Telegram Web Link
🟢🟡🔴
መስከረም 7 | የተዋሕዶ እምነት አርበኛ #ቅዱስ_ዲዮስቆሮስ ሊቀ ጳጳሳት ዐረፈ።

ስለ ቀናች ሃይማኖትም ታላቅ ተጋድሎን ከተጋደለ በኋላ ዕረፍቱ በተሰደደበት በደሴተ ጋግራ ሆነ።
አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ
🟢🟡🔴 መስከረም 7 | የተዋሕዶ እምነት አርበኛ #ቅዱስ_ዲዮስቆሮስ ሊቀ ጳጳሳት ዐረፈ። ስለ ቀናች ሃይማኖትም ታላቅ ተጋድሎን ከተጋደለ በኋላ ዕረፍቱ በተሰደደበት በደሴተ ጋግራ ሆነ።
ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ሊቅ የተዋሕዶ ሃይማኖታችን ምሰሶ ነው። በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን በግብጽ ተወልዶ አድጎ፣ በልጅነቱ መጻሕፍትን ተምሮ፣ የምናኔ ሕይወትን መርጧል።

ቆይቶም የታላቁ ሊቅ ቅዱስ ቄርሎስ ረድእ ሆኖ ተምሯል አገልግሎታል።

በጉባኤ ኤፌሶን ጊዜም ቅዱስ ቄርሎስን ተከትሎ ሒዶ ተሳትፏል። በ444 ዓ/ም ታላቁን ሊቅ ተክቶ የእስክንድርያ 25ኛ ፓትርያርክ ሆኖ ተሹሟል።

ለ7 ዓመታትም መጽሐፈ ቅዳሴውን (እምቅድመ ዓለምን) ጨምሮ ብዙ ድርሰቶችን ደርሷል። በመልካም እረኝነትም ሕዝቡን ጠብቋል።

ዘመነ ሰማዕታትን ተከትሎ የመጣው የመናፍቃን ዘመን ሲሆን ለ150 ዓመታት ያህል መናፍቃን እንደ አሸን ፈልተዋል።

በዚያው ልክ ከዋክብት ቅዱሳን ሊቃውንት ነበሩና በየጊዜው ጉባኤያትን እየሠሩ፣ መናፍቃንን አሳፍረዋል። ምዕመናንንም አጽንተዋል።

በ451 ዓ/ም የተፈጸመው ድርጊት ግን ዛሬም ድረስ ጠባሳው የሚለቅ አልሆነም። ንጉሡ መርቅያንና ጳጳሱ ልዮን የንስጥሮስን ትምህርት አለባብሰው ሊያስተምሩ ጀመሩ። ጉባኤም ጠሩ።

ቅዱስ ዲዮስቆሮስም ሲሰማ እንዲህም አለ፦ "ይህ ታላቅ ጉባኤ እስቲሰበሰብ ድረስ በሃይማኖት ላይ የተገኘው ጉድለት ምንድን ነው?"

ይህ ጉባኤ የተሰበሰበው በንጉሥ ትእዛዝ ነው አሉት።

እንዲህም አላቸው፦ "ይህ ጉባኤ ስለ ክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቢሆን ኖሮ እኔ ተቀምጬ እግዚአብሔር በሰጠኝ በአንደበቴ እናገር ነበር። ግን የዚህ ጉባኤ መሰብሰብ በንጉሥ ትእዛዝ ከሆነ የሰበሰበውን ጉባኤ ንጉሡ እንዳሻው ይምራ።"

ከዚህም በኋላ አንዱን ክርስቶስን (ክብር ይግባውና) ከተዋሕዶ በኋላ 'ሁለት ባሕርይ ሁለት ምክር' የሚያደርግ (የካቶሊክ) የክህደት ቃል በውስጡ የተጻፈበትን የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ልዮን የላከውን ደብዳቤ የከበረና የተመሰገነ ዲዮስቆሮስ ቀደደ።

በመንፈስ ቅዱስ የሚናገር የከበረ ዲዮስቆሮስም በጉባኤው ፊት እንዲህ ብሎ አስረዳ፦

"ሰው እንደመሆኑ ወደ ሠርግ ቤት የጠሩት ጌታችን ክርስቶስ አምላክ እንደመሆኑ ውኃውን ለውጦ ወይን ያደረገው ከሀሊ ስለሆነ ሰውነቱና መለኮቱ በሥራው ሁሉ የማይለይ አንድ ነው።"

ቅዱስ ዲዮስቆሮስንም ወደ ንጉሥ አቀረቡት። ከእርሱም ጋር ታላላቅ ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስቆጶሳት ከጉባኤው የሆኑ ነበሩ። ከጠዋትም እስከማታ እርስበርሳቸው ሲከራከሩ ዋሉ።

የከበረ ዲዮስቆሮስም የቀናች ሃይማኖቱን አልለወጠም። ንጉሡና ንግሥቲቱ በእርሱ ተቆጥተው እንዲደበድቡት አዘዙ። ስለዚህም ደበደቡት ጽሕሙን ነጩ፤ ጥርሶቹንም ሰበሩ።

ከዚህም በኋላ የተነጨውን ጽሕሙን ያወለቁትንም ጥርሱን ሰብስቦ ወደ እስክንድርያ አገር ላካቸው። እነሆ የቀናች ሃይማኖት ፍሬ ይህ ነው አላቸው።

ለጉባኤውም የተሰበሰቡ ኤጲስቆጶሳት በዲዮስቆሮስ ላይ የደረሰውን መከራ በአዩ ጊዜ እጅግ ፈሩ። በእርሱ የደረሰ በእነርሱ ላይ እንዳይደርስ ስለዚህም ከመናፍቁ ንጉሥ ከመርቅያኖስ ጋር ተስማሙ።

በጉባኤው የነበሩ 636 ጳጳሳት (የጉባኤ ኒቂያ 318 አባቶች እጥፍ) ስቃይና ሞትን ፈርተው በኑፋቄ መጽሐፍ ላይ በመፈረማቸው "መለካውያን" (ከእግዚአብሔር ይልቅ ለንጉሥ የሚታዘዙ) ተባሉ።

ጉባኤውም "ጉባኤ ከለባት" (የውሾች ስብሰባ): "ጉባኤ አብዳን" (የሰነፎች ጉባኤ) ተብሏል።

በሲኦል ውስጥ ይቆረጡት ዘንድ ባለው ምላሳቸውም (ክብር ይግባውና) "ለክርስቶስ ሁለት የተለያዩ  ባሕርያት አሉት" ብለው በንጉሡ መዝገብ ላይ በእጆቻቸው ጽፈው ፈረሙ።

ቅዱስ ዲዮስቆሮስም ተመልሶ ያን በውስጡ የጻፉበትን ደብዳቤ ያመጡለት ዘንድ ወደእሳቸው ላከ። እነርሱም ላኩለት። እነርሱ እንደጻፉ በውስጡ እርሱ የሚጽፍ መስሏቸዋልና።

እርሱ ግን፦ አባቶቻችን ሐዋርያት ከአስተማሯት ከቀናች ሃይማኖት፣ በኒቅያ የተሰበሰቡ ሃይማኖታቸው የቀና ሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት ኤጲስቆጶሳት አባቶቻችን ከሠሩት ሕግ የሚወጣውን ሁሉ በደብዳቤው ግርጌ ጽፎ አወገዘ።

በዚህ ምክንያት ወደ ጋግራ ደሴት ከ7 ደቀ መዛሙርቱ ጋር አሳደዱት። በዚያም ለ3 ዓመታት ቆይቶ በ454 ዓ/ም ዐረፈ።

ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ከማረፉ በፊት በተሰደደባት ደሴተ ጋግራ ለ3 ዓመታት ብዙ መከራ ከመናፍቃን ደርሶበታል። እርሱ ግን በትዕግሥቱና በትምህርቱ ብዙዎችን ወደ ሃይማኖት መልሷል።

የአባታችን ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ጽናትና በረከት ይደርብን።

🌼 www.tg-me.com/Ewnet1Nat 🌼
በረዶ ቀላቅሎ የጣለ ከባድ ዝናብ በ161 ነጥብ 5 ሄ/ር መሬት የደረሱ ሰብሎች ላይ ጉዳት አደረሰ

በዋግ ኽምራ ብሔረ-ሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ከተማ 04 ቀበሌ መስከረም 5/2017 ዓ.ም በረዶ ቀላቅሎ የጣለው ከባድ ዝናብ በ161 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት የ140 አርሶ አደሮች የደረሰ ሰብል ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደረሰ።

በሰቆጣ ከተማ አስተዳደር 04 ቀበሌ የተለላ ጎጥ አርሶ አደር ነዋሪ የሆኑት አቶ በላይ አለሙ መስከረም 5/2017 ዓ/ም ከምሽቱ 2፡30 ሰዓት አካባቢ በረዶ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ ከ6 ጥማድ በላይ በሚሆኑ የደረሱ ሰብሎች ላይ ከፍተኛ ጉዳተ አድርሶብናል ብለዋል።

የማዳበሪያ ግብአት እና ምርጥ ዘር ተጠቅመን ማሳችን በዘር በመሸፈን ከራሳችን አልፎ ለገበያ የሚተርፍ በቂ ምርት የምናገኝበት ወቅት ነበር ያሉት አቶ በላይ ባልታሰበ ሁኔታ በረዶ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ ፋታችንና ተስፋችን ከንቱ አስቆርቶታል ሲሉ ገልጸዋል።

ከዚህ በፊት 26 ኬሻ ጭነት ገብስ እና 13 ኬሻ ጭነት ጤፍ የሚያገኙበት የገብስና የጤፍ ማሳ እንዲሁም የአተርና የባቄላ ማሳ ከጥቅም ውጭ ሆኗል።
🇨🇲 በካሜሩን ከ230,000 በላይ ሰዎች ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ የጎርፍ አደጋ መጎዳታቸውን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል

💦 የሰሜን የሀገሪቱ ክፍል ታይቶ የማይታወቅ ከባድ ጎርፍ ለበርካታ ሳምንታት ተመቷል።

🌊 ከቻድ ድንበር አቅራቢያ የምትገኘው የያጉዋ ከተማ የከፋ ጉዳት ከደረሰባቸው አካባቢዎች አንዷ ስትሆን ሰፈሮቹ በውሃ ተውጠው ወደ 200 የሚጠጉ ትምህርት ቤቶች ተጎድተዋል፤ የ12 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል፣እንዲሁም ከአንድ ሺህ በላይ የቤት እንስሳት መሞታቸው ታውቋል።

ከ18,000 በላይ ቤቶች ወድመዋል። ተጎጂዎቹ በከተማ ዳርቻው በሚገኝ ካምፕ ውስጥ እንዲቆዩ ተደርጓል።

➡️ መንግስት ለተጎዱ ወገኖች የሚውል 350 ሚሊዮን ሲኤፍኤ ፍራንክ (በግምት 590,000 ዶላር) መድቧል።

ምስሎች ከማህበራዊ አውታረመረቦች የተገኙ ናቸው
🇳🇬በሰሜን ምዕራብ ናይጄሪያ በደረሰ አሰቃቂ የጀልባ አደጋ ከ40 በላይ ሰዎች ሞቱ

በዛምፋራ ግዛት ገበሬዎች ወደ እርሻ መሬታቸውን ለመድረስ ሲሞክሩ ነው ይህ አሳዛኝ ክስተት የተከሰተው። ፕሬዝዳንት ቦላ ቲኒዩ በሰጡት መግለጫ ለተጎዱ ቤተሰቦች ድጋፍ እንደሚደርግላቸው ገልጸው፤ የአደጋ ጊዜ ኤጀንሲዎች ጉዳዩን በጥልቀት እንዲመረምሩ ትእዛዝ ሰጥተዋል።

የዛምፋራ ፖሊስ ቃል አቀባይ ያዚድ አቡበከር ለምዕራቡ ዓለም መገናኛ ብዙሃን እንደገለፁት አምስት ግለሰቦችን ከሞት ሲታደጉ 40 ሰዎች ግን የደረሱበት አለመታወቁን አክለዋል። በአደጋው ​​ወቅት በጀልባው ላይ የነበሩት ተሳፋሪዎች አጠቃላይ ቁጥር እስካሁን አልታወቀም።

ጀልባው በዋነኝነት የሚያጓጉዘው ገበሬዎችን ሲሆን ገበሬዎቹ ምርቶቻቸው ለገበያ የሚያቀርቡበት መስመር ነው ። የአካባቢው ነዋሪዎች ጀልባዎቹ ብዙ ጊዜ ከአቅማቸው በላይ እንደሚጫኑ ይገልጻሉ።
❗️ ዩክሬን ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ  1,960 የሚጠጉ ወታደሮቿን ማጣቷን  የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።

በዩክሬን እየተካሄደ ያለውን ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ አስመልክቶ በሚኒስቴሩ ዕለታዊ መግለጫ የተነሱ ሌሎች ቁልፍ ነጥቦች፡-

   የሩስያ አየር መከላከያ ሥርዓት አንድ ሂማርስ ሚሳኤል እና 36 የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትተው ጥለዋል።

   የሩሲያ ጦር የዩክሬን መከላከያ ኢንተርፕራይዞች መሆናቸውን ካረጋገጠ በኋላ የሃይል ተቋማትን መትቷል።
🔔ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግስት ደብዳቤ ገጽ 8   ፦ ጥር 7 / 2012 ዓ፡ም የተጻፈ፡፡
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
❗️Over 1,000 wounded in Lebanon explosions — Reuters
Audio
መልክአ ቅድስት ሐና የቅድስት ድንግል ማርያም እናት.
Audio
መልክአ ቅድስት ሥላሴ
Audio
በእንተ ሥላሴከ
Audio
መልክአ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ .
📌 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክን የሊቃውንት ጉባኤ ተቀዳሚ ዋና ሰብሳቢ የነበሩት ሊቁ አባታችን አለቃ አያሌው ታምሩ (ሰማዕት ዘእንበለደም) ላይ የተለያየ ያልተገባ ነቀፌታና በተሳሳተ ወሬ "ክህነት አልነበራቸውም፤ አይነስውር ስለነበሩ ክህነት የላቸውም ፤ በምን ስልጣናቸው ነው አጥፊውን የሚያወግዙ.... ወዘተ" እያሉ ያለምንም መረጃና ማስረጃ ሕዝቡን ለሚያደነቁሩ ደናቁርት ይህችን ደብዳቤ ደጋግመው እንዲያነቡ ይመከራሉ !!
Audio
የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መግለጫ
08-01-2017ዓ.ም

ክፍል ሀ
Audio
የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መግለጫ
08-01-2017 ዓ.ም

ክፍል ለ
2024/09/23 12:10:38
Back to Top
HTML Embed Code: