Telegram Web Link
አሁን..!

አሁን በኦሮሚያ ክልል ከገብረ ጉራቻ እና ቱሉ ሚልኪ መሀከል አንድ የህዝብ አውቶብስ ሙሉ ተሳፋሪ ከሾፌር ረዳት ጋር በታጠቁ ሀይሎች ታፍነው ተወስደዋል!
» መሪዎች ይጮሃሉ የሚሰማቸውም ያጣሉ ያደራጁት የጸጥታና የጦር ኃይል አይታዘዝም የመዳከም የመበተንም እጣ ይገጥማቸዋል። ሕዝቦች ለማንኛውም የመንግሥት ኃይል አይታዘዙም አይፈሩምም ሕግ የተባለ ሁሉ የሚያከብረው ያጣል።

» ሰላም ስሙ እንጂ ምግባሩና ምልክቱ ፈጽሞ ይጠፋል።

ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት 3 ገጽ 58 (የፖለቲካ ቀውስ) ተጻፈ መጋቢት 19/2001 ዓ.ም

አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ
🟢🟡🔴
ነሐሴ 24 | ጻድቁ #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት#ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ፣ ክቡር #አባ_ቶማስ የዕረፍት በዓላቸው ነው።

#አባ_ተክለ_ሃይማኖት ከመድኃኔዓለም የተቀበሉት ቃልኪዳን

-☘️- እነሆ ስምህን ለሚጠራ መታሰቢያህን ለሚያደርግ ገድልህን ለሚጽፍ ለሚያነበውና ለሚሰማውም ቤተ ክርስቲያንህን ለሚሠራ በስምህ መብዓ ለሚሠጥ ለድኆችም በስምህ ለሚመጸውት በመታሰቢያህም ቀን ለሚቆርብ ስለ አንተ በጎ ሥራ ለሚሠራ ሁሉ እኔ እስከ ዐሥር ትውልድ እምርልሃለሁ"።

አባታችንም እጅግ ደስ አለው ለጌታችንም ሰገደ። ጌታችንም ከእርሱ ዘንድ በታላቅ ክብር ወደ ሰማያት ዐረገ።

ከዚህም በኋላ አባታችን በንዳድ በሽታ ታመመ። ዕድሜውም ዘጠና ዘጠኝ ዓመት ከስምንት ወር ከአንድ ቀን ሆኖት በለመለመ ዕርጅና ነሐሴ 24 ቀን ዐረፈ።

#ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ ከመድኃኔዓለም የተቀበለችው ቃልኪዳን፦

-🍀- በችግሩ ወይም በጭንቁ ጊዜ በመታመን ስምሽን ቢጠራ እኔ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ አድነዋለሁ።

-🍀- የገድልሽን ዜና የሚናገረውን መጽሐፍ የጻፈ ወይም ያጻፈ እኔ ስማቸውን በሕይወት መጽሐፍ እጽፍላቸዋለሁ። ቤተ ክርስቲያንሽን የሠራ ወይም ያሠራ ያሣነፀ ወይም ያነፀ እኔ በመንግሥተ ሰማያት ንጹሕ አዳራሽ አዘጋጅለታለሁ። በስምሽ ለተራበ ያበላ እኔ በዕለተ አርብ ከተቆረሰው ሥጋየ አበላዋለሁ። በስምሽ ለተጠማው እፍኝ ውሃ ያጠጣ እኔ በዕለተ አርብ ከጎኔ በሰሰው ደሜ አረካዋለሁ።

🍀 ሥጋሽ ከተቀበረበት ሄዶ መካነ መቃብርሽን የተሳለመ የእናቴን የማርያምን መካነ መቃብር እንደተሣለመ ይቆጠርልታል።

#ቅዱስ_አባ_ቶማስ
🌿 ከልጅነቱ ቅዱሳት መጻሕፍትን የተማረ፣

🌿 ገና በወጣትነቱ መንኖ ገዳም የኖረ፣

🌿 መርዓስ በምትባል ሃገር ጵጵስና ተሹሞ በእረኝነት ያገለገለ፣

🌿 በሐዋርያዊ አገልግሎት ብዙ አሕዛብን ወደ ክርስትና የመለሰ

🌿 በዘመነ ሰማዕታት ብዙ መከራን የተቀበለ አባት ነው።

ጨካኞቹ ቅዱሱን ለ22 ዓመታት አካሉን እየቆራረጡ ለጣዖታቸው ያጥኑ ስለ ነበር 2 እግሮቹ፣ 2 እጆቹ፣ 2 ጀሮዎቹ፣ 2 አፍንጫዎቹ፣ 2 ዐይኖቹ፣ ሁሉ አልነበሩም። ነገር ግን እንዲህም ሆኖ አልሞተም ነበር።

◈ በመጨረሻም በዘመነ መና- ፍቃን አርዮስን ካወገዙት 318ቱ ሊቃውንት እንዳንዱ ተቆጥሯል። ቅዱስ ቶማስ ጵጵስና በተሾመ በ40 ዓመቱ በዚህች ቀን ዐርፏል።


የጻድቃንን፣ የሰማዕታትን፣ የሐዋርያትንና ሊቃውንትን አክሊልም ተቀብሏል።

የአቡነ ዘርዐ ቡሩክ የአክስት ልጅ የሆኑት #አቡነ_ጊዮርጊስ_ዘግሽ ዕረፍታቸው ነው።

የተፀነሱትም ሆነ የተወለዱት በመልአክ ብሥራት ነው፡፡

ሰማዕትነት ለመቀበል ወደ ፋርስ በመሄድ ለ9 ሺህ ሰማዕታት መሪ ሆነው ጣዖትን ካጠፉ በኋላ በሰይፍ ተሰይፈው ሰማዕት የሆኑ ታላቅ አባት ናቸው።

                 #እንኳን_አደረሳችሁ
                  T.me/Ewnet1Nat
አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ
Photo
‹‹የጥቁሩን አህያ ራስ ነጩ እህያ ላይ፣ የነጩን አህያ ራስ ጥቁሩ አህያ ላይ››

አቡነ ቶማስ የመርዓስ ሀገር ኤጲስ ቆጶስ ሲሆኑ ታላቅ ሰማዕትነትን የተቀበሉ ሃይማኖት ምግባራቸው እጅግ የቀና ታላቅ አባት ናቸው።

ከሃዲው ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ ጊዜ ክርስቲያኖቹን ሲያሠቃዩ በነበረበት ወቅት ከንጉሡ መኳንንት አንዱ ወደ መርዓስ ሄዶ አቡነ ቶማስን በጭፍሮቹ አሲያዛቸው።

አባታችንን እንደያዟቸው ደብድበው በምድር ላይ እየጎተቱዋቸው ደማቸው እየፈሰሰ ወሰዷቸው።

መኰንኑ ‹‹ለአማልክት ስገድ›› አላቸው። አቡነ ቶማስም ‹‹ከእግዚአብሔር በቀር የሚሰግዱለት አምላክ የለም›› አሉት።

መኰንኑም እጅግ የበዙ ጽኑ ሥቃዮችን አሠቃያቸው። የነዳጅ ድፍድፍ አፍልተው በሰውነታቸው ላይ እንዲሁም በአፍና በአፍንጫቸው ጨመሩባቸው። ቶሎ ብለው እንዲሞቱ ሳይሆን በሥቃይ ሆነው እንዲቆዩ በማድረግ ለ22 ዓመታት በጨለማ ውስጥ እያሰሩ አሠቃዩአቸው።

ከሃዲያኑም በየዓመቱ ወደ እስር ቤቱ እየገቡ አንድ አካላቸውን ይቆርጣሉ፡፡ እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን በየተራ ቆራረጧቸው፡፡ አፍንጫቸውን፣ ከንፈሮቻቸውን፣ ጆሮዎቻቸውን ሁሉ በየተራ እየቆረጡ ለ22 ዓመታት ጣዖታቸውን ሲያጥኑበት ኖረዋል፡፡

አንዲት ደግ ክርስቲያን ሴት ግን የተጣሉበትን ጉድጓድ አይታ ስለነበር በድብቅ ሌሊት እየሄደች ትመግባቸው ነበር፡፡

ደገኛውና ጻድቁ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ በነገሠ ጊዜ ይህች ሴት ሄዳ ስለ አቡነ ቶማስ ነግረችውና አባታችንን ከተጣሉበት ጉድጉድ አወጣቸው፡፡

ቆስጠንጢኖስ የከበሩ 318 ኤጲስ ቆጶሳትን በኒቅያ አገር እንዲሰበሰቡ ሲያደርግ አንዱ አቡነ ቶማስ ነበሩ፡፡ ወደ ጉባዔውም ሲሄዱ ደቀ መዛሙርቶቻቸው በቅርጫት አድርገው በአህያ ጭነው ወደ ጉባኤ ኒቂያ ይዘዋቸው ሄደዋል፡፡

በመንገድም ሳሉ ዐላዊያኑ አግኝተዋቸው አህዮቻቸውን ሌሊት ራስ ራሳቸውን ቆርጠው ጣሉባቸው፡፡ አቡነ ቶማስም ራሳቸው የተቆረጡትን አህዮች አምጡልኝ ብለው የጥቁሩን አህያ ራስ ከነጩ፣ የነጩን አህያ ራስ ከጥቁሩ ገጥመው ቢባርኳቸው ሁሉም አህዮች ከሞት ተነሥተዋል፡፡

ከጉባዔውም ሲደርሱ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ጽድቃቸውን ዐውቆ ‹‹አባቴ በረከትዎ ትድረሰኝ›› በማለት በዐላዊያኑ የተቆራረጠ አካላቸውን ዳሶ ተባርኳል፡፡

አቡነ ቶማስ ዘመርዓስም ከሌሎቹ ኤጲስ ቆጶሳት ጋር ሆነው አርዮስን መክረውና አስተምረው እምቢ ቢላቸው አውግዘውት ወደ ሀገራቸው እንደተመለሱ ነሐሴ 24  በሰላም ዐርፈዋል፡፡

የአቡነ ቶማስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን።
🟢🟡🔴
ነሐሴ 26 | #አቡነ_ኢየሱስ_ሞዐ እና #አቡነ_ሃብተ_ማርያም የፅንሰታቸው በዓል ነው።

#አቡነ_ኢየሱስ_ሞዐ
አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ የተወለዱት ጎንደር የድሮው ስማዳ (ዳኅና) አካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ዘክርስቶስና እግዚእ ክብራ ይባላሉ።

የተፀነሱት ነሐሴ 26፣ የተወለዱት ግንቦት 26 በ1210 ዓ.ም ነው። አንዳንድ ምንጮች በ1196 ዓ.ም ያደርጉታል።

በከፋች ዮዲት ጉዲት ለ40 ዓመታት በሃገሪቱን ክርስትና ተዳከመ። ባዕድ አምልኮም ነገሠ።

አቡነ ኢየሱስ ሞዐ (ትርጉሙ ኢየሱስ ክርስቶስ አሸነፈ ማለት ነው) ደግሞ ሃይማኖታቸው የቀና ከ800 በላይ ክርስቲያኖችን ሰብስበው በሃገሪቱ ትልቅና የመጀመሪያው ሊባል የሚችል ቤተ መጻሕፍት አደራጁ።

አርድእትን በቅድስናና በትምህርት አብስለው አመነኮሱና "ሒዱ ሃገሪቱን ታበሩ ዘንድ ተጋደሉ" ብለው አሰናበቷቸው።

ከእነዚህ መካከልም፦
◆ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን
◆ አቡነ በጸሎተ ሚካኤልን እና
◆ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫን መጥቀስ እንችላለን።

በዚህም ምክንያት ጻድቁ "ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን - አእላፍ ቅዱሳንን የወለደ" ሲባሉ ይኖራሉ።

#አቡነ_ሃብተ_ማርያም
ቅዱስ አባታችን ፅንሰታቸው ነሐሴ 26፣ ልደታቸው ግንቦት 26፣ ዕረፍታቸው ኅዳር 26 ነው፡፡

ጻድቁ መካነ ሙላዳቸው ሽዋ (የራውዕይ) ውስጥ ሲሆን አባታቸው ፍሬ ቡሩክ፣ እናታቸው ደግሞ ቅድስት ዮስቴና ትባላለች። በተለይ ቅድስት ዮስቴና እጅግ ደመ ግቡ፣ ምጽዋትን ወዳጅ፣ ቡርክት ሴት ነበረች።

ልትመንን ከቤቴ ብትወጣም በባሕታዊ ትእዛዝ ተመልሳ ጻድቁን ወልዳ አሳድጋ እንደ ገና መንና በተጋድሎ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ ዐርፋለች።

#ብፅዕት_ሣራ
በዚህ ቀን በዚህች ቀን ለአብርሃም ሚስት ለተመሰገነች ሣራ መታሰቢያዋን እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶች አዘዙ።

T.me/Ewnet1Nat
ሶማሊያ

የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዛሬ ወደ ግብፅ ካይሮ አቅንተው ከግብፅ አቻቸው ጋር ውይይት አድርገዋል!

ውይይቱ ምን ላይ ያተኮረ ነው የሚለው በግልፅ ባይታወቅም በሁለቱ ሀገራት የደህንነት ጉዳዮች ላይ እንደተወያዩ የሀገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ግብጽ ከቀናት በፊት የጦር መሳሪያ ወደ ሶማሊያ ማጓጓዛ የሚታወስ ነው።

በተመሳሳይ ዜና የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ ከሀገሪቱ የጦር መሪ ጋር ውይይት ሲያደርጉ ውለዋል ።
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
2024/09/25 18:12:03
Back to Top
HTML Embed Code: