Telegram Web Link
አሰልጣኝ ውበቱ አባተ መግለጫ እየሰጠ ነው ።
🇦🇹#አሰልጣኝ_ውበቱ_አባተ
በፋሲል ከነማ ያልጨረስኩት ስራ በመኖሩ ተመልሻለው!!

ፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ አሰልጣኝ ውብቱ አባተን ለ3 አመት በሚቆይ የውል ስምምነት የአፄዎቹ አሰልጣኝ አድርጎ ሹሟል!!

የጋዜጣዊ መግለጫውን አጠቃላይ ሁኔታ በፁሁፍ እናቀርባለን ::

🇦🇹🇦🇹#አሰልጣኝ_ውበቱ_አባተ
እንኳን ወደ ቤትህ በደህና መጣህ!!🇦🇹🇦🇹

. 🇦🇹#ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ_ነው🇦🇹

@FASILSC
ፋሲል ከነማ አሰልጣኝ ውበቱ አባተን መሾሙን ይፋ አደረገ!

አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ምን ይጠበቅባቸዋል ?
አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ክለቡ ያስቀመጣቸውን ግቦች ማሳካት ይጠበቅባቸዋል የተባለ ሲሆን በመጀመሪያ ዓመታቸው ተፎካካሪ ቡድን ማሳየት ይኖርባቸዋል ተብሏል።

ምንም እንኳ በመጀመሪያ ዓመት ተፎካካሪ ስብስብ ቢገነባም ቡድኑ ለዋንጫ አይጫወትም ማለት እንዳልሆነ የክለቡ ፕሬዚዳንት እና የጎንደር ከተማ ከንቲባ አቶ ባዩህ አቡሃይ አሳስበዋል።

ክለቡ በ 2017 ዓ.ም የፕርሚየር ሊጉን ዋንጫ እንዲያነሳ ከክለቡ አመራሮች ለአሰልጣኝ ውበቱ አባተ ሀላፊነት ተሰጥቷቸዋል።

የክለቡን እቅድ ለማስፈፀም ሀላፊነት መውሰዳቸውን የገለፁት አሰልጣኝ ውበቱ አባተ " የእኔ እቅድ የክለቡ እቅድ ነው " ሲሉ " በስነ ምግባር የታነፁ ፣ ለምጫወተው ጨዋታ የሚሆኑ እና ወጣት ተጫዋቾችን " በዝውውር መስኮቱ እንደሚያስፈርሙ ተናግረዋል።

ፋሲል ከነማ አሰልጣኝ ውበቱ አባተን መቅጠራቸውን ተከትሎ ከሶስት እና አራት ዓመታት በኋላ በሊጉ በአማካይ በእድሜ ትንሹ ቡድን እንዲሆን መታቀዱ ተገልጿል።

የክለቡ ውጤት ማጣት ምክንያቱ ምን ነበር ?

የፋሲል ከነማ ፕሬዝዳንት አቶ ባዩህ አቡሃይ በ 2015ዓ.ም የውድድር ዘመን ክለቡ ላስመዘገበው ውጤት የተጫዋች ፣ ልምድ እና የስነ-ምግባር ከፍተትን በምክንያትነት አስቀምጠዋል።

አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ምን ያህል ያገኛሉ ?

አሰልጣኝ ውበቱ አባተ በክለቡ ለቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ሲቆዩ " ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ አሰልጣኞች ባልተጋነነ ዋጋ የሀገሪቱ እግር ኳስ የሚከፍለውን ክፍያ " እንደሚከፈላቸው አቶ ባዩህ አቡሃይ ገልፀዋል።

አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሀላፊነታቸው በፊት በሰበታ ከተማ ፣ ፋሲል ከነማ ፣ ኢትዮጵያ ቡና እና በሱዳን አል አህሊ ሸንዲን ማሰልጠናቸው የሚታወስ ነው።
🇦🇹#ፋሲል_ከነማ ስፖርት ክለብ አሰልጣኝ ውበቱ አባተን የአፄዎቹ አሰልጣኝ አድርጎ ሾሟል!!🇦🇹

ፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ለ2016 አመት ውድድር የቡድን ግንባታ እቅዱን ቀደም ብሎ በመጀመር አሰልጣኝ ውበቱ አባተን ለሶስት አመት በሚያቆይ የውል ስምምነት አስፈርሟል::

የአሰልጣኝ ውበቱ አባተ ውል በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የፀደቀ ሲሆን በቀጣይ ከስምምነት ላይ የደረሱ ተጫዋቾች ውላቸው ሲፀድቅ የምናሳውቃችሁ ይሆናል::

ፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ባስቀመጠው የአምስት አመት እቅድ ውስጥ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ዋነኛ አላማቸው ቅድሚያ ቡድኑን በወጣቶች መገንባት ከዛ የዋንጫ ክብሮችን ማምጣት እንደሆነ ገልፀዋል::

የጎንደር ከተማ ከንቲባ የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ፕሬዝዳንት አቶ ባዩህ አቡሃይ ፋሲል ከነማ ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፎ እዚህ ስለደረሰ እኛም መሰረታዊ ስራዎችን በማስቀጠል ከደጋፊያችን ጋር የተጀመሩ የስኬት መንገዶችን በማብቃት ክለባችን ትልቅ ተቋም እናደርጋለን በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል::

#አሰልጣኝ_ውበቱ_አባተ
እንኳን ወደ አፄዎቹ ቤት በደህና መጣህ!!

🇦🇹#ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ_ነው🇦🇹

@FASILSC
ማስታወቂያዎችን እኛ ጋር ማሰራት ምትፈልጉ @FASILKFCBOT ላይ ያናግሩን
ሀገራችን ኢትዮጵያን በዳኝነት ሙያ ከፍ አድርጋ ያስጠራች ኢንስትራክተር #ሊዲያ_ታፈሰ ለአፄ ፋሲለደስ ስታዲየም እድሳት አለሁ ከጎናችሁ በማለት 10,000 ብር አስገብታለች።

የአፄ ፋሲለደስ ስታዲየም እድሳት ላይ አሻራዎን ስላሳረፉ እናመሰግናለን🇦🇹 🙏

እስታዲየማችን ገንብተን ፋሲልን በአፄ ፋሲለደስ ማየት አልናፈቅንም ??

1000556916617 ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
9900007395047 አማራ ባንክ

#ፋሲል_ከነማ_ከክለብም_በላይ🇦🇹
ይህን ማበረታት ያስፈልጋል።

ከጥቂት ሳምንታት በፊት ፋሲል 100 ሚልየን ብር ለዝውውር መደበ ሚባል ወራ ይናፈስ በነበረ ወቅት .. የክለባችን ሙሉ ጨዋታወችን ከሜዳው ውጭ ማድረጉ እየጎዳው ነው ለሚለው የክለቡ ደጋፊዎች ያሰሙት ጥያቄ ተንተርሼ .. በቃ ለዝውውር ተመደበ ሲባል ዋናውን ጥያቅያችሁን ረሳችሁት እንዴ ብዬ ራሴ ለክለቡ ደጋፊዎች ጥያቄ ኣዘል ፖስት ኣጋርቼ ነበር። በወቅቱ ታድያ ብዙዎቹ ኮመንት የሰጡኝ የክለቡ ደጋፊዎች ኣይ ዝውውሩን ያርጉ እኛም ግን ጥያቄያችንን ኣንረሳም በተለይ የስታድየሙን ጉዳይ ኣንረሳም ኣንተውም ብለውኝ ነበር። ምንም መዋሸት ኣልፈልግም በወቅቱ ያሉኝን ምቀበልም ኣላመንኳቸውም ነበር። ግን ይህው ኣሁን ልክ ሆነው እያየዋቸው ነው። በርቱ ኣቦ ...

ይህን ክረምት እንደ ፋሲል ደጋፊዎች ለክለቡ የተጠቀመበት እስካሁን ኣላየውም። የደም ልገሳ የበጎኣድራጎት ስራ አከናውነዋል 20ሺ የክለቡ ኣባላት የተመዘገቡ ሚከፍሉ ደጋፊዎች እንዲሆን ደጋፊዎች ስራ ሰርተው ተሳክቶላቸዋል። ይህው ኣሁን ደሞ እኔን ምያስደስተኝን ስራ ሊሰሩ ጀምረዋል።

ቃል የተገባልን የእስቴዲየም ማደስ እና ለ ቤትኪንግ ብቁ ማድረግ የሚለው ኣሁን ሰሚ ኣግኝቷል። የፋሲለደስ ስታድየም እድሳት ጀምረዋል። ደጋፊውም የበኩሉን እያረገ ነው እየተደረገ ያለው ርብርብ እጅግ ኣስገርሞኛል። በንግድ ባንክና በኣማራ ባንክ በተከፈቱ ኣካውንቶች የክለቡ ደጋፊዎች ጨምሮ ሌሌች የስታድየም ጥቅም የገባቸው በሙሉ ድጋፍ እያረጉ ነው። እኔም በነገው እለት የኣቅሜን ማግዝ ይሆናል። ይህን ለማገዝ ግዴታ የፋሲል ደጋፊ መሆን ኣይጠበቅኝም። እናንተም ይህን ምታዩ ሁሉ ፋሲልን ለስታድየም እድሳቱ ኣግዙ ። ሌላም ክለብ ቢጀምር ይህን ድጋፍ ልናረግ ይገባል። ችግረኛ ሀገር ነንና ችግራችን በጋራ ማለፍ ኣለብን ባላንጣነት ከስታድየም ሊዘል ኣይገባምና ይህን ስራ ኣግዙ። የሌሎች ክለብ ደጋፊዎችስ ምን እያረጋቹ ነው ??? ኣመራሮቻችሁን ተቆጡ እንጂ ኣሁንኮ ምክንያት ኣላቹ እንደፋሲል እኛም በራሳችን ስታድየም ልንገነባ ይገባል ብላቹ ጓ በሉ እንጂ ?? ..

ዲር የፋሲል ኣመራሮች .. ስታድየም ስሩ ሚለውን የደጋፊያችሁን ጩህት መስማታቹ ያስመሰግናችዋል ግን ይህ ብቻ በቂ ኣደለም ።ምክንያቱም ደጋፊ ጩህት እንዲሰማለት ብቻ ሳይሆን እንዲተገበርለት ይፈልጋልና በቃላቹ ተገኙ። እኔም ዛሬ ጅማርያችሁን እንዳደነቁት ሁሉ .. ጨርሳችሁም ማመስገን እንጂ ምፈልገው .. ቃላቸው በሉ ብዬ መፃፍ ኣልፈልግም። ኣደራችሁን ... ።ይህን ስትሰሙ ግን ሌሎች ክለቦች ኣመራሮችና ደጋፊዎችስ ምን እያሰባቹ ነው ?? የምር ኣስቡበት።

የሚድያ ሰዎችም የውበቱ ኣባተ በ3 ኣመት ሚሰጥ 15 ሚልየን ብር ደሞዝ ብቻ ኣያሳስባቹ።ክለቡ ከዘንድሮ በጀቱ ለኣሰልጣኙ ሚከፍለው በኣመት 5 ሚልየን ብር ብቻ መሆኑ ኣትርሱ ። 15 ሚልየን በኣንድ ኣመት ሚሰጥ እስኪመስል ደሞዝ ላይ ከምናተኩር .. ይልቁንም ለ15ና ከዛ በላይ ኣመት ክለቡንም ሀገሪቷንም ልያገለግል ስለሚችለው ክለቡ ስለሚያሳድሰው ስታድየም ብዙ ብናወራ ይሻላል። ብያንስ ይህ ኣስቀንቶት ስታድየም ልስራ ሚል ክለብ ሊመጣ ስለሚችል።

የፋሲል ደጋፊዎች የ2015 ክረምት ድምቀቶች ናችሁ። እባካቹ ሌሎቻችሁም ቀጥሉ እባካቹ። ክለብ እንድያድግ ሚያረግ ስርኣት ያለው ሊግ ካምፓኒ የለንም እናማ የኳሳችን እድገት ተስፋ የደጋፊዎች ጩህት ብቻ ነውና ኣስቡበት ፕሊዝ።


ከ ግለሰቦች አስተያየት
ከ ኤርሚያስ በላይነህ እናመሰግናለን ጥሩ እይታ ነው 🙏🙏🙏
@FASILSC
@FASILSC
ለ ፋሲለደስ እስቴዲየምን ለማደስ እጃችን እንዘርጋ !!!!!
ስቴድየሞችን ማደስ፣መስራት ኢትዮጵያ እግር ኳስ እድገት አንድ አካል ነው ።

ከነጉድለቱ ሊጋችን እንዲያድግ የበኩላችንን እንወጣ ።
ስደተኛው ክለባችንን ወደ ቤቱ እና ለልጆቹ የገቢ ምንጭ እንዲሆን የበኩላችንን እንወጣ ።

@FASILSC
2024/09/30 15:25:24
Back to Top
HTML Embed Code: