Telegram Web Link
አዎን ይቻላል‼️አካል ጉዳተኝነቱን ድል የነሳ አንበሳ!!

ይህ ከሰንሰለታማው ጋራምባ ተራራ ግርጌ በመነሳት በአካል ጉዳተኝነትና በሕይወት ፈተና ሳይበገር፣ ተፈትኖ ለሰኬት የበቃው፣ የወጣቱ በለጠ ቡቱና (የአርሶ አደር ልጅ) አጭር የሕይወት መንገድ ታሪክ ነው!
በለጠ ቡቱና (ያምቡሌ) ትውልድና እድገቱ አርቤጎና ወረዳ ሲዳማ ነው። በለጠ 1989ዓ.ም አርቤጎና ጎዋ ቀበሌ ልዩ ሥፍራ ቡላ ተወለደ። በለጠ ከልጅነቱ ጀምሮ በሁለት እግሩ መራመድ አይችልም ነበር። በዚህ ምክንያት እጆቹን እንደ እግርም እንደ እጅም ለመጠቀም ተገደደ። አካል ጉዳተኝነትን  እንደ የእግዚአብሔር ቁጣ ተደርጎ በሚታሰብበት በአብዛኛው የኢትዮጵያ ማህበረሰብ በገጠር ተወልዶ፣ አይደለም ተምሮ ለወግ ማዕረግ መብቃት በተሰፋ መኖር መቻል በራሱ ፈታኝ ነው።

በለጠ በህፃንነቱ በወላጅ እናቱና አባቱ መካከል በተፈጠረው አለመግባባት በመለያየታቸው ሌላ የሕይወት ፈተና ለመጋፈጥ ተገዷል። የወላጆቹ መለያየት በአካል ጉዳተኝነቱ ላይ ታክሎበት ሕይወትን በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ዓይነት አድርገውበታል። 

በለጠ ዕድሜው ለትምህርት ሲደርስ በአካባቢ ወደ ትምህርት ቤት የሚሄዱ ልጆችን እያየ "እኔም ከእነዚህ ልጆች ጋር ትምህርት ቤት በሄድኩ!" እያለ ይብሰለሰል ጀመር። ግና አካል ጉዳተኛነቱ፣ ትምህርት ቤት በአቅራቢያው አለመገኘቱ፣ የመንገድ መሠረተ ልማት ችግር፣ የመጓጓዣ እጦት፣ ማህበረሰቡ በአካል ጉዳተኞች ላይ ያለው አሉታዊ አመለካከት፣ ወላጅ እናት ቤት ውስጥ በማጣት እህል ውሃ የሚሰጥ ሰው መጥፋቱ ይህ ሁሉ ፈተና ከፊት ለፊት ተሰልፎ የሚጠብቀው ነበር። በለጠ ልቡ ኮስታራ ነበረና ፈተናዎቹን ሁሉ ለመጋፈጥ ቆርጦ ተነሳ። "አልችልም!" በይነትን ገና በጠዋቱ ቀበረ። "አዎን ይቻላል!" አለ። አባቱ  ከGowa (ጎዋ)  ጋራምባ ተራራ አከባቢ Fiide Fooliishsho (ፊዴ ፎሊሾ) ቀበሌ ወዳለው እርሻ ተዘዋውሮ መጥቶ እያለ ከእነሱ መንደር በ5 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ወደሚገኝ Shurro (ሹሮ) አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመግባት ወሰነ።

"የት ልትደርስ ትማራለህ? በዚህ ጭቃ በእጅህ እየ ደኽህ መከራ ከምታይ አርፈህ አትተኛም!" የአብዛኛው ማህበረሰብ ቅስም ሰባሪ አሰተያየት ነበር። በሌ ለአሉታዊ አሰተያየቶች ጆሮ አልሰጠም። የአንደኛ ክፍል ትምህርቱን አንድ ቢሎ ሹሮ ት/ቤት ጀመረ።

ጋራምባ ተራራና አከባቢው በሲዳማ ክልል የደጋማ ሥፍራዎች ቁንጮ መሆኑ ይታወቃል። በዚህ ተራራ አቅራቢያ የሚገኘው ሹሮ ት/ቤ ከአርቤጎና ወረዳ የሩቅ ት/ቤት ተብለው ከሚታወቁት አንዱ ት/ቤት ነው። የአከባቢው የአየር ንብረት በጣም ዝናባማ፣ መልካ ምድሩ ተራራማ፣ የመረት አቀማመጥ አይደለም ለአካል ጉዳተኛ ለጤነኛ ሰውም ፈታኝ ነው። በለጠ ለተፈጥሮ ፈተና እጅ ሳይሰጥ ከፊዴ ፎሊሾ ቀበሌ ከመኖሪያ በቤታቸው ለሊት 11:00 ወጥቶ 5 ኪ.ሜ ከ3-4 ሰዓት በእጁ እየተራመደ ትምህርት ቤት 2:00 ይደርስ ነበር። በዚህ መልኩ ወደ ት/ቤት ሲሄድ ብዙ ፈተና ገጥሞታል። በአንድ ወቅት ወንዝ ዘሎ ለመሻገር ሲሞክር ይዞት ሄዶ እግዚአብሔር እንዳሰጣለው አጫውቶኛል። በለጠ ከአብሮ አደጎቹ እጅግ ቀድሞ ጉዞ ሰለሚጀምር ዝናብና ብርድ ከማንም በላይ ተፈራርቆበታል። እሾህ፣ ጠጠርና ጭቃ እንደ እግር የሚጠቀማቸውን እጆቹን ጎድተውታል። ከማህበረሰቡ መገለል፣ መድሎ፣ ተሰፋ እስቆራጭ ንግግሮች ተፈታትነውታል።  በለጠን ግን ከአካል ጉዳተኝነቱ ጋር ይህ ሁሉ መከራ ታክሎበት ቢሆን የልጅነቱ  ህልሙ ምን ከመኖር አላገደውም።

በለጠ የአንደኛ ክፍል ትምህርቱን በብዙ ፈተና ሹሮ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አጠናቆ የተሻለ ሕይወትና ትምህርት በመሻት ወደ አርቤጎና ወረዳ አሰተዳደር መቀመጫ ወደ ሆነቺው Yayye (ያዬ) አቀና። ያዬ ከፊዴ ፎሊሾ (ከነበለጠ ገጠር) 14 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች። በለጠ ከ2-8 ክፍል ቁኒቻ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት፣ ከ9-12 አርቤጎና ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተምሯል።  ያዬ  ከተማም ከአዲስ አበባ ከተማ እኩል የቆረቆረች ዕድሜ ጠገብ የደጋ ሀገር ከተማ ብትሆንም ለአካል ጉዳተኛ የሚመች መሠረተ ልማት የላትም። የተፈጥሮ በረከቷ እንደተጠበቀ ሆኖ ቅዝቃዜ፣ ዝናብ፣ ጭቃ የተለመደ ነው። በመሆኑም በለጠን ሕይወቱን በከተማ ቢያደርግም ፈተናዎቹ እልፍ ነበሩ።

በሌ ያዬ ከተማ ገብቶ ሦስተኛ ክፍል እስክደርስ በባዶ እጆቹ ነበር የሚራመደው። ልብ በሉ በባዶ እግሩ ሳይሆን በባዶ እጆቹ። ለእጁ የመጀመሪያ ነጠላ ጫማ ሦስተኛ ክፍል ደርሶ ነበር ማድረግ የቻው። የያዬ ከተማ ጭቃና ፒስታ መንገድ አይደለም ነጠላ ጫማ ጫማም አይችለውም። በለጠ በእጆቹ ከመራመድ ነጠላ ጫማ ማድረጉ ከጠጠርና እሾህ ሰቃይ ትንሽ ያሽለው ቢሆን እንጂ ዘላቂ መፍትሄ አልሆነለትም።

በለጠ ሰባተኛ ክፍል ደርሶ ከነጠላ ጫማ ወደ ሸበጥ  ጫማ ከፍ ማለት ቻለ። በለጠ ለመማር ያለውን ጥረትና ከሰዎች ጋር በጣም ተግባቢ መሆኑን በዚያን ጊዜ ያዬ ከተማ የግል ክሊኒክ የነበረው አቶ ካሣ ካዬሶ ዊልቼር አምጥቶ እንደ ሰጠው ይናገራል። ያዬ ከተማ በዛ የጠጠር መንገድ፣ በዚያ ጭቃ እንዴት ይንዳው? ማንስ ይግፋው? በለጠ ተማሪዎች እየገፉት ለጥቂት ጊዜ ሕይወትን በዊልቼር ሞከረው። የአየር ፀባዩና የመሠረተ ልማት ችግር ሌላ ፈተና ሆኖበት ዊልቼሩን በመተው ወደ ሸበጥ ጫማው ተመለሰ።

በለጠ በክረምትና አንገብጋቢ ማህበራዊ ጉዳዮች ሲገጥሙት ከያዬ ፊዴ ፎሊሾ አንዳንዴ በፈረሰ፣ ሌላ ጊዜ ሰው ተሸክሞት ተመላልሷል። በአንድ ወቅት ከፊዴ ፎሊሾ እሰከ ያዬ ከቤት ከለሊቱ 11:00 ተነስቶ ከምሽቱ 1:00 ( ከ12 ሰዓታት) በላይ በእጆቹ ተጉዞ እንደደረሰ ያስታውሳል። በለጠ የጥንካሬው ጥግ፣ ለአካል ጉዳተኝነትና እሱን ተከትሎ ለሚገጥሙ ፈተናዎች ሁሉ እጅ ያለመሰጠት ልክ፣ የመንፈሰ ብርታቱ መጠን የሚደንቅ ወጣት ነው። በእውነቱ በዛ ገጠር፣ በዛ ማህበረሰብ ውሰጥ አካል ጉዳተኛ ሆኖ ተወልዶ እንደ በለጠ ለመሆን የሚታሰብ አይደለም። እሱ ግን መሆን የሚፈልገውን በእግዚአብሔር ኃይል ሆኖ አሳየ። ይደንቃል።

በለጠ የአሥራ ሁለተኛ ክፍል ካጠናቀቀ በኋላ በ2012 ሐዋሳ ዩኒቨርስቲ በኤክስቴንሽን የትምህርት መርሃግብር በማኔጅመንት ትምህርት ክፍል የመጀመሪያ ድግሪ ትምህርቱን ጀመረ። ላለፉት 5 ዓመታት ኑሮውን በሐዋሳ ዩኒቨርስቲ በማድረግ፣ የማደሪያና የምግብ ድጋፍ ከዩኒቨርሲቲው በማግኘት ከምንም በላይ በእግዚአብሔር አቅም ጉልበት ሆኖለት ትምህርቱን ማጠናቀቅ ችሎዋል።

በለጠ ምንም እንኳን አካል ጉዳተኛ ቢሆንም ሥነ ልቦናው ጠንካራ ነው። በራሰ መተማመኑ ከፍ ያለ ነው። ባህሪው  ከሰዎች ጋር ቶሎ ተግባቢ፣ በግል ሕይቱ ዘናጭና ንፅህናን የሚወድ በጣም አራዳ ነው። በሌ የዋዛ አይምሰላችሁ። መብቱን ለማሰከበር ከማንም ጋር ከመጋፈጥ ወደ ኋላ የማይል ቆራጥ ተሟጋች ነው።  የሲዳማን ሀዮ (መላ) ያውቅበታል። ንቃተ ህሊናው የላቀ ነው። ሰው ሁሉ የሚደነቅበት ወጣት ነው። በለጠ የራሱ ብቻ አይደለም። ለማህበረሰቡ መብትና ጥቅም ጥብቅና ለመቆም አንደኛ ነው። በሌ ማህበራዊ ሕይወቱ ጠንካራ ነው። የታመመውን ሆስፒታል፣ የታሠረውን ማረሚያ ሄዶ ይጠይቃል። ለቅሶና ቀብር ቀድሞ ይደርሳል። በለጠ (ያምቡሌ) የስፖርት አፍቃሪ ነው። በአካል ጉዳተኞች ስፖርት በአትሌቲክስ ዘርፍ የቀድሞ ደቡብ ክልል በመወከል በልዩ ልዩ ዘርፎች ሜዳሊያ ተሸላሚም ነበር። በለጠ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ቀንደኛ ደጋፊም ነው። በለጠ "አካል ጉዳተኛ አካሉ ቢጎዳም አሰተሳሰቡና ልቡ ጤናማ እሰከሆነ ድረስ ያሰበበት ከመድረስ የሚከለክል ነገር የለም!" ብሎ
ያምናል።

በለጠ ለዚህ ስኬት እንዲበቃ እግዚአብሔር እንደረዳው ይናገራል። የግል ጥረቱና ለፈተናዎች ሁሉ እጅ አለመሰጠቱ የስኬቱ ዋነኛ ምክንያት ነው። ሐዋሳ ዩኒቨርስቲ፣ የሲዳማ ክልል ሴቶችና ህፃናት ቢሮ፥ ለጋሽ ግለሰቦች፣ የተለያዩ ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች፣ ቀና ልብ ያላቸው የማህበረሰብ አካላት፣ ወጣቶች ከስኬቱ ጀርባ እንደሚገኙ ይናገራል።

ለወደፊት ምን መሆን እንደሚፈልግ ጠይቀው
እግዚአብሔርንና ማህበረሰብን ማገልገል ዋና የሕይወት ግቡ መሆኑን አጫውቶኛል።

የተከበራችሁ አንባቢን የበለጠ ቡቱና (ያምቡሌ) የሕይወት ውጣ ውረድና ስኬት ታሪክ ማንበብ የአንድ አካል ጉዳተኛ ሕይወት መሻሻል ምክንያት ሊሆን ይችላል። የሱ ታሪክ የአካል ጉዳተኛ ቤተሰብ ተሰፋና ሞራል ሊያበረታታ ይችል ይሆናልና ጽሑፉን ለብዙዎች በማዳረሰ ማህበራዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ በፍቅር ላሳሰባችሁ እወዳለሁ።

በስተመጨረሻ በበለጠ የሕይወት ጉዞ ታሪክ የተመሰጣችሁ በሀገር ውስጥና በወጪም ያላችሁ ካላችሁ ቀጥሎ ባለው የግል የሰልክ ቁጥሩ በመደወል፣ እንድታበረታቱት በታላቅ አክብሮት እጠይቃችዋለሁ።

0918991011 [Belete Butuna]

ሳሙኤል በላይነህ ቃ'ሜ
ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
ሐዋሳ፣ ሲዳማ | ኢትዮጵያ 🇪🇹
Forwarded from True Culture University HU-Chapter (ilham🤍)
🎉Dear Hawassa University Class of 2024,🎉

Congrats on your remarkable achievement! Your dedication, hard work, and perseverance have led you to this momentous milestone.

🎓As you step into the next chapter, may you find success in your endeavors. Continue to make a positive impact, and hold dear the friendships and values you've gained here.

💐TRUE CULTURE UNIVERSITY is incredibly proud of you. Best wishes for a bright and prosperous future.


🎓CONGRATULATION CLASS OF 2024/2016! Today is your day🥂🍾

👉🏼 https://www.tg-me.com/tcuhawassa
🎓 🎉 Congratulations 🎉 🎓

A celebratory message from Hawassa University Student Union President Essey Petros extends congratulations to all Hawassa University 25th batch graduating students on their momentous achievement. This is a great opportunity to acknowledge their hard work and dedication throughout their academic journey.

Happy Graduation 2024 🎉

HU Student Union Official
🎉 🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎉

ለ 2016 የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ተመራቂ ተማሪዎች👩‍🎓👨‍🎓 በሙሉ፤ እንኳን ለዚህ የልፋታቹን ውጤት ለምታዩበት እና ስኬታቹን ለምታስመሰክሩበት ታላቅ ቀን አደረሳቹ።

ይህ ዕለት ቀጣዩን የስኬት ጎዳና የምትጀምሩበት፤ የተሻለች ኢትዮጵያን የምትሰሩ የተሻለ ትውልድ ለመሆን ጉዞ የምትጀምሩበት ቀን እንዲሆን በRVC ስም እንመኝላቹሀለን።


🎉🎓🎓መልካም የምረቃ በአል !!!🎓🎓🎉



🎉 🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎉

To all 2016 Hawassa University graduate students👩‍🎓👨‍🎓; Wishing you a great day where you will see the results of your hard work and witness your success.

On behalf of RVC, we wish that this day will be the day you start the next path of success and a day to start your journey to become a better generation that will make a better Ethiopia.


🎉🎓🎓Congratulations !!!🎓🎓🎉‌‌

#ኑ_የቆምንበትን_መሠረት_እንፈትሽ
#የተሻለ_ትውልድ_ለተሻለች_ኢትዮጵያ
#የምክንያታዊ_ባለራዕዮች_ስብስብ

@RvcClub
🎓🎓 🌎 Congratulations 🎉🎉 🌎

Geological Society of Hawassa University Wishes to all Hawassa University 2024 Graduating Students Happy Graduation. Special Congratulations to Department of Geology graduating students. May your degree open doora to a deserved success!


𝚄𝚗𝚎𝚊𝚛𝚝𝚑𝚒𝚗𝚐 𝚝𝚑𝚎 𝚙𝚊𝚜𝚝, 𝚂𝚑𝚊𝚙𝚒𝚗𝚐 𝚝𝚑𝚎 𝚏𝚞𝚝𝚞𝚛𝚎

Geological Society of Hawassa University

Telegram | Facebook | Instagram
Forwarded from UNA-ET HU CHAPTER (Sitra)
List of GC Students.docx
15.5 KB
Graduating Students whose names are on the list and all MUN participants, you can pick up your certificates today!

From 10:30 LT - 11:00 LT
Around AU Hall

📍Please be on time as this will be the last day we will be handing out certificates.
የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የመመገቢያ ካፍቴሪያ ምደባ

| የተማሪዎች መማክርት
የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የወንዶች ዶርሚሪ ምደባ

| የተማሪዎች መማክርት
የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የሴቶች ዶርሚሪ ምደባ

| የተማሪዎች መማክርት
📢 Calling all Hawassa University students!

UNA-ET-HU is seeking dedicated individuals to join our team as Executive Members!

We're looking for:

✍️ Secretary
🗣️ Head of Communication
🤝 Internal Affairs & Facilitator
👥 Membership Coordinator
💰 Head of Finance

Are you ready to make a difference?

➡️ Apply now! ➡️ https://shorturl.at/dbQUE

Eligibility:

Any undergraduate Hawassa University student is eligible!
Must not be an executive in other clubs or associations.
Submit your resume (CV) and motivational letter through the Google Form provided.
Deadline: July 16, 2024

Important Notes:

📌 Clearly state the position you're applying for in your motivational letter.

📌 Your motivational letter should not exceed one page.

📌 Highlight your past experiences and achievements in your resume.

For any questions or inquiries please contact @RaguelShitu

#Executives
UNA-ET-HU is seeking dynamic leaders to head our teams!

We're looking for:

🚀 Project Team Head
🗣️ Debate Team Head
🎗 Event Team Head
🌍 SDG Ambassadors Team Head
🏛️ MUN Team Head

Are you ready to lead and inspire?

➡️ Apply now! ➡️ https://shorturl.at/RHoQF

Eligibility:

Any undergraduate Hawassa University student is eligible!
Submit your resume (CV) and motivational letter through the Google Form provided.
Deadline: July 16, 2024

Important Notes:

📌 Clearly state the position you're applying for in your motivational letter.
📌 Your motivational letter should not exceed one page.
📌 Highlight your past experiences and achievements in your resume.

For any questions or inquiries
please contact @RaguelShitu

#TeamHeads
Forwarded from UNA-ET HU CHAPTER (Sitra Abubker)
UNA-ET-HU is seeking talented individuals to join our dynamic Communication Sub-Team!

We're looking for:

📱 Social Media Manager
🎨 Graphics Designer
🖌 Co-Graphics Designer


➡️ Apply now! ➡️ https://shorturl.at/RhZoC

Eligibility:

Any undergraduate Hawassa University student is eligible!
Submit your resume (CV) and motivational letter through the Google Form provided
Deadline: July 16 , 2024

Important Notes:

📌 Clearly state the position you're applying for in your motivational letter.
📌 Your motivational letter should not exceed one page.
📌 Highlight your past experiences and achievements in your resume.


For any questions or inquiries
please contact @RaguelShitu

#CommunicationSubTeam
Exit Exam Disciplinary Measures.pdf
6.3 MB
ከመውጫ ፈተና ጋር ተያይዞ በዲሲፕሊን ጥሰት ምክንያት የተቀጡ ተማሪዎችን ዝርዝር መረጃን የያዘ ፋይል። 

| የተማሪዎች መማክርት
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
2024/09/28 05:18:05
Back to Top
HTML Embed Code: