞ ሌላ እየወሰነው
አንቺ እንዳንቺ ሳትኖሪ ጊዜን አባከንሽው
ዛሬ ግን ይበቃል
ግቢ ለራስሽ ቃል
ያለፈውን ንቀሽ ቆጥረሽ እንዳበቃ
እንዳዲስ ለመኖር ወስኝ አሁን በቃ
ከመጣሽው መንገድ ይግባሽ ከንቅፋቱ
ንቂ ከቅዠትሽ ተፋጠጭ ከውነቱ
ላንቺ አይመጥንሽም ሳይኖሩ መሞቱ
ተንቀሳቀሽ እኔ ወደፊት ተራመጅ
የተወሽን ትተሽ ከአቻሽ ተሰደጅ
በተኖረ ታሪክ ባለፈ ትዝታ
መጪውን አትጋርጅ
አዎ አሁን ይበቃል 🚶‍♀
እኔ ሆይ ተይ በቃ እራስሺን አትደልይ
ገብቶሽ እንዳልገባው እውነትን አትከልይ
#ሼን

Join👇
https://www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ሁሉም_ሴት_አንድ_ነው 🤔

ሰው ተርቤ ሳለሁ በቀድሞው ጉዳቴ
ድንገት ቀርባኝ እሷ ባዋያት ካንጀቴ
ታጋርታ ጭንቀቴን ሁና ልክ እንደኔ
ከናለ ስጋቴ መሆን ሽታ ጎኔ
የትናንት ብሶቴን ከውስጤ ለመፋቅ ፣
ባጋጣሚው ሁሉ እኔኑ ለማሳቅ ፣
ሁሉን ረስቼ እንድኖር እንዳዲስ ፣
አንካሳውን ልቤን በተስፋ ልታድስ ፣
መንገድ ስጠቁመኝ ስትነግረኝ ደጋግማ ፣
ስለኔው ስትነግረኝ በምሳሌ ቃና ፣
አንተኮ ቆንጆ ነህ ለዛውም ጠንካራ፣
በፍፁም የማትቆም በትናንት ሰበራ ፣
በዚህ ጯሂ አለም ሰሚ በሌለበት፣
ለሌላ ማይገባን የራስ ቅኔ ብሶት፣
አምቀህ ደብቀህ ካንተነትህ ጓዳ ፣
ችለህ የተጋፈጥክ የመኖርን ፋዳ ፣
*ተምሳሌት ነህኮ*
ሰው ወድቆ እንደማይቀር የቱንም ቢጓዳ፣
ደግሞ አንተም ታውቃለህ አለህ ዕልፍ ነገር፣
ምክኒያት የሚሆንህ በደስታ ለመኖር፣
•••• እናም አየውልህ ••••
ይህ የዛሬው ፅልመት ነገህን ሊጋርድ ፣
ከመንገድህ ቁሞ ሊያነቅፍህ በግድ ፣
በትዝታ አሳቦ የዃሊት ቢያሳይህ፣
ናፍቆት ተመርኩዞ ያለፈን ቢነግርህ፣
ደርሶ ቢያንሾካሹክ ፍቅር መውደድ ብሎ፣
ጭራሽ እንዳትፈቅድ እንዲያቆምህ ችሎ
በቃ ከዚህ ወዲያ ማንባትም መተከዝ ፣
በሀሳብ ተውጦ ፊትህን ማደብዘዝ ፣
አንተ ላይ እንዳላይ ከፈገግታህ በቀር
እያለች ደጋግሞ በመምከር በመዝከር
በ መጥፎ ቀኖቼ ተመስላ በ ደግ
ምኞት አሰቀጥላኝ ያዲስ መኖር ሀረግ
ወጌሻዬ ሆና ሰበብ ለመቆሜ፣
መዳኒቴ ሆና ለቀድሞ ህመሜ ፣
ዳግም ጥርሴ ሳቀ ሀሴትን ተላብሶ፣
አይኖቼም እረሱ ማደር በእንባ ርሶ፣
ጠውላጋ እኔነቴ ፈካ ተመልሶ፣
በሴት ልጅ ቢጎዳም በሴቷ ተክሶ ••

በዚህ አጋጣሚ ላአንዳንድ ሰዎች
ማለት እወዳለሁ ለጭፍን ፈራጆች
*
*
ደግም ክፉም አዝላ በምትኖር አለም
ባንዷ ጥፋት ጥለት ሌላን በመቀለም
ሁሉም ሴት አንድ ነው ማለት ልክ አይደለም
#ሼን


Join👇👇

https://www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ከሰሞኑ ኡስታዝ አህመዲን ጀበል EMS ከተሰኘ ሚዲያ ጋር በወቅታዊ የሙስሊሙ ጉዳይ ላይ ቆይታ አድርጓል። በዚህ ቆይታው በርካታ ነጥቦች የተነሱ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ በተለይም የሰሞኑን የመጅሊስ ምርጫ አስመልክቶ ጠቃሚ ጥያቄዎች ቀርበው ኡስታዝ አህመዲን አብራርቷል። ከተነሱ ጥያቄዎች ውስጥ የመጅሊሱን መርጫ ፍትሀዊ አይደለም በሚል ያልተቀበሉ ወገኖች አሉ ከዚህም በተጨማሪ ምርጫው የመንግስት ጣልቃ ገብነት ነበረው የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው። ምርጫው የብሔር መልክ የያዘ ነበር የሚለውን ሌላው ጥያቄ ነበር። እነዚህን ጥያቄዎች ያብራራበትን ክፍል ሀሩን ሚዲያ ለተመልካቾች በሚከተለው መልኩ አዘጋጅቷቸዋል። ይመልከቱት!
..
ከ ሀሩን ሚዲያ የተወሰደ

https://www.tg-me.com/Islam_and_Science
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ክረምት ነዉ...ትንሽ ሞቅ ሞቅ የሚያደርግ ነገር ያስፈልጋል፡፡በግጥምም በቀልዱም ያስፈልጋል😊

እቴዋ መርሀባ በይ ለበይክ በይ የሚለዉን በጦቢያ...በተስፋሁን ከበደ (ፍራሽ አዳሽ) የተዘጋጀ የወሎ የዱአ አደራረግ ጋር የተያያዘ አስቂኝ አስተማሪ video


😍መርሀባ በይ
😍ለበይክ በይ
መርሀባ ስትይ ለበይክ ስትይ ኸይር ይሆናል ነገሩ🥰

ይመልከቱት ከዛም በዚህ ክረምት ለደበረዉ ለበረደዉ መርጣችሁ ሼር ያድርጉት

https://www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
Forwarded from ISLAM IS UNIVERSITY
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Audio
ከችግር ቡሀላ..መፍትሄ አለ

https://www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አንዲህ ያለ የሚያስቀና ትዳር አለ..በሞት ተለያይተዉ ሊረሱ የማይችሉ😔


https://www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካትሁ
እንዴት ናችሁ

ብዙ የሌላ ቻናል Admin እና አንዳንድ ዩቲዩበሮች ሳትወጋ ንገስ በሚለዉ ታሪክ መሀል የቀረበ የመራም ማስታወሻ የሚለዉን ለብቻዉ በyoutube እና በቻናል እናቅርበዉ ፍቀድልን ላላችሁ ይሄዉ የመራም ማስታወሻ የሚለዉን ለብቻዉ ከነገ ጀምሬ እፓስተዋለሁ፡፡ ቻናል ያላችሁና በyoutube ለመጀመር የፈለጋችሁ በጠየቃችሁኝ መሰረት አመቻችቻለሁ፡፡

☝️ በአስተያየት ለምን ፁሁፋ ማዘጋጀት አትጀምርም ላላችሁ ...ሌላ ፁሀፍ ላዘጋጅ ይቅርና እኔ ለራሱ 95% የፃፍኳቸዉን ፁሁፎች ረስቸዋለሁ፡፡ ወላሂ አሁን በአንዳንድ ቻናል የኔ ፁሁፍ ሲፓሰት ግን እኔ ነኝ የፃፍኩት ወይ ብየ ግራ እየገባኝ ነዉ፡፡እናም እንኳን ፁሁፍ አዘጋጅቶ ለሌላ ወገን ለመትረፍ ይቅርና ራስን ወደ በፊቱ ማንነት መመለስ ከባድ ነዉ...

ኢማን ይጨምራል ይቀንሳል....እኔም በሆነ ምክንያት ከበፊቱ አቋም እንደወረድኩ አቃለሁ..ብቻ ወሳኙ ዱአና ዱአ ብቻ ነዉ


በፊት ሳትዋጋ ንገስ በሚለዉ ታሪክ ላይ በመሀል የገባዉ የመራም ማስታወሻ ታሪክ ነገ ከጠዋት ይጀምራል፡፡
በድጋሜም ቢሆን መልካም ንባብ

አሚር ሰይድ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
📖 #የመራም_ማስታወሻ
           ክፍል ~ ➊
ፀሀፊ ☞አሚር ሰይድ


      ሁሉም ነገር አላህ ሁን ባለው ጊዜ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
በህይወት ዉስጥ ስቃይ የማይቀር ከሆነ ..የህይወት ችግሮች ልናስቀራቸዉ የምንችላቸዉ ካልሆኑ ጥያቄዉ መሆን ያለበት ""መሰቃየታችንን እንዴት ማቆም አለብን???""ሳይሆን ለምንድን ነዉ የምንሰቃየዉ???ለምን አላማ ??መሆን አለበት፡፡

ሁሌም ቢሆን ከችግሬ መላቀቅ እችላለሁ
የሰዉ ልጅ የማሰብ አቅም ሲመክን አይቻልም የምትለዉ ቃል ባንደበቱ ይዘወትርና ፡የአነጋገር ለዛዉ ይሆናል..ቀላልም ይሁን ከባድ ነገሮች ሲጠየቅ ወደ መፍትሄዉ ሳይሆን አልችልም የሚለዉ ሚዛን ያቃጭልበታል፡፡

የማሰብ አቅሜን ተጠቅሜ በያዝኩት ነገር ላይ ልዩነት መፍጠር እችላለሁ ማለት ካልቻልን አፋችን ቃሉን ባይጠራዉም ሁሉንም ነገር የጀመርነዉ አይቻልም እያልን ነዉ ማለት ነዉ ፡፡ በመጀመሪያ የሚቻልበትን መንገድ ለይተን እንወቅ እንጂ የምንከተለዉን መንገድ አይቻልም ብለን አንጀምር ፡፡ አይቻልም የሚሉት ቃል የሽንፈት ማረጋገጫ ማህተም ነዉ
ሰዉ ነኝ እስካልን ድረስ የማሰብ አቅማችንን አለመጠቀም ይቅርታ የሌለዉ የሒወት ከባዱ ስህተት ነዉ ፡፡ ድንቁርና የሰዉን ተፈጥሮ የማሰብ አቅም በማዳከም ላለመሆንና ላለመቻል አጋልጦ ይሰጣል፡፡
ለሁሉም ነገር የሚባክኑ ጊዜያቶች ሰከንዶች ደቂቃዎች ለዱንያ ወደ አኼራ ለመሸጋገሪያ ድልድይ ለመስራት እንቅፋቶች ናቸዉ፡፡ አሁን ዘመን ላይ ጊዜ እንደ ወራጅ ወንዝ ሰዉ ሳይጠቀምበት እየፈሰሰ ነዉ፡፡ ኸይር ለመስራት በዲነል ኢስላም ላይ ለመሳተፍ ኪታብ ለመቅራት የሁላችንም መልስ ጊዜ አጣን ጊዜ የለንም ሁኗል፡፡እኛ ያነሰን ጊዜ ትርጉም ግን ምን ይሆን??ብለን እራሳችንን ጠይቀን እናዉቃለን ???

ማንኛችንም የማንክደዉ ሀቅ አለ ..መጀመሪያ የማንሻማበትን መስመር ሳንለይ እዛም እዛም እየረገጥን -ጊዜ አጠረን- ብንል ጊዜ የምንለዉ ነገር የሰበብ ቀበቶ ብቻ ነዉ፡፡
አሁን ብለን የምንጠራዉ ወቅት ብቻ ነዉ በእጃችን ያለዉ ጊዜ..... ከቆምንበት ሳንነቃነቅ ወደ ሆላ እያልን የምንጠራዉ ጊዜ እጃችን ላይ ያገማነዉ የፋይዳህ እንቁላል መጣያ ቅርጫት ብቻ ነዉ፡፡ የገማ እንቁላል መልሶ ተፈልፍሎ ጫጬት መስጠት አይችልምና.....
ወጣትነት ጉልበት ብርታት ወኔ ሞራል ነዉ....የአአምሮህን እግር ንቀለዉና ተገትሮ የቀረዉን ራስህን ቅደመዉ.....ዛሬ በከንቱ የሚፈሱ ጊዜያቶች ነገ ለአንተ ተመልሰዉ አታገኛቸዉና....
ሂወትም የምትወሰነዉ በራሳችን የአስተሳሰብ ምርጫ እና በምትጠቀማቸዉና በምታባክናቸዉ ጊዜያቶች ላይ የተወሰኑ ናቸዉ ፡፡ ሂወት የምርጫ አይደለችም! ብትሆንማ ኑሮ ማን ችግርን ይመርጥ ነበር!? አላህ ቀድሞ የፃፈውን ነገር በፍላጎት መቀየር አንችልምና ከሚያጋጥመን የሂወት ውጣ ውረድ ጋር ራሳችንን አጣጥመን፣ ዱንያ አጭር መሆኗን አውቀን ለዛኛው ለዘላለማዊ ሂይወታችን የምንሰንቅባት ሀገር መሆኗን እና የሚያጋጥሙንን ሙሲባ በሶብር ነገ የተሻለ እንደሚሆን በአላህ ማመን እንዳለብን ያስተማረችኝ እማ ነች፡፡

እናቴ የተወለደችው ሀረር ነው፡፡ ሀረር ትወለድ እንጂ የእማ እናቷ የደሴ ልጅ ነች፡፡ ስለዚህ እማ በደም ወለየ በአፈር ደግሞ ሀረሪ ነች፡፡ እናቴ ለቤተሰቦቿ ሁለተኛ ልጅ ነች ታላቅ ወንድሟ ፈይሰል ይባላል፡፡ እናቴ ደግሞ ለይላ ትባላለች፡፡ ደስተኛ ቤተሰብ እንደነበሯት እማ ሁሌ ነግራኛለች፡፡ መተሳሰብና መከባበር የሞላበት ፍቅር የሰፈነበት ቤተሰብ ነበራት፡፡ ግን ምን ዋጋ አለው እማ ገና የ 12 አመት ልጅ እያለች እናቷ በምጥ ምክንያት ሞተችባት፣ በሰአቱ ፈይሰል የ15 አመት ልጅ ነበር፡፡ በእናቷ ሞት ምክንያት ቤተሰብ የማስተዳደር ሀላፊነት እናቴ ላይ ወደቀ፡፡ እናቴ በእናቷ ሞት ምክንያት ቅስሟ ተሰብሮ ልቧ መድማቱን አላቆመም፡፡ የእናት ናፍቆት ሲደመር ቤተሰብ ማስተዳደር ከእማ አቅም በላይ ሆነ፡፡ ሰውነቷ መመንመን ጀመረ፡፡ ይሄን የተመለከቱ የቅርብ ሰው ጎረቤቶች አባቷ ሌላ ሴት አግብቶ ልጆቹን እንድትንከባከብ መከረቱ፡፡ አቧቷም የጎረቤቶቹን ምክር ሰምቶ ልጆቹን ትንከባከብለት ዘንድ ሌላ ሚስት አገባ፡፡

ከዚህ በኃላ ግን ሂወት ይበልጥ ከብዳ ፈተነቻቸው፡፡ፈይሰል በእንጀራ እናታቸው የሚደርስባቸውን ግፍና መከራ መቻል አቅቶታል፤ አባታቸው እንደወትሮው ለነሱ መጨነቁን ቀነሰ፡፡ ይባስ ብሎ " አታናዷት የምትላችሁን ሰሙ" እያለ እነሱን መቆጣት ጀመረ፡፡ እማ ግን ችግሯን በውስጧ አፍና ይዛ ኑሮን ተያያዘችው፡፡ ከወንድሟ የምታገኘው ፍቅር ለሷ ምግብና ውሀ ሁኖ ያኖራታል፡፡ ፈይሰል ለእህቱ ችሎ የማይሆንላት ምንም ነገር የለም! እህቱን እጅግ በጣም ይወዳታል፤ አንዳቸው ለአንዳቸው እየተሳሰቡ መኖር ተያያዙ፡፡ ፋይሰል ከሱ ይልቅ እህቱ ላይ የሚደርሰው በደል እና እንግልት ያንገበግበዋል!አባታቸው ስለነሱ ማሰብ ማቆሙ ደግሞ ይበልጥ ያበሳጨዋል፡፡

እማ በጧት ወፍ ከመንጫጫቱ በፊት ነው የምትነሳው የቤቱን ስራ ስትጨርስ አርፍዳ ነው ወደ ትምህርት ቤት የምትሄደው፤ ከትምህርት ቤት ስትመለስም የማያልቀው የቤት ስራ ተከማችቶ ይጠብቃታል፡፡ የምትተኛው ከሰው ኃላ የምትነሳው ከሰው በፊት ነው፡፡ ግን አንድም ቀን አማራ አታውቅም ነበር፡፡ ይሄን እንግልቷን ማየት ያላስቻለው ፈይሰል " ቀን መቶልኝ አንችን ከዚህ ስቃይ ማውጣት ስችል እመለሳለሁ፡፡ ከማዘን ውጭ ምንም ልረዳሽ ስላልቻልኩ አዝናለሁ እህቴ ሂጃለሁ የምሄድበትን አላውቅም እና እንዳትፈልጊኝ፡፡ ያንችው ፈይሰል ነኝ" ብሎ ደብዳቤ ፅፎ አስቀምጦላት የት ገባ ሳይባል ጠፋ ፡፡
እማ ከወትሮው በበለጠ ሂወት ከበዳት፡፡ አንድ ብርታት የነበራት ወንድሟ ጥሏት ጠፋ፡፡ "የት ገብቶ ይሆን??" ብሎ የሚጨነቅለት ጠፍቶ " ጎርምሶ ጠፋ" መባሉን ስትሰማ፡፡ ብዙ የሀዘን እንባ ከአይኗ ፈሰሰ ልቧ ደጋግሞ ቆሰለ፤ ላይሽር ላያገግም ተሰበረ፡፡ የወንድሟ ትዝታ ረፍት ነሳት በስራ እያገዘ ያዝናናት ነበር፡፡ አሁን ግን ብቻዋን ቀርታለች ግን በእያንዳንዱ የስራ እንቅስቃሴ ፈይሰል ይታያታል፡፡ ትዝታው ረፍት ነስቶ አቅም አሳጣት፡፡ እናቴም ልክ እንደወንድሟ መጥፍት አሰበች፤ እናም አንድ ሀሳብ መጣላት፡፡
እማ አባቷን እንኩዋን በቅጡ ሳትሰናበተው የእናቷ ትውልድ ሀገር ወደሆነችው የወሎ መዲና ደሴ አያቶቿ ጋር ለመኖር መጣች፡፡ እማየ ደሴ ስትመጣ ለመላመድ አገሩን ለመልመድ ቀናት ወራት አልፈጀባትም..ወሎ ላይ ከየት መጣህ ሳይሆን እንኳን ሰዉ ሁነህ መጣህ ነዉ የሚባለዉና፡፡  ምን ይደረጋል ወሎ ገራገሩ እየተባለ ታሪኩን የተቀማ ህዝብ ነዉ... ትክክለኛ ታሪክ ቢሆንማ ወሎ ከኢትዮጲያ ታሪክ 70% በላይ ይዛ የቆየች ናት

በወሎ ምድር ታይተው የማይታወቁ፣ ተነግረው የማያልቁ፣ለልብ ደስታ ለአዕምሮ እረፍት የሚሰጡና የማይጠገቡ ድንቅ ድንቅ ሚስጥራዊ ክዋኔዎችና ባሕሎች ይገኛሉ።ወሎዬ ሲወድ በአፉ አይደለም፤በልቡ ነው።ፈትፍቶ  እያጎረሰ፣አውልቆ እያለበሰ፣ፀጉርን በፍቅር እየዳበሰ አቀማጥሎ የሚወድ ነዉ።
ከጫፍ እስከ ጫፍ በወሎ ምድር በተንቀሳቀሱ‹አብሽር አቦ› እያለ በፍቅር የሚቀበል ደግ ሕዝብ አለ።
የቆነጃጅቱ ውበት፣ የጎበዛዝቱ ልበ ሙሉነት ወሎን የረገጠ ሁሉ ልብ ያቀልጣል።👇👇
        ይህ ሁሉ መኳኳል ምን ያደርግልሻል
        ወሎየ ነኝ ብትይ ስሙ ይበቃሻል፡፡
        በጥብጬ ልቀባዉ የወሎን አፈር
        በጥብጬ ልቀባዉ የደሴን አፈር
        እኔም እንደነሱ ምን አልባት ባምር
ብለዉ የወሎን ዉበት ዘፍነዉ መስክረዋል
ወሎ ላይ ሲመጡ ወሎን ሲመለከቱ ወሎዬ ላልሆነ ወሎዬነትን ያስመኛል።
ወሎዬ በሠላም ቀን በደግነት በክፉ ቀን ደግሞ በጀግንነት ሺህ ጀግና ስለጣለ ከየትኛውም ሰው ልብ አይወጣም። ወሎዬዎች ኢትዮጵያውነትን አይናገሩትም፤ ይኖሩታል እንጂ፡፡ ወሎዬዎች ኢትዮጵያዊነትን በባሕላቸው፣በፍቅራቸው እና በጀግንነታቸው ተላብሰውታል።የወሎ ልጅ ሁኖ ኢትዮጲያን በፍትህ ያስተዳደረ ልጅ እያሱ ሚካኤል መቼም ከልብ ታሪኩ ሊጠፋ አይችልምና ፣ ከአይጠየፍ አዳራሽ ግርጌ፣ በጦሳና በአዘዋ ተራሮች ታጅባ ከደመቀችው ደሴ ከተማ ሲመጡ ዘረኝነት ትዝም አይለዎት፡ ወሎ ዘር አይቆጥርም፣ ሃይማኖትም አይለይም፣ለወሎዬ መለኪያው ሰውና ባሕሪው ብቻ ነው።መቻቻል፣ ፍቅር፣ አንድነትና አብሮነት መለያዎቹ ናቸው። በፍቅራቸው ተደሞ በወሎ ጭስ መልካም መዓዛ ታውጀዉ አመስግኖ መመለስ የሌላዉ ሀገር ወጉ ነዉ።
 ወሎዬዎች የመጀመሪያ ውበታቸዉና ደግነት ሁለተኛ የዋህነት ሶስተኛ ገራገርነት አራተኛ ሰውን በሰውነቱ እንጂ በሚታይ ቁሳዊ ነገር ልዪ ቦታን የማይሰጡ ንፁህ ሰውን እንጂ በገንዘብ በእውቀት እና በዘረኝነት የማይኮፈሱ ስስት ያልፈጠረባቸዉ የተቃራኒ እምነቶችን የሚያከብሩ ውበትን ከዘራቸዉ የሚወራረስ ፍቅርን በነፍስ የምታገኘው ወሎዬዎች ጋር ነው ።

ወሎየ ስትሆን ከሙስሊሙ ጋር ቀጠሮ ስትይዝ ሶላት ሰግደህ ስትመለስ እንገናኝ ትለዋለህ፡፡
ሙስሊም እንዲሁ ቤተ ክርስትያን ተሳልመህ ስትመለስ እንገናኝ ይለሀል፡፡
ክርስትያን ጓደኛህ ቤት ስትጫወት የሶላት ሰአት ሲደርስ የዉዱእ ውሀ ከጡሀራ መስገጃ ጋር ያቀርብልሀል፡፡
ከዚህ በላይ በሰውነት መጣመር ከየት ይመጣል?? ከወሎየነት እንጂ




አያቶቿ በእርጅና ተበሳቁለዋል፡፡ ከሁለቱ ውጭ ቤት ውስጥ የሚንከባከባቸው ሰው አልነበረም፡፡ ሴት አያቷ በልጃቸው ሞት ምክንያት ብዙ ከማልቀሷ ምክንያት አይኗ ተዳክሟል፡፡ የልጃቸው የስም መጠሪያ የልጃቸው ሽታ የሆነችውን እናቴን ሲያዩ የደስታ እንባ ማንባት ጀመሩ፡፡ ልጅ ወልዶ የሞተ ሰው መቸም አይረሳም በልጅ ሰሙ ሲጠራ ይኖራል ይባላል፡፡ለዛም ነበር አያቶቿ እናቴን ሲያዩ ልጃችን አልሞተችም ያሉት፡፡ እማ ለቀዘቀዘው ቤታቸው የፍቅርን ሙቀት ለጨለመው ቤታቸው ብርሀን እና ድምቀት ሆነች፤ በአመታት በፊት ያጣችውን ፍቅር አሁን በአያቶቿ ዳግም ተመለሰላት፤ እነሱን መንከባከብ እና ማስደሰት ስራዋ አድርጋ ያዘችው፡፡ሂወታቸው በእጅጉ ተቀየረ፡፡ አያቷ አሁን እንደበፊቱ ማልቀስ አቁማለች፡፡ ወንድ አያቷም በጣም ደስተኛ ሆኗል፡፡ ግን ከእድሜው ጋር በተያያዘ የተወሰነ የመስማት ችግር አለበት፡፡ እማየም ትምህርቷን ቀጥላለች፡፡ ከትምህርት ቤት መልስ ደግሞ ወደ መርከዝ በመሄድ ቂርአት ትቀራለች፡፡ እማ ሂወቷ መስመር ይዟል የሚያስብላት የሚንከባከቧት ቤተሰብ አላት፤ ሁሌ የወንድሟ ጉዳይ ረፍት ይነሳታል እሷ ስትስቅ እሱ ሲያለቅስ ይሰማታል፡፡ እሷ ጠግባ ስትበላ እሱን  ሲርበው ይታያታል፡፡" ወንድሜ የት ነህ!? የትስ ብየ ልፈልግህ? እዚህ ነኝ በለኝ ወንድሜ" እያለች ሁሌም ታስባለች፤ ግን የውሀ ሽታ ሆነና ቀረ፡፡

እማ እድሜዋ እየጨመረ ሲመጣና ራሷን መጠበቅ ስትጀምር የአደምን ልጅ ልብ አስደንጋጭ እና የልብ ቀማኛ ሆነች፡፡ እዚህ ቀረሽ የማይባልላት ሁሉን አሟልቶ የፈጠራት የጥበቡ ማሳያ ተምሳሌት እማ እንደሆነች ይመሰከርላታል፡፡ ፀባየ ሰናይ ሰናይ መሆኗ ደግሞ ከሰፈር እስከ ትምህርት ቤት እስከ መድረሳ ያሉ ሰወች በጠቅላላ ይወዷታል ያከብሯታልም፡፡ እማ ገና 18 አመት ሲሞላት ለትዳር የሚፈልጓት ወንዶች በዙና የአያቶቿን ደጅ የሚጠና ሰው ብዙ ነበር፡፡ አያቶቿ አግብታ በትዳሯ እንድትኖርና ዘር እንድታበረክትላቸው ተመኙ፡፡ እማ ግን አላማዋ ሌላ ነበር ተምራ ስራ ይዛ እነሱን መጦር ነው ህልሟ፡፡ እናም የሚቀርብላትን የትዳር ጥያቄ ወደ ጎን በመተው በትምህርቷ ፀናች፡፡ የ12ኛ ክፍል ተማሪ እያለች ግን ያልጠበቀችው ነገር ድንገት ተከሰተ፡፡.....

#ክፍል
ይቀጥላል.......

Join👇👇

https://www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
2024/09/22 06:29:12
Back to Top
HTML Embed Code: