Telegram Web Link
🟢🟡🔴
ሐምሌ 8 | የሙሽራው ገብረ ክርስቶስ አጎት #_አባ_ኪሮስ ዐረፉ፨

#አቡነ_ኪሮስ የተወለዱት በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን ሲሆን ወላጆቻቸው ነገሥታት ናቸው። ተወልደው ባደጉባት ሃገር ቁስጥንጥንያ ገና በልጅነት ምቾት ሳያሳሳቸው መጻሕፍትንና ትሕርምትን ተምረዋል።

ወንድማቸው (ታላቁ ቴዎዶስዮስ) በነገሠባቸው የመጀመሪያ ዓመታት በቤተ መንግስቱ ዙሪያ ግፍ በዝቶ ነበርና አቡነ ኪሮስ ከኃጢአት ለመራቅና ለጌታ ለመገዛት ከከተማው ጠፍተው፣ አሕጉር አቋርጠው ወደ ግብፅ #ገዳመ_አስቄጥስ መጡ።

እርሳቸውን ለመፈለግ የተደረገው ሙከራ አልተሳካም። ይባስ ብሎ የንጉሡ ልጅ #ገብረ_ክርስቶስ ሙሽርነቱን ጥሎ ወደ ሌላ ሃገር መነነ። አቡነ ኪሮስ ለሙሽራው ገብረ ክርስቶስ አጎቱ ናቸው። አቡነ ኪሮስ በገዳም ውስጥ የታላቁ #አቡነ_በብኑዳ ደቀ መዝሙር ሆነው ለዘመናት ቆይተዋል።

ቅዱስ በብኑዳን አንበሳ በበላው ጊዜ በጣም አዝነው "ለምን ጌታ ሆይ?" በሚል መሬት ላይ ወድቀው አለቀሱ። "ምክንያቱ ካልተነገረኝ አልነሳም" ብለው ከወደቁበት መሬት ላይ ሳይነሱ ለ40 ዓመታት አልቅሰዋል። በዚህ ምክንያት ግማሹ አካላቸው አፈር ሆኖ ሣር በቅሎበታል። ጌታችን ተገልጦ ምክንያቱን ነግሯቸዋል። አካላቸውንም እንደነበረ መልሶላቸዋል።

አንድ ቀን ጻድቁ ለቅዱስ በብኑዳ ሞት ምክንያት የሆነው መነኮስ ታንቆ መሞቱን ሰምተው በጣም አዘኑ። ሱባዔ ገብተው፣ ፍጹም አልቅሰው፣ ከጌታም አማልደው፣ የዛን ኃጥእ ነፍስ ከሲዖል አውጥተዋል።

በሌላ ጊዜ ደግሞ ኃጥአን የሞሉበት አንድ ገዳም በግብጽ ነበርና መቅሰፍት ወርዶ ሁሉንም ባንድ ቀን ሲያጠፋቸው አዩ።

ጻድቁ በዚህም ምክንያት ለ30 ዓመታት አልቅሰው፣ ሙታኑን አስነሥተው፣ ንስሐ ሰጥተው፣ ገዳሙን የጻድቃን፥ ሕይወታቸውንም የፍቅር አድርገውታል።

ጻድቁ #እመቤታችንን ከመውደዳቸው የተነሣ በሥዕሏ ፊት አብዝተው ይሰግዱና ያለቅሱ ነበር። እመ አምላክም ተገልጣ ትባርካቸው ነበር።

ከዚህ በኋላ ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ሒደው ለ57 ዓመታት ማንንም ሳያዩ ተጋደሉ። ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ (ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና) በየቀኑ ይጎበኛቸው፣ ቁጭ ብሎም ያወራቸው ነበር።

በመጨረሻም በዚህች ቀን ጌታ አእላፍ መላእክትን፣ ጻድቃን ሰማዕታትን፣ ድንግል እመቤታችንና ቅዱስ ዳዊትን አስከትሎ ወረደ።

"በስምህም ለድኆችና ለችግረኞች ምጽዋትን ለሚያደርግ ዓይን ያላየውን ጆሮም ያልሰማውን በሰው ልቡናም ያልታሰበውን በጎ ዋጋ እኔ እጥፍ ድርብ አድርጌ እሰጠዋለሁ።" የሚል እና ሌሎች ቃልኪዳኖችን ገባላቸው።

#ቅዱስ_ዳዊት ቀርቦ እያጫወታቸው፣ በበገናው እየደረደረላቸው፣ ከዝማሬው ጣዕም የተነሣ ነፍሳቸው ከሥጋቸው በፍቅር ተለየች። ጌታችንም ታቅፎ፣ ስሞ ይዟቸው አረገ።

ሥጋቸውን #አባ_ባውማ ቀበሩት። የአቡነ ኪሮስ ቁመታቸው ቀጥ ያለ፣ ጽሕማቸውም የተንዠረገገ ነበር።

የአባ ኪሮስ፣ የአባ በብኑዳ፣ የአባ ሲኖዳ፣ የአባ ባውማ፣ የአባ ሚሳኤል በረከት ይደርብን።
#እንኳን_አደረሳችሁ
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA ◈ ኢ/ዓ/ብ)
🇨🇬 ሐምሌ ፰፤ በዓለ እረፍቱ ለብጹዕ ወቅዱስ ባሕታዊ ማር አቡነ ኪሮስ ገዳማዊ፤ እንኳን አደረሳችሁ !
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
A fire broke out inside a factory in Kiryat Shmona, Israel after it was hit by a missile — local media reports
Forwarded from ዮሴፍ ETHIOPIA ◈ ኢ/ዓ/ብ
📌የክቡር አለቃ አያሌው ታምሩ ልዩ ልዩ ታሪካዊ፣ ትንቢታዊ ትምህርቶች
👇👇👇👇👇👇👇👇
👉የአለቃ አያሌውን ትምህርቶች በቀላሉ ለማውረድ(download ) ለመድረግ እነዚህን መስፈንጠሪያወች(links) ይጠቀሙ ፦
    👉ከጎግል ለማወረድ                                                                           📌 https://drive.google.com/drive/folders/1-uDfDVdeouGd8zg9iNnyZHUzOieChIeq?usp=sharing                                                         📌https://drive.google.com/drive/folders/1kQw8ifxKRGaYbdvGSLeO8-Y9AN2cPleI?usp=sharing
👉ከቴሌግራም ለማውረድ፦
📌https://www.tg-me.com/Yetewahedoarbegnoch/1970
📌 https://www.tg-me.com/aleqayalew/2185
#ሌሎች_ያጋሩ!
🟢 🟡 🔴
ሐምሌ 9 || አባታችን አቡነ #እስትንፋሰ_ክርስቶስ በባሕር ውስጥ ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ መጸለይ የጀመሩበት እና ከ9 ዓመታት በኋላ የምሕረት ቃልኪዳን ተቀብለው ከባሕር የወጡበት ቀን ነው።

አምላከ #እስትንፋሰ_ክርስቶስ ይቅርታውን ያድለን።

T.me/Ewnet1Nat
ከሲኦል ነፍሳትን የማውጫ.pdf
328.3 KB
በአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ቃልኪዳን የተገኘ [በአማርኛ]፦

ንስሓ የገባ ኃጢአተኛ ሰው እንኳን ቢሆን ይህችን የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስን ጸሎት በጸለየ ጊዜ ሺህ ነፍሳትን ከሲኦል እንደሚያወጣ ጌታችን በማይታበል ቃሉ ለአባታችን ነግሯቸዋል፡፡
ጸሎተ አቡነ እስትንፋሰክርስቶስ.pdf
675.4 KB
ንስሓ የገባ ኃጢአተኛ ሰው እንኳን ቢሆን ይህችን የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስን ጸሎት በጸለየ ጊዜ ሺህ ነፍሳትን ከሲኦል እንደሚያወጣ ጌታችን በማይታበል ቃሉ ለአባታችን ነግሯቸዋል፡፡
[ በግእዝ ]
በትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ

በድሬዳዋ አሥተዳደር ጀሎ በሊና ቀበሌ ቢርካ አካባቢ ሌሊት 6፡30 ገደማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

ከሟቾች በተጨማሪም በ10 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን ድሬዳዋ አሥተዳደር ፖሊስ መረጃ አመላክቷል፡፡

አደጋው የደረሰው ከድሬዳዋ ወደ ሐረር ሰው አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ በተለምዶ “ዶልፊን” የሚባለው ሕዝብ ማመላለሻ በተቃራኒ መስመር ይጓዝ ከነበረ በተለምዶ “ሲኖትራክ” ተብሎ ከሚጠራው የደረቅ ጭነት ተሸከርካሪ ጋር በመጋጨታቸው መሆኑ ተገልጿል፡፡
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የ9 ሰዎች ህይወት አለፈ

ዛሬ ሐምሌ 10/2016 ጌድኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ሻእሳ በተባለ ቀበሌ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ9 ሰው ህይወት ማለፉን ከስፍራው የደረሰኝ መረጃ ያመለክታል። ቀላልና ከባድ ጉዳት የደረባቸው 4 ሠዎች ለህክምና ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል ሲሉ ምንጮች ጠቁመዋል።
🟢🟡🔴
ሐምሌ 10 | የከበሩ አባቶቻችን፦

🍀 ስምዖን ቀለዮጳ የተባለው #ቅዱስ_ናትናኤል ሐዋርያ ስምዖን ቀለዮጳ በሰማዕትነት ዐረፈ።

ይህንንም ሐዋርያ አይሁድ የጌታችንን ወንድም ያዕቆብን ከገደሉት በኋላ ለኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ አድርገው ሐዋርያት ሾሙት። እርሱም ክብር ይግባውና ስለ ጌታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ አስተምሮ ከአይሁድ ብዙዎችን ጌታችንን ወደማመን መለሳቸው ተአምራትንም አድርጎአልና በሽተኞችንም አድኗልና።

ንጉሡ እንድርያስም ሴቶችን ከባሎቻቸው እንደሚለይ ንጽሕናቸውንም እንዲጠብቁ እንደሚአዝዛቸው ስለ እርሱ ሰማ ወደርሱም አስቀርቦ ጽኑ ሥቃይን አሠቃየው።

ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ ከእርሱም ጋር #ቅድስት_ቴዎና የምትባል አንዲት ድንግል ተገደለች።
🍀

#አቡነ_ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ ልደታቸው ነው።

ጻድቁ እንድርያስና አርሶንያ ከሚባሉ የበቁ ደጋግ አባትና እናታቸው የተወለዱት በሸዋ ሀገረ ስብከት ቀድሞ ጽላልሽ ዛሬ ቡልጋ በሚባለው አውራጃ ነው፡፡

የወላጆቻቸው በጎ ምግባርና ሃይማኖት ቅዱስ ተክለሃይማኖትን ከደብረ ሊባኖስ አነሣስቶ በቤታቸው ሄደው እንዲስተናገዱ አድርጓል።

ልጅ ስላልነበራቸው ያዝኑ ነበርና አቡነ ተክለሃይማኖትም በጸጋ እግዚአብሔር ተገልጾላቸው ‹‹እግዚአብሔር ጣዖታትን የሚሰብር፣ አጋንንትን በጸሎቱ የሚያርቅ፣ ሕዝብን ከኃጢአት በሽታ የሚያድን፣ ፈጣሪውን የሚያስደስት ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ›› ብለው ትንቢት ነግረዋቸዋል፡፡

በትንቢቱም መሠረት አቡነ ሳሙኤል ሐምሌ 10 ቀን 1248 ዓ.ም ሲወለዱ መልካቸው በአራት ልዩ ልዩ ኅብራት ታይተዋል፡፡

አቡነ ተክለሃይማኖትም በ40 ቀን ክርስትና አንስተው ስመ ክርስትናውን ‹‹ሳሙኤል›› አሉት፡፡ ትርጓሜውም ‹‹እግዚአብሔር ጸሎቴን ሰማኝ›› ማለት ነው፡፡
🍀

www.tg-me.com/Ewnet1Nat
🟢🟡🔴
ሐምሌ 12 |
#እግዚአብሔር #ቅዱስ_ሚካኤልን ያጠፋቸው ዘንድ ወደ ሰናክሬም ሠራዊት ላከው።

ይህም እንዲህ ነው፦ ሰናክሬም ኢየሩሳሌምን በከበባት ጊዜ ሕዝቅያስንና ፈጣሪው እግዚአብሔርን እየዘለፈ ወደ ሕዝቅያስ መልእክተኞችን ላከ። እንዲህም አለ፦ "እግዚአብሔር ያድናችኋል እያለ ሕዝቅያስ አያስታችሁ ከእጄ የሚያድናችሁ ማን ነው?"

የይሁዳ ንጉሥ ሕዝቅያስም እጅግ አዘነ። ወገኖቹንና ሀገሩ ኢየሩሳሌምንም ያድን ዘንድ ማቅ ለብሶ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ። እግዚአብሔርም ልመናውን ተቀብሎ ወደ ፋርስ ንጉሥ ወደ ሰናክሬም ሠራዊት የመላእክት አለቃ ሚካኤልን ላከለት።

በዚያችም ሌሊት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ከሰማያት በግርማ ወርዶ የሰናክሬምን 185 ሺውንም የጦር ሠራዊት በአንዲት ሌሊት በእሳት ሰይፉ ፈጅቷቸው አደረ፡፡

በለኪሶ የነበረው ሰናክሬምም በጧት ቢነሣ ሠራዊቱን ሁሉ የአስከሬን ክምር ሆኖ አገኘው፡፡ በታላቅ ድንጋጤ ሆኖ ወደ ነነዌ በመሄድ ወደ ጣዖት ቤቱ ሲገባ የራሱ ልጆች በሰይፍ ገደሉት፡፡

ትዕቢተኛው ሰናክሬምም ለአሕዛብ ሁሉ መዘባበቻ ሆነ፡፡ ቅዱስ ሕዝቅያስ ግን በፈጣሪው ታምኗልና ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም ሞገስና ረዳት ሆኖታልና የዓለም ነገሥታት ሁሉ ፈሩት፣ እጅግ አከበሩትም፡፡

[2ኛ ነገ ምዕ 18 እና 19 ይነበቡ]

ስለዚህም የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ የሚካኤልን በዓል መታሰቢያ በዚች ቀን እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አዘዙ።

                      ◦☘️☘️☘️
#እንኳን_አደረሳችሁ
T.me/Ewnet1Nat
2024/09/27 11:23:57
Back to Top
HTML Embed Code: