Telegram Web Link
🔥#በዝሙት_በሽታ_የተበከለ_ትዉልድ🔥🔥
        
          🔰 #ምዕራፍ_አስር_ሰባት ➊➐
                  አሚር ሰይድ


╔═════════════════╗
      🎖 #የዩኒቨርሲስቲ_ገመና 🎖
╚═════════════════╝

ዩኒቨርስቲዎች ሁለት ጥቅም አላቸዉ ለሀገር የሚጠቅሙ ተማሪዎችን ማፍሪያና በዛ በተዘዋዋሪ ደግሞ ዩኒቨርስቲ ከገቡ ቡሀላ  ለአገር የማይጠቅሙ እነሱ ተበላሽተዉ ሌላ ትዉልድን የሚያበላሹ ተማሪዎች መፈልፈያ ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ዩኒቨርስቲዎች ለወላጆች #ወልዶ_መጣያ ከሆኑ ሰነባብተዋል፡፡
ወላጅ ተጨንቆ አስቦ ከራሱ ቀንሶ ለተማሪ ልጄ ይላል ..ተማሪ ግን በጓደኛ ግፊት..የቤተሰብ ቁጥጥር ዩኒቨርስቲ ዉስጥ አለመኖር አላማቸዉን ዘንግተዋል፡፡በፊት ሴት ልጅ ሰነፍ ከሆነች አትማር ስል ብዙ ተከታዮች ለሌላ ይመስላቸዋል ግን ዩኒቨርስቲ ገብተዉ ያለዉን ፈተና መቋቋም ስለማይችሉ በማሰብ ነዉ ለምን በፊት ተማሪ በዉጤቱ በጉብዝናዉ ሳይሆን በኩረጃዉ በትቤት ህግ መላላት ምክንያት ነበር ወደዩኒቨርስቲ የሚገቡት..,እድሜ ይስጠዉና ዶክተር ብርሀኑ ነጋ እየሰራ ያለዉ ስራ በጣጣም አበረታች ነዉ...ተማሪን እያየን የtiktok ትዉልድ እያየን ነዉ በጀመአ ሲወድቅ፡፡ እኔ የሚገርመኝ እኛን የሚያስተዳድሩን በየመስሪያ ቤቱ ያሉ የመንግስት ሰራተኞች ከስንት አንድ ካልሆነ ጎበዝ ሁነዉ በትምህርት ደረጃቸዉ የሚያስተዳድረን እንጂ ከዛ ዉጭ ያለዉ በፊት በነበረዉ የዩኒቨርስቲ ፓሊሲ የተማሩ መሆናቸዉ በነዚህ ሰዎች ሙስና ይቀራል ማለት ዘበት ነዉ፡፡ ግን አሁን የተጀመረዉ ዩኒቨርስቲዎች ራሳቸዉን በራሳቸዉ ማስተዳደራቸዉ በጣም አሪፍ ነዉ፡፡
የዩኒቨርስቲ ትርጉሙና ትክክለኛ ተማሪ የሚገባት ከዘንድሮ ጀምሮ ይሆናል፡፡
በተጨማሪ በግል ኮሌጅ የሚማሩ ተማሪዎችም ከዩኒቨርስቲ ህይወት ጋር በዚና መስመር እንደሚመሳሰሉ ማወቅ አለብን....

ለወደፊት ትምህርት ጥረት ይጠይቃል ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተዘፍዝፎ የtiktok ፎሎዉ በመቁጠር ትምህርትን መጨረስ አይቻልም፡፡


ከታች ያለዉ ፁሁፍ በዝሙት መዘመን ስልጣኔ ወይስ የአለም ፍፃሜ በሚለዉ መፅሀፍ ከዛሬ 8አመት በፊት የተፃፈና የጥናት ፁሁፍ አቀርባለሁ...ዛሬስ ከ8ወይከ9አመት ቡሀላ የዚና ስልጣኔ መንገዶች በዝተዉ ዛሬ ላይ የዩኒቨርስቲ ዘመቻ በስንት ፐርንሰት ጨምሮ ይሆን??

╔══════════════════╗
        🎖 #ሐዋሳ_ዩኒቨርስቲ 🎖
╚══════════════════╝

«ዩኒቨርሲቲው ፆሙን ነው የሚያድረው፡፡» (ብሌን ሰይፈ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማጅመንት

ሄለን አለሙ የዩኒቨርስቲ ገመና በሚለዉ መፅሀፏ ሀሐዋሳ ዩኒቨርስቲ  ከተማረች ይሄንን ፅፋለች

‹‹ከዩኒቨርሲቲው ልጀምር፤ በተለይ ማታ ላይ ባዶ ይሆናል፡፡ ተማሪው ውልቅ ብሎ ይወጣል፡፡ ከዚህ ይልቅ ‹ዩኒቨርሲቲው ፆሙን ነው የሚያድረው የሚለው ቃል ይገልፀዋል፡፡ የቀን ተማሪ ከማታ ተማሪ ጋር ተቀላቅሎ በባጃጅ እየተጋፋ ይወጣል። የሚገርመው የማታ ተማሪዎች የባጃጅ እጥረት እየገጠማቸው ግማሽ መንገድ በእግር ለመሄድ ይገደዳሉ፡፡ ለቀን ተማሪዎች ያ ሰዓት የማምለጫ ሰዓት ነው የሚመስለው። ውልቅ ብለው ሲሄዱ ሴት ከወንዱ በጣም ብዛት አለዉ

   አንዳንዴ ትልልቅ የቤት መኪኖች ቆመው ሲታይ ሠርግ እየታጀበ ይመስላል፡፡ አንዳንዴ ደግሞ የመኪና ኤግዚቢሽንም ሊመስል ይችላል፡፡ በርካታ መኪና ይቆማል፡፡ መኪኖቹ የሚቆሙት ተማሪ ጥበቃ መሆኑ ይታወቃል። ሆን ተብሎ እዚያ አካባቢ ሴት ተማሪዎችን ለመጠበቅ ይቆማሉ፡፡ ተማሪዎች የሚወጡበት ሰዓት ይታወቃል፤ ይቀጣጠራሉም፡፡

ተማሪዎችን የሚያሻሽጡ ደላሎችም አሉ፡፡ ደላላ የሌለበት ምን ነገር አለ? ያለ ደላላ ይሄ ነገር ሊፈጠር አይችልም፡፡ ለምሳሌ አንድ ሀብታም ዩኒቨርሲቲ መጥቶ ተማሪ ለመጥበስ ይጓተታል ማለት ዘበት ነው:: ቢሞከርም የሚሳካለት ከስንት አንዱ ነው፡፡ ይሄም ይሳካል ብዬ የማስበው አንዳንዴ ከግቢ በፀሐይ ትወጪና ባጃጅ ልታጪ ትችያለሽ፡፡ ያኔ ሊፍት ሲሰጥ የሚሄድ ተማሪ ሊኖር ይችላል፡፡ መጠባበሱም
ሊፈጠር የሚችለው በዚህ አጋጣሚ ነው፡፡ ከዚህ በተረፈ ብዙ ነገር የሚጧጧፈው በደላላ ነው፡፡ ሀብታምም መጥቶ በር ሲቆም ያለቀ ነገር ይዞ ለመሄድ ነው፡፡ ልክ ተጠቅሎ እንደተቀመጠ የሱቅ ዕቃ እንጂ ገና ዋጋ አይደራደርም፡፡ ደላሎቹ ደግሞ ከውጭ ብቻ የሚመጡ አይደሉም፡፡ ከውስጥም (ከተማሪዎች) አሉ፡፡ የእነሱ የሱሳቸው የመሸፈኛ ገቢ የሚገኘው ሴትን ከሀብታሞች ጋር በማቃጠር ነው::


╔═══════════════════╗
     🎖 #አርባ_ምንጭ_ዩኒቨርሲቲ 🎖
╚═══════════════════╝


«የሴቶችና የወንዶች ዶርም በጣም ተቀራራቢ ስለሆነ ሴት ለማግኘት ድካም የለብንም፡፡»(ዳዊት ተስፋሁን፣ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒዉተር ሳይንስ ተማሪ)

«እንደ እንስሳ በየሜዳው የሚፈፅሙት ወሲብ ከአዕምሮ በላይ ነው የሆነብኝ (አዜብ ኃይሉ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሶሺዎሎጂ ዲፓርትመንት ተማሪ)

‹‹የካምፓስ ሕይወት ከባድ ነው፡፡ወደዛ ስንገባም ብዙ ነገሮች ይነገሩናል፡፡ተማሪ ጥሩም መጥፎም እንዳለ፣ ተማሪ በኤች.አይ.ቪ እንደሚያዝ፣ ከእንዲህ ዓይነት ልጆች ጋር አትግጠሚ፤ እንዳትበላሺ የሚሉና መሰል ምክሮች ከቤተሰብ ተነግሮኝ ነበር፡፡ ያኔ ምክሩን ባልንቅም ግን እውነት አይመስለኝም ነበር፡፡ነገር ግን ብዙ ነገር አየሁ፡፡ጥሩ የሚሆነው ግልፅ ካወራን ነው፡፡ ግልፅ እንነጋገር ከተባለ እዛው ሜዳው ላይ በግልፅ ወሲብ ይደረጋል፡፡ ወሲብ በጣም ከሚደረግባቸው ቦታዎች ውስጥ በጣም ከፍተኛው ስቴዲየም አለ፤ ኳስ ሜዳው ላይ ጨለም ሲል እዛ ሁሉም ተማሪ ወሲብ ያደርጋል፡፡
ከማስታውሰው ነገር አንዱን ልናገር፡፡አንድ ቀን እያጠናን ድንገት መብራት ይጠፋል፡፡አብራኝ ስታጠና የነበረችው የዶርሜ ልጅ ናት፡የሄደችውም እንደኔው ከአዲስ አበባ ነው፡፡እና ከዚህች ጓደኛ ጋር ስናጠና መብራት ጠፍቶ ወደ ዶርም ለመሄድ መንገድ ስናቋርጥ ድምፅ ሰማን፤ እያጠኑ ነው ብለን ነበር፡፡ነገር ግን እነሱ ወሲብ እያደረጉ ነው፡፡ የምሬን ነው! እረግጠናቸው ነው የተራመድነው፤ በጣም በጣም የሚያስጠላ እንደዚህ ዓይነት ነገር አለ፡፡ እኔ ይህ እንደ እንስሳ በየሜዳው የሚፈፅሙት ወሲብ ከአዕምሮዬ በላይ ነው የሆነብኝ፡፡ በየሜዳው ወሲብ ሲያደርጉ በጥበቃዎች ይያዘሉ፡፡»የላይኛዉ ምንጭ መፅሀፍ ገፅ 61


╔═════════════════╗
     🎖 #ባህር_ዳር_ዩኒቨርሲቲ 🎖
╚═════════════════╝

    

«በ2003 ብቻ 600 ተማሪዎች አስወርደዋል፡፡» (እየሩሳሌም ፍቃዱ - በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሊትሬቸር ተማሪ)

«እዚህ ገምቼ የሄድኩት ትምህርት ፈልጌ ነው፡፡ነገር ግን እዚያ ከሄድኩ በኋላ ብዙ ነገር አይቻለሁ፡፡ እኔ በነበርኩበት ጊዜ ግቢ ውስጥ በፀረ-ኤድስ ክበብ እሳተፍ ነበር፡፡ እዚያ ውስጥ ስታቶች ሲሰሩ አያለሁ፤ በዓይናችንም የምናየው አለ፡፡ ብዙ መጥፎ ነገሮች አሉ፡፡ በዚያው ልክ ብዙ ጥሩ ነገሮች አሉ፡፡

#ለምሳሌ እኔ ካየሁት ዉስጥ ባህርዳር ፓፒረስ የሚባል ትልቅ ሆቴል አለ፡፡ፈረንጆች ይጠቀሙበታል፡፡የግቢ ልጆች ስልክ ቁጥር ከሆላ የተፃፈበት ፎቷቸዉ ከዚያ ይገባል፡፡ልክ እንደ ካታሎግ፡፡የመረጣትን ደዉላችሁ ጥሩልኝ ይላል፡፡በዚህ መልክ ከትምህርት ባሻገር ሌላ ስራ ይሰራሉ ማለት ነዉ፡፡ግቢ ዉስጥ በ2003 ብቻ 600 ተማሪ ነዉ ያስወረደዉ፡፡በአንድ አመት ዉስጥ የተሰራ ስታቲክስ ነዉ፡፡ግቢ ዉስጥ የሚወልዱም አሉ፡፡👇👇👇
እኔ በአይኔ ሁለት ልጆች ወልደው አይቻለሁ፡፡»የላይኛዉ ምንጭ መፅሀፍ ገፅ 54

🔰 እቴጌ ገረመዉ ባዘጋጀችዉ የጭን መነባንብ በሚለዉ መፅሀፏ ገፅ 98 ላይ እንዲህ ብላለች

    «የኮሌጅ ተማሪዎች ድብቅ እውነታዎች ባሕር ዳር፦ የሀገራችን ተማሪዎች ከሚታሙባቸው የዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች ይማግጣሉ ከሚባሉት ከተማ እንደመሆኗ ለመታዘብ ቸኮልን፡፡ ወሲብ ንግድ ያጧጡፋሉ የተባለላቸውን ተማሪዎቻችን አመሸሽ ለመቃኘት የሚባለውን ነገር ለመታዘብ አንድ ቤት ከ30ደቂቃ በላይ መቆየት እያስፈልግም::ግን ይህን የሚያዩ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሆነ አፎን ከፍተው ሲመለከቱ ሊመሽብዎት ይችላል፡፡

  የአብዛኞቹን የሴት ልጆች አለባበስ የቡና ቤት ሴቶችም ሲሞክሩት የምንሸማቀብበት አይነት ነዉ፡፡እጆቻቸዉ እግሮቻቸዉ ሁሉ ስራ የበዛባቸዉ ናቸዉ፡፡ በአንድ እጅ ሲጋራ በአንድ እጅ ቢራ፣ መጨፈር፣ መጮኸ፤ በየሙዚቃዉ የሚያስጨፍሩት ወንድ መለያየት
ከሚያስጨፍሩት ወንድ ስልክ መቀበል፣ በሚያስጨፍሩት ወንድ አንገት ውስጥ መወሸቅ፣ በሚያስጨፍሩት ወንድ መተሻሸት፣ወዘተ ....እነዚሁ ሁሉ እጅግ አሸማቃቂ ድርጊቶች ናቸው፡፡ ይሄ ለእነሱ ጀብዱ ሁሉ የመሰላቸው ይመስለኛል፤ ያለማፈራቸውና ድንገት የሚያውቀኝ ሰው ቢመጣ ብለው ግራ ቀኝ ያለመገለማመጣቸው፡፡ ተመልካች ሆነው እንኳን ያፍራሉ፡፡ በተለይ እነሱን በማስተናገድ የሚታወቁት ቤቶችም ጢም ያሉ ናቸው:: እኛ ተማሪዎች የሚገኙበት ቤት ብለን እንደመጣን ሁሉ የመጡ ይሄኔ ስንት ይኖራሉ? በዚያ ላይ ጥሩ ዋጋ ያወጣሉ ሲሉም ሰማሁ፤ እንግሊዘኛ ይሞካከራሉና፡፡ የዚያኑ ያህል ሴቶቹ ከገንዘቡ ይልቅ የሚማርካቸው ግዳይ ጥለው ማደራቸው መሆኑ ይወራል፡፡



     ╔═══════════════╗
        🎖 #ዲላ_ዩኒቨርሲቲ 🎖
     ╚═══════════════╝

 
በዲላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ የሚስተዋሉ አጓጉል ወሲባዊ ባህሪያት (ዓባይነህ አናሾ እና ታረቀኝ ታደሰ የታተመ ጥናታዊ ጽሑፍ)

     እስካሁን እንደተገለፀው በዲላ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች የሚታዩ ዋና ዋና አደገኛ ተያያዥ የወሲብ ባህሪያት እርስ በርስ ለወሲብ መነሳሳት።በአደባባይ መሳሳምና መተሻሸት፣ አስገድዶ መድፈር፣ ያለ ኮንዶም ወሲብ መፈፀም፣ በርካታ የወሲብ ጓደኞችን ማፍራት፣ ያልተፈለገ እርግዝና፣ ማስወረድና ከሴተ አዳሪዎች ጋር መዳራት ናቸው፡፡

አደገኛ ወሲባዊ ባህሪይ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በሌሎች የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ላይ፣ በኮሌጆችና በዩኒቨርሲቲዎች፣ የ ኮሌጆችን ጨምሮ የሚስተዋል ነው፡፡



╔═════════════════╗
   🎖 #ሐረማያ_ዩኒቨርሲቲ 🎖
╚═════════════════╝

    

   ከአዲስ አበባ ከተማ 513 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘውና በ2010 እ.ኤ.አ ለ14ሺ ተማሪዎች የትምህርት ገበታ በዘረጋው ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ላይ የኤች.አይሺ ሥርጭትን የሚገመግም ጥናት ተካሂዶ በአቶ ታሪኩ ደንጌታ አማካኝነት ለሕትመት በቅቷል፡፡ በጥናቱ መግቢያ ላይ ከቤተሰቦቻቸው ርቀው በዩኒቨርሲቲ የሚኖሩ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ከሌሎች ወጣቶች በተለየ መልኩ ለኤች አይ.ቪ በሚያጋልጡ አደገኛ ድርጊቶች ላይ እንደሚሰማሩ ተገልጿል፡፡

⚡️⚡️በጥናቱ ላይ ከተሳተፉት ተማሪዎች ዉስጥ  
☞ 22.8% የሚሆኑት ወሲብን ለመጀመሪያ ጊዜ የፈፀሙት ዩኒቨርሲቲ ከገቡ በኋላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
☞ ወሲብ የመፈፀም ልምድ እንዳላቸው ከተናገሩት ወንድ ተማሪዎች ውስጥ ግማሽ ያህሉ ከሴተኛ አዳሪዎች ጋር አንሶላ የሚጋፈፉ መሆናቸውን እራሳቸው አምነዋል፡፡
☞ እንዲሁም ኮንዶም በአግባቡ የማይጠቀሙት 60% መሆናቸው ጉዳዩን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል፡፡

   ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከሌሎች ወጣቶች በተሻለ ተምረዋል የሚባሉ ቢሆኑም ኮንዶም አለመጠቀምን ጨምሮ ሌሎች ጥንቃቄ የጎደላቸው ድርጊቶችን ሲፈፅሙ የሚስተዋሉ እነርሱ ናቸው፡፡ በተለይ ወሲብ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈፅሙ ወንዶችም ሆኑ ሴቶች ኮንዶም የመጠቀም ዝንባሌያቸው በእጅጉ ያነሰ ነው፡፡ የዚህ ምክንያቱ መደብር ጎራ ብለው ኮንዶም ለመግዛት ስለሚያፍሩ ነው፡፡

╔═══════════════════╗
    🎖 #አዲስ_አበባ_ዩኒቨርሲቲ 🎖
╚═══════════════════╝
      

እትጌ ገረመዉ የጭን መነባንብ ሌሎችም በሚለዉ መፅሀፍ ከገፅ44-45 ድረስ ስለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ይህ ሰፍሯል

   (ሊሊ!) እኔ የምልሽ! የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ወንዶች እናንተ ጋ ሊዝናኑ አይመጡም? ሊሊ ይመጣሉ፤ ግን እነሱን ሌላ ቢዝነስ መፈለጊያ ነው የምንጠቀምባቸው፡፡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ከየት አምጥቶ ያወጣሻል? ማታ ቺቺኒያ አመሸሁ ለማለት ነው የሚመጡት፡፡ ለአልጋ መያዣ እንኳን ብር ስለማይተርፋቸው እስኪነጋ ድረስ ሲጨፍሩ ነው የሚያድሩት፡፡ እነሱን ለዳንስ ነው የምንጠቀምባቸው፡፡ በጣም አሪፍ ደናሾች ናቸው፡፡ ከነርሱ ጋር ሰትደንሺ የሚጎትትሽ አይጠፋም፡፡ ደግሞም የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ቢኖረውም ማውጣት የለብሽም፤ አይፋቱሽማ፡፡ አንድ ቀን ካወጡሽ በቀን ሊያገኝሽ ይፈልጋል፤ ካልቃምን፣ ወደድኩሽ ምናምን እያሉ ይጃጃላሉ፡፡ስራ ቦታ በዚያ ምሸት ባዶ እጁን መጥቶ ውጭ አስጠርቶ እትት ሊል ይፈልጋል፡፡ አሁን አሁን ሁሉም ሴት ሰላወቀ ብር ቢኖራቸው እንኳን ማንም እሺ አይላቸውም፡፡»

በምን ታውቋቸዋላችሁ? ይለያሉ ማለት ነው? ልጅነታቸው፣ ሁለትና ሶስት ሆነው መምጣታቸው፤ አስሬ ብራቸውን እያወጡ መቁጠራቸው በአንድ ዕይታ ያሳልቀባቸዋል:: የሚጀምሩት በዳንስ መሆኑ መለያቸው ነው፡፡ እየደነሱ ሊገቡ ሁሉ ይችላሉ፡፡ ብታያቸው በዳንስ እና ስራችን የሆነ ቢዝነስ ማሯሯጫ በየቀኑ የምናስነካዉ እንኳን አንደርስባቸው ... የመጀመሪያ ጥያቄያቸው ፌስቡክ የለሽም? የፌስቡክ አድራሻሽን ስጪኝ ስለሆነ #ላይክ ነው የምንላቸዉ፡፡ካለ እነሱ አራዳ ያለ አይመስላቸዉም፡፡ነገ ከቤተሰብ ስለሚላከልኝ ለዛሬ ተቸገሪልኝ የሚለው ብዛቱ ቀላል እንዳይመስልሽ፤ ባለፈው ሳምንት እምቢ ብለሽው ተመልሶ እንደ ጫትና ሲጋራ ለዱቤ ጥየቃ ይንጓተትሻል፡፡ ዱቤ መጠየቅ ከልክል ነው ብለን እንነቀስላቸው እየተባለ ሙድ የሚያዝባቸው ናቸው:፡»”


  ✏️✏️በጥቅሉ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቻችን ገመና ባጭሩ ከሞላ ጎደል እስካሁን ያየነውን  ይመስላል፡፡ የዩኒቨርሲቲዎች መብዛት ብቻውን ለምሁር መፍለቅ በቂ አይደለም፤ ምናልባትም ትምህርትን ለብዙኃን ለማዳረስ ካልሆነ በቀር፡፡ ልክ ዩኒቨርሲቲዎች የበዙትን ያህል ተማሪውን ከትምህርቱ የሚያግዱ ነገሮችም አብረው ይበዛሉ! ምናልባትም ከዚያ በብዙ እጥፍም ሊያድጉ ይችላሉ፡፡ በዚህን ጊዜ ተማሪው ከትምህርቱ ይታገዳል፡፡ ተማሪው ካልተማረ ደግሞ አስተማሪው አያስተምርም፡፡ ይህም በመሆኑም ተማሪው ትምህርቱን እንዲማር የተለያዩ ሥራዎች መሠራት አለባቸው:: በዚያው ልክ ተማሪውን ከትምህርቱ የሚያግዱ ነገሮችም እንዲጠፉ አብዝተው መሥራት ግድ ይላል፡፡


#በመጨረሻዉ_ክፍል
በዚና የተበከለ ትዉልድ የመጨረሻ ዉጤቱ
ጋብቻን ማዘግየትና ማጣጣል..የፍች መበራከት...እራስን የማጥፋት ወንጀሎች መበራከት በህብረተሰቡ ላይ ተፅዕኖ እንደፈጠረ እንዳስሳለን


join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
Live Aljezera tv ተመልከቱ

በተጨማሪ Bbc እና CNN tv

ኢራን ወደ እስራኤል የሚሳኤል ጥቃት እያደረሰቸች ነዉ፡፡

የንፁሀን እምባ የሚመለስበት ጥቃት አላህ ያድርገዉ


ከ250 በላይ የሚቆጠሩ ሚሳኤሎች ከኢራን ወደ እስራ *ል ተተኩሷል

የእስራ *ል ዋና ዋና ከተሞች ደወል በደወል ሆነዋል።



🇮🇷 በኢራን አብዮታዊ ዘብ መግለጫ ሰጥተዋል፡-

"እስራኤል መልስ ከሰጠች እኛ ሺህ ጊዜ የበለጠ እንመታቸዋለን"

"በሁሉን ቻይ አላህ ስም;  ለኢስማኤል ሀኒዬ፣ ለሰይድ ሀሰን ናስራላህ እና ለአባ ኒልፎሮሻን ግድያ ምላሽ ለመስጠት የጽዮናውያንን ወረራ አካል ልብ ላይ አነጣጠርን - እስራኤል ምላሽ ከሰጠች በሺዎች እጥፍ የበለጠ እንመታቸዋለን።


#አል_ጀዚራ_ይከታተሉ
2024/10/01 22:27:07
Back to Top
HTML Embed Code: