Telegram Web Link
እንዴት እንዲያጠፉት
መዝሙረ ዳዊት በ Tlegeram
#_ረቡዕ_ምክረ_አይሁድ
✥••┈•┈•• ✞ ••┈•┈••✥
እንዴት እንዲያጠፉት

እንዴት እንዲያጠፉት ካህናት መከሩ
ያመነቱ ነበር ህዝብን እየፈሩ
ሰይጣን በይሁዳ ገብቶ ነበረና
አሳልፎ እንዲሰጥ ልቡናውም ጸና

ከመቅደስ አዛዦች ከካህናት ጋራ
ስለጌታ መሞት በአንድ ላይ አወራ
ካህናት በደስታ ይሁዳን አቀፉት
አምላኩን እንዲያሲዝ ፴ ብር ሰጡት
#_አ_ዝ_ማ_ች

ህዝብ በሌለበት በአሳቻ ስፍራ
ጌታውን እንዲያሲዝ አደረገ ሴራ
ኧረ እንዴት ጨከነ ይሁዳ አንጀትህ
ጌታህን ያስያዝከው እንደዚያ ሲወድህ
#_አ_ዝ_ማ_ች

በረከቱን በእጅህ ስልጣኑን በራስህ
ሊሰጥህ አስቦ ኢየሱስ ሊያከብርህ
ሰማያዊ ሀብትን ሰማያዊ ጸጋ
አድሎህ ነበረ አልፋና ኦሜጋ
#_አ_ዝ_ማ_ች

የቃየን መስዋዕት የኤሣው ብኩርና
ጌታውን የሚሸጥ ከፍጡር ሆነና
በሠላሳ ዲናር በሚጠፋው ብዕል
እንዲህ ያለ ጌታ ኧረ እንዴት ይከዳል?
✥••┈•┈•• ✞ ••┈•┈••✥
በቻይና አውራ ጎዳና ተደርምሶ የ24 ሰዎች ህይወት አለፈ

በቻይና ጓንግዶንግ ግዛት ለቀናት በጣለው ከባድ ዝናብ በአንድ ተራራ ዳር ላይ የሚገኝ አውራ ጎዳና ተደርምሶ የ24 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡አደጋዉ ረቡዕ እለት በሜይሎንግ የፍጥነት መንገድ ላይ የደረሰ ሲሆን ሌሎች 30 ሰዎች ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።

በቻይና በሕዝብ ብዛት ቀዳሚ በሆነችው ጓንግዶንግ ባለፈው ሳምንት በጎርፍ ምክንያት አራት ሰዎች ሲሞቱ 110 ሺ ሰዎች መፈናቀላቸው ይታወሳል።በጎርፍ አደጋው በደርዘኖች የሚቆጠሩ ቤቶች ወድመዋል፣ ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል፣ የበረራ መሰረዝ እና መጓተት ተከስቷል።በከባድ አውሎ ነፋሱ በጓንግዙ ግዛት ዋና ከተማ የፋብሪካ አውራጃ ላይ ባስከተለዉ አደጋ ደግሞ አምስት ሰዎች ሲሞቱ 33 ሰዎች ቆስለዋል።የጎልፍ ኳሶችን የሚያክል የበረዶ ድንጋይም በከተማዋ ላይ ሲዘንብ ታይቷል።
#የሕማማት_ኀሙስ
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
#_የምሥጢር_ቀን
#_የሐዲስ_ኪዳን_ኀሙስ
#_ሕጽበተ_ወጸሎተ_ኀሙስ

ራስኽን የተወደደ መሥዋዕት አድርገህ የሰጠኸን #_መድኃኔዓለም ሆይ፥ ስለ እናትህ ብለህ ለትንሣኤው ዘመን፥ ለሥጋወደምኽ፥ ለደጀ ሰላምኽ የበቃን አድርገን፨

#_ኪርዬኤሌሶን_እብኖዲ_ናይናን!
#_ተፋቀሩ_አልቅሱ_ጸልዩ ለቤተክርስቲያናችሁ!

▸ አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ | www.tg-me.com/Ewnet1Nat
#ሕጽበተ_እግር_ኀሙስ

"ተራሮችን በኃይሉ የሚያስታጥቃቸው ለማገልገል ማበሻ ጨርቅ ታጠቀ፡፡ የባሕርን ውኃ እንደ አቁማዳ የሚሰበስበው በቀላያትም መዝገቦች የሚሾማቸው ርሱ ከወዳጁ ከአልዓዛር ቤት የውኃ ማድጋ አንሥቶ እግሮችን ለማጠብ ያገለግልባት ዘንድ ወደ  ኩስኩስት አፈሰሰ፡፡

እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን በሚታጠቡበት ገንዘብ የናስ ኩስኩስት ሠርቶ በደብተራ ኦሪት ደጃፍ እንዲያኖራት ሙሴን ያዘዘው ውኃውን በኩስኩስት ሞልቶ የደቀ መዛሙርቱን እግር ሊያጥብ ዠመረ፡፡ የተረከዞቻቸውንም እድፍ በታጠቀው ማበሻ ጨርቅ አሸ፡፡"

— (አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ) —

"በወገቡ የታጠቀውን ማድረቂያ አይተው መላእክት አደነቁ፤ ስሙ ከፀሓይና ከጨረቃ በፊት የነበረ ርሱ አገልጋይ ኾነ! ሕያው ጌታን ሱራፌል ያመሰግኑታል፤ ቦታውን ግን አያውቁም። ሱራፌልን የፈጠረ ርሱ በራት ጊዜ ወገቡን ዘርፍ ባለው ዝናር ታጠቀ፤ እንዳያቃጥል በመፍራት የማይታይ እሳት ለሐዋርያት አገልጋይ ኾኖ አብነት ይኾናቸው ዘንድ የትሕትና ሥራን የሚሠራበትን ውሃ በኩስኩስት ቀዳ የደቀ መዛሙርቱን አለቃ ጴጥሮስንም እግሩን ሊያጥበው ጠራው"

— (ሃይማኖተ አበው ዘያዕቆብ ዘሥሩግ) —
#Kenya

በጎረቤት ኬንያ ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 188 ደርሷል።

ካለፈው መጋቢት ጀምሮ በደረሰው አውዳሚ የጎርፍ መጥለቅለቅ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 188 መድረሱን የሀገር አስተዳደር ሚኒስቴር አሳውቋል።

እስካሁን ያልተገኙ በርካታ ሰዎች መኖራቸውም ተገልጿል።

በኬንያና ሌሎች የምሥራቅ አፍሪካ ሀገሮች በተከታታይ እየጣለ ባለው ከባድ ዝናብ የብዙ ሰዎች ህይወት እየጠፋ ሲሆን የከፍታ ቦታዎች መናድም ነዋሪዎችን ካለመጠጊያ አስቀርቷል፡፡

መንገዶችን ድልድዮችን እና ሌላም የመሰረተ ልማት አውታሮችን ውድሟል።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የዱባይ እጣ ፈንታ የገጠማት ሳውዲ ዐረብያም ትናንት እንዲህ በጎርፍ ተጥለቅልቃለች።
" ልጄ ፡ ሆይ ከዚህ ፡ ካገኘህ ፡ የሞት ፡ ፃዕር ፡ የተነሣ ፡ ግፌን የሚመለከትልኝ ፡ ሹም ፡ ወይም ፡ በሐዘን ፡ የተሰበረውን ፡ ልቤን ፡ አይቶ ፡ በማስተዋል ፡ የሚፈርድልኝ ፡ ዳኛ ፡ አላገኘሁም። "

ላሐ ማርያም [  የማርያም ለቅሶ  ]
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA ◈ ኢ/ዓ/ብ)
Forwarded from ቅድስት በርባራ ዘኒቆመዲያ Saint BarBara Αγία Βαρβάρα (ገድላት እና ስንክሳር)
#በግብረ_ሕማማት ውስጥ የሚገኙ #እንግዳ_ቃላት_እና_ትርጉማቸው

በግብረ ሕማማት ውስጥ ወደ ግእዝም ሆነ በኋላ ወደ አማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የዕብራይስጥ፣ የቅብጥ እና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ፡፡ የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፡፡

#ኪርያላይሶን
ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ "ኪርዬ ኤሌይሶን" ነው፡፡ "ኪርያ" ማለት "እግዝእትነ" ማለት ሲሆን "ኪርዬ" ማለት ደግሞ "እግዚኦ" ማለት ነው፡፡ ሲጠራም "ኪርዬ ኤሌይሶን" መባል አለበት፡፡ ትርጉሙ "አቤቱ ማረን" ማለት ነው፡፡ "ኪርያላይሶን" የምንለው በተለምዶ ነው፡፡ ይኼውም ኪርዬ ከሚለው "ዬ" ኤላይሶን ከሚለው ደግሞ "ኤ" በመሳሳባቸው በአማርኛ "ያ" ን ፈጥረው ነው፡፡

#ናይናን
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "መሐረነ፣ ማረን" ማለት ነው፡፡

#እብኖዲ
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "አምላክ" ማለት ነው፡፡ "እብኖዲ ናይናን" ሲልም "አምላክ ሆይ ማረን" ማለቱ ነው።

#ታኦስ
የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "ጌታ፣ አምላክ" ማለት ነው፡፡ "ታኦስ ናይናን" ማለትም "ጌታ ሆይ ማረን" ማለት ነው፡፡

#ማስያስ
የዕብራይስጥ ቃል ሲሆነ ትርጉሙ "መሲሕ" ማለት ነው፡፡ "ማስያስ ናይናን" ሲልም "መሲሕ ሆይ ማረን" ማለት ነው

#ትስቡጣ
"ዴስፓታ" ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ደግ ገዥ ማለት ነው።

#አምነስቲቲ_ሙኪርያ_አንቲ_ፋሲልያሱ
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም "ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከ- አቤቱ በመንግሥትህ አስበኝ" ማለት ነው፡፡

#አምንስቲቲ_ሙዓግያ_አንቲ_ፋሲልያሱ
የቅብጥ ቃል ሲሆን "ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግሥትከ ቅዱስ ሆይ በመንግሥትህ አስበን" ማለት ነው፡፡

#አምንስቲቲ_ሙዳሱጣ_አንቲ_ፋሲልያሱ
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም "ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግሥትከ የሁሉ የበላይ የሆንክ ሆይ በመንግሥትህ አስበን" ማለት ነው፡፡

▰ ▰ ▰
      ✥ ••┈•┈•• ✞ ••┈•┈•• ✥

#ዘበእንቲአሃ_ለቤተክርስቲያን_ተጸፋእከ በውስተ ዐውድ ከመ ትቀድሳ በደምከ ክቡር ዘበእንቲአሃ ዝግሐታተ መዋቅሕት ፆረ ወተዐገሰ ምራቀ ርኩሰ እንዘ አልቦ ዘአበሰ #አምላክ_ዲበ_ዕፀ_መስቀል_ተሰቅለ

❮ትርጉም❯
#ለቤተክርስቲያን_ብለህ
ልትቀድሳት በደምህ በአደባባይ በጥፊ ተመታህ።

ንጹሕ ክርስቶስ በአዳም ጥፋት ልትወቀስ በከንቱ ልትከሰስ አመላለሱህ ከጲላጦስ ወደ ሄሮድስ ሁሉን ቻይ ሳለህ ምንም ማድረግ ሳይሳንህ በአይሁድ እጅ ተገረፍህ!

ወዮ! ወሰን ለሌላት ትዕግስት ስለኛ ብለህ መከራ ተቀበልህ ምንም በደል ሳይኖርብህ አምላክ በእንጨት መስቀል ላይ ሰቀሉህ።

#ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ
Forwarded from አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ (ዮሴፍ ETHIOPIA ◈ ኢ/ዓ/ብ)
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
«የራስ ቅል የሚሉት ስፍራ !!»
📌የአለቃ አያሌው ታምሩ ድንቅ ትምህርት፡፡
www.tg-me.com/christian930
🌿🌿🌿🌿🌿  ✤ 🌿
✤ ••┈┈•• በመስቀሉ ሰላምን አደረገ ••┈┈•• ✤

#ቀዳሚት_ሥዑር (#ሥዑር_ቅዳሜ)
እግዚአብሔር ሥነ ፈጥረትን ከመፍጠር ዕረፍት እንዳደረገባት ዅሉ፣ የፍጥረት ርእስ የኾነውን አዳምን ለማዳን ሕማምና ሞት የተቀበለው አምላካችን ክርስቶስ በከርሰ መቃብር አርፎባታል፡፡ (ማቴ. ፳፯፥፷፩)፡፡

‹ሥዑር› የተባለችበት ምክንያትም በዓመት አንድ ቀን ስለምትጾም (በሰንበት አይጾምም ግን የጾም ቀን በመኾኗ) "የተሻረች - ሥዑር" ለማለት ነው።

የጌታችን እናት ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ወዳጆቹ ቅዱሳን ሐዋርያትና ሌሌችም የጌታ ወዳጆች ጌታችን ተላልፎ ከተሰጠበት ዕለት ጀምሮ ብርሃነ ትንሣኤውን እስኪያዩ ድረስ፥ አምላካቸው በመቃብር ስላረፈ ዕለቷን ሞቱን በማሰብና ትንሣኤውን በመናፈቅ በጾም አክብረዋታል፡፡

#_ለምን_ቄጠማ_እናስራለን?

ቅዳሜ የጠዋቱ ጸሎት ሲፈጸም ካህናቱ ‹‹ገብረ ሰላመ በመስቀሉ፤ በመስቀሉ ሰላምን አደረገ፥ መሠረተ›› እያሉ በቤተ ክርስቲያን ለተሰበሰቡ ምእመናን የምሥራች ቄጠማ ያድላሉ፡፡

ቄጠማው በኖኅ ዘመን በንፍር ውኃ ምድር በተጠለቀለቀች ጊዜ፤ አባታችን ኖኅ የውኃውን መጉደል ለመረዳት ርግብን ልኮ እርሷም ቄጠማን እንደ የምሥራች ምልክት በአፏ ይዛ በመመለስ፥ የውኃውን መድረቅ እንደተነገረችውና እንደተደሰተ ሁሉ (ዘፍ. ፱፥፩-፳፱) ‹‹በክርስቶስ ሞት፤ ሞተ ነፍስ ከሰው ልጆች ተወገደ፤›› ስንል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቅዳሜ ጠዋት ቄጠማ ታድላለች፡፡

የምሥራች ተምሳሌት የኾነውን ቄጠማም፤ ከሲኦል ቃጠሎ ወደ ጥንተ ማኅደራችን ገነት መመለሳችንን  ለመመስከር በግንባራችን እናስረዋለን፡፡

▸ አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ | www.tg-me.com/Ewnet1Nat
🌿🌿🌿🌿🌿🌿
2024/09/25 18:13:03
Back to Top
HTML Embed Code: