Telegram Web Link
ፀሐይ ወጣ ከሮሜ
ያሬዳውያን መንፈሳዊ የቅዱስ መርቆሬዎስ ማኅበር
ፀሀይ ወጣ ከሮሜ

ፀሀይ ወጣ ከሮሜ ብርሀን ነው ለአለም
መርቆሬዎስ /2/ የአምላክ ባለሟል


በእግዚአብሔር መላክ አሮስ ከሞት ድኗል
በሮም ሀገር መርቆሬዎስ ተወልዷል
እንደእናት አባቱ ኖህና ታቦት
በምግባር የፀና ሆነ በእምነት /2/

አዝ.........

ከእግዚአብሔር መላክ ሰይፍን ተቀናጅቷል
በጠላቶቹ ላይ ግርማውም ያስፈራል
ዲያብሎስ ይርዳል ስሙ ሲጠራበት
መርቆሬዎስ ብሎ ለተማፀነበት/2/

አዝ...........

እንደ ባስልዮስ እና ጎርጎርዮስ
ጋሹ አምባ ላይ ያለው ቅዱስ መርቆሬዎስ
ስለቴ ተሰማ ዘምር ዘምር አለኝ
መርቆሬዎስ ደርሶልኝ ችግሬ ቀለለኝ/2/

አዝ...........

ደምህን እንደጎርፍ ዳኬዎስ ቢያፈሰው
ስጋህን በእሳት ላይ ደፍሮ ሊያቃጥለዉ
የእሳቱን ቶን ደምህ አጥፎቶታል
ስለቅድስናው ሶስት አክሊል አግኝቷል/2/

አዝ............

አንገትህ ሲታረድ ቂሳርያ ታወከች
የተጋድሎ ፅናት ባይኖቿ ስላየች
ዝክርህን ዘክሮ ስምህን ለጠራ
በመንግስተ ሰማይ ይኖራል ካንተ ጋራ/2/
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
✞ቅዱስ መርቆሬዎስ✞
♡የመዝሙር ግጥሞች♡
#ቅዱስ_መርቆሬዎስ

ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕታዊው የኛ አባት
ተዋህዶን ምሰሶ ሆንካት
ከእናትህ ማህጸን ቸር አምላክ ሲያስብህ
ለኢትዮጲያ ብርሃን አረገህ(፪)
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
#ኅዳር_26_ #_ኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_አቡነ_ሀብተማርያም፡፡
#Share ያድርጉ
፠ አቡነ_ሀብተማርያም በሽዋ (የራውዕይ /ቡልጋ/) ከአባታቸው ፍሬ ቡሩክ ከእናታቸው ቅድስት ዮስቴና ነው የተወለዱት፡፡
፠ ወላጆቹ በተለይም እናቱ ከማግባቷ በፊት መናኝ ነበረች፡፡ ጻድቁን እንደምትወልድ በበቃ ባሕታዊ ተነግሯት ጻድቁን ወልዳ በጽድቅ ኑሮ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ በክብር አርፋለች፡፡
፠ ጻድቁ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ ‹‹እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ›› ሲባል ይሰማሉ፤ ይህንንም በሕፃን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ ‹‹ማረን እባክህን›› እያሉ ይሰግዱ ነበር፡፡ ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ፡፡ ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል፤ የፈጣሪውን ስም ያቃለለውን አንድ እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል፡፡
፠ ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው ትምህርትን ከቀሰሙ በኋላ መንነዋል፤ በታላቁ አባት በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ ከመነኰሱ በኋላም ብዙ ትርፋትንና ተጋድሎን ሠሩ፡፡ ለአብነትም፤
*ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ፤
*በየቀኑ 4ቱን ወንጌልንና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ፤
*በ40 ቀናት ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ፤
*ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ነው፤
*በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ፤
*ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ፥ ክቡር ደሙን ይጠጣሉ፤
*በልባቸው ውስጥ በፍጹም ቂምን፥ መከፋትን አላሳደሩም፡፡
* ረአዬ ኅቡዓት በመባል ይታወቃሉ፡፡
* በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ ቦታውን ሲባርኩት ሦስት አጋንንት በጸሎቱ ሥልጣን የታሠሩለት ታላቅ ጻድቅ ነው፡፡
* ‹‹#ጽድቅና_ትሩፋት_እንደ_ሀብተ_ማርያም፠››
፠ ጌታችን ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ተለያዩ ቦታዎች ይሔዱ ነበር፡፡ ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በኋላም የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ እንዲህ አላቸው፤
* ‹‹ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ፤ ስለ ምናኔህ፣ ስለ ተባረከ ምንኵስናህ፣ ስለ ንጹሕ ድንግልናህ፣ ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ፣ ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ፣ ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ፡፡››
* በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን፤ 500 የዕንቊ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ፡፡ በስምህ የሚለምኑ፤ በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ ‹አማንየ በርእስየ› ብዬሃለሁ›› አላቸው፡፡
* ቅዱሳን መላእክትም ‹‹ሀብተ ማርያም ወንድማችን›› ሲሉ አቀፏቸው፡፡ ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው፡፡ ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች፡፡ በዝማሬም ወሰዷት፡፡
✤ ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ሥልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነርሱም፤
1ኛ. #_መብረቅ
2ኛ. #_ቸነፈር
3ኛ. #_ረሃብ
4ኛ. #_ወረርሽኝ
5ኛ. #_የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡
፠ በተሰጣቸው ቃል ኪዳንም ከላይ ያሉትን 5ት መቅሰፍቶች የሚያርቁ በመሆናቸው፤ ከጥንት ጀምሮ እስከ አሁን በደብረ ሊባኖስ ገዳም እነዚህ 5ቱ መቅሰፍቶች እንዳይቀርቡ የሀብተማርያም ካህናት ከኅዳር 1-7(10) ማዕጠንት ያጥናሉ፤ ደብረ ሊባኖስ ገዳምም ለደብረ ይሰበይ አቡነ ሀብተማርያም ገዳም 1ድ በሬ ስጦታን ያበረክታሉ፡፡
፠ በዛሬው ዕለት በኅዳር 26 ባረፈ ጊዜ፤ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው፤ በዝማሬ ፥ በማኅሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በጻድቁ መቃብር ቀበሩት፡፡
(ከወርቅ ንፁህ ፥ ከብርም የጠራ ፥ ከሁሉ የሚበልጥ ፥ የተመረጠ ፥ ሀብተማርያም መልአክ ዘበምድር ነው መልካሙ ዜናው እስከ አጽናፍ ተሰማ፡፡)
#_በዛሬዋ ዕለት #በናግራን ያሉ ክርስቲያኖች በ6ኛው ክፍለ ዘመን ሰማዕታት የኾኑበት ዕለትም ነው፡፡

@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
+ቤተ ክርስቲያን+
ወርቅ በእሳት በተፈተነ ቁጥር ጥራቱ እየጨመረ ይሄዳል። እንዲያውም በትርጓሜያችን ወርቅን ሰባት ጊዜ በከውር (በወርቅ ማቅለጫ) ሲያቀልጡት ከወርቅ የበለጠ ዕንቍ ይሆናል ይላል። ሰውም እንዲሁ ነው በመከራ በተፈተነ ቁጥር እንደ ወርቅ እየጠራ ይሄዳል። ሰማዕታት መከራውን አልፈው ቅድስናቸውንና ንጽሕናቸውን ገለጡ። ከመ ወርቅ በእሳት ፈተኖሙ የተባሉ ሰማዕታት ናቸው። እሳቱ የበለጠ ቢነድ ወርቁን የበለጠ ያጠራዋል። እሳት የሚያስፈራው ገለባን እንጂ ወርቅን አይደለም።

ቤተክርስቲያን ንጽሕት ናት። የንጽሕናዋ ምንጭ ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ከውስጥም ከውጭም የሚፈትኗት ብዙዎች ቢሆኑም ይህ ፈተናና መከራ ንጽሕናዋን የበለጠ ይገልጣል እንጂ በፈተናው አትጠፋም። የቤተክርስቲያን ራሷ ክርስቶስ ነው። በእርሱ ሁልጊዜ ደስ ይለናል።

ቤተክርስቲያን ለክፉዎች ሰይፍ ናት። እርሷን ተመርኩዘው በስሟ ቢነግዱ የሚጎዱት ራሳቸው ናቸው እንጂ ቤተክርስቲያን አይደለችም። በሽተኞች መድኃኒታቸውን ቢያቃጥሉ በሽተኞች ራሳቸው ይሞታሉ እንጂ መድኃኒቱ አይጎዳም።

ፈተናዎች እስከ ዕለተ ምጽአት መልካቸውን እየቀያየሩ ቢመጡ እኛ የበለጠ እየጠነከርን መሄድ አለብን እንጂ ተስፋ መቁረጥ አይገባም። "ዝናብም ወረደ፥ጐርፍም መጣ፥ነፋስም ነፈሰ፥ያንም ቤት ገፋው በአለት ላይም ስለ ተመሠረተ አልወደቀም" ማቴ. ፯፣፳፭። ራሳችንን ዐለት በተባለ በክርስቶስ አስተምህሮ ላይ መመሥረት አለብን።

© በትረማርያም አበባው

@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
ተጠያቂው ማን ነው?

ከሰሞኑ በቀዳማዩ አቡነ ጴጥሮስ ሕይወት ዙሪያ ፊልም እሠራለሁ ያለ አንድ አካል ስማቸውን በልጅነታቸው በቤተሰብ ይጠሩበት በነበረው ስም እየተጠቀምሁ ፊልም እሰራለሁ ማለቱን ተከትሎ (ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ እንዳነበብኩት ነው) ቤተ ክህነታችን ተቃውሟል። ይህን ተከትሎም ብዙ ሰዎች ድርጊቱን እያወገዙት ነው፤ መወገዝም አለበት። በርግጥ ቤተ ክህነት የከለከለበትን ምክንያት በይፋ ስላላየነው ለመደምደም ሊያስቸግር ይችላል።

የሚያስወግዘውም ሆነ ተቃውሞውን ያመጣው ስማቸው የተለወጠ ከፖለቲከኞች አንዳንዶቹ እንደሚሉት የእርሳቸው የሚባለውን ማንነት ወደማያሳይ የተለወጠውን ስም መልሶ በማምጣት ለዚያ ለእርሳቸው ለተሰጠው ማንነት ማዳመቂያ ለማድረግ ታስቦ ነው በሚል ነው። መነሻ የተደረገውም የኦሮሚያ ቤተ ክህነት አቀንቃኞች ከነበሩት አንዳንዶቹ የያዙትን መስቀል ረስተው ጳጳሳት ለምን በኦሮሞ ስም አልተሰየሙም ብለው ካነሡት ፖለቲካዊ ትግል ውስጥ ይመስለኛል። ይህን ሁሉ ያሉት የተደረገው ሁሉ እነርሱ ሊያደርጉት እንደሚፈልጉት ጥንቱንም በፖለቲካ ምክንያት የተደረገ መስሏቸው ሊሆን ይችላል፤ ወይም ደግሞ እንዳልሆነ እንኳ ቢያውቁ አሁን የሚፈልጉትን ለማድርግ የቀደመውንም ፖለቲካዊ አድርጎ ማቅረብ የስልቱ አካል ስለሆነ ሊሆን ይችላል። ለሁሉም እውነታውን እናስቀድም።

ምንኩስና ውስጥ ሲገባ ይልቁንም ደግሞ ከቅዱስ ጳኩሚስ በኋላ ጎልቶ በሚታወቀው ሥርዓተ ጳኩሚስ መሠረት ምንኩስና ሦስት ደረጃዎች አሉት ። እነዚህም ረድዕነት፣ (ልብሰ) ምንኩስና እና ሥርዓተ አስኬማ ናቸው። እነዚህ ደረጃዎች ደግሞ የራሳቸው ትርጉም ያላቸው ከመሆኑም በላይ በደረጃዎቹ የሚጠበቁ ለውጦች አሉ።

የመጀመሪያው የረድእነት ደረጃ ራስን የመካድ ደረጃ ነው። አንድ ሰው ወደ ምንኩስና ሲመጣ “ማንም ሊከተለኝ የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ ፣ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ” /ማር 8 ፡ 34/ ከሚለው የጌታ ትእዛዝ ውስጥ የመጀመሪያዋን መፈጸም አለበት ። ምንም እንኳ ይህ የወንጌል ትእዛዝ ለሁሉም ክርስቲያኖች የታዘዘ እና ሁላችንም ልናደርገው የሚጠበቅ ቢሆንም ወደ ምንኩስና የሔደ ግን ያለማንገራገር ይህን ከመፈጸም መጀመር ይኖርበታል። በዚህም መሠረት ራስን መካድ ማለት፣ ለራስ ደስታ፣ ለራስ ጥቅም፣ ለራስ ማድላት፣ ለራስ ቅድሚያ መስጠትን ሙሉ በሙሉ ሲተው ራሱን ካደ ይባላል። ይህም ማለት ገዳም ገብቶ በረድእነት ያለ ሰው የታዘዘውን ይሠራል እንጂ የፈለገውን አይሠራም። ራሱን ክዷል ማለት ፈቃዱን ትቶ የእግዚአብሔርን ፈቃድ በሚያዙት ሰዎች በኩል በመታዘዝ ይፈጽማል። ለገዳሜ፣ ለወንድሜ፣ ለአባቴ፣ በአጠቃላይ ለሌሎች ይሁን ይደረግ ይላል እንጂ ለእኔ ማለትን ለማቆም ይለማመዳል። የተሰጠውን ይጠቀማል እንጂ የመብት ጥያቄም አያነሣም። ሥርዓተ ገዳም፣ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እና ሕገ እግዚአብሔር እንዳይጣስ ይጠይቃል እንጂ ፍላጎቱን ለማሟላት ሊጠይቅ አይችልም። ይህን ሲያደርግ ደግሞ ወደ እርሱ ፍላጎት እና ፈቃድ እንዲመለስ የቀደመ ልምዱም ሆነ ሰይጣን ፈተና ቢያመጡበት ዕርፍ ይዞ ወደ ኋላ ማረስ የለምና ምን ማድረግ እንዳለበት ወይም ፍላጎቱን፣ ዓለምንና ሰይጣንን እንዴት መዋጋት እንዳለበትም ልክ እንደ አንድ ወታደር ልምምድ የሚያደርግበት የምንኩስና ቀዳሚ ደረጃ ነው፤ ረድእነት ። ይህን በአግባቡ የሚወጣ ረድእም ረድእ ዘበኅድአት ይባላል። ጸጥ ብሎ የሚታዘዝ ራሱን በትክክል የካደ ማለት ነው። ስለዚህም ወደሚቀጥለው ተጋድሎ እንዲገባ ይፈቀድለታል።

ይህን የረድእነት ደረጃ ቢያንስ ለሦስት ዓመት አንዳንዴ ደግሞ ከዚህ በታች ወይም ከዚህ በላይ ለሆነ ጊዜ ከቆየ በኋላ ወደ ምንኩስናው ይሄዳል። በዚህ ጊዜ ደግሞ በረድእነት ራሱን እንደካደ አሁን ደግሞ ዓለምን ጨርሶ ይክዳል። ይህም ማለት ራሱን ለዚህ ዓለም እንደ ሞተ ይቆጥራል። “ዓለምን መውደድ ለእግዚአብሔር ጥል እንዲሆን አታውቁምን? እንግዲህ የዓለም ወዳጅ ሊሆን የሚፈቅድ ሁሉ የእግዚአብሔር ጠላት ሆኖአል” / ያዕ 4 ፡ 4/ የሚለውን እያሰበ ከእግዚአብሔር ጋር ለመሆን ሲል ዓለምን ይክደዋል። ለዚህም ከዚህ ዓለም ጋር የሚያገናኙትን ክርሮች በሙሉ ይቆርጣል። ስለዚህም ልክ እንደሞተ ሰው ሥርዓተ ግንዘት ተደርጎለት የፈቃድ ሞቱን ይቀበላል። ከዚህ በሁላ ዘመዴ ወገኔ፣ ሀገሬ፣ ቋንቋዬ፣ መንደሬ ይቀራል። ንብረት ማፍራት፣ በዚህ ዓለም ጉዳይ እንደ ዓለም ሰዎች ሆኖ ጣልቃ መግባት ሁሉ ይቀራል።

በዚህ ዓለም ጉዳዮች ከገባም የሚገባው ልክ እንደ እግዚአብሔር መላእክት ከአድሎ ነጻ ሆኖ ከፈቃደ እግዚአብሔር ጋር ሳይቃረን ከገባበት አዲስ ዓለም ሳይወጣ ብቻ ይሆናል ማለት ነው። ልክ አንድ አምባሳደር በሚኖርበት ሀገር የሚያደርገው ሁሉ የወከለውን ሀገር ጥቅም፣ ክብር እና ደረጃ የጠበቀ እንደሚሆነው ሁሉ መነኩሴም እንዲያ ነው የሚሆነው። የቀደመ ስሙ የሚቀረውም በዚህ ምክንያት ነው። ሌላ ስም ይሰጠዋል። አዲሱ ስሙ የገባበት አዲስ ዓለም ውስጥ ለሚኖረው ሕይወት የሚሰጥ ያንን የሚመለከት ስም ነው። ለዚህ ዓለም ሙቶ ለዓለመ መላእክት ተወልዷልና። ስለዚህም አክሊለ ሦክ (ቆብ) ይደፋል፣ ልብሰ ምንኩስና ይለብሳል፣ በዚህም ከዚህ ዓለም ፈጽሞ ይለያል። ይህን ዓለም ክዶ ያኛውን ዓለም ተቀልቅሏል። ከዚህ በኋላ በአዲስ ዓለም ወዳለው ከፍተኛ ደረጃ ለመድረስ ትግሉን አበርትቶ ይቀጥላል። ያ የመጨረሻ ደረጃም አስኬማ የተባለው ደረጃ ነው።

አንድ መነኮስ ለአስኬማ የሚበቃው ከላይ እንደጠቀስነው መስቀል ከመያዝ መስቀል ወደ መሸከም ሲደርስ ነው። በዚህ ጊዜም እኔን ሊከተለኝ የሚወድድ ቢኖር ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ ከሚለው ቃል ውስጥ የመጨረሻው መስቀል መሸከም ላይ ይደርሳል ማለት ነው። ይህም ማለት በፈቃዱ መከራ ይቀበላል። ሥጋ መብላት ፈጽሞ ያቆማል። መሬት ላይ አንጥፎ መተኛት ያቆማል። ልክ ጌታ በደብረ ዘይት ተራራ ሲጸልይ ያድር እንደነበረው ሲጸልይ ይውላል ያድራል። በአእምሮው ሙሉ በሙሉ ተዘክሮ እግዚአብሔር (እግዚአብሔርን ብቻ ማሰብ) እና ልክ እንደ እግዚአብሔር መልአክ ለመምሰል ወይም ጌታን በመምሰል ይኖራል ማለት ነው።

በዚህ ምክንያት ለአስኬማ የሚበቃ አንድ መነኮስ ሥርዓተ አስኬማ ይፈጸምለታል። በጥንቱ ትውፊት መሠረትም ቅናተ ዮሐንስ ይታጠቃል፣ ይህም ዮሐንስ መጥምቅ የበረሃ ማር እንደበላ እና ከዚህ ዓለም ነገር ምንም እንዳልወሰደው ከምንም ነገር ይለያል። በንጽሕናው እና ተጋድሎው እንደ መልአከ እግዚአብሔር ወይም እንደ ዮሐንስ መጥምቅ ይሆናል ማለት ነው። ከዚያም መስቀል እና ሌሎች ከስቅለተ እግዚእ ጋር የተገናኙ ነገሮች የተጠለፉበት ቀሚስ ወይም ደግሞ አሁን በቅዳሴ ጊዜ እንደሚደረገው ሞጣህት ያለ ይለብሳል። በከፍተኛ ዝምታ (አርምሞ) ውስጥ የመኖር ግዴታ ውስጥ ራሱን ያስገባል። በስቅለቱ ጊዜ ከተቆጠሩ ነገሮች በቀር ጌታ ምንም እንዳልተናገረ ለዚህ መዓርግ ወይም ደረጃ የበቃ መነኮስም ከአስፈላጊ እና የግድ በእርሱ በቻ ሊነገሩ ከሚገባቸው ጉዳዮች ውጭ አይናገርም። ቢነቅፉትም፣ ቢሰድቡትም፣ ቢያምሰኙትም፣ እንደ አንሥተ ገሊላ ቢያለቅሱለትም ዝም በቃ ዝምምም ይላል። ይህ ሁሉ የሚሆነው መስቀል ለመሸከም መብቃቱን ለመናገር ነው። በሌላ ቋንቋ ለአስኬማ የደረሰ ማለት ጸዋሬ መስቀል የሆነ ማለት ነው። “ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ” /ገላ 6 ፡14/ ሲል ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው ራሱን መስቀል ላይ ያውላል፤
2024/09/21 23:40:35
Back to Top
HTML Embed Code: