Telegram Web Link
👨‍🌾👩‍🌾..የእረኛው የፍቅር ቃላት..👩‍🌾👨‍🌾

🗣...
ሳገኝሽ-
ላሜ ጠፍታ ሳገኛት እንደሚሰማኝ አይነት ስሜት፣
🗣
ስትስቂልኝ-
ከብቶቼ በልተው ሲጠግቡ እንደሚሰማኝ አይነት ሃሴት፣
🗣
ስታኮርፊ-
በሬዬን ዋዥማ የነፋው ያህል ይጨንቀኛል፣
እይዘው፣
እጨብጠው፣
የማደርገው ይጠፋኛል።
😍😍😍
አደራሽን በንግግሬ በምሳሌዬ አትሳቂ፣
የፍቅሬን ጽናት ለማውቅ ከፈለግሽ ከብት ጠብቂ።    😊😊😊

📖.....ዋዥማ ማለት የላሞችን ሆድ ውጥር አድርጎ ነፍቶ እስከሞት የሚያደርስ ችግር ይፈጥራል ተብሎ በተለምዶ የሚወሰድ የሳር አይነት ነው።

@ethioleboled ▬▭🌹▬▭▬🌹
❤️እንደምትሄጂ ባውቅ -❤️

በእግሬ አንቺን ጋ ለመምጣት ከቃሊቲ አራብሳ እሄድ ነበር ?
አናደድሽኝ ብዬ ብዙ አረቄ በባዶ ሆዶ አጠጣ ነበር ?
ደክሞኝ ዝዬ አልጋ ላይ እንደበድን ተንጋልዬ <<አንገናኝ ወይ?>> ስትይኝ ተወርውሬ ያለሽበት እመጣ ነበር ?

ተሳፈጠሽ ብዬ ከወጠምሻ ጋ ታግዬ እሰበር ነበር?

እንደምቴጂ ባቅ ....!

ድብን ፤ቅንት ፤ እርር ብዬ ስሜቴን አፍን ነበር ?
ሁሉን ትቼ ከሷ በቀር ብዬ አለምን ችላ እል ነበር ? 🔠

እንደምቴጂ ባቅ ...!
ሳልሳሳ በደንብ እስምሽ እተኛሽ አልነበር?
በራስሽ ጥፋት የተጣላሽውን ተደርቤ ጠላት አደረገው ነበር ?
ደብሮኝ ተደሰተች ብዬ እቦርቅ ነበር ?

እንደምቴጂ ባቅ ...

ብቻዬን ሆኜ ሳልም እቅዴ ውስጥ አኖርሽ ነበር?
ገመናሽን ገመናዬን እንደዛ አርቀን እንገላለጥ ነበር?

እንኳን እንደምቴጂ አላወኩ ይሄን ሁሉ ትዝታ ከየት አመጣ ነበር ?
!
ሌሊት ነበር፤ አንድ ሰው በመንገድ ላይ እየነዳ መኪናው በገዳሙ አቅራቢያ ይበላሽታል። እናም ወደ ገዳም ሄዶ በሩን አንኳኳ። መነኩሴው ወደ ውጭ ወጥቶ በሩን ሲከፍት “መኪናዬ ተበላሸ። እዚህ ለአንድ ሌሊት መቆየት እችላለሁን?” አለ። መነኩሴውም ጥያቄውን ተቀበለ። መነኮሳቱንም ማቆየት ብቻ ሳይሆን መገቡት አልፎ ተርፎም መኪናውን አስተካከሉለት።

ሰውየው ለመተኛት ሲሞክር እንግዳ የሆነ ድምጽ ሰማ። በሚቀጥለው ቀን ጠዋት ስለዚያ ድምጽ መነኩሴውን ጠየቀ ነገር ግን መነኩሴው “መነኩሴ ስላልሆንክ ልንነግርህ አንችልም” አለው። ሰውየው ቅር ቢሰኝም አመስግኖት መንገዱን ቀጠለ።

ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ፤ ያው መኪና በተመሳሳይ ገዳም ፊት ለፊት ይበላሻል። አሁንም እንደበፊቱ ሁሉ መነኮሳት ተቀብለው መግበውት መኪናውን አስተካከሉለት። እናም ለመተኛት ሲሄድ ሰውዬው ከዚህ ቀደም የሰማውን ተመሳሳይ እንግዳ ድምጽ ይሰማል።

በማግስቱ ጠዋት ስለዚያ ጫጫታ መነኩሴን ይጠይቃል፤ ግን መነኩሴም ተመሳሳይ መልስ ሰጡት “መነኩሴ ስላልሆንክ ልንነግርህ አልችልም" ሰውዬውም "ስለዚያ ድምጽ ለማወቅ መነኩሴ መሆን ግድ ከሆነ፤ "እንዴት መነኩሴ መሆን እችላለሁ?” መነኩሴም መለሰ ፣ “መነኩሴ ለመሆን ከፈለክ የምድርን አሸዋ መቁጠር እና ቁጥሩን ለኔ መንገር አለብህ ይህን ስታገኝ መነኩሴ ትሆናለህ ” አለው።

ሰውየው ለዚህ ተግባር ተነስቶ ከአርባ ዓመታት በኋላ ተመልሶ የገዳሙን በር አንኳኩቶ “መላውን ምድር ተዘዋውሬ 222,345,323,954,110,958,203 የአሸዋ ጠጠር በምድር ላይ እንዳለ አገኘሁ” አለ።

መነኩሴ ሰውየውን በማመስገን “አሁን ወደ ድምጹ የሚወስደውን መንገድ እናሳይሃለን” አለው። መነኩሴ ወደ አንድ የእንጨት በር እየመራው “ሰውየው የሚፈልገው ድምፅ ከዚያ በር በስተጀርባ ነው” ሲል ተደሰተ። በሩን ለመክፈት ሲሞክር ግን ያ በር እንደተዘጋ ተረዳ። ስለዚህ በሩን ለመክፈት ቁልፉን እንዲሰጠው መነኩሴውን ጠየቀ። መነኩሴ ቁልፉን ሰጠው። ሰው በሩን ከፍቶ ከዚያ በር ጀርባ ከድንጋይ የተሠራ ሌላ በር አየ። ዳግመኛ ሰው በሩ እንደተቆለፈ ስላየ የዚያ በር ቁልፍ ጠየቀ። ሰው የድንጋይ በር ሲከፍት ከወርቅ የተሠራ ሌላ በር አገኘ ግን ተቆልፏል።

መነኩሴው የዚያን በር ቁልፍም ሰጠው። እንደገና ከሩቢ የተሠራ ሌላ በር ነበር። በሌላ ተከታታይ በር እስኪያልፍ ድረስ ይህ ይቀጥላል። በመጨረሻ መነኩሴው “ይህ የመጨረሻው በር ነው እና እዚህ የዚህ በር ቁልፍ ይኸው” አለ። ሰውየው በመጨረሻ እፎይታ አግኝቶ በሩን ከፍቶ ገባ እና ከዚያ በር በስተጀርባ የድምፅ ምንጭ በማግኘቱ ተገረመ ግን ምን እንደ ሆነ ልነግራችሁ አልችልም .. ምክንያቱም እናንተ መነኩሴዎች አይደላችሁም።
***

ኃሳባችሁን በኮሜንት አጋሩን። ሌሎች ታሪኮችን እና የመጻሕፍት ጥቆማዎች ለማግኘት ገጻችንን ላይክ፤ ለሌሎች እንዲደርስ ደግሞ ሼር ያድርጉ። እናመሰግናለን!
***
ሁሉንም ነገር ማወቅ አለብን ብላችሁ ታስባላችሁ
?
ከአእምሮ በላይ ነው።

በቅድሚያ ምስሉን በማስተዋል ተመልከቱና
ወፊትዋን ምን አየሰራች እንደሆነና ግንዱ ላይ ያለውን ምን እንደሆነ ገምቱ?

ወፊትዋ በእንጨት ላይ የተጠጠጠች የተዋጣላት መሃንዲስ የግንደ ቆርቁር ወፍ አይነት ናት።የምትመገበው ፍራፍሬ ሲሆን በክረምት ወቅት ዛፎች ፍሬን አፍርተው ፍሬያቸውም እስኪ በስል ደሰረ ለሷንም ለልጆቿኝም የሚሆን ምግብ
አይኖርም።

ይህም ማለት ክፉ ጊዜ መሆኑ ማለት ነው። ታዲያ ወፊትዋ ምኔ ሞኙ ሆነችና?ሲበዛ ብልህና አርቆ አሳቢ የእዋፍት አዋቂ ናት። ለክፉ ጊዜ የሚሆን ምግብ ማስቀመጥ ሊኖርባት ነው።
🚢🚢🚢
ዛፎቹን ፍሬ አፍርተው ፍሬያቸውንም ደርቆ ከማራገፋቸው በፊት በጠንካራ
ምንቃርዋን የዛፎቹን ግንድ ጥንቃቄ ጥበብን በተሞላበት ዲዛይን በመበሳሳት
አስቀድማ የፍራፍሬ ማስቀሙጫ ቀዳዳዎች ታዘጋጃለች።

ግንዱ የመበሳሳት ስራን እንዳጠናቀቀች ቀጣዩ ስራዋ የሚሆነው ፍራፍሬ ለቀማ ነው። ከየዛፎቹ እየሄደች አንዳንድ ፍሬ በመልቀም ፍሬዎቹ በበሳሳችው ቀዳዳ ውስጥ ትወትፈዋለች። ፍራፍሬዎቹ ስታስቀምጥ በዘፈቀደ ሳይሆን እያንዳንዱ ፍሬ እንደየ የጨቀዳዳው ስፋት መጠን መጠን ሄዶ ግጥም የሚል ነው።

ፍሬውን ቀዳዳው ውስጥ እንዲገባ ቀዳዳውንም በደንብ እንዲይዝ ፍሬውን ቀደዳዳው አፍ ላይ ወተፍ ታደርግና በምኝቃርዋ ወደ ውስጥ መታ መታ ታደርገዋለች።አንድም ፍሬ አይወድቅም።
🚢🚢🚢

ፈጣሪ ፍጥረታቱን እንዴት አድሮጎ ነው የፈጠራቸው? ፋጣሪ ሆይ ከማር
በላይ የሚጣፍጠው የጥበብን ስራ እንዳይ ስለፈቀድክልኝ አመሰግናለሁ።
ተፈጥሮን ማንበብና ማስተዋልን ከፍጥረታቱም መማር ባለመቻላችን ከጥበብ ቅና እውቀት አራራቀን።
👉🏾Rezenom Almaw

🚢
ርእስ፦ የስኬት ፍልስፍና

📝💓 ፀሀፊ ናፖሊዮን ሂል

✍️ተርጓሚ ራሴለህ ጋሻው

✍️✍️ዘውግ Psychology

✍️📝የገፅ ብዛት 203







OUTWITTING THE DEVIL የተሰኘው መጽሐፉ ለ70 አመታት ሳይታተም ተደብቆ ቆይቷል፡፡ ይህ #የስኬት_ፍልስፍና በሚል ተተረጎመ
የስኬት ፍልስፍና @Enmare.pdf
54 MB
የስኬት ፍልስፍና


ርእስ፦  የስኬት ፍልስፍና

📝💓 ፀሀፊ  ናፖሊዮን ሂል

✍️ተርጓሚ  ራሴለህ ጋሻው

✍️✍️ዘውግ Psychology

✍️📝የገፅ ብዛት 203







OUTWITTING THE DEVIL የተሰኘው መጽሐፉ ለ70 አመታት ሳይታተም ተደብቆ ቆይቷል፡፡ ይህ #የስኬት_ፍልስፍና በሚል ተተረጎመ
አባቴ ድሃ ታግሎ ኗሪ ነበር ። ነፍስ እስካውቅ የሆነ ኮት ነበረው ፤ ዘወትር ነበር የሚያደርገው ፤ እሱን ኮት ሳይለብስ ከመንገድ ባገኘው የማልፈው ሁላ ነው የሚመስለኝ ።

ረጋ አባባሉ የሞላለት ያስመስለዋል ።
በትንሽ በትልቁ አይናደድም ፤ በትንሽ በትልቁ አይመክረኝም ። ከሰው ጋ ሲጣላ አጋጥሞኝ አያውቅም ።

ሰላማዊ ሰው ነው ፤ ሁሉንም ሰው በሙሉ ስም ነው የሚጠራው እኔንም ጭምር ። እናቴን ግን ያቆላምጣታል ። እሷ ጋ ሲደርስ የሚሆነው መሆን ለየት ይላል ፤ ይቀልዳል ፣ ያሾፍባታል ግንባሯን ይስማታል ።

አጠገባችን ላሉ እጅግ ከእኛ የበለጠ ደሃ ለነበሩት እማማ አዛሉ እና ከእኛ ቤት ፊት ለፊት ሰፊ ትልቅ ግቢ ላላቸው ለዲታው ጋሽ ይልማ የሚሰጠው ሰላምታም ተመሳሳይ ነው።

አባቴ ችግር ሲያወራ አይቼው አላውቅም ፤ ዝም ብሎ የቻለውን ያደርጋል ፤ ምን አልባት ለእኔ ማውራት አያበድረኝ ፣ አይሞላልኝ ብሎ ይሆናል እንዳልል ስራ ላለው ለታላቅ ወንድሜም እንኳን አያወራም ።

ስራ በያዝኩ በሶስተኛ ወሬ በአንዴ አራት ሙሉ ልብስ ገዛሁለት ። ደስ አለው በጣም ።
እጄን ይዞ
አትጣ
ሞገስ ልበስ
የአንተ የሆነ ሁሉ ይባረክልህ ብሎ መረቀኝ

በአራተኛው ቀን ........ከገዛህልኝ ሁለቱን ሙሉ ልብስ ለወዳጄ እና ለበሪሁን መስጠት ፈልጌ ነበር አለኝ (ወዳጄ እና በሪሁን ወንድሞቹ ናቸው)

ቅር ይልህ ይሆን ብሎ አይን አይኔን አየኝ

አጠያየቁ አስተያየቱ የሆነ የሚያሳዝን ነው ፤ አንጀቴን በላው

ከእነሱ ጋ በጋራ መዘነጥ ፈልጎ ከእነሱ ተለይቶ ላለመድመቅ ነው መሰለኝ

ሌላ ቃል ስላጣው አይ ጋሼ ብዬ እጁን ሳምኩት!!!
© Adhanom Mitiku
💥📚ኢትዮ-ልቦለድ📚📖💥
Photo
🦅 ከንስር ልንማራቸው የሚገቡ ሰባቱ የአዕምሮ ለዋጭ ባህሪያት 🦅

1⃣ #ንስሮች_ብቻቸውን_በታላቅ_ከፍታ_ይበራሉ

ንስሮች ከእርግቦች፣ ከድንቢጦች ወይም ከትናንሽ የወፍ ዝርያዎች ጋር አብረው አይበሩም።

📝 ትርጉም:- ጠባብ አስተሳሰብ ካላቸው ሰዎች ራቅ። ከአቅምህ በታች እንድትበር ያደርጉሀል። ንስሮች ሲበሩ ሊታዩ የሚችሉት ከንስር ጋር ነው። በአካባቢህ እንዲሆኑ የምትፈቅድላቸው ሰዎች ለአንተ ማንነት መለያዎች ናቸው። ጥሩ ጓደኞችን አጥብቀህ ያዝ።

2⃣ #ንስሮች_ታላቅ_የማየት_ችሎታ_አላቸው

ከአምስት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሆነው አንድን ነገር በአትኩሮት መመልከት ይችላሉ። የተመለከቱትንም እንቅፋት ቢኖር እንኳ እስከሚያገኙት ድረስ አትኩሮታቸውን አይለውጡም።

📝 ትርጉም፡-  በህይወትህ የራስህን አላማ ያዝ። እንቅፋቶች ቢኖሩም ከአለምከው ነገር ፍንክች አትበል።

3⃣ #ንስሮች_ፍርሀት_የለሽ_ናቸው

ንስሮች በሚያድኑት ታዳኝ ጥንካሬ እና ግዝፈት አይበገሩም። ታዳኛቸውን ለማሸነፍ ወይንም ግዛታቸውን ለማስመለስ ሁልጊዜም ይፋለማሉ።

📝 ትርጉም፡- የገጠመህ ችግር ምንም ያህል ትልቅ ወይንም አዳጋች ቢሆን ተስፋ አትቁረት። ይልቁንም ተጋፈጠው። ስኬታማ ሰዎች የማይፈሩ ናቸው። ችግሮቻቸውንም በቀጥታ የሚጋፈጡ ናቸው።

4⃣ ንስሮች_ግትር_ናቸው።

ንስሮች ማዕበልን ይወዳሉ። ዳመናዎች ሲሰበሰቡ ንስሮች በደስታ ይሞላሉ። የማዕበሉንም ንፋስ በመጠቀም ወደ ከፍታ ይወጣሉ። ሀይለኛ ንፋስም ካለ ከዳመና በላይ እንዲያወጣቸው ይጠቀሙበታል።  ከዳመና በላይ መሆንም ለክንፋ እረፍትን ይሰጠዋል። ሌሎቹ አዕዋፋት ግን እራሳቸውን በቅርንጫፎች እና በዛፎች ደብቀው ይቆያሉ።

📝 ትርጉም፡- ስኬታማ ሰዎች በሚገጥማቸው ማዕበል በፍርሀት ከመዋት ይልቅ  ማዕበሉን ለትርፋማነታቸው ይጠቀሙበታል።

5⃣ #ንስሮች_የሞቱ_ነገሮችን_አይመገቡም

ራሳቸው ያልገደሉትን ካልሆነ ሞቶ የተገኘን ነገር አይመገቡም።

📝 ትርጉም፡- ባለፉ ስኬትህ ደስተኛ ሆነህ አትርጋ ይልቁንም አዳዲስ ወሰኖችን ለመግዛት እራስህን አዘጋጅ። ያለፈውን ነገር ቦታው አስቀምጠው። ቦታውም ኋላ ነውና።

6⃣ ንስሮች_እራሳቸውን_ያሰለጥናሉ

ንስሮች ላባቸውንና የሚኖሩበት ጎጆ የተሰራበትን ሳር ያስወግዷቸዋል። ምክንያቱም አዳዲሶቹ ጫጩቶች ለመብረር የሚያደርጉትን ጥረት አዳጋች ለማድረግ ብለው። ጫጩቶቹም በሚኖሩበት ጎጆ ውስጥ መቆየት ሊቋቋሙት የማችሉት ደረጃ ላይ ሲደርስ መብረር ይጀምራሉ።

📝 ትርጉም፡- የምቹነት ቦታህን (Comfort Zone) ለቀህ ውጣ። ምክንያቱም በዚያ እድገት የለምና።

7⃣ #ንስሮች_ህያውነትን_ይተገብሩታል

ንስሮች በሚያረጁበት ሰዓት ላባቸው በጣም ደካማ ይሆንና የሚፈልጉት ቦታ በሚፈልጉት ፍጥነት መሄድ ያዳግታቸዋል። ይህም ሞቱን የሚያፈጥን ስለሆነ ራቅ ብሎ 🗻 ተራራ ላይ ይወጣና ደካማ ላባዎቹን ይነቅላቸዋል። መንቁረንና ጥፍሩን ሙሉ በሙሉ ራቁቱን እስከሚሆን ድረስ ከአለቶች ጋር እያጋጨ ይሰባብራቸዋል። ከከፍተኛ ህመም በኋላም ድብቅ ስፍራ በመሄድ ላባው፣ ጥፍሩ እና መንቁሩ እንደአዲስ እስከሚበቅሉ በዚው ይቆያል። ከዛም ከዚህ በፊት ያልወጣውን ትልቅ ርቀት መጓዝ ይጀምራል።

📝 ትርጉም፡- ምንም ያህል ከባድ ቢሆን ከዚህ በኋላ በህይወትህ ለውጥን የማያመጣልህን ወይንም የሚያቃጥሉህን መጥፎ ልማዶች አስወግዳቸው ምክንያቱም ውድቀትህን ያፋጥኑታልና።


📚 @ethioleboled
18+

ክፍል አንድ- ፩

ወንድ ልጅ ሆዱን ይወዳል ፦

ላጤ ህይወት አሰልቺ የሚያደርገው ጠዋት ማታ ወጥ መቀቀሉ ነው መሰለኝ ።

መጀመርያ ስድስት ቀን ስራዬ ብዬ ወጥ እየሰራሁ፣ ባለሙያ ነኝ፣ እያልኩ እየሸለልኩ ነበር ፤ ሰለቸኝ። መሰልቸቴን እና ርሃቤን ለማስታረቅ ሉሊት የምትባል ተመላላሽ የምታግዘኝ ልጅ ቀጠርኩ።

ምን ልስራ እያለች አንድ ሶስቴ ስትወተውተኝ ፤
ይሄውልሽ ሉሊት ዱባ እና ቂንጬ ብቻ አትስሪ እንጂ ምንም አይነት ምግብ እበላለሁ አልኳት ። ዱባ ወይ ቂንጬ ትወዳለች መሰለኝ አብዝተን የምንወደውን አብዝተው የሚጠሉ ሰዎች ሲገጥመን የምናየው አይነት ነው ያየቺኝ።

እኛ የምንወደውን የማይወዱ ሰዎችን ማክበር የስልጣኔ ምልክት ነው አይደል ?

በርግጥ ሉሊት እኔ የምወደውን መቃወም አትችልም አለቃዋም አይደለሁ ። በርግጥ ስልጣኔ ወደ ታች ብቻ ማክበር አይደለም ወደ ላይም እንጂ !

ሉሊት እና እኔ ብዙ ግዜ አንገናኝም ወጥ ሰርታልኝ ፣ ቤት አፅድታልኝ ፣ ልብስ አጥባልኝ ትሄዳለች

የሰራችሁ ወጥ ብዙ ካልተበላ
" አልጣፈጠህም? ፣ ምነው ጨው በዛ? ፣ ምን ሆነ ምን ላስተካክልልህ ? ... "ትለኛለች።

"ኧረ ቆንጆ ነው ሰሞኑን ግብዣ እየገጠመኝ " ገለመሌ አይነት ምክንያት እነግራታለሁ ።

የተቀበሉትን ሃላፊነት በዋዛ አለመመልከት ሉሊትን ይመስለኛል ።

ሉሊት አስቤዛ የጎደለ ቀን ስልኬን ፋታ አትሰጠውም ቴክስት ታደርጋለች ደጋግማ ትደውላለች ።

ኋላፊነቷን ለመወጣት ይሉኝታ የላትም !

በቀደም እለት ከአራት ሰዓት ጀምሮ ስልኬን መቀጥቀጥ ጀመረች ። "ሉሊት እየነዳሁ ነው ሳቆም እደውላለሁ" ቴክስት ላኩላት ።

አስራ አንድ ሰዓት ላይ አልጨረስክም ወይ ብላ ከሚስቅ ስቲከር ጋር ቴክስት ላከችልኝ።
የሚስቀው ስቲከር ምን ያደርጋል ? ?

የላኩትን ቴክስት መልሼ አየሁት

"እየበዳሁ ነው መልሼ እደውላለሁ ነው የሚለው።"

ክው አልኩ ምን ልበላት : እምለው አጣሁ ።

"ሉሊት ያው ቃላት ገድፌ ነው
እ ...እየነዳሁ ነው ለማለት" የሚል ቴክስት እያንዳንዶን ቃላት በጥንቃቄ አይቼ ደጋግሜ አንብቤ ላኩ

ጥንቃቅያችን ከሰራነው ስህተት ይመነጭ የለ !?

"ገብቶኛል ኧረ አብሽር፤ ሙሉ ቀን ስትበዳ ማለቴ ስትነዳ እንደማትውል እገምታለሁ" አለችኝ።

ሌላ መደንገጥ፦

ሃሙስ ከሰዓት የሆነ ዶክመንት አስፈልጎኝ እቤት
ስሄድ ሉሊትን ወጥ እየሰራች አገኘኋት።

እንደ ድሮ ሰፊ ቀሚስ ሻሽ ሹራብ አለበሰችም ። ቱታ እና ቲሸርት ነው የለበሰችው ።

የበቀደምለታው ቴክስት መቀመጫዋን፣ ጡቷን፣ ዳሌዋን እንዳየው መራኝ።

ሞንዳላ ናት፣ ዳሌዋን፣ መቀመጫዋን፣ ጡቷን ላለማየት አይኔን ወደ ቁምሳጥኑ፣ ጥግ ላይ ወዳለው መወልወያ፣ ወደ መፅሃፍ መደርደርያ ጠርዝ... እልከዋለሁ ብዙ አይቆይም አይኔን ሉሊት መቀመጫ ወይ ጡት ላይ አገኘዋለሁ።

ወንድ ልጅ የተሞናደለ ይወዳል !

መቀመጫዋ፣ ጡቷ፣ ፊቷን እንዳስተውለው ገፋኝ
ያይኗ ሽፋሽፍት ያምራል ። ቅላቷ ያምራል ፣ ከንፈሯ ያምራል፣ ሉሊት ቆንጆ ናት መልኳ ድህነቷን ድል አድርጎታል።

ሉሊት የተሟላች ነች ለካ። ሙያዋ ....መልኳ.... ከሁሉ ከሁሉ መሞናደሏ ...!

ከአራት ወር በኋላ ሉሊትን አዳም ሄዋንን እንዳወቃት ለማወቅ ሻትኩኝ ።

ተሳስቼ የፃፍኳት ሆሄ የተሞናደለ ሰውነቷን ውበቷን ገላለጠልኝ።

ኤጭ እንኳን ተሳሳትኩ
ከምታነብ ሴት ጋር አትከራከር!

ካደኩበት ሀይቅ ዳር አካባቢ ከሁሉ የተለዩ የሚመስሉኝ አንድ አሳ አጥማጅ ባልና እጅግ በጣም አንባቢ የሆነች ሚስቱን አውቅ ነበር፡፡

✍️አንድ ቀን ታዲያ አሳ አጥማጁ ባል ደክሞት ለማረፍ ወደ ቤቱ መጣና ከሶፋው ላይ ወድቆ እያንኮራፋ እንቅልፉን ይለጥጠው ጀመር፡፡ ሚስት ማንበብ አልቻለችም ስለዚህ ለየት ያለ ነገር ማድረግ አሰበችና መጽሃፏን ይዛ ከቤት ወጣች፡፡

✍️የባሏን ጀልባ ወደ አንድ ጸጥተኛ የሀይቁ ክፍል ቀዘፈችና በስሱ በሚዳብሰው ነፋሻማ አየር እየተዝናናች መጽሃፏን ገልጣ ማንበቧን ቀጠለች፡፡

✍️ከጥቂት ቆይታዎች በኋላ በድንገት የባህሩ ላይ ጠባቂዎች ጀልባ ከች አለ፡፡ ኮስታራው ፖሊስም ማይክራፎኑን በእጁ አንከርፍፎ ይለፈልፍ ጀመር

✍️‹‹ምን እያደረጉ ነው እመቤቴ!››
‹‹መጽሃፍ እያነበብኩ!›› (ምን እንደማደርግ አይታየውም እንዴ! በማለት እየተገረመች!)

🎮‹‹ እመቤቴ በተከለከለው የሀይቁን ክፍል ላይ ስለሚገኙ በፍጥነት አካባቢውን ይልቀቁ!››
‹‹ምን አጠፋሁ ጌታው!›› አለች ደርባባዋ እመቤት
‹‹በዚህኛው የሀይቁ ክፍል አሳ ማጥመድ አይፈቀድም እመቤት!››

🤔‹‹እሱን አውቃለሁ ጌታው! ሆኖም እንደሚያዩኝ አሳ እያጠመድሁ ሳይሆን መጽሃፍ እያነበብኩ ነው!››

🟠ፖሊሱ ፈገግ ብሎ ‹‹እንደማየው ጀልባዎ በአሳ ማጥመጃ መሳሪያዎች ተሞልቷል፤ ስለዚህ እኛ በሌለንበት በማንኛዋም ደቂቃ መረብዎን ጥለው እንደሚያጠምዱ እገምታለሁ፡፡ ስለዚህ አሁኑኑ አካባቢውን ጥለው የማይሔዱ ከሆነ ባልተፈቀደ ቦታ አሳ በማጥመድ በሚለው አንቀጽ መሰረት በቁጥጥር ስር የማውሎት መሆኑን ይገንዘቡ!››

✍️ሴትየዋም ፈገግ ብላ አየችውና ‹‹ጌታው እንዲያ የሚያደርጉ ከሆነ እኔም ጾታዊ ትንኮሳና አስገድዶ መድፈር በሚለው አንቀጽ መሰረት የምከስዎ መሆኑን ይወቁ!›› አለች ኮምጨጭ ብላ

✍️‹‹አይቀልዱ እመቤቴ ይህ የስራ ጉዳይ ነው! እንኳን ልተነኩስዎና ልደፍርዎ ቀርቶ አጠገብዎ እንኳን እንዳልደርስኩ ያውቃሉ!››

✍️‹‹ እውነት ነው አውቃለሁ፡፡ ሆኖም ያንን ለማድረጊያ (መድፈሪያና መተንኮሻ ይሆን!) የሚያገለግል ማንኛውንም አይነት መሳሪያ እንደያዙና ጭር ሲልልዎ በማንኛዋም ደቂቃ ያን ሊያደርጉ እንደሚችሉ እገምታለሁ!›› አለች ደፋሯ እመቤት

🛡ፖሊሱም ጥቂት አሰብ አደረገና ‹‹ መልካም ቀን ይሁንልዎ እመቤቴ! ይጠንቀቁ!›› የጀልባውን ሞተር ኮርኩሮ ጉዞውን ቀጠለ፡፡

➡️ከአንባቢ ሴት ጋር አትከራከር!
ብልህና አስተዋይ ስለምትሆን ትቀጣሃለች
!
ግልድፍድፍ ያልኩኝ ነኝ ። የሃይማኖት እወቀት የለኝም ። ሚስጥረ ሥላሴ አይገባኝም የመላዓክት እና የሰማዓታት ድርሻ አላውቅም ።

የሃይማኖት ጉዳይ ላይ ተመራምሬም ጠይቄም ተምሬም አላውቅም ። ክብረ በዓል ሲደርስ እሳለማለሁ ።

በቃ እንዲ ነኝ!

ፈሪሃ እግዜር ያለኝ ኢ አማኝ ነው የምመስለው ።
አልፀልይም ፣አልፆምም ፣ተስዬ አላቅም ።

ዝም ብዬ የሆነልኝ መልካም ነገር ከጌታ ጋ አገኘናኛለሁ ። ደስ ሲለኝ ተመስገን፣ ተመስገን እላለሁ ፦

በቃ ይቺ ብቻ ነኝ ።

ሚስቴ ምጧ መጥቶ የመንግስት ሆስፒታል ገባች ። ምጧ በረታ .....ስትጮህ ሰማኋት ። አጯጯኋ ሆዴን አንጀቴን ገለባበጠው ....ከሞተች አስር አመት የሆናትን እናቷን አልማ.....ዜ. እና...ቴ እያለች ትጣራለች .....

ተ...ሼኤኤኤ( ተሼ እኔ ነኝ) ድረስልኝ ሞትኩብህ ስትለኝ እምባዬን እያፈሰስኩ አጠገባችን ወደ ነበረው ቤተክርስትያን ሄድኩ ።

አጠገቧ እኮ ነው መሆን ያለብኝ ግን አቃተኝ ።

ጌታዬ ጋ ልነግረው እየሆነ ያለውን ሄድኩ። በሩ ላይ ስደርስ መሬት ላይ ተዘርፍጬ ጌታዬ ሚስቴ ልትወልድ አይደል?? ምጡ በረታባት እርዳት እንጂ....🙏እርዳን እንጂ ...

በሰላም ከተገላገለች አንድ ጥላ አስገባለሁ ...እንደውም ሁለት... ምን ይሄ ብቻ ፍስለታን እፆማለሁ ...እምባዬ አላስለምን አለኝ

ጌታዬ ካንተ በቀር ማን አለን ....

ተመልሼ እየሮጥኩ ወደ ሃኪም ቤት ደረስኩ ወደ ውስጥ መግባት አቃተኝ እግሬ ብርክ ያዘው ልቤ ዝም ብሎ ድው ድው ይላል

ከስንት ደመነፍሳዊ እርምጃ በኋላ

በር ላይ ደረስኩ ። ዘመዶቿ ተሰብስበው እንኳን ደስ አለህ ሴት ልጅ ተገላገለች አሉኝ አሁንም እምባዬ ዝም ብሎ ፈሰሰ።

ወደ ውስጥ በምልክት አስፈቀጄ ገባሁ ሚስቴን
አየኋት እንቅልፍ ሸለብ አድርጓት ፣ ህፃኔን አየኋት

ሌላ ሳግ ሌላ እምባ

ሌላ ምስጋና ሌላ መባባት ሌላ ደስታ

ጌታዬ ሆይ ተመስገን ደሞ በጭራሽ ስለቴን አልረሳም
የቷ?

ይቺ:-

ሊነኩት ሊዳስሱት እንደሚጓጉለት ውድ ነገር ናት። ሁለመናዋ ሚያሳሳ የሆነ ህልም ብጤ ።

የልብሶቿ quality ህያው የሚመስሉ። ንግግሯ፣እውቀቷ፣ውበቷ፣ትህትናዋ፣ሀብቷ፣ልግስናዋ ሁሉን አሟልቶ የሰጣት(ወይስ ዋጋ ከፍላ ያገኘችው? እንጃ)

ብቻ ህመም፣ለቅሶ፣ስቃይ፣ብቸኝነት፣ተስፋ መቁረጥ እንኳን ሊደርሱባት ሰምታ የምታውቅ የማትመስል(የሷ ለሊቶችስ እንቅልፍ አልባ ቢሆኑስ?አንተ ህልም ናት ብትልም ህልሟ ገና ካልተፈታላትስ ማን ያውቃል) 

ያቺ:-

ምን ገዷት የአለም ጣጣ።መንፈሳዊውስ ቢሆን ለሷ ያው ነው ለሷ መሆን ካልቻሉ (ወይስ እሷ ናት እንዲ ብላ ምታስበው?)

ያም ሆነ ይህ እሷ ስለምን ትጨነቃለች ስለ ልብስ፣ስለ     ሀብት፣ቤተሰብ፣ባህል፣ልማድ፣ሀይማኖት፣ሀገር፣ያለፈው፣የሚመጣው ይሄ ሁሉ ለሷ ምንድናቸው?ምንም በቃ የትም ውላ ይመሽላታል ደሞ ይነጋላታል የት? አንዱ ዛፍ ስር ደሞ ደግነቱ አውሬ አይነካት ብርድ አይቀስፋት በቃ ትኖራለች?በምንም።

ስትለፈልፍ የሰማት ደስ ያለው ብር ይሰጣታል ወይ ሚጎረስ ነገር በቃ ትኖራለች ።ያውስ መኖር ቢሉ መኖር ነው ምትፈልገውን አውርታ ያውም በነፃነት የወር የአመት ቀለብ የለባት ልጅ የላት ድስት በቃ እንዲሁ መኖር። የሷ የምናገር ነፃነት ከድፍን አለም ህዝብ አይበልጥም ብላችሁ ነው?

በመሀል:-

"አለች አንዲት ምስኪን" ተብሎ የህይወት ታሪኳ ሚጀምር ።በቃ ኑሮ ሳይሆን ችግር ምትኖር።

ሁሌም የትም የበታች የሆነች ምትበላው በባሏ ልግስና የሆነ ፤በአናት በአናቱ ወልዳ ተስፋ ቢስ የሆነች ፤ገና መኖር ሳትጀምር ያረጀች፤ ሰዎች የመረጡላትን ብቻ የምትኖር ፤ብትለብስ ብትወልድ ብትኖር ሰዎች ስለፈቀዱ ነው።

ህልም የሚታለም እንጂ የሚኖር አደለም ብለው ያሳመኗት (ፈርደውባት ወይስ ፈቅዳ እንጃ?)

ግን ማንስ ቢሆን ምገፋትን ይወዳል?ሁሌ አዳፋ የልጆቿ ማደግ እንጂ የሷ መጎስቆል ማይታያት አለች በመሀል

ታዲያ የትኛዋ ቀልብህን ገዛችው? የትኛዋ አሳዘነችህ? በየትኛዋ ቀናህ? መልስህ ምንም ይሁን ምን እኔ ግን ይቺን ወይ ያቺን እሆናለሁ እንጂ በመሀል ከመዋለል ሞት አይሻልም እንዴ? ብላ ጥላኝ ሄደች

ሆሆ ይሄ ሁሉ ዝብዘባ እኮ ምን አይነት ሴት መሆን ትፈልጊያሽ ብያት እኮ ነው የሆነች ወፈፌ

©nani
ያደረግኩትን ካደረግኩ በኃላ ፈገግ አለች....በስነስርአቴ የተደሰተች መስሎኝ ደስ አለኝ....አብሬያት አገጠጥኩ....


"ለምንድን ነው የሳቅከው..."....ስትለኝ የምመልስላት አጣሁ..."ስትስቂ ነው የሳቅኩት... "..ይባላል....?

"እኔንጃ.... ስለሳቅሽ መሰለኝ....".....ሳቋን ደገመችው...አሁን ነው ያስተዋልኳት...ሳቋ ላይ ፌዝ አለ....

"ምን ያስቃል....?"

"ቅድም ነበር ይሄን መጠየቅ የነበረብህ...."

"አሁን ጠየቅኩሻ...."....ስናደድ በማወጣው ድምፅ ነው ይሄን ያልኳት...

"ይልቅ ስለ ቅድሙ ሳቄ ልንገርህ...."....አለችኝ ረጋ ብላ...ለመስማት ተመቻቸሁ....

"ቅድም ምንድን ነው ያደረግከው..."

"ምን አደረግኩ....?....."....ከልቤ አላደረግኩትም መሰለኝ ከመቅፅበት ረሳሁት...

"የወደቀውን እንጀራ አነሳኸው...ከዛ ሳምከው...ከዛ ጣልከው..."

"እና ምን ያስቃል...ሲደረግ አይተሽ አታውቂም...እንጀራ ሲረገጥ ግፍ እንደሆነ አታውቂም...."....ከዚህ ንግግሬ በኃላ ሳቋ አላባራ አለ......


"አልመለስሽልኝም ምን ያስቃል...."....ጮህኩባት....

"የሹፈት ሳቁን ምን አመጣው...."...ሳቋን አልገታ ስትለኝ ጥያቄ ደገምኩ...

"ልትጥለው ለምን ሳምከው...."...መልሳ ጠየቀችኝ....

"እንዳይረገጥ...."...መለስኩ

"ግፍ ፈርተህ ማለት ነው...."....አዎ አልኳት በአንገቴ ንቅናቄ....ዝም ብዬ ሳያት እስቲ ዝም ብዬ ልከራከረው..ላናደው....ልቃረነው ብላ እኔ ጋር የምትመጣ ይመስለኛል....ብዙ ጊዜ አይቻታለሁ ግን ልትገባኝ አልቻለችም....



"ለማንኛውም ተረጋጋ...ይሄ ነገር ስለማይገባኝ ነው...መልሰህ ለምትጥለው መሳሙን ምን አመጣው...ላትበላው ነገር አቧራውን ማራገፉ ምንድን ነው...ከመሬት ላታላቅቀው ጥግ ማስያዙ ምን ይፈይዳል...እንጀራው ነብስ ቢኖረው ስታነሳው የሚሰንቀው ተስፋ ...ካፍህ ስታስጠጋው ደግሞ አስበው...ቤቱ ጠፍቶበት መንገድ የወደቀን ህፃን አንተ ቤቱን እያወቅከው አንስተህ ልብስ ገዝተህ መልሰህ ጥግ አስይዘህ እንደመጣል ነው..."

በተራዬ ከት ብዬ ሳቅኩ....."ለምን ትስቃለህ...ምን ያስቅሀል...?"...ብላ እንድትጠይቀኝ ጠበቅኩ...እሷ እኔን ትታ አየር አየሩን ታያለች....


"ምን ያስቅሀል አይባልም...?"

"ምን እንደሚያስቅህ እያወቅኩ ምን አሰጠየቀኝ...."

"እሺ አትናደጂም...?"

"ካንተ ከዚህ የተሻለ አረዳድ ስለማልጠብቅ አልናደድም....".....

"ምን ማለት ነው...."....በገንኩ....

"ኡፍ አቤል ሳትጠይቅ ለመረዳት ሞክር...አንዴም ተረድተኃኝ ስለማታውቅ እንድትረዳኝ አልጠብቅም...ባልጠበቅከው ነገር ደግሞ አትናደድም...."

ዝምታ መሀላችን ተመቻችቶ ተቀመጠ.....ቡናችን ከእጣን ጢስ ጋር መጣ....አስተሳሰቧ ያስደነግጠኛል....ስታስተውል ጉድ ታስብላለች...ቡናዬን ሳማስል ሳይቀር እየተጠነቀቅኩ ነው...ደግሞ ምን ትላለች እያልኩ...ብዙ አትከራከረኝም...የዛሬ ሁለት አመት የነበረው ጭቅጭቃችን በርዷል....ተስማምተን ወይም አንድ ሆነን አይደለም...ሁሉ ነገሬን አስተውላ ደክሟት ነው.....አንዳንዴ እንትጨቀጭቀኝ እና ለምን እንትለኝ እያወቅኩ አጠፋለሁ...የእርሷ መልስ ዝምታ ወይንም የሹፈት ሳቅ ነው....


"ታውቃለህ አቤላ አሁን አንስተህ ስለጣልከው እንጀራ ስናወራ የሆነ ቁም ነገር ታስተውላለህ ብዬ ነበር...ማለት አንድ አንዴ እንኳን ታስባለህ ብዬ አስብ ነበር...."

"ምን ማለት ነው አንዳንዴ ታስባለህ ማለት..."....ድምፄ ላይ ንዴት አለ....

"ኡፍ አቤል ኡፍ...."....ከተቀመጠችበት ተነሳች....ተከትያት ስነሳ ላየኝ ሰው በእሷ መቀመጫ የምጠቀም ነው የምመስለው...

"ምን እየሆንሽ ነው...."

"እየሄድኩ...."

"መሄድን ምን አመጣው...."

"ፍራቻ...እና ስልቸታ...."

"ምን እንደሰለቸሽ አውቃለሁ....ግን የምን ፍርሀት ነው....."

"ስመህ እንደጣልከው እንጀራ ትጥለኛለህ የሚል ፍራቻ...."

"ኧረ ሄሉ ተረጋጊ...ብለን ብለን በእንጀራ እንጣላ...ከዚህ በኃላ የምን ማንሳት የምን መሳም አሽቀንጥሬ ነው የምጥለው....ቁጭ በይ እናውራ...."

"መቼም አይገባህም...ደነዝ ነህ አንተ....".....ብላኝ ፈረጠጠች....


ከገባችሁ አስረዱኝ...እኔ ምንም አልገባኝም...🤷‍♂









https://www.tg-me.com/ethioleboled
የዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል ፤

ታህሳስ - 1947 ዓ.ም

አዲስ አበባ

#ታሪክን_ወደኋላ
ነበር......1




"ብቸኝነት እየተሰማኝ ነው...እንደውም አንዳንዴ ከሌላ ፕላኔት የመጣሁ እስኪመስለኝ ድረስ "....


ከብዙ ጊዜ በኃላ ይቺን አለ...ላለፉት 6 ወራት ዝምታ መርሁ ነበር...ዝምምምም...በቃ ጭጭጭጭጭ...አንዳንዴ ብቻ ከመኝታ ቤቱ ከሚወጣው ሙዚቃ በቀር ምንም አይሰማም... የእሱ የሚባል ድምፅ ካለ ሲያስነጥስ አልያም ሲያስል የሚሰማ ነበር...

"ምነው ልጄ ብትተው...ከሰው ተፈጥረህ እንደ አውሬ ብቻህን ...ምነው ሳንሞት ገደልከን ...አሄሄሄሄ"....ከሚል የእናቱ ምሬት ጀምሮ

"ምነው በማምሻችን የወላድ መካን ባታደርገን ..." ከሚል የአባቱ ወቀሳ

"ቀለል አርገው እንጂ ...ያጋጥማል...just learn from it and move on with your life"....ከሚል የተመልካች አስተያየት ጭምር...


"ተበላሸ ...አይይይይ ተስፋም የለው...መጋኛ አግኝቶታል መሰል ...አይይይ ተምሮ ተምሮ መና..."...እስከሚሉ ሽሙጫዎች ...ሁሉንም ጠግቧል።


ለምን ለነዚህ እረፍት ለሚነሱ ድምፆች ትኩረት ነሳ...? ማንም አያውቅም..ደፍሮ የሚጠይቀውም የለም....ለታ ከእነዚህ ሁሉ ድምፆች የሚልቅ ድምፅ አእምሮው ውስጥ ስለሚደጋገም ለእነዚህ ድምፆች ባዳ ነው....


"ጓደኛዬ ጥለኧኝ አትሂድ..."...የክብሮም ድምፅ.......

"ያንተን ሚስትማ ያሳየኝ ካካካ እኔኮ ግርም የምትለኝ ከዝንጀሮ ትንሽ መለስ ብለህ አይኗ ፣ጥርሷ፣ ወገቧ...ምናምን ካካካ ምንድን ነው እንዲህ ያዙኝ ልቀቁኝ"...የክብሮም ተረባ

"የመጀመሪያ ሚዜህ እንዳታደርገኝ አደራ....ሙሽራው ማነው ምናምን ሲባል አስበኧዋል..."....የተለመደ ጨዋታው...

"አለውልህ..."....የሚያሳርፍ ተገንነቱ.....

"ለታ አትተወኝ...."....የመጨረሻ ንግግሩ...በቃ አእምሮው በእሱ ድምፅ ታጭቋል....



"ልጄ የክብሮም እናት መጥተዋል...እንደው እኛ መሄድ ሲገባን...በዚህ ሀዘናቸው ላይ ሊጠይቁን መጡ...በል ና እና ሰላም በላቸው..."

"የክብ...ማለት እቴቴ...ለምን....?ስለ እኔ ጠይቀውሻል...ስለዛን እለት..የክብ"....ተንተባተበ.....እናቱ ደነገጡ....ደርቀው ቀሩ...

"ምነው ልጄ ደነገጥክ...."....አሉ የሞት ሞታቸውን...

"አይ እማዬ...በቃ የለም በያቸው ...."...ከቅድሙ መርበትበቱ ላይ መንቀዥቀዥም አከለበት...ጠባብ ክፍሉን በቅፅበት ፈረስ የሚያስጋልብ ሜዳ አረጋት ተንጎራደደባት.....


"ምን ሆነሀል...ልጥራው ብዬ መጥቼ...ምነው ልጄ በዚህ እድሜዬ በአንድ አፍ ሁለት ምላስ ይኑርሽ ባትለኝ...ትንሽ አጫውተሀቸው ትመለሳለህ...ደግሞም ብቻቸውን መሆኑ ከብዷቸው ይሆን ይሆናል እንጂ ወጉማ እንዲህ አልነበረም...ልጅን ቀብሮ ሰው ጥየቃ አሄሄሄሄሄ ተወው እስኪ..."

"እማዬ እባክሽ...ተኝቷል ...አሞታል...ከፈለግሽም ሞቷል...የለግሽውን በያቸው በቃ በቃ እማ የፈለግሽውን...".....ተርበተበተ...


"የዲማው ጊዮርጊስ....ምነው አንተ ምነው ልጄ ...አዬዬዬዬዬ ወልዶ መና ወልዶ መና...አበደ ልጄ ለየለት...."....ይሄን ጊዜ እዛው ለቅሶ ጀመሩ...ድምፃቸው እንኳን ሳሎን ቤት ከተቀመጡትን እንግዳ ሊደበቅ ቀርቶ ጎረቤት የሚረብሽ ሆነ...

"አንቱ...አንቱን እኮ ነው የምጠራው...አዳነ ኧረ አንቱ ሰውዬ...."...ባለቤታቸውን አንቱ ብለው የሚጠሩት እናቱ ድምፃቸው ከቅድሙ እጥፍ ሆነ።


ከክብሮም እናት ሊደበቅ የተናገራት ንግግር ለሙሉ ጎረቤቱ አጋለጠው...


"አይ እርኩስ መንፈስ...".....ይላሉ አንደኛዋ...

"አዎ አይነ ጥላ ማይሰራው የለ..."...አይነቱን ደግሞ ሌላኛዋ ይወስናሉ...

"አይ ይሄ የሰው አይን ነው...የቡዳ መዘዝ ቀልድ መስሎሻል..."...ያርማሉ ሌላኛዋ...

"ኧረ ይሄ አይነጥላ ነው...የሰው አይን እንዲሁ ጠቁሮ ከተደቦለለ ነገር ያርፋል እንዴ ተያ...እርሱን በልቶ ማን በቃር ይሞታል...."....በአይነጥላ ላይ specialized ያረጉት ዶክተር ቢቸግር አሁንም አልተረቱም...

"አወቅሽ አወቅሽ ሲሉሽ ኤድያ...ያንቺም ልጅ የቡዳ መድሀኒት አስሮ ይሄዳል...አሁን እግዜር ያሳያችሁ ቢበላ ቢበላ የእርሷ ልጅ...ሆሆሆ"....

"ከልጄ አናት ወረድ...እንደውም ልጄን የቀረጠፍሽው አንቺ ነሽ...'የእርሷ ልጅ አይበላም' ኧረ አፈር ከድሜ ብይ ...እኔ አስካለ አይደለሁም ደቼ ካላበላሁሽ...ቱ..."....ሙያተኞቹ ሀሜታቸው ወደጥል ተቀየረ....

"ምን ታመጫለሽ...እስኪ እናይሻለን...ልጅ አለኝ ትያለሽ ደግሞ...ይሄ ሌባ ...ደግሞ የሰረቃትን ማንደጃዬን ቁጭ ካላረገ እሰራለታለሁ...."

"መኩሪያዬን ነው ሌባ ያልሽው...?..."...ብለው ቀሚሳቸውን እና ከስር ያሉ ተጨማሪ 3 ውስጥ ልብሳቸውን ሰብስበው ሰፈሩባቸው....በዚህ መሀል ለታ ከአባቱ እና ከእናቱ ንትርክ አረፍ አለ... ለአፍታም ቢሆን የማሰቢያ እና ከክብሮም እናት የማምለጫ ጊዜ አገኘ...... ከመሀላቸው ከአንድ ሰው በቀር ሁሉም ትኩረቱ ተሰረቀ...



ለታ ይሄን አጋጣሚ እንደ ቀላል አላየውም....ግርግሩን ተጠቅሞ ጥግ ጥጉን ሄዶ የጊቢው በር ላይ ደረሰ.....ደስ አለው...የገነትን ቁልፍ ያገኘ ያህል....በሩን ከፍቶ አንድ እግሩን እንዳስወጣ ከኃላ ድምፅ ሰማ...ከጫጫታው የተገነጠለ ድምፅ...የተረጋጋ...


"አቡ...."......'አቡ' የሚሉት የክብሮም እናት ብቻ ናቸው.....ባለበት ደርቆ ቀረ።






ይቀጥላል.....ኮመንት ማድረግ እንዳይረሳ🙏




Shewit dorka





https://www.tg-me.com/ethioleboled
ከነገ ጋር



"አልፈራህም..."


"እንዴት...."


"አልፈራህማ በቃ...."


"እኮ እንዴት"


"በቃ አልፈራህም አትነዝንዘኝ!"


"ከነገ ጋር ግን እንዲህ መሳፈጥ ልክ ነው...?"


"አካሄዴ ከፈጠረኝ ጋር ስለሆነ አንተ ጥሩ ነገሮችን ይዘህ ከመምጣት ውጪ አማራጭ የለህም..."


"በእኔ እንዲህ እርግጠኛ መሆን አትችይም!!!"


"ያንተ ደራሲ ፈጣሪ ነው...እርሱ ነው ጌታህ...እሱ ካለህ ዝንፍ አትልም....ከእሱ መራቅ የጀመርኩ እንደሆነ ያኔ አትጠራጠር ያለቅጥ እፈራሀለሁ!...."


"እኔ ራሴ ፈራሁሽ"


"ወደህ ነው"



😊በርቱ💪



Shewit dorka
2024/09/22 15:27:17
Back to Top
HTML Embed Code: