Telegram Web Link
"ከቤተ ክርስቲያን የሚበልጥ ብርቱ (ጠንካራ) ምንም የለም። ይህችውም ከሰማይ ከፍ ያለች ከምድርም ይልቅ የሰፋች ናት። አታረጅም ነገር ግን ዘወትር ታበራለች።"…

"ቤተ ክርስቲያን በዘመናት ሁሉ ትሰፋለች። መታሰቢያዋም የሚጠፋ (የሚሞት) አይደለም።"…

"ቤተ ክርስቲያን በስንቶች ውጊያ ተደርጎባት ነበር? አልተሸነፈችም እንጂ። የተዋጓት አላውያን፣ የጦር መሪዎች፣ ነገሥታቱስ ምን ያህል ናቸው? የተማሩና ኃይልን የተሞሉ ጎበዞች ሐዲሲቷን ቤተ ክርስቲያን በብዙ ጎዳናዎች ተዋግተዋት ነበር። ሊነቅሏት ግን አልቻሉም። ነገር ግን እርሷን የተዋጉ ጥቂቶች ለዝምታና ቶሎም ለመረሳት ተላልፈው ተሰጥተዋል። የወጓት ቤተ ክርስቲያን ግን ከሰማይ በላይ ከፍ ከፍ ብላለች። ቤተ ክርስቲያንን ድል ከማድረግስ ፀሐይን ማጥፋት (ማጨለም) ይቀላል። ሰው ሆይ! ከቤተ ክርስቲያን የሚበልጥ ኃያል ምንም የለም። ከሰው ብትጣላ ወይ ታሸንፋለህ አልያም ትሸነፋለህ። ቤተ ክርቲያንን ግን ብትጣላ፣ ታሸነፍ ዘንድ የሚቻልህ አይደለም። እግዚአብሔር ከሁሉ ይልቅ ኃያል ነውና። እግዚአብሔር መስርቷታል፣ እንግዲህ ማን ሊነቀንቃት ይችላል? "

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
(በዲያቆን አቤል ካሳሁን የተተረጎመ)
ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ):
እንኩዋን ለአበው ቅዱሳን "አባ ዳንኤል" : "አባ ዸላድዮስ" : ወቅዱስ "ፊላታዎስ ሰማዕት" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

+*" ማር ዳንኤል "*+

=>"ዘዓምድ" በሚል ስም ከሚታወቁ የቤተ ክርስቲያን አበው መካከል 4ቱ ቅድሚያውን ይይዛሉ:: እነዚህም:-
1.ቅዱስ ስምዖን ዘዓምድ:
2.ቅዱስ አጋቶን ዘዓምድ:
3.ቅዱስ ዳንኤል ዘዓምድ እና
4.ቅዱስ ሉቃስ ዘዓምድ ናቸው::

+"ዘዓምድ" የሚለውን ቃል ምሥራቃውያን በልሳናቸው 'THE STYLITE' ይሉታል:: የእኛው ቃል ደግሞ ከግዕዝ የተወረሰ ነውና በቁሙ ቢተረጐም "የምሰሶው" የሚል ትርጉምን ይይዛል:: ይህም በ2 ምክንያቶች ነው::

+አንደኛው ቅዱሳኑ ተጋድሏቸውን የፈጸሙት ከረዥም ምሰሶ ላይ ወጥተው በመጸለይ ስለሆነ ነው:: ሌላኛው ምክንያት ደግሞ እነዚህ አባቶች በዘመኑ ለነበሩ ምዕመናንና መነኮሳት አጽናኝ: አስተማሪ: መሪና ፈዋሽ በመሆናቸውና እንደ ምሰሶ ተተክለው ሳይነቃነቁ በመጸለያቸው ነው::

+ልክ ከዓለም ሃገራት ብዙ ስውራንን እና ቅዱሳን ነገሥታትን በመያዝ ሃገራችን ቀዳሚ እንደ ሆነችው ሁሉ ምሰሶ ላይ ወጥተው የሚጋደሉ ቅዱሳንም ሶርያውያንና ምሥራቃውያን ናቸው:: በዚህ ዕለትም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የታላቁን ቅዱስ ማር ዳንኤልን በዓል ታከብራለችና ከዜና ሕይወቱ ለበረከት ጥቂት እንካፈል::

=>ይህ ቅዱስ ሰው (በስዕሉ የሚታየው) ሶርያዊ ሲሆን ተወልዶ ያደገባት አካባቢ በቀድሞው አጠራር "ሃገረ ዓምድ" ይሏታል:: "ማር" የሚለው ቃል በቤተ ክርስቲያን ቅድስናንና አለቅነትን የሚገልጽ ስም ነው:: በዚህ ስም ጥቂቶች ብቻ ሲጠሩበት ለሊቃውንትም: ለሰማዕታትም: ለጻድቃንም አገልግሏል::

+ቅዱሱ "ማር" ብቻ ሳይሆን "ዘዓምድ" ተብሎም ተጠርቷል:: ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ እርሱም በፊት እንደ ጠቀስናቸው አበው ምሰሶ ላይ ተጠግቶ (ቆሞ): ትኩል ከመ ዓምድ ሆኖ በመጸለዩ ነው::

+ማር ዳንኤል በምድረ ሶርያ ስመ ጥር ጻድቅ ነው:: በዘመነ ጻድቃን መጨረሻ አካባቢ ከክርስቲያን ወገኖቹ ተወልዶ: በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አድጐ: ገና በልጅነቱ ለቤተ እግዚአብሔር ተሰጥቷል::

+የወቅቱ የሃገረ ዓምድ ዻዻስ (አባ ዼጥሮስ) ለማር ዳንኤል ፍኖተ ጽድቅን (የሕይወት - የእውነትን ጐዳና) በማሳየት ከፍ ያለውን አስተዋጽኦ አበርክቷል:: አስተምሮም ለመዓርገ ክህነት አብቅቶታል::

+ቅዱሱ በእድሜው እየበሰለ ሲሔድ ግን ምርጫው ምናኔ ሆኖ በመገኘቱ በፈቃዱ ወደ በርሃ ሔደ:: በዚያም መዓርገ ምንኩስናን ተቀብሎ በጾም: በጸሎትና በትሕርምት ይጋደል ገባ::

+ማር ዳንኤል በበዓቱ ተወስኖ ሲጾም: ሲጸልይና እግዚአብሔርን ሲያመልክ ከጸጋ (ከብቅዓት) ደረሰ:: ብዙ ተአምራትንም በመሥራቱ ስም አጠራሩ በአካባቢው ተሰማ:: እርሱ ግን ከሰው: ይልቁንም ከሴቶች ይርቅ: ላለማየትም ራሱን ይከለክል ነበር::

+ለአንድ መናኝ በሰዎች መካከል: ይልቁንም በተቃራኒ ጾታ ጐን መኖር ያልተፈቀደ: ፈታኝም ድርጊት ነውና ከፈጣሪው ጋር እንዲህ የሚል ቃልን ገባ:: "ከዚህ በሁዋላ ሴት ልጅን አላይምም" አለ:: በእንዲህ ያለ የቅድስና ሕይወት ሳለ ወላጅ እናቱ ልታየው ተመኘች::

+ወደ ገዳሙ መጥታም "ልጄ! ላይህ ሽቻለውና ልግባ : ወይ ብቅ በል" ስትል ላከከችበት:: ቅዱሱ ግን "እናቴ! ሴትን አላይም ብየ ቃል ስለ ገባሁ አልችልም" ሲል መለሰላት:: በጣም አዝና "እኔ ወልጄ: አዝዬ: አጥብቼ: አሳድጌ እንደ ሌሎች ሴቶች አስመሰልከኝ? በል ፈጣሪ 2 ሴቶች በአንድ ልብስ ሆነው ይዩህ!" ብላ ረግማው ወደ ቤቷ ተመለሰች::

+የሚገርመው ማር ዳንኤል በበርሃ የበቃውን ያህል እናቱ በዓለም ሳለች በጐ ሰርታለችና እርሷም ጸጋውን አብዝቶላታል:: በምን ይታወቃል ቢሉ:- ያቺ የተናገረቻት ነገር ሁሉ ደርሶበታልና::

+አንድ ቀን ለገንዘብ ሲል አንድ ሰው የገደለውን አምጥቶ በቅዱሱ በር ላይ ጣለው:: ቅዱሱም ያለ አበሳው ታሥሮ ወደ ከተማ ሲወሰድ መታጠቢያ (shower) ቤት ውስጥ የነበሩ ሴቶች ሊያዩት ቸኩለው: አንድ ልብስ ለብሰው ወጥተዋል:: ማር ዳንኤል ይህንን ሲያይ የእናቱ ነገር ትዝ ብሎት ሳቅ ብሏል::

+በታሠረበት ቦታ ግን የሞተውን ሰው በጸሎቱ በማስነሳቱ በክብር ወደ በዓቱ ተመልሷል:: የከተማዋ ንጉሥም ገዳምን አንጾለታል:: በተረፈ ዘመኑም ለብዙ ቅዱሳን አባት ሆኖ እስከ እርጅናው አገልግሏል:: በዚህች ቀንም በክብር ዐርፏል::

+*" አባ ዸላድዮስ "*+

=>አባ ዸላድዮስም በተመሳሳይ የዘመነ ጻድቃን ፍሬ ነው:: በርሃ ከገባባት ቀን ጀምሮ ጾምን: ጸሎትን አዘውትሮ ክርስትናውን አጽንቷል:: ሙሉ እድሜውን በጐ በመሥራት በማሳለፉ ፈጣሪውን ሲያስደስት ለብዙዎች አንባ: መጠጊያ መሆን ችሏል::

+በጸሎቱ አካባቢውን በደህንነት ይጠብቅ ነበር:: ምዕመናን እንኩዋን ወደ እርሱ መጥተው ተባርከው ባሉበት ቦታ ሁነው ተማጽነው እንኩዋ መሻታቸውን አያጡም ነበር:: ምንም ያህል ኃጢአተኞች ይሁኑ እግዚአብሔር ስለ አባ ዸላድዮስ ሲል ይለመናቸው ነበር::

+አንድ ቀን አንድ ነጋዴ ሰው በባሕር ላይ ሲሔድ ድንገት ማዕበል ይነሳበታል:: ብቻውን ነበርና ጨነቀው:: እሱ ያለባት ጀልባም ትንሽ በመሆኗ ልትሠበር ደረሰች:: መዳን እንደ ማይችል ሲያውቅ ተስፋ ቆረጠ::

+ድንገት ግን አባ ዸላድዮስ ትዝ ብሎት ቀና ብሎ "ጌታየ! ስለ ቅዱሱ አባት ብለህ ብትምረኝ ለወዳጅህ መቶ ዲናር ወርቅ እሰጣለሁ" ሲል ተሳለ:: ቃሉን ተናግሮ ሳይጨርስ አባ ዸላድዮስ በጀልባው ላይ ቁጭ ብሎ ታየው:: ማዕበሉም ጸጥ እንዲል አድርጐ ከወደብ አድርሶ ተለየው::

+ነጋዴውም ፈጣሪውን ስለ ድኅነቱ እያመሰገነ 100 ዲናር ወርቁን ይዞ አባ ዸላድዮስን ፍለጋ ወጣ:: የሚያውቀው በዝና ብቻ ነበርና:: መንገድ ላይም ሞሪት የሚባል መሪ አግኝቶ ከአባ ዸላድዮስ በዓት ደረሰ::

+ከቅዱሱ ተባርኮ ወርቁን ቢያቀርብለት "ልጄ! እኔ ይህን አልፈልገውም:: ለነዳያን በትነው" አለው:: ነጋዴው ሲወጣ ግን ሞሪት (መሪው) ገንዘቡን ፈልጐ ገደለውና ከጻድቁ በር ላይ ጣለው:: ሃገረ ገዢውም ሲሰማ አባ ዸላድዮስን አሠረው::

+ጻድቁ ግን የሞተውን ባርኮ አስነሳውና "ማን ገደለህ" ቢለው "ሞሪት" ሲል መልሷል:: መኮንኑ ሞሪትን ሊገድለው ቢልም "የለም" ብሎ ነጋዴውን በደስታ: ሞሪትን ደግሞ በንስሃ ሸኝቷቸዋል:: አባ ዸላድዮስ ግን ተረፈ ዘመኑን በቅድስና ሲጋደል ኑሮ በክብር ዐርፏል::

+*" ቅዱስ ፊላታዎስ ሰማዕት "*+

=>"ፊላታዎስ" ማለት "መፍቀሬ እግዚአብሔር - እግዚአብሔርን የሚወድ: እርሱም የሚወደው" ማለት ነው:: ቅዱሱ የዘመነ ሰማዕታት (3ኛው መቶ ክ/ዘመን) ፍሬ ሲሆን ለየት ያለ ታሪክ ያለው ቡሩክ ወጣት ነው::

+እርሱ የባለ ጸጐች ልጅ: ስለ ክርስትና ምንም ሰምቶ የማያውቅ ሕጻን ነበር:: ወላጆቹ የሚያመልኩት ላምን ሲሆን የአካባቢው ሰው ደግሞ ለጸሐይ ይንበረከክ ነበር:: ቤተሰቦቹ ስለ አምልኮ ሲጠይቁት "እናንተ የምታመልኯቸው ፍጡራን ስለ ሆኑ አልፈልግም" አላቸው::

+ሕጻን ቢሆንም ስለ ፈጣሪው ተመራመረ:: በመጨረሻውም ፀሐይን "አንተ ምንድነህ?" ቢለው "እኔ ፍጡር ነኝ" ሲል መልሶለታል:: በዚያች ዕለት ግን ቅዱስ መልአክ ወርዶ: ሁሉን ነገር አስተምሮ የክርስቶስ ወታደር አድርጐታል::
+ወደ ቤቱ ተመልሶም የወላጆቹን ላም "እውነትን ተናገር" ብሎ ገስጾታል:: ላሙም ሰይጣን እንዳደረበት በሰው ልሳን ተናግሮ: የቅዱሱን ወላጆች ወግቶ ገድሏቸዋል:: ቅዱስ ፊላታዎስ ግን ላሙን አስገድሎ: ወላጆቹን ከሞት አስነስቶ ከአካባ

ቢው ሰው ጋር በስመ ሥላሴ አስጠምቁዋቸዋል::

+በድንግልና ኑሮም ዘመነ ሰማዕታት ሲጀምር በርጉም ዲዮቅልጥያኖስ እጅ ብዙ ተሰቃይቷል:: በጸሎቱም ጣዖታቱን (እነ አዽሎንን) ከነ አገልጋዮቻቸው ወደ ጥልቁ አስጥሟቸዋል:: እርሱም በዚህች ቀን በሰይፍ ተከልሎ ለክብር በቅቷል:: ለእኛ ለኃጥአን የሚሆን ቃል ኪዳንንም ከጌታው ተቀብሏል::

=>የቅዱሳን አባቶቻችን አማናዊት ርስት ድንግል ማርያም አትለየን::

=>ጥር 16 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ፊላታዎስ ሰማዕት
2.አባ ዸላድዮስ ገዳማዊ
3.ማር ዳንኤል ሶርያዊ
4.አባ ዮሐንስ መሐሪ (ሊቀ ዻዻሳት)
5.11,004 ሰማዕታት (የቅ/ቂርቆስ ማሕበር)
6.11,503 (የቅ/ፊላታዎስ ማሕበር)
7.አባ ጽሕማ (ከተስዓቱ ቅዱሳን አንዱ)

=>ወርሐዊ በዓላት
1.በዓለ ኪዳና ለድንግል
2.ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሥ
3.ቅዱስ ገብረ ማርያም (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
4.ቅድስት ኤልሳቤጥ
5.አባ ዳንኤል
6.አባ አቡናፍር ገዳማዊ
7.አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ

=>+"+ ጻድቅ እንደ ዘንባባ ያፈራል::
እንደ ሊባኖስ ዝግባም ያድጋል::
በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ ተተክለዋል::
በአምላካችንም አደባባይ ውስጥ ይበቅላሉ::
ያን ጊዜ በለመለመ ሽምግልና ያፈራሉ::
ደስተኞችም ሆነው ይኖራሉ:: +"+ (መዝ. 91:12)

   <<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
õ-3 ªó (u ØÈ- %- Ø 5
ASR by NLL APPS
ድርሳነ ኪዳነ ምህረት ዘወርሃ ጥር ዘሐሙስ
https://www.tg-me.com/SinkisarZekidusan2
Audio
ስንክሳር ዘወርሃ ጥር አሥራ ስድስት(፲፮)
https://www.tg-me.com/SinkisarZekidusan2
ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ):
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞

✞✞✞ ጥር 17 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ✞✞✞

" አበዊነ መክሲሞስ ወዱማቴዎስ "

=>እኒህ ቅዱሳን የሥጋ ወንድማማቾች ሲሆኑ በቤተ
ክርስቲያን ታሪክ እጅግ ተወዳጅ አባቶች ናቸው::
ስንጠራቸውም "አበዊነ
ቅዱሳን: ወክቡራን: ሮማውያን: መስተጋድላን:
ወከዋክብት ብሩሃን" ብለን ነው::

+ይኸውም "እንደ ንጋት ኮከብ የምታበሩ: ተጋዳይ:
ቅዱሳንና ክቡራን የሆናችሁ ሮማውያን አባቶቻችን" ማለት
ነው:: ሃገረ
ሙላዳቸው ሮም ሁና አባታቸው ንጉሥ ለውንድዮስ
ይባላል::

+ይህ ንጉሥ ሮምን በምታክል ታላቅ ሃገር በ4ኛው መቶ
ክ/ዘመን ነግሦ ሳለ መልካም ሰው ሆኖ ተገኝቷል::
ከመልካም ሚስቱ
(ንግሥቲቱ) ከወለዳቸው መካከልም 2ቱ ከዋክብት
ይጠቀሳሉ:: 2ቱ ቅዱሳን በአጭር የጊዜ ልዩነት የተወለዱ
በመሆናቸው
እንደ መንትያ ይቆጠራሉ::

+ንጉሡ ለውንድዮስም ከእግዚአብሔር ዘንድ ላገኛቸው
ልጆቹ ስም ሲያወጣ ታላቁን መክሲሞስ: ታናሹን ደግሞ
ዱማቴዎስ
ብሎታል:: ቅዱሳኑ በንጉሥ አባታቸው መልካም ፈቃድ
ክርስትናን ተምረዋል::

+ምንም እንኳ የንጉሥ ልጆች እና ልዑላን ቢሆኑም
ተቀማጥለው አላደጉም:: ምቾት ብዙዎችን አጥፍቷልና::
ይህንን የተረዳ
አባታቸው ሞገስን በፈጣሪያቸው ዘንድ እንዲያገኙ እንዲህ
በበጐ ጐዳና አሳደጋቸው::

+ቅዱሳን መክሲሞስና ዱማቴዎስ ካደጉና ለአካለ መጠን
ከደረሱ በኋላ ቅዱሳት መጻሕፍትን ለማንበብ ይተጉ ነበር::
በተለይ
ዜና ቅዱሳንን ከማንበብ አይጠግቡም ነበር::
እግዚአብሔርንም በፍቅር እያመለኩ በጾምና በጸሎት
ይገዙለት ነበር::

+ቅዱሳኑንም ለየት የሚያደርጋቸው አንዱ ይሔው ነው::
ወርቅና ብር በፊታቸው ፈሶ: በእግራቸው እየረገጡት:
አገሩና ምድሩ
እየሰገደላቸው: የላመ የጣመ ምግብ እየቀረበላቸው:
የሞቀ የደመቀ መኝታ እየተነጠፈላቸው . . . ሁሉንም ስለ
ፍቅረ
ክርስቶስ መናቃቸው ይደነቃል::

+እነርሱ በክርስቶስ ፍቅር ሆነው የዚህን ዓለም ጣዕም
ንቀዋልና የአባታቸውን ቤተ መንግስት ሊተዉ አሰቡ::
አሳባቸው
ደግሞ በመመካከር ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ መሪነት:
እንደ አንድ ልብ መካሪ: እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ እንዲሉ
አበው
በጌታ መሪነት ነው::

+ወደ በርሃ ሔደው ለፈጣሪ ለመገዛት ሲያስቡ መውጫ
መንገዳቸውን ይሹ ነበርና አንድ ጐዳና ተገለጠላቸው::
ከዚያም ለንጉሥ
አባታቸው ሔደው "አባ! እኛ ወደ ኒቅያ (ታናሽ እስያ)
ሔደን መባረክ እንፈልጋለን" ሲሉ ጠየቁት::

+ወቅቱ ቦታዋ ስለ 318ቱ ቅዱሳን ሊቃውንት ሞገስን
ያገኘችበት ጊዜ ነበር:: አባታቸውም መንፈሳዊ ሰው ነበርና
ደስ
እያለው ፈቀደላቸው:: ብዙ ወርቅን ሰጥቶ: ሸልሞ ከብዙ
ሠራዊት ጋር ሸኛቸው::

+ቅዱሳኑ መክሲሞስና ዱማቴዎስም ለጥቂት ጊዜ
በኒቅያ ሲጸልዩና ሲባረኩ ሰነበቱ:: ቀጥለውም
የአባታቸውን ሰራዊት ሰብስበው
"እኛ ሱባኤ ልንይዝ ስለ ሆነ እንመጣለን" የሚል
ደብዳቤን ሰጥተው ወደ ሮም ሸኟቸው::

+ወታደሮችን ከሸኙ በኋላ ቅዱሳኑ በአካባቢው ወደ ሚገኝ
አንድ ገዳም ሒደው ለአንድ ደግ መናኝ ምሥጢራቸውን
ገለጹለት::
ልክ የንጉሡ ለውንድዮስ ልጆች መሆናቸውን ሲያውቅ
'አመንኩሰን' ያሉትን እንቢ አላቸው::

+"ለምን?" ሲሉት "ደጉን አባታችሁን ማሳዘን
አልፈልግም:: ግን ፈቃዳችሁ እንዲፈጸምላችሁ ወደ ሶርያ
ዝለቁ:: በዚያ
አባ አጋብዮስ የሚባል ጻድቅ ገዳማዊ ሰው ታገኛላችሁ"
ብሎ ወደ ሶርያ አሰናበታቸው::

+በምድረ ሮም: በተለይም በቤተ መንግስቱ አካባቢ የ2ቱ
ልዑላን መጥፋት (መሰወር) ሲሰማ ታላቅ ሐዘንና ለቅሶ
ተደረገ::
ንጉሡ አባታቸው በወታደሮቹ ዓለምን ቢያካልልም
ሊያገኛቸው አልቻለም:: እርሱ ፈጽሞ ሲያዝን እናታቸው
ፈጽማ መጽናናትን
እንቢ አለች::

+መክሲሞስና ዱማቴዎስ ግን ምድረ ሶርያ ገብትው
የጻድቁ አባ አጋብዮስ ደቀ መዛሙርት ሆኑ:: በእርሱም
ዘንድ ለምናኔ
የሚያስፈልጉ በጐ ምግባራትንና ትሩፋትን ከተማሩ በኋላ
2ቱንም አመነኮሳቸው:: በዚያ ቦታም እየታዘዙ: ፈጣሪን
እያመለኩ:
በጾም: በጸሎትና በትህትና ኖሩ::

+አንድ ቀን ግን አባ አጋብዮስ ጠርቶ "ልጆቼ! ተባረኩ!
በእናንተ ምክንያት ደስ ብሎኛልና:: በዚህች ሌሊት
የመነኮሳት
ሁሉ አለቃ ታላቁ ቅዱስ መቃርዮስ በራዕ ተገልጦ: ልጆች
እንዲሆኑኝ ስጠኝ ብሎኛልና እኔ ሳርፍ ወደ ግብጽ ገዳመ
አስቄጥስ
እንድትሔዱ" አላቸው::

+አባ አጋብዮስ ካረፈ በኋላ ግን እንደ ትዕዛዙ
አልሔዱም:: ውዳሴ ከንቱን ይፈሩ ነበርና:: በዚያው
በምድረ ሶርያ ግን
በጥቂት ጊዜ: ገና በወጣትነት ከብቃት መዓርግ ስለ ደረሱ
በርካታ ተአምራትን ሠሩ:: በሰው ዘንድም ፍጹም ተወዳጅ
ሆኑ::

+ስም አጠራራቸውም ሶርያን መላት:: በዘመኑ
በአካባቢው አንድ ግዙፍ ዘንዶ ተነስቶ ሰውንም
እንስሶችንም ፈጃቸው::
ሕዝቡም ሒደው በቅዱሳኑ ፊት አለቀሱ:: ያን ጊዜ ቅዱስ
መክሲሞስ (ትልቁ) ክርታስ አውጥቶ "አንተ ዘንዶ ይህ
ክርታስ
ወደ አንተ ሲደርስ ከማደሪያህ ውጣ: ሙት: ወፎችም
ይብሉህ" ሲል ጻፈበት::

+"ሒዳችሁ በበሩ ጣሉት" አላቸው:: አንድ ደፋር ሰው
ተነስቶ ሰዎች ሁሉ እያዩት ወስዶ በዘንዶው መውጫ ላይ
ጣለው::
በቅጽበትም ዘንዶው ወጥቶ ሞተ:: አሞሮችም ተሰብስበው
በሉት:: ከዚህ ድንቅ ተአምር የተነሳ ሕዝቡ የቅዱሳኑን
አምላክ አከበረ::

+ከዚህ በተረፈም በቅዱሳኑ ስም ታላላቅ ተአምራት
ተደረጉ:: ርኩሳት መናፍስት ሁሉ ስማቸውን እየሰሙ
ይሸሹ ነበርና::
ድውያን እነሱ በሌሉበት ስማቸው ሲጠራላቸው ይፈወሱ
ነበር:: የአካባቢው ሰው ስማቸውን እየጠራ: በእነርሱም
እየተማጸነ
ከመከራው ሁሉ ይድን ነበርና ለሕዝበ ክርስቲያኑ ሞገስ
ሆኑ::

+መርከበኞች ደግሞ ከማዕበል ለመዳን የቅዱሳኑን ስም
በጀልባዎቻቸው ላይ ይጽፉ ነበር:: አንድ ቀን ግን የንጉሡ
ለውንድዮስ ባለሟል ይህንን ጽሑፍ ተመልክቶ ስለ
ጠረጠረ መርከበኛውን በንጉሡ ፊት አቀረበው::

+ንጉሡም መርከበኛውን "የጻፍከው የማንን ስም ነው?"
ቢለው "በሶርያ የሚገኙ 2 ወንድማማች ቅዱሳን ስም
ነው" አለው::
ልጆቹ እንደ ሆኑ ገምቶ በመርከበኛው መሪነት
ንግሥቲቱንና ሴት ልጁን ላካቸው:: እነርሱ በሐዘን
ተሰብረው ነበርና::

+ወደ ሶርያ ወርደው ባገኟቸው ጊዜም ከናፍቆትና ደስታ
የተነሳ ታላቅ ጩኸትን እየጮሁ አለቀሱ:: "እንሒድ ወደ
ሮም"
ሲሏቸው ግን ቅዱሳኑ "የለም! እኛ የክርስቶስ ነን" ብለው
እንቢ ስላሏቸው እያዘኑ ተመለሱ:: ንጉሡ ግን ይህንን
ሲሰማ
ደስ አለው:: "እነርሱ የዚህን ዓለም ኃላፊነት ተረድተዋል"
ሲልም አወደሳቸው::

+በኋላ ግን "የሮሜ ሊቀ ዻዻሳት መሆን አለባችሁ"
የሚል ነገር ሲሰማ ቅዱሳን መክሲሞስና ዱማቴዎስ
ከሶርያ ወጥተው ወደ
ግብጽ ወረዱ:: የከታላቁ ቅዱስ መቃርስ ዘንድ ደርሰውም
ልጆቹ እንዲሆኑ ለመኑት::

+"ልጆቼ! በርሃ አይከብዳችሁም?" ቢላቸው "ግዴለም!"
አሉት:: በዚያም ከተራራው ሥር በዓት ሠርቶላቸው ለ3
ዓመታት
በአርምሞ ቆዩ:: አንድ ቀንም ቅዱሳኑ እየጸለዩ ከአፋቸው
የወጣ የብርሃን ምሰሶ ከመንበረ ጸባኦት ሲደርስ አይቶ
ታላቁ
መቃርስ አደነቀ::
+በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን መጀመሪያ አካባቢም ጥር 14
ቀን ታላቁ ቅዱስ መክሲሞስ ዐረፈ:: በዕለቱም የሰማይ
ቅዱሳን ሁሉ
ወርደው እየዘመሩ ወሰዱት:: ከ3 ቀን በኋላ ደግሞ ቅዱስ
ዱማቴዎስ ዐረፈ::+በተመሳሳይ ቅዱሳኑ ሲወስዱት 2ቱንም ቅዱሳን ታላቁ
መቃርስ በበዓታቸው ቀብሯቸዋል:: ቦታውም ደብረ
ብርስም (በርሞስ)
ተብሏል:: ትርጉሙም የሮማውያኑ ቅዱሳን ደብር እንደ
ማለት ነው::

✞አምላከ ቅዱሳን በእነርሱ ላይ የበዛች ፍቅሩን ለእኛም
ያድለን:: ፍሬ ትሩፋት: ፍሬ ክብር እንድናፈራም ይርዳን::
ክብራቸውንም አያጉድልብን::

✞ጥር 17 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱሳን እና ክቡራን የሚሆኑ አባቶቻችን "መክሲሞስ
እና ዱማቴዎስ"

በ 17 የሚከበሩ ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት (ቀዳሜ ሰማዕት)
2.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ ዘብዴዎስ)
3.ቅዱሳን አበው መክሲሞስና ዱማቴዎስ
4.አባ ገሪማ ዘመደራ
5.አባ ዸላሞን ፈላሢ
6.አባ ለትጹን የዋህ
7.ቅዱስ ኤዺፋንዮስ ሊቅ (ዘደሴተ ቆዽሮስ)

++"+ ፍቅር ያስታግሳል:: ፍቅር ያስተዛዝናል:: ፍቅር
አያቀናናም::ፍቅር አያስመካም:: ፍቅር አያስታብይም::
ብቻዬን
ይድላኝ አያሰኝም:: አያበሳጭም:: ክፉ ነገርን
አያሳስብም:: ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ ዓመፃ
ደስ
አይለውም:: ሁሉን ይታገሣል:: ሁሉን ያምናል:: ሁሉን
ተስፋ ያደርጋል:: በሁሉ ይጸናል:: +"+ (1ቆሮ. 13:4)

✞✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞✞
Audio
ስንክሳር ዘወርሃ ጥር አሥራ ሰባት(፲፯)
https://www.tg-me.com/SinkisarZekidusan2
ለዐፅምህ ሰላም እላለሁ
… በጌታው ፊት ለተወደደው

ሃይማኖቱን ሲመሰክር
… በአደባባይ ለነደደው

ዳቦ ርቦት ተቸግሮ
… ወዳባቱ ለሚሮጠው

የቱ ወላጅ ነው ጨክኖ
… ከእጁ ድንጋይ የሚሰጠው

ጊዮርጊስ ሆይ!

ያስለመድከውን በረከት
… ከልጅህ ሥር አትለውጠው! (አሜን)

ዲያቆን ዶር. ቴዎድሮስ በለጠ (መጋቤ ሐዲስ)
Forwarded from መዝሙር ዘዳዊት (አክሲማሮስ 21)
ጊዜው ገና ነው

አንድ ምንጩ የማይታወቅ አስተማሪ የሆነ አፈ ታሪክ አለ ።
በዚህም አፈ ታሪክ መሰረት ፤ ከእለታት በአንዱ ቀን አጋንንት ስብሰባ አደረጉ ይባላል ። ይህንን ስብሰባ የጠራው የአጋንቱ አለቃም " ዓለምን ሁሉ ከኔጋ ለማሰለፍ እፈልጋለሁ ።ምን ይደረግ ? ማንንስ ልላክ ? " ብሎ ጠየቀ ። ከሥሩ ያሉትም አንድ በአንድ እየተነሱ አሳቦችን ማቅረብ ጀመሩ 

አንዱ ተነሳና ፥ " እኔን ብትልከኝ ፥ ፈጣሪ የለም ብዬ ሰዎችን ማሳመን እችላለሁ !" ብሎ ተናገረ ። የአጋንቱ አለቃ ግን ፥ "እርሱ አይሠራም  ።  ብዙዎቹ  አያምኑህም ፈጣሪ እንዳለ ያውቃሉ " ብሎ መለሰለት ።

ሌላኛው ተነሳና ፥" እኔን ከላክኸኝ ፥ ገነትም ሆነ ሲኦል የሚባል ቦታ እንደሌለ አሳምናቸዋለሁ !"  አለ ። የአጋንንቱ አለቃ ግን ፥ " እርሱም አይሰራም ። ብዙዎቹ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለ  ያውቃሉ ።" ብሎ መለሰ ።

ሌላኛው ደግሞ ተነሳና ፥" እኔን ላኩኝ ። ፈጣሪም አለ ገነትም አለ ፥ ሲኦልም አለ ፤ ነገር ግን ስለዚህ ነገር  ሁሉ ለማሰብ ጊዜው አሁን አይደለም ብዬ አሳምናቸዋለሁ አለ "። የአጋንንቱም አለቃ ደስ እያለው " ይህ ጥሩ መንገድ ነው ! " በማለት ሀሳቡን ተቀበለና ላከው ይባላል ።

ሰይጣን ማዘግየት ጥሩ ስልት መሆኑን ስለሚያውቅ ፥ ለማዘግየት ይፋጠናል ። በሐዲስ ኪዳን ላይ ቅዱስ ጳውሎስ " ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበርና ፥ እኔ ጳውሎስም አንድና ሁለት ጊዜ ፥ ሰይጣን ግን አዘገየን ።" ( 1 ተሰ 2 ፣18 ) ሲል እናገኘዋለን ። ሰይጣን ላያስቀረን ይችላል ፥ ግን ቢያንስ ሊያዘገየን ብዙ ይሞክራል ።

እርሱ ዓለማዊ ጉዞቻችንን ለአፍታ ስንኳ አውርደን ከእግዚአብሔር ጋራ ስላለን ግንኙነት እንድናስብ አይፈልግም ። ስለ ጸሎት ብታስብ ፥" አሁን ደክሞሃል  ። ጊዜው አይደለም ሌላ ጊዜ ትጸልያለህ " ይልሃል ለመጾም ብትዘጋጅ " አሁን ጉልበት ስለሚያስፈልግህ ብላ ። የምትጾምበት ጊዜ አይደለም ሌላ ጊዜ ትጾማለህ ይልሃል ።" ለመስገድ ብትዘጋጅ " ኧረ ተረጋጋ ፥ ጊዜው አይደለም ፥ ጾም ሲገባ ትሰግዳለህ ይልሃል ። ንስሃ ልትገባ ብትዘጋጅ " ቆይ እንጂ ዘልለህ ጨርሰህ አንዴየ ብትታጠበው አይሻልህም ?"  ለማለት የሚቀድመው የለም  ። ቅዱስ ቁርባን ልቀበል ነው ካልክ " አንተኮ ገና ነህ ፥ ለወደፊት ጣጣህን ስትጨርስ ቀስ ብለህ አመቻችተህ ትቆርባለህ " ብሎ ያዘነጋሃል

በዚህ ሁሉ መዘግየት ውስጥ መልአከ ሞት መቼ እደሚመጣ ማን ያውቃል ? ለመንፈሳዊ ነገር ስንነሳ  ፥ ሰይጣን ጊዜውን ገና ነው ማለቱ አይቀርም ። እኛ  ደግሞላችሁ  የእግዚአብሔር ቃል የተወደደውን ስዓት አሁን ነው እነሆ የመዳን ቀን አሁን ነው  ( 2 ኛ ቆሮ  6 ፥ 2 ) እደሚል እናስታውስ ለመዳናችን ቀጠሮ እንስጥ ።
https://www.tg-me.com/mezmure_dawit150
#ማግባት_ለሚሹ
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር

ከምንም በፊት የጋብቻ ዓላማን ማወቅ አለባችሁ፡፡ በሕይወታችን ለምን ጋብቻ እንደሚያስፈልገን መረዳት አለባችሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገርን አትጠይቁ፡፡ እናስ የጋብቻ ዓላማው ምንድነው? ለምንድነው እግዚአብሔር ጋብቻን የሰጠን? ብጹዕ ጳውሎስን እናድምጠው፤ እንዲህ ያለውን፦ "ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑሮው፤ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት" (1ኛ ቆሮ.7፥2)። "ከድህነት ይወጣ (ትወጣ) ዘንድ" ነው የሚለውን? ወይስ "ሀብት ለማግኘት ሲባል" ነው የሚለውን? አይደለም፡፡ ታዲያ ምንድነው የሚለው? ከዝሙት እንጠበቅ ዘንድ፤ ራሳችንን መቆጣጠር እንችል ዘንድ፤ ንጽህናን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ፤ በትዳር አጋራችን ደስ ተሰኝተን እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ፡፡ አያችሁ ይኼ ነው የጋብቻ ስጦታው ይኼ ነው የጋብቻ ፍሬው፤ ይኼ ነው የጋብቻ ጥቅሙ፡፡

ስለዚህ #ልጆቼ! እማልዳችኋለሁ ትልቁን ጥቅም ዘንግታችሁት ዓይናችሁን በትንሹ ላይ አታሳርፉ፡፡ የትዳር አጋርን ስትመርጡ የሀብት ጉዳይ የእናንተ ትልቅ አጀንዳ ሊኾን አይገባም፡፡ ስለ ሀብት ብሎ የትዳር አጋርን መምረጥ ድንቁርና ነው፤ ሀብት ነገ ሊጠፋ ይችላልና፡፡ ስለዚህ ለትዳር የምትመርጡት ሰው ከምንም በላይ መንፈሳዊ ሀብቱን ተመልከቱ፡፡ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይበልጥ የሚጠቅማችሁ ይኼ ነውና፡፡

#አባቶች_ሆይ! አብርሃምን ምሰሉት፡፡ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስትን ሲፈልግለት፦ ሀብትን አላየም፤ የንጉሣውያን ቤተሰብን አልተመለከተም፤ አፍአዊ ውበትን መመዘኛ አላደረገም፤ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ መስፈርትን አልደረደረም፡፡ የነፍስ ንጽህናን እንጂ፡፡

#እናቶች_ሆይ! ሴት ልጆቻችሁን እንደ ርብቃ አሳድግዋቸው፡፡

እናንተ ማግባትን የምትሹ #ወጣቶች_ሆይ! ይስሐቅን ምሰሉት፦ ዘፈንን፣ ዳንኪራን፣ ሳቅና ስላቅን፣ የከበሮንና የዋሽንት ጫጫታን፣ ሌላውንም የዲያብሎስ ትርኢት በሰርጋችሁ ቀን አታስቡ፡፡ ከዚህ ይልቅ በምታደርጉት ኹሉም ላይ እግዚአብሔር እንዲቀድማችሁ ለምኑት፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ትዳራችሁ ፍቺ፣ ዝሙት፣ ቅናት፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ የሌለበት ኾኖ ይፀናላችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ፥ ሌላው በረከትም ተትረፍርፎ ይመጣላችኋል፡፡ የአውሎ ነፋስ ዓይነት በዙሪያችሁ ቢነፍስም፥ አትነዋወፁም፡፡

#እናንተ_ልጃገረዶች_ሆይ! ርብቃን ምሰሏት፡፡ የትዳር አጋራችሁን ፍጹም ለማፍቀር የተዘጋጃችሁ ኹኑ፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ቤታችሁ ፍጹም ሰላማዊ ባሎቻችሁ የምትልዋቸውን የሚያደርጉና በፍቅራችሁ የሚንበረከኩ ይኾናሉ፡፡ ትዳር እንዲህ ኾኖ ሲጀመር፥ እግዚአብሔርንና ወላጆቹን ደስ የሚያሰኝ ልጅ ይገኝበታል፡፡

የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ፥ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡

@yehiwot_meaz
@yehiwot_meaz
2024/09/29 22:22:58
Back to Top
HTML Embed Code: