Telegram Web Link
የእህታችን ወለተ ብርሃን እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ኃይለ ገብርኤል እንዳቀረበው
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = አዲስአበባ
28/11/2016

👉 ሕዝቡም ከጭንቁ የተነሳ
ዓይኑ እያየው ቤቱ ንብረቱ ስለሚፈርስ፤ ሞትን አይፈራም። ስለሆነም በመንግሥትም ሆነ በሚታመንበት
ኃይል ላይ ዘምቶ መተላለቅ ይሰፍናል።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት አምስት ገፅ 38 የተወሰደ
የወንድማችን ወልደ ገብርኤል እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከደቡብ አፍሪካ = ኦጊስ
28/11/2016

👉 ይህም ብቻ አይደለም
ትእግስትም ተሟጦ የመጨረሻው ምድር ከተፈጠረችበት ጊዜ አንስቶ ያላየችው ተደራራቢና ተከታታይ
የእሳትና የማዕበል የቸነፈር የምድር ነውጥ እሳተ ጎሞራ ፍጅት ብርቱ አውዳሚ በረዶ ጎርፍ የመጣበትና
የሚወርድበት መሆኑን ለማሳወቅ የመጣ ነው።

👉 የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ዘጠኝ ገፅ 27 የተወሰደ
እስካሁን የ11 ሰዎች አክስሬን ተገኝቷል።

በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ ዛሬ ረፋድ 5 ሠዓት አካባቢ በተከሰተ የመሬት ናዳ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰምቷል፡፡

በተከሰተው አደጋ እስካሁን በተደረገ ፍለጋ የ11 ሰዎች አስከሬን ተገኝቷል።

የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል የካዎ ኮይሻ ወረዳ አስተዳደር አሳውቋል።

ከቀናት በፊት በዚሁ አካባቢ በተከሰተ የመሬት ናዳ 1 ሰው ህይወቱ ማለፉ እና 1 ሰው ከባድ ጉዳት እንደረሰበት ይታወሳል።

*ወረዳው ኮሚኒኬሽን
◦●●●◦
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም፨

~❴ ሐምሌ ፴/30 ❵~
     በዚህች ቀን፦

● ሐዋርያው_ቅዱስ_እንድርያስ አስገራሚ ተአምር በማድረግ ማትያስን ሰውን ከሚበሉ ሰዎች እጅ ያዳነበት ዕለት ነው፡፡

● ስለ ጽድቅ ሲል ራሱን የሸጠው አባ_ጳውሎስ_መናኒ ዕረፍቱ ነው፡፡

● ቅዱሳን የገሊላ ሰማዕታት መርቆሬዎስና_ኤፍሬም ዕረፍታቸው ነው፡፡

● ቅዱስ_ሱርያል_መልአክ ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበት ዕለት ነው፡፡

● ሃይማኖትን ከምግባር አስተባብራ የያዘች፣ ጾም ጸሎትን ገንዘብ በማድረግ በመንፈሳዊ ተጋድሎዋ የተመሰገነች ንግሥት፣ የንጉሥ ናዖድ ሚስት ንግሥት_ማርያም_ክብራ ዐረፈች።

◦●●●◦

    •• ቅዱሳን መርቆሬዎስ እና ኤፍሬም ••
                          ๏-❀-๏   

ሐምሌ ሠላሳ በዚች ቀን ቅዱሳን የገሊላ ሰዎች መርቆሬዎስና ኤፍሬም በሰማዕትነት ዐረፉ።

እሊህም ከአክሚም ከተማ የመጡ የሚዋደዱ በመንፈስ ቅዱስ ወንደማሞች በሥጋም ዘመዳሞች ነበሩ። መንፈሳዊ ስምምነትንም ተስማምተው በላይኛው ግብጽ ካሉ ገዳማት በአንዱ ገዳም መነኰሱ። በጾም በጸሎትና በስግደት እየተጋደሉ በገዳሙ ውስጥ ሃያ ዓመት ያህል ኖሩ። 

ከዚህም በኋላ ጠላት ሰይጣን በአብያተ ክርስቲያናት ላይ ከአርዮሳውያን ችግርን በአመጣ ጊዜ አርዮሳውያኑ በአርዮሳዊ ንጉሥ ትእዛዝ መሥዋዕትን ሊሠው ወደ ኦርቶዶሳዊት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገቡ። ቀንተው ወደ ቤተ ክርስቲያን ገቡና አርዮሳውያን ያኖሩትን መሥዋዕት በተኑት። 

እንዲህም አሏቸው፦ በሥሉስ ቅዱስ ስም ያልተጠመቀ መሥዋዕትን ያሳርግ ዘንድ አይገባውም።

ያን ጊዜም አርዮሳውያን ይዘው ደበደቧቸው ታላቅ ግርፋትንም ገረፏቸው። ዐጥንቶቻቸውም እስኪሰበሩ ድረስ በምድር ላይ ጥለው ረገጧቸው። ነፍሶቻቸውንም በእግዚአብሔር እጅ ውስጥ ሰጡ።

የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበሉ። ምእመናንም መጥተው ሥጋቸውን ወሰዱ። በአማሩ ልብሶችም ገንዘው በመልካም ቦታ አኖሯቸው። ከእነሱም ለበሽተኞች ታላቅ ፈውስ ሆነ። 

                 ◦🌿🌿🌿

            •• ቅዱስ ጳውሎስ መናኒ ••
                          ๏-❀-๏

በዚህችም ቀን ክብርንና ብልጽግናን ንቆ የተወ ጳውሎስ ዐረፈ።

ይህም ቅዱስ ባለጸጋ ነበር። ደግ የሆነች ሚስትና የተባረኩ ልጆችም ነበሩት። መነኮስ ሊሆን ወደደ ሚስቱንና ልጆቹንም ጠርቶ፦

« እነሆ ክብር ይግባውና ስለ ክርስቶስ ፍቅር እሸጣችሁ ዘንድ ወደድኩ » አላቸው። እነርሱም አሳዳሪያቸን ነህና የወደድከውን አድርግ አሉት። 

ከዚህም በኋላ ገንዘቡን ሁሉ ወስዶ ለድኆችና ለችግረኞች በተነ። ሚስቱንም ወደ ደናግል ገዳም ወሰዳት። እመምኔቷንም ጠራትና እንዲህ አላት፦

« ለገዳምሽ አገልጋይ ትሆን ዘንድ ሚስቴን ልሸጥልሽ እወዳለሁ።» እርሷም እሺ አለችው። የመሸጫዋንም ደብዳቤ ጻፈ የሺያጭዋን ዋጋ ተቀብሎ ለድኆች ሰጠ።

ልጆቹንም ወደ አበ ምኔቱ ወስዶ እንደ እናታቸው ሸጣቸው። ለአበ ምኔቱም አሳልፎ ሰጣቸው። 

ከዚህም በኋላ ወደ ሌላ ቦታ ሔደ። ራሱንም ለገዳሙ አለቃ ሸጠ። አለቃውንም ወደ ቤተ ክርስቲያን ብቻዬን ልገባ እሻለሁ አለው።

በገባም ጊዜ በሩን በላዩ ዘጋ። እጆቹንም ዘርግቶ ቆመ በታላቅ ድምፅም እንዲህ ብሎ ጮኸ፦ አቤቱ በፍጹም ልቡናዬ ወዳንተ እንደ መጣሁ አንተ ታውቃለህ። 

ወደርሱም እንዲህ የሚል ቃል መጣ፦ ሀሳብህን ሁሉ አወቅሁ፤ በፍጹም ልቤም ተቀበልኩህ።

ከዚህም በኋላ መነኮስ አስጨናቂ የሆኑ የገዳሙን ሥራዎች ሁሉ እንደ ባሪያ እየሠራ ኖረ ራሱንም ከሁሉ እጅግ አዋረደ፤ ነገር ግን ስለ መዋረዱ እግዚአብሔር ከፍ ከፍ አደረገው።

ከእርሱም ብዙዎች ድንቆችና ተአምራቶች ተገለጡ ከዚህም በኋላ በሰላም ዐረፈ።

                  ◦🌿🌿🌿
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሰቆቃወ  ጴጥሮስ
የሊቁ ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስ ዘኢትዮጵያ
ረድኤት በረከት ይደርብን።
🍀 🌹 🍀 🌹 🍀 🌹
ቅድስት ጾመ ፍልሠታ ለማርያም

ቸር #እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ከሰጠው ጸጋ አንዱ ጾም ነው። የሰማይና የምድር ፈጣሪ የክብር ሁሉ ባለቤት ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ሥጋችንን በተዋሐደ ጊዜ በአርአያነት ከጥምቀት ቀጥሎ የሥራው መጀመሪያ ያደረገው ጾምን ነው።

ስለዚህም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን 7 አጽዋማትን በጉባዔ ሠርታ፣ በአዋጅ እንዲጾሙ ታደርጋለች። ከእነዚህም አንዱ ጾመ ፍልሠታ ነው።

"ፈለሠ" - ሔደ፣ ተጓዘ እንደ ማለት ሲሆን " #ፍልሠታ" ማለት የእመቤታችን ቅድስት #ድንግል_ማርያምን የዕርገት ጉዞ የሚያዘክር ቃል ነው።

#እመ_ብርሃን በዚህ ዓለም ለ64 ዓመታት ኖራ ካረፈች በኋላ ሥጋዋ እንደ እኛ አልፈረሰም።

ለጊዜው በዕፀ ሕይወት ሥር ቆይታ እንደ ልጇ ትንሳኤ ተነሥታ ዐርጋለች። እርሷ በሁሉ ነገሯ ቀዳሚና መሪ ናትና።

ጾመ ፍልሠታን የጀመሩት አበው #ሐዋርያት ሲሆኑ እንድትጾምም ሥርዓት የሠሩ ራሳቸው ናቸው። ከ7ቱ አጽዋማትም እጅግ ተወዳጅና እየተናፈቀች የምትፈጸም ናት።

ካህናትና ምዕመናንም ጾሟን እንደየአቅማቸው ክብር በሚያሰጥ መንገድ ይፈጽሟታል።

🍀 የቻሉ ወደ ገዳማት ሔደው ጥሬ እየቆረጠሙ፣ ውሃ እየተጎነጩ ክብርን ያገኛሉ።

🍀 ሌሎቹ ደግሞ ባሉበት ደብር አካባቢ እያደሩ ሌሊት ሰዓታቱን፣ በነግህ ኪዳኑንና ውዳሴ ማርያም ትርጓሜውን፣ በሰርክ ደግሞ ቅዳሴውን ይሳተፋሉ።

🍀 ይህ ሁሉ ባይቻል በቤታቸው ክትት ብለው በትጋት ይጾሟታል።

#ጽንዕት_በድንግልና#ሥርጉት_በቅድስና #እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን።

አእምሮውን፥ ለብዎውን፥ ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን።


ጾሙን የፍሬ፣ የትሩፋትና የበረከት ያድርግልን።
🌹🍀🌹🍀🌹

#እንኳን_አደረሳችሁ
T.me/Ewnet1Nat
በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት  የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ።
ዛሬ በ29/11/2016 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ እስካሁን በተደረገ ፍለጋ የ11 ሰዎች አስከሬን መገኘቱንና የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል የካዎ ኮይሻ ወረዳ አስተዳዳሪ መግለጻቸውን የወረዳው መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ገልጿል።
አዲስ አበባ ጉርድ ሾላ አካባቢ በአንድ ቀን ዝናብ  ተጥለቅልቋል።
#ትግራይ

" በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም " - ፅ/ቤቱ

በትግራይ ማእከላዊ ዞን ዓድዋ ወረዳ የመሬት መደርመስ አደጋ ተከስቷል።

የመሬት መደርመስ አደጋው በሰው ህይወት ያደረሰው ጉዳት ባይኖርም  የእህል አዝርእት ሙሉ በሙሉ አውድሟል።

የመሬት የመደርመስ አደጋ ያጋጠመው ሀምሌ 29/2016 ዓ.ም በዓድዋ ወረዳ በታሪካዊትዋ የይሓ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ነው።

የወረዳው የቁጠባ ዘርፍ ፅ/ ቤት ፤ " በአደጋው የ21 አርሶ አደሮች የተዘራ እህል ሙሉ በሙ ወድሟል " ብሏል። 

' ደምባፍሮም ' በተባለች መንደር የተዘራው ስንዴ ሙሉ በሙሉ መውደሙ ተመላክቷል።

" ከአሁን በፊት በትግራይ ያልተለመደ የመሬት የመደርመስ አደጋ አሁን አሁን መታየት ጀምሯል "  ያለው ፅ/ቤቱ " አርሶ አደሩ የክረምቱን ሀያልነት ከግምት ያስገባ ሁሉን አቀፍ ጥንቃቄ እንዲያደርግ " ሲል አሳስቧል።

ዘንድሮ በትግራይ ክልል ያለው ኃይለኛ ክረምት በንብረትና በእንስሳት አደጋ በማደረስ ላይ ይገኛል።

ባለፈው ሳምንት በክልሉ የራያ ጨርጨር ወረዳ ዝናብ ያስከተለው ኃይለኛ ጎርፍ በ106 የቤት እንስሳትና በ11 ሄክታር የእርሻ መሬት ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።

በጎርፉ 91 እንስሳት ሲወሰዱ ፣ 15 ቱ የአካል ጉዳት ደርሷቸዋል። በ11 ሄክታር የተዘራ እህል ከጥቅም ውጭ ሆኗል
በድሬደዋ አስተዳደር በደረሰ ድንገተኛ የመሬት መሽራተት አደጋ የአራት አርሶ አደሮች የእርሻ ማሳ መወድሙ ተገለፀ

በድሬዳዋ አስተዳደር ዋሂል ወረዳ ሁሉል ሞጆ ገጠር ቀበሌ ለመስኖ የሚውል ኩሬ በመሬት መንሸራቱቱ ሳቢያ 50 መኖሪያ ቤት ላይ ጉዳት በማድረሱ የአካባቢውን ዜጎች ወደ ተሻለ ቦታ የማስፈር ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ተናግረዋል ።

በድሬዳዋ አስተዳደር ዋሂል ወረዳ ሁሉል ሞጆ ገጠር ቀበሌ አካባቢ በደረሰው ድንገተኛ የመሬት መሸራተት አደጋ ሳቢያ የ4 አባወራዎች የእርሻ ማሳ የወደመ ሲሆን ለመስኖ ሲውል የነበረ ግድብ በመሬት መንሸራተቱ ሳቢያ ሀምሳ መኖሪያ ቤቶች ላይ ጉዳት በመድረሱ የአካባቢውን ነዋሪዎች ወደ ተሻለ አካባቢ ለማስፈር ስራ ተጀምሯል ።
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሰደድ እሳት በካሊፎርኒያ ያደረሰው ውድመት‼️
2024/09/24 10:18:05
Back to Top
HTML Embed Code: