Telegram Web Link
-⚜️⚜️⚜️-
ለተዋሕዶ ኦርቶዶክስ ልጆች በሙሉ፥
◦◦◦
ባንዲራን መቀበል የዜግነት እንጂ የክርስትና አይደለም፣ አረንጓዴ ቢጫ ቀዩ ሰንደቅ አላማችን ሀገራዊ እንጂ መንፈሳዊ ምንጭና ምሥጢር የለውም ለሚሉ የቀረበ መልስ
◦◦◦
የቤ/ክናችን "መምህራን" በተባሉት ግለሰቦች የሚተላለፉ ሐሰት (ማደናገሪያ) የያዙ ትምህርቶችን በቤ/ክ አስተምህሮ መሠረት ለምእመኑ ለማሳወቅ የተዘጋጀ፥
                       °༺ ༒ ༻°
🟢 🟡 🔴
መጋቢት 27 | የነፍስ ዋጋ ተከፍሎ፣ ዓለም ኹሉ የዳነበት #_የመድኃኔዓለም የስቅለቱ በዓል ነው።

⓷ በዚህች ዕለት ክፉዎች አይሁድ ከምሽቱ 3:00 ጌቴሴማኒ ውስጥ ያዙት።

ሙሉውን ሌሊት ከቀያፋ ወደ ሐና: ከሐና ወደ ቀያፋ ሲያመላልሱት፣ አስረው ሲደበድቡት አደሩ።

ዝም ቢላቸው ዓይኑን ሸፍነው በጥፊ መቱት። ምራቃቸውን ተፉበት፤ ዘበቱበት፤ ራሱንም በዘንግ መቱት። እርሱ ግን ሁሉን ታገሰ።

❮❸ ሰዓት በጧት❯ ከገዢው ዘንድ ሞት እንዲፈረድበት አቀረቡት። በሠለስት (ሦስት ሰዓት ላይ) አካሉ እስኪያልቅ እየተዘባበቱ 6,666 ገረፉት።

ሊቶስጥሮስ አደባባይ ላይ እርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት።

❮❻ ስድስት ሰዓት ላይ❯ በረዣዥም ብረቶች አምስት ቦታ ላይ ቸንክረው ሰቀሉት። ሰባት ታላላቅ ተአምራት በምድርና በሰማይ ታዩ። ዓለም በጨለማ ሳለች ጌታ በመስቀል ላይ ሰባት ቃላትን ተናገረ።

❮➒ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ❯ በባሕርይ ሥልጣኑ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ። በዚያች ሰዓትም ወደ ሲዖል ወርዶ የታሠሩትን ሁሉ ፈታ።

❮⓫ አሥራ አንድ ሰዓት ላይ❯ ደጋጉ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብርና ሐዘን ጋር በአዲስ መቃብር ቀበሩት።

በዚያች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በሐዘን ተቃጠለ። ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍጹም ለቅሶን አለቀሰ። ቅዱሳት አንስት በዋይታ ዋሉ። [ማቴ 27:1፣ ማር 15:1፣ ሉቃ 23:1፣ ዮሐ 19:1]
~ ~

ለእኛ ለኀጥአን ፍጡሮቹ ሲል ይህንን ሁሉ መከራ የታገሰ አምላክ ስለ አሥራ ሦስቱ ሕማማቱ፣ አምስቱ ቅንዋቱ፣ ስለ ቅዱስ መስቀሉ፣ ስለ ድንግል እናቱ ለቅሶና ስለ ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስ ብሎ ይማረን።
~ ~

ትሑታን፣ የዋሃን ክርስቲያኖች፣ የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች እንኳን አደረሳችሁ፨
www.tg-me.com/Ewnet1Nat
#_ቃሉ
❮ትንቢተ ዘካርያስ ፲፫፥ ፮-፱❯

⁶ ሰውም፦ ይህ በእጅኽ መካከል ያለ ቍስል ምንድር ነው፧ ይለዋል። እርሱም፦ በወዳጆቼ ቤት የቈሰልኹት ቍስል ነው ይላል።

ሰይፍ ሆይ፥ ባልንጀራዬ በኾነው ሰው በእረኛዬ ላይ ንቃ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። እረኛውን ምታ፥ በጎቹም ይበተናሉ፤ እጄንም በታናናሾች ላይ እመልሳለኹ።

⁸ በምድርም ዅሉ ላይ ኹለት ክፍል ተቈርጠው ይሞታሉ፥ ይላል እግዚአብሔር። ሦስተኛውም ክፍል በርሷ ውስጥ ይቀራል።

#_ሦስተኛውንም_ክፍል ወደ እሳት አገባለኹ፥ ብርም እንደሚነጥር አነጥራቸዋለኹ፥ ወርቅም እንደሚፈተን እፈትናቸዋለኹ።

እነርሱም ስሜን ይጠራሉ፥
እኔም እሰማቸዋለኹ።

እኔም፦ ይህ #ሕዝቤ_ነው እላለኹ።
እርሱም፦ እግዚአብሔር አምላኬ ነው ይላል።
◦✥◦  ◦✥◦  ◦✥◦
http://www.tg-me.com/Ewnet1Nat
                 ◦✥◦  ◦✥◦  ◦✥◦
<< መጋቢት 28 | ጥንተ ቀዳም ስዑር >>

. . . ዘውኅዘ እምአዕይንትኪ ከመ ማየ ክረምት ዘይፈለፍል፥
ድንግል ድንግል ወላዲተ አምላክ ቃል፥
ቤዛ ይኩነኒ ማየ አንብዕኪ እምኃጉል።


❴ትርጉም❵
(. . . የቃለ አብ እናቱ ድንግል እመቤቴ ሆይ! . . . ከዓይኖችሽ እንደ ክረምት ውሃ ምንጭ የፈሰሰው እንባሽ . . . ለእኔ ለባሪያሽ ከጥፋት የምድንበት ቤዛ ይሁነኝ !!)
◦◆◦
⚜️⚜️⚜️
ስለ #_በዓለ_እግዚአብሔር
ስለ #_በዓለ_ወልድ
⚜️⚜️⚜️

«...በእየወሩ...፳፱ኛው ቀን ደግሞ ጌታ የተፀነሰበት የተወለደበት ቀን ስለሆነ የጌታ የፅንሱ የልደቱ መታሰቢያ እንዲሆን ተወሰነይህም ከ፩፼ (ከ አንድ ሺ) ዓመት በኋላ ነው እንዲህ አይነቱ ነገር የተመሠረተው። ....

ከዚህ ፳፱ኛው ቀን ግን በስያሜው ምክንያት ስሙ ተለውጦ ነው የሚታየው።
#_በዓለ_እግዚአብሔር_ነው የሚባል።

#_በዓለ_እግዚአብሔር

(#1) በመጀመሪያ አምላክ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ሰው በመኾን በድንግል ማሕፀን ያደረበት፥ የፅንስ ሥርዓትን የፈጸመበት፣

(#2) ፪ኛ ማኅተመ ድንግልናዋን ሳይከፍት እንደተፀነሰ ማኅተመ ድንግልናዋን ሳይከፍት የተወለደበት በመሆኑ #_በዓለ_እግዚአብሔር የእግዚአብሔር በዓል እየተባለ ይጠራል።

ዛሬ ግን ሕዝቡ
#_በዓለ_እግዚአብሔር የሚለውን እንደ ስም ነው የወሰደው። እንደ አንድ ሰው ስም እንጂ የዕለቱ ስያሜ አድርጎ አይደለም የሚጠራው። በዓለ እግዚአብሔር ብሎ አንድ ስም ነው የሚያደርገው።

ኢየሱስ ማለትና በዓለ እግዚአብሔር ማለት፣ ክርስቶስ ማለትና በዓለ እግዚአብሔር ማለት፣ መድኃኔዓለም ማለትና በዓለ እግዚአብሔር ማለት፥ ኹሉም ራሳቸውን የቻሉ መጠሪያ ናቸው ብሎ ነው የሚያምን።
#_በዓለ_እግዚአብሔር የተባለው #_የኢየሱስ_በዓል_ነውቢሉት የሚቀበል የለም ዛሬ።

እዚህ ላይ ችግር አለ። መምህራኑ አንዱን እናስለምዳለን ሲሉ በሌላ በኩል የጎደለ ነገር አለ ማለት ነው። ይህንን አስተካክሎ ማስተማር ያስፈልጋል። "ስለ ቅዱስ በዓለ እግዚአብሔር" ነው የሚል። አንድ አንዱ አንድ ስም አድርጎት "ባለወልድ" ይላል። አንዳንዱ "ባለ እግዚአብሔር" ይላል።

በመሠረቱ ግን እንዳልኳችሁ "
#_በዓለ_እግዚአብሔር " የተባለው የተፀነሰበትን የተወለደበትን ድርብ ምሥጢር ለማስታወስ የተነገረ ነው።

ከልምዱ የተነሣ ታዲያ ሰው ቀኑን ነው እንደዚያ አድርጎ የሚጠራው። ፳፯ ቀንን መድኃኔዓለም ይላል ዝም ብሎ። ክርስቶስ ነው ወይ ቢሉት ይቃወማል። እንዲያውም "፮ኛው ቀን ኢየሱስ ነው" የሚል የቀረው የእርሱ አይደለም ማለት ነው።

ይህንን ከብዛቱ ከቀን ብዛት አንድ አንዱ ነገር ከትምህርትነት ወደባህልነት ይለወጣልና ይህ
ንን ጠንቅቆ ማስተማር ያስፈልጋል ።...»

▰ ▰ ▰
📌
ታላቁ ሰማዕት ዘእንበለ ደም ሊቀ ሊቃውንት አለቃ አያሌው ታምሩ ዘደብረ ድማኅ፥ግንቦት ፳፩ ቀን ፲፱፻፺፮ ዓ.ም የእመቤታችን በዓላት በሚል ካስተማሩት የተወሰደ።

www.tg-me.com/Ewnet1Nat  🇨🇬
http://www.tg-me.com/AlphaOmega930  🇨🇬
. ▰ ⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️
መጋቢት 29 | የበዓላት ኹሉ ራስ
(በዓለ እግዚአብሔር )
━━━━ ✦ ━━━━ ✦ ━━━━ ✦ ━━━━
ይህች ቀን ለቤተ ክርስቲያን በእጅጉ ልዩ ናት። በዓመቱ ከሚከበሩ በዓላትም አንደኛውን ሥፍራ ትይዛለች።

በዚህች ዕለት አምላካችን እግዚአብሔር፦

1. ሰማይና ምድርን ፈጠረ። [ዘፍ. 1፥1]
#_ጥንተ_ዕለተ_ፍጥረት

2. በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት በድንግል ማርያም ማኅፀን አደረ (ተጸነሰ)። በዓሉም "በዓለ ትስብእት" ይባላል። "አምላክ ሰው ፥ ሰው አምላክ የሆነበት" ማለት ነው። [ሉቃ. 1፥26]
#_በዓለ_ጽንሰት

3. የክብር ባለቤት መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ ተነሣ። [ማቴ. 28፥1፣ ማር. 16፥1፣ ሉቃ. 24፥1፣ ዮሐ. 20፥1]
#_በዓለ_ጥንተ_ዕለተ_ትንሣኤ

4. ጌታችን ዳግመኛ ለፍርድ በዚህች ቀን ይመጣል። [ማቴ. 24፥1]
#_ዕለተ_ዳግም_ምጽአት

በእነዚህ ታላላቅና ድርብርብ በዓላት ምክንያት ቀኑ "ርዕሰ በዓላት" (የበዓላት ራስ)፣ "በኩረ በዓላት" እየተባለም ይጠራል።

ቸሩ እግዚአብሔር ዓለምን ከመፍጠሩ፣ ከጽንሰቱ፣ ከልደቱና ከትንሣኤው በረከትን ይክፈለን። በጌትነቱም ሲመጣ በርኅራኄው ያስበን።

•๏• •๏• •๏• •๏• •๏• •๏• •๏• •๏• •๏•

ትሑታን፣ የዋሃን ክርስቲያኖች፣ የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች እንኳን አደረሳችሁ፨
www.tg-me.com/Ewnet1Nat
🟩 🟨 🟥
ሰንደቃችን

❝ ወደፊትም በትንሣኤው ዘመን የምትነግሠው ይኽችው ሰንደቃችን ናት!

🇨🇬 ምድርንም የምትሸፍነው፣ የምትውለበለበውም ይኽችው ሰንደቅ ናት!

🇨🇬 የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት መለያ ሰንደቁም ይኸው ነው!

🇨🇬 የትንሣኤው ዘመን ሙሽሮችም መለያቸው ሰንደቃቸው ይኸው
#አረንጓዴ_ቢጫ_ቀዩ ባንዲራ ነው! ❞

— የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መግለጫ፥ ፳፻፲፩ ዓ/ም፥ 2 ሰዓት 34 ደቂቃ ከ56 ሰከንድ እስከ 2 ሰዓት 35 ደቂቃ 36 ሰከንድ

www.tg-me.com/Ewnet1Nat  🇨🇬
http://www.tg-me.com/AlphaOmega930  🇨🇬
2024/09/27 09:23:13
Back to Top
HTML Embed Code: