Telegram Web Link
የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻና ግብረ ሰዶማዊነትን አስመልከቶ እየተደረጉ ያሉ ሁለገብ ተጽእኖዎችንና መመሪያ የማስለወጥ ማግባባቶችን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡
Forwarded from Bketa @¥
“ብዙ እናቶች ስቃይ ካለበት የወሊድ ሰዓት በኋላ ልጆቻቸውን ሌሎች እንዲመግቡላቸው ለእንግዶች ይሰጣሉ። ክርስቶስ ግን እኛ ልጆቹን በብዙ መከራ እና ስቃይ በመስቀል ላይ ከወለደን በኋላ ሌሎች እስኪመገቡን ድረስ አይተወንም። በገዛ ሥጋ እና ደሙ እየመገበ ራሱ ያሳድገናል። በዚህ ሁሉ መንገድም ከራሱ ጋር አንድ ያደርገናል።”

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን †

††† እንኩዋን ለአባታችን "አባ ብሶይ ዼጥሮስ" እና "ቅዱስ ዕብሎይ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †††

††† አክርጵዮስ †††

በዚች ቀን የእስክንድሪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት አክርጵዮስ አረፈ። እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አስረኛ ነው። ይህም አባት እግዚአብሄርን የሚፈራ ንፁህ ቅዱስ ነው ።

በእስክንድርያ አገርም ቄስ ሆኖ የሚያገለግል ነበር ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ከላድያኖስ በአረፈ ጊዜ የእስክንድር አገር ህዝብና ኤጲስቆጶሳቱ መረጡት በወንጌላዊው ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት።

ከዚህም በኃላ እንደ ሀዋሪያት መልካም ጉዞን ተጓዘ የእግዚአብሄርን ሀይማኖት ህይወት የሆነ ህጉንም እያስተማረ ቅዱሳት መፅህፍትንም እያነበበላቸውና እያስተማራቸው መንጋዎቹን ይጠብቃቸው ነበር ሁል ጊዜም ይመለከታቸዋል አንድ የብር አላድን ወይም አንድ የወርቅ ዲናርን ጥሪት አላኖረም ከእለት ምግቡ ከቁርና ከሀሩር ስጋውን ከሚሸፈንበት ልብስ በቀር ምንም አላከማቸም።

በዚህም ተጋድሎ አስራ ሁለት አመት ኑሮ ጌታችንንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።

+*" ቅዱስ ዕብሎይ "*+

=>አባ ዕብሎይ በቀደመ ሕይወቱ ለ40 ዓመታት በኀጢአት የኖረ: እግዚአብሔር ለንስሃ ሲጠራው "እሺ" ብሎ : ለ40 ዓመታት በንስሃ ሕይወት ተመላልሶ በበርሃ የተጋደለ: እንባው እንደጐርፍ ይፈስ የነበረ: አጋንንትንም ድል የነሳና ለፍሬ: ለትሩፋት የበቃ ቅዱስ አባት ነው:: እግዚአብሔርም ብዙ ቃል ኪዳን ገብቶለታል::

<< ባርያ ሆኖ ያለ ኀጢአት: ጌታ ሆኖ ያለ ምሕረት የለምና ይቅር በለን !! >> (የአባ ዕብሎይ የንስሃ ጸሎት)

+*" አባ ብሶይ (ዼጥሮስ) "*+

=>ብሶይ (ቢሾይ) በቤተ ክርስቲያን ታሪክ የተለመደ
የቅዱሳን ስም ነው:: በተለይ በምድረ ግብ በዚህ ስም
ሰማዕታትም : ጻድቃንም ተጠርተውበታል:: ከእነዚህ
ቅዱሳን (ከገዳማውያኑ) አንዱ የሆነው አባ ብሶይም
(አንዳንዴ አባ ዼጥሮስም ይባላል) የዘመነ ጻድቃን ፍሬ
ነው::

+ቤተ ክርስቲያን የቅዱሳን ቤት ናት:: ያ ማለት ራሳቸውን
ለክርስቶስ የለዩ ሰዎች ይኖሩባታል:: እነዚህ ሰዎች
ከተለያየ ጐዳና እና ማንነት ሊመጡ ይችላሉ:: ቢያንስ ግን
በንስሃ የታጠቡ መሆናቸው ወደ ተቀደሰው አንድነት
እንዲገቡ ትልቅ መሠረት ይሆናቸዋል::

+ቅዱሳንም አንዳንዶቹ ከእናታቸው ማኅጸን ሲመረጡ :
ሌሎቹ ደግሞ ከኃጢአት ሕይወት የተመለሱ ሆነው
ይታያሉ:: ደስ የሚለው ደግሞ በንስሃ ከታጠቡ በሁዋላ
በፍጹም ልባቸው በመጋደላቸው እነሆ በሰማያዊ አክሊል
ተከልለዋል::

+አባ ብሶይ ዼጥሮስም ከኃጢአት ተመልሰው ለቅድስና
ከበቁ ቀደምት አበው አንዱ ነው:: ቅዱሱ ተወልዶ
ባደገባት ምድረ ግብጽ የታወቀ ሽፍታ : ዝሙተኛና ክፋቱ
የተገለጠ ሰው ነበር:: ለብዙ ዘመናት በእንዲህ ካለ ግብሩ
መላቀቅ ባይችል እግዚአብሔር ጥሪውን ላከለት::

+የአምላካችን የጥሪ መንገዱ ብዙ ነውና ለእርሱ ደዌን
ላከለት:: መቼም ወደድንም ጠላንም በሽታ ወደ
እግዚአብሔር የሚያቀርብ ጥሩ ፈሊጥ (አጋጣሚ) ነው::
ዛሬም ቢሆን ዘለን : ዘለን ስንሰበርና የሐኪም መፍትሔ
ሲጠፋ የግዳችን ወደ እግዚአብሔር ቤት (ወደ ጸበሉ)
እንቀርባለንና:: አምላካችን ስለዚህ ጥበቡ ይክበር
ይመስገን::

+ቅዱስ አባት ብሶይም በሽፍትነትና በኃጢአት ኑሮ ሳለ
ለሞት የሚያበቃ ደዌ ደርሶበት የአልጋ ቁራኛ ሆነ::
ኃይሉም ደከመ:: በእንዲህ እያለም በራዕዩ ያየው ነገር
ፍጹም አስደነገጠው::

መላእክት ነፍሱን ወስደው መካነ ኩነኔን ካሳዩት በሁዋላ
አለቀሰ::

+ይልቁን ሌቦችና ዝሙተኞችን ከ4 ሲቆራርጣቸው ስላየ
ፈጽሞ አዘነ : ተጸጸተ:: ፈጣሪውንም ዕድሜ ለንስሃ
እንዲሰጠው ተማጸነ:: ጌታንም "አምላኬ ሆይ! ከበሽታየ
ብታድነኝ : ዳግመኛ አልበድልህም:: ዓለምን ሁሉም ንቄ
አገለግልሃለሁ" ሲል ተማጸነው::

+እግዚአብሔርም ሰምቶት ፈጥኖ ፈወሰው:: አባ ብሶይም
እንደ ቃሉ በፍጹም ልቡ ንስሃ ገብቶ መነነ:: በገዳመ
አስቄጥስ (ግብጽ) ለ38 ዓመታት ሲኖር የላመ የጣመ
በልቶ : ከሞቀ መኝታ ተኝቶ አያውቅም::

+ሰውነቱን ይቀጣት ዘንድም እስከ 30 ቀን ያለ እህል ውሃ
ይጾም ነበር:: በዘመኑ ሁሉም የሴት መልክን አላየም::
ንስሃን የሚወድ ጌታም ጸጋውን አብዝቶለት ብዙ ድርሳናትን
ጽፏል:: የሚገርመው ደግሞ ከትህትናውና ቅድስናው
የተነሳ የእያንዳንዱ ሰው ኃጢአት ተገልጦ ይታየው ነበር::

+ቅዱሱ አባታችን ብሶይ ዼጥሮስ በንስሃና በቅድስና
ሕይወት እንዲህ ተመላልሶ በዚህች ቀን ዐርፎ በገዳሙ
ተቀብሯል:: የድካሙን ዋጋም አድልዎ ከሌለበት :
ከእውነተኛው ፈራጅ ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ተቀብሏል::

=>አምላከ ቅዱሳን ዕድሜ ለንስሃ : ዘመን ለፍስሐ
አይንሳን:: ከክብረ ቅዱሳንም ያካፍለን . . . አሜን !!

=>የካቲት 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ አባ ዕብሎይ ገዳማዊ
2.ቅዱስ አባ ብሶይ ጻድቅ
3.አባ አክርዽዮስ
4."49" አረጋውያን ሰማዕታት (ፍልሠታቸው)
5.ቅዱስ አሞኒና ሚስቱ ቅድስት ሙስያ (የታላቁ ዕብሎይ ወላጆች)
6.አባ ኖብ ጻድቅ : መነሳንሱ ዘወርቅ

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
2.ቅዱስ ዻውሎስ ሐዋርያ
3.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
4.ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
5.ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ

=>አምላክ በበረከታቸው ይባርከን::

=>+"+ መቶ በግ ያለው : ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋ ዘጠና ዘጠኙን በበርሃ ትቶ የጠፋውን እስኪያገኘው ድረስ ሊፈልገው የማይሔድ ከእናንተ ማን ነው? ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በጫንቃው ይሸከመዋል:: ወደ ቤትም በመጣ ጊዜ ወዳጆቹንና ጐረቤቶቹን በአንድነት ጠርቶ 'የጠፋውን በጌን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ' ይላቸዋል:: እላችሁአለሁ: እንዲሁ ንስሃ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሃ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል:: +"+ (ሉቃ. 15:3-7)

†ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
†ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር አሜን †
Audio
ስንክሳር ዘወርሃ የካቲት አምስት(፭)
@SinkisarZekidusan2
"ላለማመን እንጂ ለማመን በዙሪያችን ብዙ ምስክሮች አሉልን"

ዓይነ ሥውሩ ቅዱስ ዲዲሞስ በአንድ ወቅት የእግዚአብሔርን መኖር የሚክዱ ተመራማሪዎች የራሳቸውን እውቀት መነሻ በማድረግ የእግዚአብሔርን አለመኖር ከነገሩት በኋላ "እስኪ አንተ እግዚአብሔር መኖሩን በተጨባጭ አስረዳን?" ሲሉ ጠየቁት። ቅዱስ ዲዲሞስ ተመራማሪዎቹ ጭልጥ ብለው መሳሳታቸውን ቢያውቅም በጥሞና ያዳምጣቸው ነበር እንጂ አልተበሳጨም። ለጠየቁት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት "ምሽት ተመልሳችሁ ኑ" አላቸው።

እነርሱም የቀጠሮአቸውን ሰዓት አክብረው ምሽት ተመልሰው መጡ። ቅዱስ ዲዲሞስም "እስኪ ወደላይ አንጋጣችሁ የሰማዩን ገጽታ ተመልከቱ" አላቸው። እነርሱም እንዳላቸው ሰማዩን ተመለከቱ። እርሱም "በሰማይ ላይ ምን ምን ይታያችኋል?" አለ። እነርሱም "ከዋክብት" ብለው መለሱለት። እርሱም "በስጋዊ አይናችሁ የማየት ችሎታ እነዚህን ክዋክብት በቀን ማየት ትችላላችሁን?" አላቸው። እነርሱም "አንችልም" አሉት። እርሱም "ለምን ማየት ያቅታችኋል?" ሲል ጥያቄውን በጥያቄ ደገመላቸው። እነርሱም "ምክንያቱም ከዋክብትን ለማየት የግድ መምሸት አለበት" አሉት። እርሱም "በእርግጥ ትክክል ናችሁ የመለሳችሁት ምላሽ ትክክል ነው። ይሁን እንጂ በተፈጥሮ እንደምናውቀው የተሰወረውን ነገር ለማግኘት ብርሃን ያስፈልጋል እነዚህን የምታዩአቸው ከዋክብት ለማየት ግን ብርሃን ሳይሆን ጨለማ ሊኖር የግድ ነው። እንደዚሁ ሁሉ እግዚአብሔርንም ለማየት ቁሳዊ ነገርን ማየት በሚቻልበት በሳይንስ መሳሪያና ፍልስፍና ሳይሆን በእምነት ብቻ ማረጋገጥ እንደሚቻል ልነግራችሁ እወዳለሁ።" በማለት አስረዳቸው።

 በድጋሚ "በሰማያት ገጽታ ላይ ከዋክብት እንደሚታዩ ነግራችሁኛል። ይሁን እንጂ እኔ ዓይነ ሥውር ስለሆንኩ በምን ታረጋግጥሉኛላችሁ?" ሲል አዲስ የጥያቄ ርዕስ ከፈተላቸዉ። እነርሱም ግራ ተጋብተው ምላሽ አጡ፤ እናም ከመናገር ይልቅ ዝምታን መረጡ። እርሱ ግን የእኔ ዓይነ ስውርነት የከዋክብቱን አለመኖር አያረጋግጥም፤ እኔ አየሁም አላየሁም ከዋክብቱ ዘወትር አሉ። እኔም ምንም ዐይነ ሥውር ብሆንም እንኳን ከዋክብቱን ሳልመለከት እናንተ አይታችሁ በነገራችሁኝ ምስክርነት ብቻ የከዋክብቱን መኖር አምኜ ተቀብየዋለሁ አላቸው። እኔ አንዳች ከዋክብት ሳልመለከት የከዋክብቱን መኖር እንዳመንኩ እናንተም በሥጋዊ አይናችሁ ባትመለከቱም እንኳን በእምነት እግዚአብሔር መኖሩን አታምኑምን? ብታምኑ መልካም ነው።" ሲል በትሕትና ጠየቃቸው። እነርሱም በጥያቄ መልክ ያቀረበላቸውን አስተሳሰቡን እና ምስክርነቱንም ተቀብለው የእግዚአብሔርን መኖር በእምነት አረጋገጥን አሉት። በዚህ የክርክርና የውይይት ሁኔታ ዓይነ ሥውሩ ቅዱስ ዲዲሞስ (በትሕትናውና በድክመቱ) የተናገሩትን አድምጦ የእነርሱን ዕውቀታቸውንና አስተሳሰባቸውን ተጠቅሞ ክብራቸውን ሳይጋፋ የእግዚአብሔርን መኖር በማሳመን ረታቸው። ክርክራቸውም በዚህ ተደመደመ።

(#ብፁዕ_ወቅዱስ_አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ "የሕይወት መንገድ" በመምሕር ሰለሞን በቀለ ከተተረጎመ መጽሐፍ የተወሰደ)
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ

አሜን

✍️"ችግር ለራሳችን እንድንጸልይ ያነቃቃናል፤ ፍቅር ደግሞ ለሌሎች ሰዎች እንድንጸልይ ያስገድደናል"
📚ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ቀናችንን በጸሎት እንጀምር


🔔 ስንክሳር ዘወርኀ የካቲት ፯


አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የካቲት ሰባት በዚች ቀን የእስክንድርያ ሀገር ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት እለእስክንድሮስ አረፈ እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ ሦስተኛ ነው።

❖ ይህም አባት ታሮን በሚባል ገዳም መነኰሰ ትርጓሜውም የአባቶች ገዳም ማለት ነው በጌታችንም ፈቃድ በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ተሾመ እርሱ የተማረ አዋቂ ጻድቅ ሰው ነበረና።

❖ በሹመቱ ወራትም ብዙ መከራ ደረሰበት የግብጽ ንጉሥ ልጁን ሹሞ በመንግሥቱ ላይ አሠለጠነው እርሱም በአስቄጥስ በረሀ ያለውን የመነኰሳቱን ገዳማት አፈረሳቸው።

❖ ከክፋቱና ከክህደቱ ብዛት የተነሣ ከምስር በስተሰሜን ወዳለች ገዳም ገብቶ በዚያ አምላክን የወለደች የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ሥዕሏን አየና ይች ምንድን ናት አለ እርሷም በሽልማት ሁሉ የተሸለመችና ያጌጠች ናት በልብሶቿም ላይ ያማረ የሐር ልብስ ነበረ ስዎችም የክርስቶስ እናት የሆነች የእመቤታችን የድንግል ማርያም ሥዕል ናት አሉት እርሱም ተሳድቦ የረከሰ ምራቁን በፊቷ ላይ ተፍቶ ደኅና ከሆንኩ ክርስቲያኖችን ፈጽሜ አጠፋቸዋለሁ አለ ዳግመኛም በክብር ባለቤት በጌታችን ክርስቶስ ላይ የስድብ ቃልን ተናገረ።

❖ ሌሊትም በሆነ ጊዜ የሚያስፈራና የሚያስደነግጥ ታላቅ ራእይን አየ በነጋም ጊዜ ለአባቱ እንዲህ ብሎ ነገረው ዛሬ በዚች ሌሊት ታላቅ መከራና ብዙ ቅጣት ደረሰብኝ ታላቅ ዙፋንንም አየሁ በላዩ የተቀመጠበት ሰው እጅግ የሚያስፈራ የሚያስደነግጥ ነው ፊቱም ከፀሐይ ይበራል የብዙ ብዙ የሆኑ ሠራዊት የጦር መሣሪያ ይዘው በዙሪያው ቁመው ነበር እኔና አንተም እሥረኞች ሁነን በኋላው ቁመን ነበር እኔም በዙፋን ላይ የተቀመጠው ማነው ብዬ ጠየቅሁ ትላንት አንተ የዘበትክበት የክርስቲያን ንጉሥ ክርስቶስ ይህ ነው አሉኝ ከዚህም በኋላ የጦር መሣሪያ ከተሸከሙት አንዱ ወደ እኔ መጥቶ ጐኔን በጦር ወጋኝ ጦሩንም ከጐኔ ውስጥ አላወጣውም፤ አባቱም ሰምቶ ደነገጠ እጅግም አዘነ ያ ልጁም ወዲያውኑ ታመመ አንደበቱም ተዘግቶ በክፉ አሟሟት ሞተ።

❖ ዳግመኛም ከአርባ ቀን በኋላ አባቱ ሞተ፤ በርሱም ፈንታ ሌላ ንጉሥ ተሾመ እርሱም ክርስቲያኖችን እጅግ አሠቃያቸው ይህንንም አባት ሊቀ ጳጳሳት እለእስክንድሮስን አብዝቶ አሠቃየው ከሕዝቡ ሦስት ሺህ የወርቅ ዲናር ለምኖ እስከ ሰጠው ድረስ ጌታችንም ይህን ንጉሥ ፈጥኖ አጠፋው።

❖ ከዚህም በኋላ አሁንም ሌላ ንጉሥ ተሾመ እርሱም ሊቀ ጳጳሳቱን ይዞ እንደ ቀድሞው ሦስት ሺህ የወርቅ ዲናር እንዲሰጠው ፈለገ እርሱም ከወገኖቼ እስከምለምን ታገሠኝ ብሎ ማለደው ንጉሡም ቀጠሮ ሰጠውና ይለምን ዘንድ ወደ ላይኛው ግብጽ ወጣ።

❖ በተራራ ላይ አንድ ገዳማዊ ሰው ነበር ከእርሱም ጋር ሁለት ደቀ መዛሙርት አሉ በተራራውም በአንድ ቦታ እንዲቆፍሩና እንዲጠርጉ አዘዛቸው ወርቅን የተመላ አምስት ማሰሮ አገኙ አንዱን ሸሽገው አራቱን ወደ ገዳማዊ መምህራቸው አመጡ እርሱም ይረዳበት ዘንድ እንዲስጡት ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ ላካቸው፤ እነርሱ ግን እነዚያን የወርቅ ማሰሮዎች ይዘው ተመልሰው ወደ ዓለም ገቡ የምንኵስና ልብሳቸውንም ጥለው ሚስት አገቡ በዚያም ወርቅ ወንዶችና ሴቶች ባሮችን እንስሳትንም ገዙ።

❖ የዚያችም አገር አስተዳዳሪ ያዛቸው ገንዘብንም ከወዴት እንዳገኙ በመግረፍ መረመራቸው እነርሱም አምስት የወርቅ ማሰሮዎችን እንዳገኙ አመኑ መኰንኑም ለንጉሥ የጭፍራ አለቃ አሳልፎ ሰጣቸው እርሱም ወደ ንጉሥ አቀረባቸውና አምስት የወርቅ ማሰሮ እንዳገኙ አስረዳው ንጉሡም ጭፍሮቹን ልኮ የሊቀ ጳጳሳቱን ቤት በረበረ የአብያተ ክርስቲያናት ከሆነ ከንዋየ ቅድሳት ያገኘውን ሁሉ ወሰደ ሊቀ ጳጳሳቱንም አሠረውና ወርቅን የተመሉ አራቱን ማሰሮዎች ደግሞም ሦስቱን ሽህ የወርቅ ዲናር አምጣልኝ አለው እርሱም ከዚህ ከኃላፊው ዓለም ገንዘብ ምንም ምን የለኝም አለው ወደ ሕዝቡ ልኮ ሦስቱን ሽህ የወርቅ ዲናር አምጥተውለት እስከ ሰጠው ድረስ አልተወውም ይህንንም ክፉ ንጉሥ ጌታችን አጠፉው።

❖ ከዚህም በኋላ ከእርሱ የከፋ ሌላ ንጉሥ ተሾመ እርሱም የሐሰተኛውንና የርኵሱን ነቢይ ስም በከበረ መስቀል ፈንታ በእጆቻቸው ውስጥ እንዲአትሙ የክርስቲያንን ወገኖች አስገደዳቸው፤ ይችም ምልክት የመለኮትን ነገር የሚናገር ወንጌላዊ ዮሐንስ የተናገራት ትንቢት ናት ይህም ክፋ ንጉሥ ወደ ሀገሮች ሁሉ ይህን እንዲአደርጉ አዘዛቸው ሊቀ ጳጳሳቱንም እንዲሁ ያደርግ ዘንድ አዘዘው።

❖ ሊቀ ጳጳሳትም ይተወው ዘንድ ብዙ ለመነው አልተቀበለውም ዳግመኛም እስከ ሦስት ቀን ይታገሠው ዘንድ ለመነው ከዚህም በኋላ ደግሞ እንዳይጥለውና ወደዚህ ወደረከሰ ሥራ እንዳያስገባው ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ማለደ ጌታችንም ልመናውን ተቀብሎ በጥቂት ደዌ ጐበኘው ወደ ቤቱ እስክንድርያ ይሔድ ዘንድ እንዲአዝዝለት

❖ ጉሡም ከለከለው ሰለ እጅ ኀትመት ምክንያት ለመፍጠር ሰለ መሰለው የእግዚአብሔርም መልአክ ተገለጠለትና ነገ ታርፋለህ አለው እርሱም አርድእቱን እግዚአብሔር ነገ ስለሚጐበኘኝ አርፋለሁና መርከብን አዘጋጁ አላቸው፤ አንዳለውም በማግሥቱ አረፈ ሥጋውንም በመርከብ ተሸክመው ወስደው ከአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሥጋ ጋር ቀበሩት።

❖ በዚህም አባት አለእስክንድሮስ ዘመን በግብጽ አገር ለሚኖሩ መለካውያን ስሙ አንስጣስዮስ የሚባል ሊቀ ጳጳሳት ነበራቸው ያዕቆባውያን ምእመናንን ይወዳቸዋል ስለዚህም ወገኖቹ መለካውያን ተጣሉት፤ እርሱም ነፍሱን ያድን ዘንድ አስቦ ወደዚህ አባት አለእስክንድሮስ መጥቶ ከሥልጣኑ በታች በመሆን የሚታዘዝ ሆነ እለእስክንድሮስም አንስጣስዮስን በእርሱ ፈንታ የሊቀ ጵጵስናውን ሥልጣን ይዞ መንጋውን ይመራ ዘንድ እርሱ ግን ከመነኰሳት እንዳንዱ ሁኖ በገዳም ይኖር ዘንድ እንዲተወው ለመነው።

❖ አባ አንስጣስዮስም አልወደደም እንዲህም አለ ይህን የምሻ ከሆነ አኔ እስከ ዛሬ ሊቀ ጳጳሳት አልነበርኩምን ላንተ ደቀ መዝሙርህ ሁኜ ላገለግልህ ወደድኩ እንጂ አለ፤ በመካከላቸው ከተደረገው ከብዙ ልመና ከብዙ ምልልስም በኋላ ኤጲስቆጶስ ይሆን ዘንድ አንስጣስዮስ ፈቀደ በአንዲትም ሀገር ላይ ኤጲስቆጶስነትን ሾመው፤ መንጋውንም እንደሚገባ በጎ አጠባበቅን ጠበቀ፤ አባት እለእስክንድሮስም በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር የኖረው ሃያ አራት ዓመት ከስድስት ወር ነው እግዚአብሔርንም አገለገለው።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑን ለዘላለሙ አሜን።
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞

❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖

❖ የካቲት 8 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

+" በዓለ ስምዖን "+

=>ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን ጌታ በተወለደ በ40 ቀኑ ራሱ የሠራውን ሕግ ይፈፅም ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቷል::
እንደ ሥርዓቱም እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምና
አገልጋዩዋ ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ የርግብ ግልገሎችና
ዋኖስ አቅርበዋል::

+ለ284 ዓመታት የአዳኙን (የመሢሁን) መምጣት
ይጠብቅ የነበረው አረጋዊው ስምዖን በዚህች ዕለት
ስላየውና ስለታቀፈው
ዕለቱ በዓለ ስምዖን ይባላል:: (ሉቃ. 2:22) ከዘጠኙ
የጌታ ንዑሳን በዓላት አንዱ ነው::

+ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

+ከዓለም ፍጥረት በ5,200 ዓመታት (ማለትም
ከክርስቶስ ልደት 300 ዓመታት በፊት) በጥሊሞስ
የሚሉት ንጉሥ በግሪክ
ነገሠ::

+በጊዜውም በኃይለኝነቱ ሁሉን አስገብሮት ነበርና
"ዓለሙን እንደ ሰም አቅልጬ: እንደ ገል ቀጥቅጬ
ገዛሁት:: ምን
የቀረኝ ነገር አለ?" ሲል ተናገረ:: ባሮቹም "አንድ ነገር
ቀርቶሃል:: በምድረ እሥራኤል ጥበብን የተሞሉ 46
መጻሕፍት
አሉ:: እነርሱን አስተርጉም" አሉት::

+ያን ጊዜ እሥራኤላውያንን አስገብሯቸው ነበርና 46ቱን
የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከ72 ምሑራን (ተርጉዋሚዎች)
ጋር
እንዲያመጡለት አዛዦቹን ላከ:: እነርሱም 46ቱን
መጻሕፍተ ብሉይ ኪዳን ከ72 ምሑራን ጋር አመጡለት::

+አይሁድ ክፋተኞች መሆናቸውን ሰምቷልና 36 ድንኩዋን
አዘጋጅቶ: ጥንድ ጥንድ ሆነው እንዲሠሩ: ሲተረጉሙ
እንዳይመካከሩ
36 ጠባቂዎችን ሾመባቸው:: ይህ ነገር ለጊዜው ከንጉሡ
ቢመስልም ጥበቡ ግን ከእግዚአብሔር ነው::

+ምንያቱም በጊዜ ሒደት መጻሕፍተ ብሉያት በአደጋ
እንደሚጠፉ ያውቃልና ሳይበረዙ ለሐዲስ ኪዳን
ክርስቲያኖች ለእኛ
እንዲደርሱ ነው:: ስለዚህም ከክርስቶስ ልደት 284 ዓመት
በፊት 46ቱም ሁሉም መጻሕፍት (ብሉያት) ከእብራይስጥ
ወደ
ጽርዕ ልሳን በ70ው ሊቃናት አማካኝነት ተተረጐሙ::
(በእርግጥ ከዚያ አስቀድሞ መጻሕፍት (ብሉያት) ወደ
ሃገራችን መምጣቸውና ወደ ግዕዝ ልሳን መተርጐማቸውን
ሳንዘነጋ ማለት ነው)

+ወደ ዋናው ጉዳያችን ስንመለስ ከ70ው ሊቃናት
መካከል በእድሜው አረጋዊ የሆነ (እንደ ትውፊቱ ከሆነ
216 ዓመት
የሆነው) ስምዖን የሚሉት ምሑረ ኦሪት ነበር:: በፈቃደ
እግዚአብሔር ለእርሱ መጽሐፈ ትንቢተ ኢሳይያስ ደርሶት
እየተረጐመ
ምዕራፍ 7 ላይ ደረሰ::

+ቁጥር 7 ላይ ሲደርስ ግን "ናሁ ድንግል ትጸንስ:
ወትወልድ ወልደ" የሚል አይቶ "አሁን እንኳን የአሕዛብ
ንጉሥ
የእሥራኤልስ ቢሆን ድንግል በድንግልና ጸንሳ ትወልዳለች
ብለው እንዴት ያምነኛል!" ሲል አሰበ:: "በዚያውስ ላይ
ኢሳይያስ በምናሴ የተገደለው ስለዚህ አይደል!" ብሎ
ቃሉን ሊለውጠው ወሰነ::

+አመሻሽ ላይም 'ድንግል' የሚለውን 'ወለት-ሴት ልጅ'
ብሎ ቀየረው:: እርሱ ሲያንቀላፋ ቅዱስ መልአክ ወርዶ
'ድንግል'
ብሎ አስተካከለው:: ከእንቅልፉ ሲነቃ ግራ ተጋብቶ እንደ
ገና ፍቆ ቀየረው::

+አሁንም መልአኩ 'ድንግል' ሲል ቀየረበት:: 3 ጊዜ
እንዲህ ከሆነ በኋላ ግን መልአኩ ተገልጦ ገሰጸው::
በዚያውም ላይ
"ይህችን ድንግልና መሲሑን ልጇን ሳታየውና ሳትታቀፈው
ሞትን አታይም" ብሎት ተሰወረው:: አረጋዊ ስምዖን
ከዚያች ዕለት
በኋላ የመድኅን ክርስቶስን መምጣት ሲጠብቅ ለ284
ዓመታት የአልጋ ቁራኛ ሁኖ ኖረ:: አካሉም አለቀ::

+ለስም አጠራሩ ስግደት የሚገባው አምላካችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ሰው በሆነበት በዚያ ሰሞን እመቤታችን ቅድስት
ድንግል
ማርያምና ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ ወደ ቤተ መቅደስ ወጡ::

+ሕግን የሠራ ጌታ እርሱ 'ፈጻሜ ሕግ' ይባል ዘንድ
የርግብ ግልገሎችን (ዋኖሶችን) ይዘው በተወለደ በ40
ቀኑ ወደ ቤተ
መቅደስ አስገቡት:: በዚህች ቀንም ቅዱስ መልአክ
መጥቶ ቅዱስ ስምዖንን ከአልጋው ቀሰቀሰው:: ተስፋ
የሚያደርገው አዳኙ
(መሲሑ) እንደ መጣም ነገረው::

+ይህን ጊዜ አረጋዊው አካሉ ታድሶ እንደ 30 ዓመት
ወጣት እመር ብሎ ከአልጋው ተነሳ:: እንደ በቅሎ
እየሠገረም ወደ
መቅደስ ወጣ:: በዚያ መሲሑን (ፈጣሪውን) ሲመለከት
እንደ እንቦሳ ዘለለ:: ቀረብ ብሎም ሕጻን ጌታን ከድንግል
እናቱ እጅ ተቀበለው::

+ከደስታው ብዛት የተነሳም "ይእዜ ትስዕሮ ለገብርከ:
በሰላም እግዚኦ በከመ አዘዝከ-አቤቱ ባሪያህን እንደ
ቃልህ በሰላም
አሰናብተው" ሲል ጸለየ:: ትንቢትንም ተናገረ:: በዚያችው
ዕለትም ዐርፎ ተቀበረ::

+"+ ሐና ነቢይት +"+

+ዳግመኛ በዚህች ቀን አረጋዊቷን ነቢይት ቅድስት ሐናን
እናስባለን:: ይህች ቅድስት ትውልዷ ከነገደ አሴር ሲሆን
አባቷ
ፋኑኤል ይባላል:: በትውፊት ትምሕርት ሐና የተዳረችው
በልጅነቷ (በ12 /15/ ዓመቷ) ነው:: ለ7 ዓመታት ከልጅነት ባሏ
ጋር
ኖራ ዕድሜዋ 19 (22) ሲደርስ ሞተባት::

+እንደ እሥራኤል ልማድ ሌላ እንድታገባ ብትጠየቅም
'እንቢ' ብላ መበለት ሆነች:: ራሷንም ለእግዚአብሔር
አሳልፋ
ሰጠች:: በቤተ መቅደስም ለ84 ዓመታት ለፈጣሪዋ
ተገዛች:: ፈጽማ ትጸልይና ትጾም ነበርና በእነዚህ ሁሉ
ዓመታት ውጪውን
አልተመለከተችም::

+ለእርሷ 103 (106) ዓመት ሲሆን መድኃኒታችን ተወለደ::
በዚህች ቀን ወደ ቤተ መቅደስ ሲገባ ተመልክታም ጌታን
ባረከች::
ደስ እያላትም ትንቢትን ተናገረች:: ወደ ቤቷ ገብታም
ነፍሷን ሰጠች:: (ሉቃ. 2:36-38)

❖ቸሩ መድኃኒታችን ተርፎ ከሚቀረው ዘመን ዕድሜ
ለንስሃ: ዘመን ለፍሥሐ አይንሳን:: ከቅዱሳኑ በረከትም
አይለየን::

✞የካቲት 8 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ስምዖን አረጋዊ
2.ቅድስት ሐና ነቢይት (የፋኑኤል ልጅ)
3.ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ እግዝእት
4.አባ ኤልያስ ገዳማዊ (በትህትና ያጌጠ ቅዱስ ሰው)

ወርሐዊ በዓላት

1.ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት
2.ኪሩቤል (አርባዕቱ እንስሳ)
3.አባ ብሶይ (ቢሾይ)
4.አቡነ ኪሮስ
5.አባ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን
6.ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ (ከ12ቱ ሐዋርያት)


❖አረጋዊ ስምዖንን ከድካም አልጋ ያነሳ አምላከ ቅዱሳን
እኛንም ድካመ ነፍስን ከሚያመጣ የበደል ምኝታ በቸርነቱ
ያንሳን::

++"+ እንደ ሕጉ ልማድ ያደርጉለት ዘንድ ሕጻኑን ጌታ
ኢየሱስን በአስገቡት ጊዜ እርሱ ደግሞ ተቀብሎ
አቀፈው::
እግዚአብሔርንም እየባረከ እንዲህ አለ:-
'ጌታ ሆይ! አሁን እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም
ታሰናብተዋለህ:: ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን
ማዳንህን
አይተዋልና:: ይህም ለአሕዛብ ሁሉን የሚገልጥ ብርሃን:
ለሕዝብሕም ለእስራኤል ክብር ነው::'
ዮሴፍና እናቱም ስለ እርሱ በተባለው ነገር ይደነቁ ነበር::
+"+ (ሉቃ. 2:27)

✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞
5•­3- ØÈ- è«ru 5 •u---
ASR by NLL APPS
ስንክሳር ዘወርሃ የካቲት ስምንት (፰)
https://www.tg-me.com/SinkisarZekidusan2
2024/09/29 16:18:36
Back to Top
HTML Embed Code: