Telegram Web Link
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እንቆቅልሽ በ እንቆቅልሽ
(ሳሙኤል አለሙ)
.
.
እንዴት ነሽ ሀገሬ
እንደምንድነሽ ምድሬ
በስራ ስንዳክር ነግቶ የመሸ
ለአይነ-ስጋ ሳኖን ጊዜ ጥሎን ሸሸ
እናም
አሁን ካገኘሁሽ ዘንዳ
አንዳንድ እንቆቅልሽ ከርመው ያልተፈቱ
ቅር አለኝ
አንቺን ዋስ አድርጌ አንቺን ማስፈታቱ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በአንዱ ጋር ስቀደድ
በአንዱ ጋር ስሰፋ
ህመሜን የሚያውቅ አዋቂ ሲጠፋ
እኔው የታመምኩ
እኔኑ ያስታመምኩ....ነበረ የከረምኩ
ብቻ ግን ለክፉ አልሰጥም
ልጆች ያላት እናት
አመመኝ እያለች ከአልጋ አሰነብትም
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እንቆቅልሽ
ምን አውቅልህ
እንቆቅልሽ
ምን አውቅልህ
በጠቢባን ዘመን
ፈርኦኖች ሞተው ከጎን ሎሌ ይኖራል
ድንገት ነፍሱ ነፍስን ብትዘራ
ከምግብ መጠጡ
ሎሌው ያቀርበዋል ከሞላው ጎተራ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አያድርገውና
በድንገት ቢባንን ባለራዕይው ከመቃብር
መለስ ቀለስ ይላል
መለዮ ለባሹ ከመቃብር ስርስር
ምግብ አልሰነቀ ውሃ አላስቀመጠ
ጠብ"መቅጃ" ብቻ ነው ከጎን የሸጎጠ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አውጥተሽ አውርደሽ ካልመጣልሽ መልሱ
ከአንድ አንቺ ውጪ
ሀገር ስጪኝ እና ልገላግልሽ በሱ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
መቐሌ ሄጄ
ሁሉ መስሎኝ ደጄ
ፈልጌ የማገኝ ጌጥአቸውን በጄ
(ለአንባቢያን ደህንነት ሲባል "ጥ" በ "ታ" ተተክቶል😂)
ግና ምን ያደርጋል
እንቆቅልሹን ተረስቶ ስኳትን ከርሜ
"ሳላየው አልመጣም"
ከሚል ሀሳብ ጋራ ግብግብ ገጥሜ
እዚያው ነኝ
እዚያው ነኝ ቆዝሜ
@Gitemenlenante
እንቆቅልሽ በ እንቆቅልሽ
(ሳሙኤል አለሙ)
.
.
እንዴት ነሽ ሀገሬ
እንደምንድነሽ ምድሬ
በስራ ስንዳክር ነግቶ የመሸ
ለአይነ-ስጋ ሳኖን ጊዜ ጥሎን ሸሸ
እናም
አሁን ካገኘሁሽ ዘንዳ
አንዳንድ እንቆቅልሽ ከርመው ያልተፈቱ
ቅር አለኝ
አንቺን ዋስ አድርጌ አንቺን ማስፈታቱ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በአንዱ ጋር ስቀደድ
በአንዱ ጋር ስሰፋ
ህመሜን የሚያውቅ አዋቂ ሲጠፋ
እኔው የታመምኩ
እኔኑ ያስታመምኩ....ነበረ የከረምኩ
ብቻ ግን ለክፉ አልሰጥም
ልጆች ያላት እናት
አመመኝ እያለች ከአልጋ አሰነብትም
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እንቆቅልሽ
ምን አውቅልህ
እንቆቅልሽ
ምን አውቅልህ
በጠቢባን ዘመን
ፈርኦኖች ሞተው ከጎን ሎሌ ይኖራል
ድንገት ነፍሱ ነፍስን ብትዘራ
ከምግብ መጠጡ
ሎሌው ያቀርበዋል ከሞላው ጎተራ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አያድርገውና
በድንገት ቢባንን ባለራዕይው ከመቃብር
መለስ ቀለስ ይላል
መለዮ ለባሹ ከመቃብር ስርስር
ምግብ አልሰነቀ ውሃ አላስቀመጠ
ጠብ"መቅጃ" ብቻ ነው ከጎን የሸጎጠ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አውጥተሽ አውርደሽ ካልመጣልሽ መልሱ
ከአንድ አንቺ ውጪ
ሀገር ስጪኝ እና ልገላግልሽ በሱ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
መቐሌ ሄጄ
ሁሉ መስሎኝ ደጄ
ፈልጌ የማገኝ ጌጥአቸውን በጄ
(ለአንባቢያን ደህንነት ሲባል "ጥ" በ "ታ" ተተክቶል😂)
ግና ምን ያደርጋል
እንቆቅልሹን ተረስቶ ስኳትን ከርሜ
"ሳላየው አልመጣም"
ከሚል ሀሳብ ጋራ ግብግብ ገጥሜ
እዚያው ነኝ
እዚያው ነኝ ቆዝሜ
@Gitemenlenante
እምነት
""""""""
አቤት ለበይክ ብሎ
እምነት አንጠልጥሎ
ትርፍ ሀሳቡን ጥሎ ለአላህ ይታዘዛል፤
የእግዜር ቃል ነውና
ያለ አንዳች ድርድር
ልጁን ለመሰዋት ሰይፉን ይመዛል፥
ለፈጣሪ ይገዛል!

የእምነት ጥግ
የእውነት ምርግ
ጠንካራ ምሰሶ መቼም የማይላላ፤
ሰውኛ ባህሪን
አሽቀንጥሮ ጥሎ
ልጅን ለመሰዋት ያሲዛል ሻሞላ፤
የፈጣሪ ስራ!

ምን ሊረባው እሱ
የኢስማኢል ህይወት በከንቱ ቢቀጠፍ፤
ምን ሊረባው እሱ
ከሳር ክዳን ጎጆ አንድ ሳር ቢመዘዝ!
ምን ሊረባው እሱ
ፍጥረት ለዱንያ በከንቱ ቢማልል፤
ምን ሊረባው እሱ
ከጥቅጥቅ ጎፈሬ አንድ ፀጉር ቢጎድል!
ምን ሊረባው እሱ
ከእህል ጎተራ አንድ ዘር ቢጠረግ፤
ይለውጥ የለም ወይ
ነፍስን በነፍስ ሽሮ መስዋቱን በበግ!
@Gitemenlenante
ቀረሽ እንደዋዛ
•┈┈•✦•┈┈•
እንደ ድመቶቹ
የትም እንደሚያድሩት
እንደ ስልክ እንጨቶች
እንደ ዛፍ ሃረጎች
እንደ ቤት ክዳኖች
ብርድ አቆራመደኝ
ስጠብቅ ስጠብቅ
"ትመጫለሽ ብዬ ሳይ ማዶ ሳይ ማዶ
የልጅነት ዓይኔ ሙዋሙዋ እንደ በርዶ"
ትመጫለሽ ብዬ ደቂቃ ስ ቆጥር
ትመጫለሽ ብዬ ሰዓቱን ስቆጥር
ትመጫለሽ ብዬ ባዝን ባንጎራጉር
ትወጫለሽ ብዬ በበራፍሽ ብዞር
ብርድ አቆራመደኝ
የመንገድ መብራቶች አይተው አፌዙብኝ
ውርጩ ቀለደብኝ
ጨለማው ሳቀብኝ።
አለመምጣትሽን
አውቀዋል ያውቃሉ
መስኮቶች ጨልመው
ቤቶች ተቆልፈው
ከተማው ሲተኛ
አይተዋል ያያሉ
አለመምጣትሽን
አውቀዋል ያውቃሉ።

ገብረክርስቶስ ደስታ
@Gitemenlenante
Channel photo updated
እየጠበኩሽ ነዉ
(ሠለሞን ሳህለ)

በሄድሽበት እንደ መንገድ
በቆምሽበት እንደ ጥላ
ንፁህ ነፍሴ ተከትላሽ
አንቺን አምና አንቺን ብላ
ሲመሽ ሲመሽ በህልሜ ላይ
ዘላለሜን እያየሁሽ
ተመልሼ ማልመልሰዉ
ሙሉ እድሜየን ያዉ ሰጠሁሽ
እየጠበኩሽ ነዉ...
በቸኮለዉ በዚህ ዘመን
መጣደፉ በበዛበት
አሁን አለ ያልነዉ ነገር
ትንሽ ቆይቶ በሌለበት
አንቺን የሚል የኔ ፍቅር
አንቺን የሚል የኔ አንደበት
ብቻ ፀንቶ ይጠብቃል
ዉብ ፍቅርሽን በቅንነት
እየጠበኩሽ ነዉ...
ደማቅ ፀሃይ ይሄዉ ገባች
ጨለማዉን አስከትላ
ብርቱ ክንዴን ሊፈትነዉ
የእድሜየ ጎርፍ ኸንዙን ሞላ
በልጅነት ጨዋታችን
በዉሃ የተጫወቱ
ዉሃ አጣጬን ስጠብቅሽ
ትዳር ጎጆ መሠረቱ
እየጠበኩሽ ነዉ...
በመንገዱ ግራና ቀኝ
የበቀሉት አበባዎች
ቢራቢሮ የሚጠሩ
የልጅነት እምቡጥ መልኮች
ድንገት በፀሃይ ሳይደርቁ
ድንገት በንፋስ ሳይረግፉ
እንደጠበኩሽ ነይና
ከድካማቸዉ ይረፉ!!!
እየጠበኩሽ ነዉ...
@Gitemenlenante
ናፍቆት
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
እንዲህ እንደዛሬ...
በመሀከላችን
ንፋስ ሳይግባብን ፣ ፍጥረት ሳይፈጠር
በኔና አንቺ መሀል...
የነበረው ክፍተት ፣ አንድ ስንዝር ነበር።
አንቺ ሰማይ ሆነሽ እኔ ደግሞ ምድር!!!
............................................
በዚህ ስንዝር መሀል....
እስትንፋስ ያላቸው ሰዎች ተፈጠሩ
እነዚህ ሰዎችም....
ቅርብ ላለች ሰማይ
የምድርን ሀጥያት ይነግሯት ጀመሩ።
"ምድር ዘማዊ ነው
ምድር ሀጣዊ ነው
ብትሸሺው ይሻላል ይህ ዓለም ጠፊ ነው"
እያሉ ሲነግሯት የሰው ወሬ ሰምታ
ሰማይ ፊኛ ሆና...
ትለጠጥ ጀመረ ከኔ ተለይትል
በሰዎች እስትንፋስ...
ወደ ላይ ተነፍታ
ወደጎንም ሰፍታ።
.......................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
................................................
እንደውም እንደውም...
በዛ ስንዝር መሀል ያኔ የተፈጠሩ
እዛሬ ላይ ሆነው..
"ሰማይ ቅርብ ነበር" እያሉ ሚያወሩ
እድሜ የሰጣቸው
ጥቂት ሰዎች አሉ
የኔና ያንቺ ፍቅር የሚመሰክሩ።
.............................................
እንደውም እንደውም....
ሌላ አይነት ማስረጃ ሌላ አይነት ምስክር
ሰማይ ቅርብ ሳለሽ ምጣድ ሆኜ ምድር
እንዲህ እንደዛሬው...
ነፋስ አቀጣጥሎት
ነፋስ የሚያጠፋው እሳት ሳይፈጠር
የሰው ልጆች ሁሉ
በፀሐይ በርሀን ምግብ ያበስሉ ነበር።
.............................................
ፀሐይ ውበትሽ ነው ጠዋት የምሞቀው
ቀን ተቃጥዬበት ሌት የምናፍቀው።
ለሊት ላይ ያመኛል ህመሜም አንቺው ነሽ
ቀኑ ጨለማ ነው...
ነግቶ እስካይሽ ድረስ ትናፍቂኛለሽ።
...........................................
መቼ ነው ሚነጋው?
ፀሐዩ ውበትሽ ምድርን የሚከድነው
መርዙ መድሀኒትሽ...
በሽታዬን ገድሎ ህመሜን ሚያድነው
ካፈቀሩት ጋራ....
እንኳን ላንድ ለሊት
ላፍታ ያህል እንኳን መለያየት ሞት ነው።
.............................................
መቼ ነው ሚነጋው ልቤን ይበርደኛል
ንጋት ላይ የሚሸሽ..
ወረተኛ ፍቅር ጤዛው በዝቶብኛል
አንቺ የሌለሽበት...
ራሴን ሳስበው ራሴን ያዞረኛል።
ለራስ ምታት ህመም..
መድሀኒት እንዲሆን
በሽታን የሚገድል መርዝ ነው ሚቀመም።
...................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ.
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
........................
እየሔዱ መጠበቅ
@Gitemenlenante
የቀበሮ ፀሎት
(ታገል ሰይፉ)
------
እባክህ አምላኬ- ብትሬን ቀባና
እኔም ልወዝወዘው-የሙሴን ጎዳና
ያላንዳች ፍርሃት-ያለምንም ችግር
ባህሩን ከፍዬ- ህዝቤን እንዳሻግር፡፡
*
አቤት የኔ ጌታ ይህም አያረካም
በቃልህ ታምኜ -ከሆንኩልህ መልካም
ለእኔም ፍቀድልኝ-ያብራምን ምልክት
ከምድር አሸዋ-ዘሬ እንዲበረክት፡፡
*

አቤቱ ምን ልሁን-ይህም አልጠቀመኝ
እስቲ እንደ ዮናስ-ህዝብ ፊት አቁመኝ
*
ትንቢቴን ሰምቶልኝ-ሀገር ይተራመስ
ሰው እህል ይጡም-ከብቱም ሳር አይቅመስ፡፡
ይህም አያረካም-ይልቅ እንደዳዊት
አንተን በሚፈራ-ብዙ ሺህ ሠራዊት
ዙፋኔ ተከቦ-በደስታ እንዳመልክህ
የዚህን ሰው ኮከብ -አውጣልኝ እባክህ
*

አደራህን ታዲያ- ጭንቅ አትወድም ነፍሴ
ልመናዬን ሰምተህ-ካደረግከኝ ሙሴ
መከራውን ማረኝ-ያርባ ዓመት ስደቱን
በሲና በረሃ-መራብ መጠማቱን፡፡
*
ነቢዩ ዮናስን -አርገህም ስትፈጥረኝ
የባህሩን ፍዳ- ያሳውን ሆድ ማረኝ፡፡
*

አብረሃምን ሆኜም-በደስታ ሳመልክህ
ልጅህን እረደው-አትበለኝ እባክህ፡፡
***
የዲዊትም ኮከብ-በኔ ላይ ሲወጣ
እባክህ አምላኬ -ጎልያድ አይምጣ፡፡
#የቅርብ_እሩቅ
•••••••••••••
ከተመኙም አይቀር ~ ዞማነት መመኘት
እራስን ሳይለቁ ~ ከሰው ላይ መገኘት
ሃገሬ ባትመጪ ~ ሀገርሽ ባልመጣም
ሰርክ ከምግቤ ውስጥ ~ ፀጉርሽን አላጣም
===||===
ከሙሉቀን
@Gitemenlenante
#የመፀሀፍ_አለም
————-ሴት———-

እዪ መስታወት በማለዳ
ፈግጊ ፊቱ፡ ፊትሽ ትዋል ተስፋን ወልዳ፡፡
ሁኚ መስታወት አንፀባርቂ
ንፁህና ገፅ አዋቂ፡፡
እዪ መብራት በጨለማ
በድቅድቁ ተስፋሽ አይቀማ፡፡
ሁኚ መብራት ባለጨረር፡
ብርሃን ለቀሽ ፅልመት ይወረር፡፡
እዪ ውሀ እርጋታውን
ደግነቱን፡
ዝም ማለቱን፡
ሁኚ ውሀ ሩህሩህ አርኪ
ለሰው ፈሰሽ ሰውን ባርኪ፡፡
እዪ ንፋስ፡አቅጣጫውን፡
ብልሀቱን፡
ብልጥነቱን፡፡
ሁኚ ንፋስ የቀደመች ውል ጠቋሚ፡
ያዘመመች ወደመልካም፡
መልካም ሰሚ፡፡
እዪ አፈር ለም ማልማቱን፡
ሁኚ አፈር ባለ እንቁ
ለሰው እህት ሁኚው ብርቁ፡፡
እዪ ጠፈር ኮከብ ሀብቱን፡
ሁኚ ጠፈር ባለ ሚስጥር፡
ባለ ጥበብ ዝሪ ፍቅር፡፡
እዪ እነሱን፡ ሁኚ እነሱን፡፡
ተነጠቂ በልህቀት
ተመንጠቂ በሰው'ነት
ለሀዋም መልካሚቷ
ለአዳማን እናቲተቷ፡፡
ውሰጂ ዘር ስጪኝ ፍሬ፡
ልወድስሽ በከንፈሬ፡፡
ፊቴ ይብራ ፊትሽን ሲያይ፡
መንፈሳችን አይለያይ፡፡
ሰርክ ለምለም አስቢልኝ፡
በጎ ውለሽ ቸር አምሺልኝ፡፡
እዪ ሰማይ፡
ሁኚ ሰናይ፡፡
የሚስኪናን ማረፊያችን፡
የብቻነት መጠጊያችን፡፡
እዪ መስታወት፤ ሁኚ ውሀ፡
እዪ አፈር፤ ሁኚ ንፋስ፡
እዪ መብራት፤ ሁኚ ጠፈር፡፡
ምን ተስኖሽ፡ ምን ነስተሸኝ፡
ኩራቴ ነሽ ለእኔ ያለሽኝ
ሴት፡፡

- ርብቃ ሲሳይ
@Gitemenlenante
""" "እናቴ"" """
ፀጉርሽን አይቼ የኔን ፀጉር ሳየው
እንደ ወንድ ፀጉር ገባ ገባ ያለው
እሳት እንደነካው የተኮማተረው
----ለካ ለፍቅር ነው
የፊትሽ ላይ ቆዳ የተሸበሸበው
እንደ ወየበ ልብስ እንዲህ የገረጣው
እንደ ቼዙ ሜዳ የተዥጎረጎረው
--ለካ ለፍቅር ነው
በጉብዝናሽ ወራት በወጣትነትሽ
እነዚያ ውብ አይንሽ
ጎላ ጎላ ያሉት
ከለሊት ጨረቃ ደምቀው የሚታዩት
አሁን ደም ለብሰዋል
አንቺ ለእኔ ብለሽ በጪስና አቧራ
ሰውተሻቸዋል
---ይሄም ለፍቅር ነው
አንቺ የፍቅር አምድ
ተምሳሌት የመውደድ
አንቺ የፍቅር ማዕድ
ልክ እንደከዘራ ጀርባሽ የጎበጠው
አሁን ነው የገባኝ እኔ ቀና እንድል ነው
------አንቺ እንዲህ የሆንሺው ለካ
ለፍቅር ነው
መዳፍሽን ሳየው
አሻራ እንኳን የለው
ድህነት በልቶታል
ሸክም አጥፍቶታል
-----እናም ውዷ እናቴ
ዝምብየ ሳስበው
ምን አይነት ፍቅር ነው
ይሄን ሁሉ የሆንሺው
አንዴት በትወጂኝ ነው።
እማ ዛሬ ፍቅርሽ ገባኝ!!!
#jerry
@Gitemenlenante
እንዲሁ ለምወድሽ
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
አንቺ ባትኖሪም ፣ ስላንቺ እፅፋለሁ
አንቺ ባትሰሚኝም ፣ ስላንቺ አወራለሁ
አንቺ ባትቀጥሪኝም ፣ አንቺን 'ጠብቃለሁ
ውዴ ሙሽራዬ ፣ ፍቅሬ አፈቅርሻለሁ ።
@Gitemenlenante
የሰማይ ቤት ግሮሰሪ
(አሱ እንደፃፈዉ)
.
.
"ጨረቃ" ምንላት
ግሮሰሪ ቤት ናት!!!
"ሰማይ" ለምንለው ፣ ቀውጢ ከተማ
ሥራ ምትጀምረው ፣ሲሆን ነው ጨለማ!!!
..................................................
በር እንደከፈተች ፣ አብረው የሚወጡ
ከዋክብት ደሞ...
ሰካራሞች ናቸው ፣ እሷ ጋ ሚጠጡ!!!
*********************
በጣም የሰከረው...
ከሰማይ ፈጥፍጦ ፣ ራሱን ሲገድል
"ተወርዋሪ ኮከብ" ..
ማለት ነው የኛ እድል!!!
********************
ተወርዋሪ ጠርሙስ ሊሆንም ይችላል!
ማን ያውቃል?
@Gitemenlenante
2024/09/27 09:34:10
Back to Top
HTML Embed Code: