Telegram Web Link
27/08/2017

🎶ሸብ እረብ አለች ምድር አሆሆ አለች ምድር፤
RVC ልጆች ስትሾም አሃሃ አለች ምድር🎶

ወዳጆች እንዴት ቆያችሁ ጠፋሁ አይደል? 😁

ዛሬ ቤታችን ከወትሮ ደመቅመቅ ብላለች። ሽርጉድ ወዲህ ወዲያ  በዝቶባታል ምነው አትሉኝም? ዛሬ አዳዲሶቹን አመራሮች ይሾማሉና ነው ። እናላችሁ ይህች ቅዳሜ ሲመት ናትና ስለ መሪነት ተወያይተን፤ አመራሮችን
ተዋውቀን ተለያየን።

እኔም ታዲያ  ምን፣ምን ሃሳቦች እንደተንሸራሸሩ አጠቃላይ ሲመቱን ላቃኛችሁ ወደድኩ።

መሪነት ምንድነው ብለን ጀመርን ከብዙ እጆች መሃል፦
" ሙሴ እስራኤላውያንን መንገድ እንዳመላከታቸው ከፊት ሆኖ መንገድ ማመላከት ነው  "

"እረኛ መሆን ማለት ነው ከኋላ ሆኖ ሳይሆን ከፊት ሆኖ በር መክፈት ነው "

መልካም ተመሪነትስ ምንድነው ቢባል  ?

"ለመሪዎቻችን ቀና መሆን ማለት ነው"እንዴት አላችሁ?  ወዲህ ነው ነገሩ።

"ባህል አስተሳሰብ የህዝቡን መልክ የያዘ ነው። ክፉ የሆነ ህዝብ አለ። ምቀኛ አግላይ ከዛ ውስጥ የሚወጣ መሪ ጨካኝ ክፉ ይሆናል። "ስለዚህ መልካም ተመሪዎች ካልሆንን ጥሩ መሪ አናገኝም ነው ።ሃሳቡ መቼ በዚህ በቃና 🙂ሁሉ ሰው መሪ አይሆንም አሁን ዘመን አመጣሹ  ትችላለህና ትችያለሽን መልካም ተመሪ እንዳንሆን ያደረግን ቢባል አዎን ነበር የብዙዎች መልስ።

ሁሉም አዛዥ / አለቃ /መሪ መሆን ይፈልጋል።  ምክንያቱም መልካም ተመሪ መሆንን  እንደ ምንዝር መሆን እንድንመለከተው ስላደረጉን...

"መሪዎች ይፈጠረሉ /ይወለዳሉ
በተፈጥሮ መሪ የሆኑ ልጆች ይወለዳሉ በቃ ህፃን ሆነው ህፃናትን ሰብስበው የሚያሳምፁ ከፍ ሲሉም ከኋላቸው ሰው የሚያስከትሉ ስለዚህ መሪነት ለሁሉም አይደለም። "

"መሰጠት ያስፈልገዋል  "
በተቃራኒው ደግሞ መሪ እንዲሆን ከፈለግን የሆነን ሰው ማድረግ እንችላለን "
ወዲህ ወዲያ በሃሳብ ስንሸራሸር ወደ ማገባደዱ ደረስን።

እኔም የመጨረሻውን ሃሳብ ለእናንተ ልተው

አለቃ ወይስ መሪ ?

እንዲህ እንዲህ እያልን ውይይታችን ወደ ማገባደዱ ደረስን የነበሩትን አመራሮች አመስግነን፣ አዲሶቹን አደራ ጭምር ሰጥተን፣ዳቦ በጋራ ቆርሰን፣የጥበብ ስራዎችን አይተን ዳግም በቀጣይ ሳምንት ልንገናኝ ተቀጣጥረን ተለያየን።

ውብ ውሎ 🙏

📝 በማክዳ ጸጋዬ

#የምክንያታዊ_ባለራዕዮች_ስብስብ (2017)
#የተሻለ_ትውልድ_ለተሻለች_ኢትዮጵያ🇪🇹🇪🇹🇪🇹

@RvcClub
@RvcClub
👍4
Forwarded from HU STUDENT UNION OFFICIAL (Кαℓ 🫧)
እንኳን ደስ አላችሁ 🎊
መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ለሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወርቃማ እድል ይዞ ከተፍ ብሏል!!

🕹 በ ድሮን ቴክኖሎጂ
🧪 በጦር መሳሪያ ማምረት ቴክኖሎጂ
🛰 በሳይበር ሴክዩሪቲ
🚀 በሮኬት ሳይንስ
🩺 በጤና ሳይንስ
⚖️ በህግ እና አመራር ዘርፎች
👷‍♂በኢንጅነሪንግ ዘርፎች እና በመሳሰሉት ፊልዶች ላይ ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች የተዘጋጁትን እንቁ እድሎች ለተማሪዎች ገለጻ የሚደረግበት ፕሮግራም ሰለተመቻቸ ይህ እድል እንዳያመልጣችሁ::

🗓 ማክሰኞ, ሚያዝያ 28
🕓 ከቀኑ 8:00
📍በአፍሪካ አዳራሽ

‼️ይህ የትምህርት እድል በሁሉም የትምሀርት ዘርፍ ላይ ያሉ ተማሪዎችን እንዲሁም ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በተያያዥ ዘርፎች ላይ ለመስራት የሚያስቡ ተማሪዎችን በሙሉ ይመለከታል::
2
የምክንያታዊ ባለራዕዮች ስብስብ (rvc)

‼️ በrvc ቤት በአባልነት ቆይታችሁ በዘንድሮው አመት ተመራቂ ለሆናችሁ  ተማሪዎች በሙሉ⁉️


በብዙ ቆይታችሁ የተማማርንበት፣ ፣ጠይቃችሁ የመለሳችሁበት፣ወዷችሁ እና  ወዳችሁት የቆያችሁበት ቤታችሁ ወዳጆቼንማ አመስግኜና መርቄ ልሸኝ እንጂ በማለት ሽርጉዱን ተያይዞታል ።

ታዲያ እንናንተም በዚሁ መሰረት :-


📌ላለፉት አመታት RVCን ያገለገላችሁ(በሁሉም ረገድ)


📌የአባልነት መታወቂያ ያላችሁ


📌በሳምንታዊው ውይይቶቻችን እና ልዩ ልዩ ዝግጅቶቻችን ላይ ስትሳተፉ የቆያችሁ (attendance ይታያል ታዲያ )

ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች  የምታሟሉ ቤተስቦቻችን የሰርተፍኬት ማሰሪያ 50 ብር በ👇1000532041019
(Melak girmaw) በተሰኘው account በሞባይል ባንኪንግ ብቻ ማስገባት ይኖርባችኋል!

🛑 ማሳሰቢያ 👉ሙሉ ስማችሁን እና ገንዘቡን ማስገባታችሁን የሚያረጋግጥ ምስል(screen shoot ) ከታች👇 በተቀመጡት በሁለቱም አድራሻዎች(username) እስከ አርብ ድረስ ብቻ በመላክ በተለመደው ትብብር መሰነባበቻችንን በጋራ እናዘጋጅ ።


የቤትና የቤተሰብ ትርጉሙ ይሄም ነውና እንደ ወጉ ቸር ይግጠማችሁ ብለን ቀድመን መርቀን እንሸኛችሁ ።

1) @ruth827
2)@Mom2306

🛑 እስከ አርብ (30/8/2017) ብቻ እንድታስገብ።

📌 ክፍያውን ባለመክፈላችሁ ምክንያት ሰርተፍኬት ሳይሰራላችሁ ቢቀር ተጠያቂነቱን እንደማንወስድ ቀድመን ለማሳወቅ እንወዳለን ‼️⁉️

#ኑ_የቆምንበትን_መሠረት_እንፈትሽ
#የተሻለ_ትውልድ_ለተሻለች_ኢትዮጵያ
#የምክንያታዊ_ባለራዕዮች_ስብስብ
@RvcClub
@RvcClub
👍3
Forwarded from HAYLEAB TEREFE(Mickey)
መቅረዝ የኪነ-ጥበብ አፍቃርያን ሕብረት

💥መቅረዝ ይሄን ቅዝቃዜ የምንረሳበትን ሞቅ ያለ ደማቅ የጥበብ ምሽት አዘጋጅቷል።
አርብ ግንቦት 1 በሐዋሳ ዩንቨርስቲ ሞቅ ደመቅ ያለ ልዩ የጥበብ ምሽት አዘጋጅቶ ይጠብቃቿል። በዕለቱ አዝናኝ አስተማሪ እንዲሁም ፈገግታን ጫሪ የሆኑ ፕሮግራሞችን እያቀረበ ለውድ ታዳሚዎች የማይረሳ ጊዜን ያካፍላል።

📜በምሽቱ ከሚቀርቡ ፕሮግራሞችም መካከል
🌟ግጥም
🌟ስነ-ፅሁፍ
🌟ሙዚቃ
🌟ጭውውት
🌟ውዝዋዜ
እንዲሁም በተለያዩ እዝናኝ ጨዋታዎች እየተዝናናን ሞቅ ደመቅ ሸብረቅረቅ ያለ ደማቅ ግዜን እናሳልፋለን።

🗓️አርብ ግንቦት 1
📌 አፍሪካ ሕብረት አዳራሽ
ቀን 10፡00ጀምሮ

💬ለበለጠ መረጃ እንዲሁም አዲስ መቀላቀል ለምትፈልጉ በመቅረዝ
🎤በሙዚቃ🎤
🎭በትወና 🎭
🖋️በስነ-ፅሁፍ እና 🖋️
🕺በውዝዋዜ 💃አዲስ መሳተፍ ለምትፈልጉ ተማሪዎች ከታች በተቀመጡት ልታገኙን ትችላላችሁ ፡-
☎️0989058688
☎️0904417552
☎️0929042323
☎️0934700730

Join Telegram
https://www.tg-me.com/mekerezeactingstudents

መኖር መሆን ስኬት
መቅረዝ!!!
👍2
Forwarded from Hawassa university
ነገ! ማለትም ሃሙስ ሚያዝያ 30 የ2017 ተመራቂ ተማሪዎች "50 days left” day በTechno (IoT) ግቢ ከከሰዓት 9:00 ጀምሮ ሞቅ ደመቅ ተደርጎ ይከበራል!

For Night Event ticket and related issues Contact : @Zewdnssh
👍3
2025/07/10 05:57:15
Back to Top
HTML Embed Code: