Telegram Web Link
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በኤፍራታና ግድም ወረዳ በሁለት ቀበሌዎች በመሬት መንሸራት ምክንያት በ 156 የግለሰብ ቤቶች ላይ ጉዳት አደረሰ‼️

በሰ/ሸዋ ዞን ኤፍራታና ግድም ወረዳ በበርግቢ ቀበሌ እና በመንተኬ ሸረፋ ቀበሌ የመሬት መንሸራተት ተከስቷል።

በመሬት መንሸራተቱ ምክንያት በዕለቱ በሰው ህይወት ላይ ያደረሰው ጉዳት ባይኖርም በአንድ መቶ ሃምሳ ስድስት የግለሰብ የመኖርያ ቤትን ጨምሮ፣ ማሳ ላይ እና ቋሚ ተክሎች ላይ ጉዳት አድርሷል።

በዚህም መሠረት በርግቢ ቀበሌ በነሃሴ 07/2016 ዓ.ም ባስከተለው ከባድ ዝናብ የ24 ግለሰቦች ቤት የመፈራረስ እና ከነበረበት ቦታ ዝቅ የማለት(የመስጠም) አደጋ የደረሰባቸውና ቤቶቹ ከጥቅም ውጭ የሆኑ ሲሆን በዚሁ ቀበሌ በነሃሴ 12/2016 ዓ.ም በ12 አርሶ አደሮች ማሳ ላይ የመሬት መንሸራተቱ ተከስቷል።
📌 የታዘዙ የቅጣት ዓይነቶች ከዚህ በፊት በመልእክቶቹም የተጠቀሱ ቢሆንም ዛሬም ደግሜ ላነሳቸው ግድ ይለኛል፡፡
በ አገራችን ----- እጅግ ከባድ ቋጥኝንና ሕንጻን ነቅሎ የሚወስድ አውሎ ነፋስ ፤ከባድ የመሬት ነውጥና  እሳተ ገሞራ ፤ ከባድ ርሀብና ችጋር ፤ ተሰምተው የማያውቁ እንደ ሰደድ እሳት የሚዘምቱ ገዳይ በሽታዎች፤ ጎርፍ ፤ የርስ በእርስ መተላለቅ  ፤ከባድ በረዶ ፤ የዘር ፍጅት ፤ከባድ  የገንዘብ ቀውስ-----

ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዢ መልእክት 8ገጽ 47
በቀን 21/4/2011 ዓ፡ም የተጻፈ፡፡
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ www.tg-me.com/kyrieelesion)
"የዛሬዎቹ ነቃፊዎች በእሳት እራት እመስላቸኋለሁ። ሁላችሁም እንደምታውቁት ከሰል ተያይዞ በሚንቀለቀልበት ሰዓት የእሳት እራት ብትከለክሏት እንኳን ባለመመለስ እሳቱን ዞራ ዞራ እውስጡ ገብታ ተቃጥላ ትደመደማለች የዛሬዎቹም ነቃፊዎች ተችዎች በማያጠራጥር ሁኔታ ነው የማረጋግጥላችሁ አንዳቸውም ሳያመልጡ ከፊታችን በመጣው እሳትና መጥረጊያ ይሰናበታሉ። ተው! ሲባሉ በንስሀ በእግዚአብሔር እጅ ካልወደቁ በስተቀር መፈፀሚያቸውም ሆነ መደምደሚያቸው ይኸው መጪው እሳትና መጥረጊያው ይሆናል። ዛሬ ሁላችሁም እንደምትረዱት መላው አለም በታላቅ ጭንቀት እና ተስፋ መቁረጥ መጨነቅ ውስጥ ወድቋል። በሰላም ወቶ መግባት ያለጭንቀት ቀርቷል። አፍ ተለጉሞ እንደ ቦለድ ዝንጀሮ ተራርቆ ታጥቦና ተለቅልቆ ነው የሚንቀሳቀሰው ሰው ሁሉ ይህ ሁሉ ተደርጎ እርግጠኛ መዳን ይቻላል ወይ ለማለት በማይቻልበት ሁኔታ ውስጥ መላው አለም በሙሉ የወደቀ ሆኗል። የዘመኑ መቅሰፍት ውስጥ ከሆነው አንዱ ኮረና ቫይረስ የሚሉት አለምን እየናጣት እንዳለ ትውልድ ሁሉ ምስክር ነው። ይህ ሆኖ ወደፈጣሪው ማን ተመለሰ? ብልሀትና ዘዴ ያለውን ሁሉ ቀኑን ሙሉ ሲያስተጋባና በዚሁ ሳይንሳዊ ዘዴ እንደሚፈታው ሲናገሩ እየሰማን ነው ወገኖቼ ከመልእክታቱ ቀጥሎ የወጡት ጥር 7 ቀን 2012 ዓ-ም የተገለፁት የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ደብዳቤዎች እንደገለፁልን የሚመጣው መከራና መቅሰፍት የማይቆም እንደውም ሰው በትእቢቱ እየገፋ ከዘለቀ እጅግ የማንገምተው ከኛ አይምሮ እና እውቀት በላይ በላይ የሆነ ጠረጋ እንደሚሆን ግልፅ ነው። በሁላችን ደጅ ቆሞ ለእርምጃ ትእዛዝን እየጠበቁ ያሉ መቅሰፍቶችም ወገኖቼ እጅግ ብዙ ናቸው።"

ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ፪ኛ የእረኝነት ትምህርት
13 ደቂቃ 30 ሰከንድ እስከ 16 ደቂቃ 42ሰከንድ◈ ሰኔ 29/2012ዓ.ም
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA ◈ ኢ/ዓ/ብ)
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
🍀 አባ ጳውሎስ የተወገዙት ራሳቸውን በጌታ መንፈስቅዱስ ቦታ ስላስቀመጡ ነው።

(አለቃ አያሌው በራሳቸው ድምፅ ያብራሩት)

ከ30 በላይ የሲኖዶሱ ጳጳሳት የፈረሙበት ቤተ ክርስቲያንን ያፈረሰው የአባ ጳውሎስ ሕግ ምን ይላል?

#_ዝክረ_አለቃ_አያሌው_ታምሩ
            
#የአለቃ_ሳምንት

💚 አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ
💛
www.tg-me.com/AlphaOmega930
❤️
www.tg-me.com/Ewnet1Nat
«አርቲስቶች እና የሚድያ ሰዎች እንደ እናንተ ሕዝብን ወደ ጥፋት የነዳ የለም። እጅግ የከፋችሁ የሀገሪቱ ጠላቶች የተዋሕዶ እምነትንና ስርአቱን የተዋጋችሁ አጥፊዎች ናችሁ። የሚዲያ ሰዎች በየቴሌቪዥኑ በብዙ ቻነል እየተከሰታችሁ ህዝብን ለአጥፊ ገዢዎች እንዲንበረከክ የምታደርጉ ለምንዝርና ለክህደት ለዘርፈ ብዙ ጥፋት ህዝቡን የምትነዱ ክፉ ሆድ አደሮች በየሲኒማ ቤቱ ለሆዳችሁ የተሰበሰባችሁ አርቲስት ተብየዎች እንደጋሪ ፈረስ የሕዝቡን ዐይንና ጆሮ በዲያብሎሳዊ ስራችሁ የዘጋችሁ ሌላኛው የዲያብሎስ እጆች በመሆናችሁ በአንደኛ ደረጃ ቅጣት ውስጥ ተካታችኋል። በመሆኑም እንደገዢዎቹ ጥፋታችሁ አብሮ ደርሶአል።»

📌 ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግስት ደብዳቤ ኢብመ/001/21/2012 ገፅ 10፣ ተጻፈ ጥር 7/2012 ዓ.ም

📌 በኦዲዮ ካለው ደብዳቤ ደግሞ 1 ሰአት ከ 8 ደቂቃ 13 ሰከንድ እስከ 1 ሰአት ከ 8 ደቂቃ 55 ሰከንድ ካለው የተወሰደ።
🟢🟡🔴
ነሐሴ 16 | የእመቤታችን ዕርገት መታሰቢያ ነው።

ይኸውም ተደርጎ በማያውቅ ክብርና ድምቀት ከሞተች በኋላ ደግሞ መሞት ወደሌለበት እውነተኛ ሐዲስ ሥጋ (ከጌታችን ምጽአት በኋላ የሚኖረን ሥጋ) ተሸጋግራ ለሐዋርያት የታየችበት ነው።

🌹

#ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ሊቀ_ሰማዕታት

ሥዕሉን ከሥዕሏ አጠገብ የሚሥሉት የቅዱስ ጊዮርጊስ ፍልሠተ ሥጋው ነው።

የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋው ከፋርስ አገር ወደ አገሩ ልዳ በክብር የፈለሰበት ነው።

ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ እመቤታችንን “ዕረፍተ ሞቴን በዕረፍተ ሞትሽ ዕለት አድርጊልኝ ይህም ባይሆን በዚህ አሕዛብ አገር ተቀብሬ አልቅር ከሚያምኑት አገር እቀበር ዘንድ ፍልሰተ ሥጋዬን ከፍልሰተ ሥጋሽ ዕለት አገናኝልኝ” ብሎ ተማጽኗት ነበርና።

 🍀

#ቅዱስ_ጊጋር_ሰማዕት

በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ስለ #እመ_አምላክ_ፍቅር
የተሰዋ #የመጀመሪያው_ሰው ተብሎ ይታወቃል።

ይህም ሰማዕት የሆነበትም ምክንያት ጌታችን ከእመቤታችን ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋራ በተሰደደ ጊዜ በሊባኖስ ተራራ ሳለ ኄሮድስ ሰምቶ ከበው ይዘው ይገድሏቸው ዘንድ ጭፍሮቹን ላከ። ጊጋርም ጭፍሮች እንዳያገኟቸው አሸሻቸው።

ስለዚህም ኄሮድስ ተቆጣ። ጊጋርንም ይዞ ጽኑ ሥቃይን አሠቃየው። ሕዋሳቱንም ሁሉ ቆራረጠ። ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጦለት ስሙን ለሚጠራ መታሰቢያውን ለሚያደርግ ገድሉንም ለሚጽፍ ቃል ኪዳን ሰጠው ከዚህም በኋላ ራሱን በሰይፍ ቆረጡት።

ጌታም ስለ ሃይማኖቱ፣ ፍቅሩና ሰማዕትነቱ 3 አክሊላትን ሰጥቶታል።

🌹🌹🌹

#_እንኳን_በምሕረቱ_አደረሳችሁ
T.me/Ewnet1Nat
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA ◈ ኢ/ዓ/ብ)
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ www.tg-me.com/kyrieelesion)
''ነገር ግን ይህች የሞት መርዶአችሁን የያዘችው ደብዳቤ ታሪክን ልታሳያችሁ እነሆ መጣችባችሁ። አንድ ጊዜ ለከፋ ጥፋት ተፅፋችኋልና እንኳን በደብዳቤ ከደጃችሁ ነጋሪት ቢጎሰም እንቢልታ ቢነፋ አትሰሙም።

ዛሬም የማይሆን መስሏችሁ በትእቢታችሁ እንደምትዘልቁ ምንም አያጠራጥርም። ተረት ነው እንደምትሉም ሁሌም ይህንኑ ቃል እንደምትናገሩት የተረጋገጠ ነው። ግን ልታውቁት ይገባል የእግዚአብሔርም የሕዝቡም የእውነትም ጠላቶች ናችሁና! ተረት የምትሆኑት እናንተ ናችሁ።''


📌 ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ ገጽ- 4
ተፃፈ ጥር 7 ቀን 2012ዓ.ም
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
አሸንዳ - አሸንድዬ - ሶለል - ሻደይ
🌹🌱🌹🌱🌹

ይሄ በዓል (ኧኸ) የማነው በዓል?
የአባታችን (ኧኸ) የሙሴ በዓል
ሙሴ ነቢያት(×፬)

ወገባችን (ኧኸ) ያሠርነው ቅጠል፥
በምን በምን (ኧኸ) በምን ይመሰል፥

ሙሴ ነቢያት(×፬)
አሸንዳችን (ኧኸ) ቅጠሉ ማለት፥
የሙሴ ነው (ኧኸ) የተጣለበት፥

ሙሴ ነቢያት(×፬)...

ሶለላዬ (ኧኸ)
በገነት የወጣው አባቷ ዳዊት፥
ሶለል በዪ

ሶለላዬ (ኧኸ)
ወደ ላይ ስታርግ የአምላክ እናት፥
ሶለል በዪ


🌹🌱🌹🌱🌹
www.tg-me.com/Ewnet1Nat
2024/09/29 16:21:33
Back to Top
HTML Embed Code: