Telegram Web Link
🟩 🟨 🟥

የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው

🍀
ኢትዮጵያውያን ሌላው ከእግዚአብሔር የተሰጣቸው ሀብት ሰንደቅ ዓላማ ነው። «ይህ የኪዳኔ ምልክት ነው» ይላል።
[ዘፍ ፱፥ ፲፫]

🌼 ዛሬ ያለን ሰዎች ግን ብዙ ሰንደቅ ዓላማ ይዘን እያውለበለብን ነው። ለምንድነው? ከየት አመጣነው? ከምንስ ተነሥተን ነው? የሃይማኖትና የፖለቲካ ጥገኛ ስለ ሆንን ብቻ ነው።

🌺 «ቀስቴን በደመና አኖራለሁ፤» ሲል የሰው ልጆችን በዕርቁ ጸንቶ እንደሚጠብቃቸው ቃል የተሰጠበት የአምላካችን ምልክት ስለሆነ፥ ከታላቁ አባታችን ከኖኅ ዘመን ጀምሮ ፭ ሺህ ዓመት ጸንቶ የኖረና የተውለበለበ የቀለማት ምልክት ነው።

#የኢትዮጵያ_ሰንደቅ_ዓላማ በሰውና በእግዚአብሔር መሓል ያለ የዕርቅ ምልክት ስለ ሆነ ዛሬም ልናከብረው ይገባል!

~ ከሊቀ ሊቃውንት አለቃ አያሌው ታምሩ የሕይወት ታሪክ መጽሔት የተወሰደ
▱ ▰ ▱
የኔታ በረከቶ ይደርብ
ን !!!

▮አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ
▯t.me/Ewnet1Nat
▮t.me/AlphaOmega930
#ሰበር_መረጃ‼️
በጋምቤላ ከተማ በአኝዋክና ኑዌር ጎሳዎች መካከል በትጥቅ የተደገፈ ውጊያ እየተካሄደ ነው።

ግጭቱ አድማሱን እያሰፋ መሆኑን ምንጮቻችን ገልፀዋል።
አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ
#መጋቢት_12 #ልዑል_እግዚአብሔር #ቅዱስ_ሚካኤልን ወደ ጠንቋዩ በለዓም ላከው። www.tg-me.com/Ewnet1Nat
የታሪኩም መነሻ እንዲህ ነው፦
ከግብፅ ከወጡ በኋላ የእስራኤል ልጆች በዮርዳኖስ ማዶ በሞዐብ ምድር ሰፈሩ።

የሞዐብ ንጉሥ ባላቅም እስራኤል በአሞራውያን ላይ ያደረጉትን አይቶ፣ ብዛታቸውንም ተመልክቶ ፈራ። በወንዙ አጠገብ ባለች ፋቱራ በምትባል ቦታ ወደሚኖረው በለዓም እንዲያሟርትለት መልእክተኛ ሽማግሌዎችን ላከ።

ሽማግሌዎቹም የሟርቱን ዋጋ ይዘው ባላቅ እንዳላቸው፦ "... ይህ ሕዝብ ከእኔ ይበልጣልና ልወጋቸውና ከምድሪቱ ላሳድዳቸው እችል እንደ ሆነ፥ እባክህ፥ ና ርገምልኝ። አንተ የመረቅኸው ምሩቅ የረገምኸውም ርጉም እንደ ሆነ አውቃለሁና" ብለው የተላኩበትን ነገሩት።

በለዓምም "ዛሬን እዚሁ እደሩ። እግዚአብሔር እንደሚነግረኝ እመልስላችኋለው" አላቸው።

እግዚአብሔርም በለዓምን የሽማግሌዎቹን ማንነት ጠየቀው። እርሱም ከግብፅ የወጣውን ምድርን የሸፈነውን የእስራኤል ሕዝብን እንዲረግምላቸው እንደተላኩ ነገረው። እግዚአብሔርም እንዲመለሱ ንገራቸው ብሎት ወደመጡበት ሸኛቸው።

ባላቅም ያሰበው ባለመሳካቱ ከፊተኞች የበዙና የከበሩ ሌሎችን አለቆች ሰደደ። እነርሱም ባላቅ ላንተ "እባክህ፥ ና፥ ይህን ሕዝብ ርገምልኝ" አለ ብለው ነገሩት።

ዳግመኛም በለዓም አለቆቹን እደሩ ብሎ የእግዚአብሔርን መልስ ጠየቀ። እግዚአብሔርም "አብረኻቸው ውጣ፤ ነገርግን የምነግርህን ቃል ብቻ አድርግ" አለው።

በለዓምም ሲነጋ ተነሣ፥ አህያይቱንም ጭኖ ከሞዓብ አለቆች ጋር ሄደ። እርሱም ስለ ሄደ እግዚአብሔር ተቈጣ፤ የእግዚአብሔርም መልአክ ሊቋቋመው በመንገድ ላይ ቆመ። እርሱም በአህያይቱ ላይ፥ ሁለቱም ሎሌዎቹ ከእርሱ ጋር ነበሩ።

አህያይቱም የእግዚአብሔርን መልአክ በመንገድ ላይ ቆሞ የተመዘዘም ሰይፍ በእጁ ይዞ አየች። ከመንገዱም ፈቀቅ ብላ ወደ እርሻው ውስጥ ገባች።

በለዓምም ወደ መንገድ ይመልሳት ዘንድ አህያይቱን መታት። የእግዚአብሔርም መልአክ ከወይኑ ቦታዎች መካከል በወዲያና በወዲህ ወገን ግንብ በነበረበት በጠባብ መንገድ ላይ ቆመ። አህያይቱም የእግዚአብሔርን መልአክ አየች፥ ከበለዓምም በታች ተኛች።

በለዓምም እጅግ ተቈጣ፥ አህያይቱንም በበትሩ ደበደባት። እግዚአብሔርም የአህያይቱን አፍ ከፈተ፥ በለዓምንም። ሦስት ጊዜ የመታኸኝ ምን አድርጌብህ ነው? አለችው። በለዓምም አህያይቱን፦ ስላላገጥሽብኝ ነው፤ በእጄስ ሰይፍ ቢኖር አሁን በገደልሁሽ ነበር አላት።

አህያይቱም በለዓምን፦ ከብዙ ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ የምትቀመጥብኝ አህያህ አይደለሁምን? በውኑ እንዲህ አደርግ ዘንድ ልማዴ ነበረን? አለችው። እርሱም እንዲህ አላደረግሽብኝም አላት።

እግዚአብሔርም የበለዓምን ዓይኖች ከፈተ፤ የእግዚአብሔርን መልአክ በመንገድ ላይ ቆሞ የተመዘዘም ሰይፍ በእጁ ይዞ አየ፤ ሰገደም፥ በግምባሩም ወደቀ።

የእግዚአብሔርም መልአክ፦ አህያህን ሦስት ጊዜ ለምን መታህ? እነሆ፥ መንገድህ በፊቴ ጠማማ ነውና እቋቋምህ ዘንድ ወጥቼአለሁ፤ አህያይቱም አይታኝ ከፊቴ ሦስት ጊዜ ፈቀቅ አለች፤ ከፊቴስ ፈቀቅ ባላለች በእውነት አሁን አንተን በገደልሁህ፥ እርስዋንም ባዳንኋት ነበር አለው።

በለዓምም የእግዚአብሔርን መልአክ፦ በድያለሁ፤ አንተ በመንገድ ላይ በፊቴ እንደቆምህብኝ አላወቅሁም፤ እንግዲህም አሁን አትወድድ እንደ ሆነ እመለሳለሁ አለው።

የእግዚአብሔርም መልአክ በለዓምን፦ ከሰዎቹ ጋር ሂድ፥ ነገር ግን የምናገርህን ቃል ብቻ ትናገራለህ አለው። በለዓምም ከባላቅ አለቆች ጋር ሄደ። ባላቅም በለዓም እንደ መጣ በሰማ ጊዜ በአርኖን ዳር ዳርቻ በመጨረሻ ወዳለችው ወደ ሞዓብ ከተማ ሊገናኘው ወጣ።

ባላቅም በለዓምን፦ በውኑ አንተን ለመጥራት አልላክሁብህምን? ለምንስ ወደ እኔ አልመጣህም? በውኑ አንተን ለማክበር እኔ አልችልምን? አለው።

በለዓምም ባላቅን፦ እነሆ፥ ወደ አንተ መጥቼአለሁ፤ በውኑ አሁን አንዳችን ነገር እናገር ዘንድ እችላለሁን? እግዚአብሔር በአፌ የሚያደርገውን ቃል እርሱን እናገራለሁ አለው።

ባላቅም መሠዊያንና መሥዋዕትን አዘጋጀ። 3 ጊዜ እንዲረግምለት ሕዝቡን እያሳየ ጠየቀው። እግዚአብሔር ግን በበለዓም አፍ ቃል አደረገና 3 ጊዜ መረቃቸው።

(ሙሉ ታሪኩን ኦሪት ዘኁልቁ  ምዕራፍ ፳፪፣ ፳፫፣ ፳፬ እስከ ፍጻሜ ይነበብ)

www.tg-me.com/Ewnet1Nat
🟢 🟡 🔴
መጋቢት 13 | አርብዓ ሐራ ሰማይ (አርባው የሰማይ ጭፍሮች/ወታደሮች) ሰማዕትነትን ተቀበሉ፨

አርብዐ ሐራ ሰማይ ማለት በዘመነ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ሰማዕትነትን የተቀበሉ 40 ጭፍሮች ናቸው።

"ሐራ ሰማይ" የተባሉት በምድር ሲሠሩት የቆዩትን የውትድርና ሥራ ትተው የክርስቶስ (የሰማያዊው ንጉሥ) ጭፍራ ለመሆን በመብቃታቸው ነው።

www.tg-me.com/Ewnet1Nat
ኢየሱስ ክርስቶስ ካህኑ ለዓለም ንጉሠ ፅዮን ወንጉሠ ነገሥታት ዘኢትዮጵያ
ድንግል ማርያም እሙ ወእምነ ንግሥተ ፅዮን ወንግሥተ ነገሥታት ዘኢትዮጵያ

በ 12/7/2016 ድንቃ ድንቅ አስተማሪ ምስክርነት ይለቀቃል 👇👇👇
ወለተ_ማርያም_ከ_አሰላ_ምስክርነት_1_55.amr
1.1 MB
የእህታችን ወለተ ማርያም እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ =አሰላ
12/7/2016
ክፍል ፩

👉 በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት በ ታህሣሥ 21 ቀን 2013 ዓ.ም ታወጀ!! ከየካቲት 21
ቀን 2013 ዓ.ም በኋላ በማናቸውም ጊዜና ወቅት ሥላሴዎች ብቻ በሚያውቁት ማንም በማያውቀው ጊዜ
እርምጃውና ጠረጋው ይጀምራል።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ዘጠኝ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተወሰደ ።
ወለተ_ማርያም_ከ_አሰላ_ምስክርነት_2_54.amr
1.1 MB
የእህታችን ወለተ ማርያም እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ =አሰላ
12/7/2016
ክፍል ፪

👉 በኢትዮጵያ የአለም ብርሃን በቤተሰብነት ያሉ ሁሉ ቅኖችም ሁሉ በዙሪያቸው
የተለየ ጥበቃ የሚደረግላቸው የእግዚአብሔር ሕዝቦች ስለሆኑ በእንቅስቃሴያቸው ማንም ከልካይ የለባቸውም ፡፡
ፈቅደው አምነውበት ይሁነን ብለው በቤታቸው ያስጠለሉት ሰው ብቻ ይድናል ፡፡ በእርግጥ ይህን እርምጃ ሲወስዱ
ለፈጣሪያቸው ለቸሩ መድሃኒያለም ለድንግል ለቅዱሳን ሊቀመላእክት ላንዳቸው አሳውቀው መሆን ይገባዋል ፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ በደጃቸው የቃልኪዳን ምልክቱን ሰንደቃችንን አረንጓዴ ቢጫ ቀዩን ባንዲራችንን በደጃፋቸው መስቀል
ይገባቸዋል ፡፡ ከዚሁ ጋር አራቱም የከበሩ የቃል ኪዳኑ የዘወትር መገለጫ ቃሎች ----

ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመሥገኛ ምድር
ኢትዮጰያ ርስተ ድንግል ማርያም
ኢትዮጵያ የአለም ብርሃን
ኢትዮጵያ የአለም ገዢ

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት አሥር የተወሰደ
ወለተ_ማርያም_ከ_አሰላ_ምስክርነት_3_0521056.amr
890 KB
የእህታችን ወለተ ማርያም እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ =አሰላ
12/7/2016
ክፍል ፫

👉 ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመሥገኛ ምድር
ኢትዮጰያ ርስተ ድንግል ማርያም
ኢትዮጵያ የአለም ብርሃን
ኢትዮጵያ የአለም ገዢ
Voice 001
<unknown>
የወንድማችን ገብረ ሚካኤል እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = ባህርዳር
12/7/2015

👉 እንግዲህ ወገኖቼ እግዚአብሔር
ቀጠሮ አክባሪ ነው። የተናገረውን የገባውንም ቃል ኪዳን አክባሪና ፈጻሚ ነው። እነሆ ዛሬም ቃሉን ለመፈጸም
ከብዙ ሺህ ዘመናት ትእግስት በኋላ ምድርንና መላውን ነዋሪ የአዳም ዘር ከእናቱ ከእናታችን ከድንግል
ጋር በመሆን ጎብኝቶ የሰውን ዘር ልማትና ጥፋት አክራሞቱን ሁሉ መዝኖ አጠናቀቀ። ከላይ እንደገለፅኩት
የሰው ልጅ እንደምርጫው ተሰማርቶ ስለጠበቀው፣ በዚያው መሠረት እንደመጸጸቱ እንዲሁም እንዳለመጸጸቱ
እንደልቡ ጥንካሬና እንደ ቅንና የዋህነቱ ፍርዱን አጸና። በዚህም መሠረት ለቅዱሳን ሊቃነ መላእክት
የአፈጻጸም ትእዛዝ ሰጠ።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ዘጠኝ የተወሰደ
"...መንግሥት አልደረሰልህም ! ስትታረድ ስትጨፈጨፍ መግለጫ እንኳን አላወጣልህም ፤ መንግሥት መንግሥት የሆነው ዜጎቹን ሊጠብቅ ነው ይህ መንግሥት ግን ፍፁም ጨካኝ የሆነ ስለሥልጣኑ ብቻ የሚጨነቅ ነው፤ ለዚህ ደግሞ የማይክደው ተግባሩን ስናነሳ በመላው የአዲስ አበባ የመንግስት ተቋማት ውስጥ ከአንድ የኦሮሞ አካባቢ በወጡ ዘሮቹ መሙላቱ ሲሆን ለዚህ ምንም የሰጠው የጥፋት ምክንያት የለም "በቃ እኛ ተራችን ነው ውጡ" እያለ ከሥራ ገበታቸው እያባረረ አይኑን በጨው አጥቦ ተቀምጧል ፤ ደግሞም አያፍርም "ለእድገት ለሰላም ለእኩልነት ነው የምደክመው" ይላል ፡፡ የምታየው መንግሥት ግን አንተን ንፁህ ኢትዮጵያዊውን እጅግ ነው የሚጠላህ ። ምክንያቱም እምነቱ በእግዚአብሔር የተጠላ መናፍቅነት #እስልምና ነውና አይፈልግህም ፡፡ በገዛ ሀገርህ እሱ መወገድ ሲገባው በቤትህ በሃገርህ ያንተን ሕልውና የሚወስን ሆኖ እያሰቃየህ ነው ።.........."

ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ዘጠነኛ መልዕክት ገፅ 14 (በድምፅ ክፍል 2) የተወሰደ ፥ ተፃፈ ታኅሣሥ 21/2013ዓ.ም!
አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ
🟢 🟡 🔴 መጋቢት 13 | አርብዓ ሐራ ሰማይ (አርባው የሰማይ ጭፍሮች/ወታደሮች) ሰማዕትነትን ተቀበሉ፨ አርብዐ ሐራ ሰማይ ማለት በዘመነ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ሰማዕትነትን የተቀበሉ 40 ጭፍሮች ናቸው። "ሐራ ሰማይ" የተባሉት በምድር ሲሠሩት የቆዩትን የውትድርና ሥራ ትተው የክርስቶስ (የሰማያዊው ንጉሥ) ጭፍራ ለመሆን በመብቃታቸው ነው። www.tg-me.com/Ewnet1Nat
ማንም የቆመ ቢመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ! ❯

በ330ዎቹ አካባቢ የዓለም ንጉሥ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ አንዱን መኮንኑን ወደ ቂሣርያ አካባቢ ይልከዋል። የተላከው አካባቢውን ለማስተዳደር ሲሆን ቦታው ስብስጥያ (ሴባስቲ) ይሰኛል።

መኮንኑ ክርስቲያኖችን እንዲንከባከብ ጥብቅ ትዕዛዝ ከንጉሡ ቢሰጠውም ፍቅረ ጣዖት በልቡ የነበረበት ሰው ነውና ክርስቲያኖችን ይጨቁን፣ ያሰቃይ፣ ይገድል፣ አብያተ ክርስቲያናትን ያፈርስ ገባ።

በጊዜው ይህንን የተመለከቱት 40ው ጭፍሮች በአንድነት መክረው መኮንኑን ገሠጹት። ስመ ክርስቶስንም ሰበኩለት። እርሱም በፈንታው 40ውን አስሮ ብዙ አሰቃያቸው።

በመጨረሻ ግን 40ውንም የበረዶ ግግር አስቆፍሮ፣ ከነ ሕይወታቸው እስከ አንገታቸው ቀብሮ፣ ለ39 ቀናት ያለ ምግብ በጽኑ ስቃይ አቆያቸው። በ40ኛው ቀን ግን ከ40ው አንዱ "ይህን ሁሉ መከራ የምቀበል ለምኔ ነው?" ብሎ "አውጡኝ!" እያለ ጮኸ።

ክርስቶስን አስክደው ወደ ውሽባ ቤት ('ሻወር' ቤት) ሲያስገቡት ፈጥኖ ሞተ። በነፍስም በሥጋም ተጎዳ። ነገር ግን ከአረማውያን ወታደሮች አንዱ "እኔን አስገቡኝ" ስላለ እንደገና 40 ሆኑ።

ነገር ግን ከአረማውያን ወታደሮች አንዱ 40 የሰማይ አክሊሎች ለሰማዕታቱ ወርደው አንዱ ግን በአየር ላይ በመልአኩ እጅ ተንጠልጥሎ ሲቀር አይቶ "እኔን አስገቡኝ" ስላለ እንደገና 40 ሆኑ።

እሊህም ጎልማሶች ሰማዕታት በዚያች ዐዘቅት በነበሩበት ጊዜ እናቶቻቸው ያጽናኗቸውና ያስታግሷቸው ነበር። እርሱም ብዙ ጊዜ ቆዩ እንጂ ቶሎ አልሞቱም። ከሀድያንም ጭኖቻቸውን ሊሰብሩ ፈለጉ ፈጥነው እንዲሞቱ እግዚአብሔርም ወዲያውኑ #መጋቢት_13 ቀን ነፍሳቸውን ወሰደ። ጭኖቻቸውን መስበር አልተቻላቸውም።

ከዚህ በኋላ በእሳት ሥጋቸውን እንዲያቃጥሉ በተሽከርካሪም ጭነው ወስደው ወደ ባሕር እንዲጥሏቸው መኰንኑ ወታደሮችን አዘዘ።

ሲጭኗቸውም ያልሞተ ሕፃን አገኙና ተዉት። እናቱም ከሠረገላው ውስጥ ልትጥለው ተሸክማው ሮጠች። ወታደሮችም ስለአልሞተ ከለከሉአት።

ወዲያውኑ በጫንቃዋ ላይ ሙቶ ከቅዱሳን ጋር እንዲሆን ወደ ተሽከርካሪው ጣለችው። ወደ ስብስጥያ ከተማ ጭነው ወስደው በእሳት አቃጠሉአቸው ወደ ባሕርም ጣሏቸው።
🌿 ❄️ 🌿

ብጹዕ አባታችን አባ ሕርያቆስም በቅዳሴ ማርያም ድርሰቱ ላይ በቅዱሳኑ ላይ የሆነውን ነገርና ሥልጣነ እግዚአብሔርን እያደነቀ እንዲህ ሲል ተናግሯል።

በውስጥ ያለውን የምታስወጣ
በውጪ ያለውንም የምታስገባ
እንግዲህ በእውነት የሚጠሩህን የወገኖችህን ጩኸት ስማ
[ቅዳሴ ማርያም ቁ.146]

❄️ ስለዚህ በውስጥ ያለን አንታበይ። ያለንበት እንድንገኝ ያደረገን የእኛ ብቃት አይደለምና። እንዳንወድቅም እንጠንቀቅ። ብዙዎቹ የቆሙ ሲመስላቸው ወድቀዋልና። ያሉ ሲመስላቸውም ወጥተዋልና።

🌿 በውጪ ያለንም ተስፋ አንቁረጥ። ወደ ኋላም አንበል። ወደ ቤቱ ሊመልሰን በክብሩ ማደሪያ ሊያኖረን የታመነ አምላክ አለንና።

የ40ው ሰማዕታት አምላክ መጽናትን ያድለን። በረከታቸው ትድረሰን፨

www.tg-me.com/Ewnet1Nat
Audio
መልከዓ ቅዱስ ሩፋኤል እና ድርሳኑ.mp3
Audio
መልከአ አቡነ ዘርዓብሩክ .mp3
Audio
ገድለ አቡነ ዘርዓብሩክ የአርብ.mp3
ከሴተኛ አዳሪዎች ጋር የሚያድረው መነኵሴ

በአንዱ ገዳም መንኵሶ የሚኖር አንድ መነኰስ ነበር። እሱ ያለበት ገዳም አበምኔት፥ እዛው ባሉ መነኰሳት ላይ ነገረ ሠሪን እንደሚቀበል ሲሰማ በዓቱ ትቶ ይወጣል። ሹልክ ብሎ ወጥቶ፣ ከተማ ገብቶ የቀን ሥራን ይሠራ ጀመር።

ከቀን ሥራው የሚያገኘውን ገንዘብ ጥቂት ለሆዱ ያደርግና የተቀረውን ይዞ ወደ ሴተኛ አዳሪዎች ይሄድ ነበር። የምንኵስናውንም ልብስ ሳይጥል በዚህ ድርጊቱ ገፋበት። ነዋሪውም ያዝንበትና ያማው ጀመር።

ነገሩ ግን እንዲህ ነው፦
ይሄ በሰው ድርጊት ሰውን ማማት የማይወድ መነኰስ የቀን ሥራውን ሂሳብ ተቀብሎ ይሔድና በከተማ ያሉትን ሴተኛ አዳሪዎች ስም ይጽፋል፤ ይመዘግባል።

ለምን?
ምክንያቱም ከቀን ገቢው ላይ የሽንብራ ቂጣ ይበላና ያስተረፈውን ገንዘብ በቀን አንድ ሴተኛ አዳሪ ወደ ኃጢአት እንዳትገባ ይሰጣታል። ልብ በሉ #_ወደ_ኃጢአት_እንዳትገባ❗️

በየቀኑ ወደ ሴተኛ አዳሪ ጋር እየሔደ፦ "በዚች ቀን ከአንቺ ጋራ አድራለሁና ራስሽን ለእኔ አዘጋጂ" ይላታል። ከኃጢአትም ሊጠብቃት ከእርስዋ ዘንድ ያድራል። #_ሌሊቱን_ሁሉ_ተነሥቶ_ሲጸልይና_ሲሰግድ_እግዚአብሔርንም_ሲለምን_ያድራል። ሲነጋም ሥራውን ለማንም እንዳትገልጥ አምሏት (ቃል አስገብቷት) ወደ ቀን ሥራው ይሔዳል።

በዚህም የተነሣ በከተማው እጅግ ይታማ ጀመር። ይህንን መታማቱን ያልወደደች አንዲቱ አመንዝራ ምሥጢሩን (ንጽሕናውን) ተናገረችበት። እርሷም "እንዳናመነዝር ገንዘብ በመስጠት ከኃጢአት ይጠብቀናል እንጂ ነውር የለበትም" አለች።

ስትናገርም ጋኔን ይዞ አሳበዳት። የአካባቢው ሰዎችም "ስለዚህ ክፉ ሽማግሌ 'ክፉ ሥራ የለበትም' ብላ ዋሽታለችና እግዚአብሔር መልካም አደረገባት" ተባባሉ።

የቀሩት አመንዝራ ሴቶች ደሞ በእርሷ ላይ የሆነውን በአዩ ጊዜ ደነገጡ። እንደርሷም እንዳያብዱ "አልዋሸችም፤ እውነቷን ነው" ማለትን ፈሩ። መነኰሱም እውነቱን ሳይናገር ወደ አመንዝራዎቹ ጋር መግባቱን ቀጠለ። ሰዎችም ሁሉ እጅግ ይነቅፉትና ይንቁት ጀመር። (የሚያዝንለትና ከክፉ ድርጊቱ እንዲመለስ የሚጸልይለት ኖሮ ይሆን?!)

በሚወራበት ሐሜት ያልተበገረው መነኰስ "መነኰስ ሰው አይደለምን። በፍትወት መቃጠልና መሞት አለበትን" ይላቸው ነበር። እነርሱም "ልብስህን ለውጠህ ሚስት አግባ" አሉት።

እርሱም፦ "አዎን ብወድ በሚስቴ እጠነቀቃለሁ። በዚህም በክፉ አኗኗር እኖራለሁ። እናንተ ግን ከእኔ ዘንድ ሒዱ ምን ትሻላችሁ? በእኔ ላይ እግዚአብሔር ፈራጆች አድርጓችኋልን? ይልቁንስ #_እናንተ_እንዳይፈረድባችሁ_ለራሳችሁ_አስቡ። ፈራጅ አንድ ነውና ዕለቲቱም አንዲት ናትና" አላቸው።

ይህም #_ቅዱስ_መነኰስ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነትን አገኘ፤ በሰው ዘንድ ግን የተናቀ ሆኖ ኖረ።

#_ታዲያ_መጨረሻው_ምን_ሆነ?

ከመነኰሱ ድርጊት በኋላ ከእርሱ ጥቅም የአገኙ አመንዝራዎች ዝሙታቸውን ተዉ። አንዳንዱ በሕጋዊ ጋብቻ ተወስነው መኖር ጀመሩ። አንዳንዱ ወደ ገዳም ገብተው መንኵሰው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው ኖሩ።

ይህ መነኰስ እንደለመደው፥ በአንዲት ዕለት፥ ከአንዲት አመንዝራ ቤት ሲወጣ ያቺን ሴት አስቀድሞ የለመዳት (ለዝሙት ወደ የሚሔድ) አንድ ሰው አገኘውና "ይህ ሽማግሌ እስከ መቼ ድረስ በዚህ በክፉ ሥራ ይኖራል" ብሎ ፊቱን በጥፊ መታው። ጥፊውንም በጸጋ ተቀበለ።

ከዚህም በኋላ በአንዲት ቀን በበዓቱ ውስጥ ሰግዶ ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ውስጥ ሰጠ። ባረፈም ጊዜ በቤቱም መድረክ ላይ እንዲህ የሚል ጽሑፍ ተጽፎ ተገኘ፦

"የዚች አገር ሰዎች ጊዜው ሳይደርስ በማንም ላይ አትፍረዱ፤ እንዳይፈረድባችሁ" የሚል ጽሑፍ ተጽፎ ተገኘ።

እኚህ መነኰስ ፍጹማን መነኰሳት ከሚባሉት ውስጥ አንዱ የሆኑት #_አባ_ባጥል_ዘእስክንድርያ ናቸው። #መጋቢት_14 የዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል ነው።
🍀

በባሕርይህ ንጹሕ የሆንክ አምላከ አባ ባጥል ሆይ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልን፤ የቀናውንም መንፈስ በውስጣችን አድስ" እያልን በስማቸው እንማፀን፤ እንዘክራቸው።

www.tg-me.com/Ewnet1Nat
2024/09/27 19:23:16
Back to Top
HTML Embed Code: