Telegram Web Link
"እውነትና ፍቅር ሊለያዩ የማይችሉ ክንፎች ናቸው እውነት ያለ ፍቅር መብረር እንደማይችል ሁሉእንዲሁም ፍቅር ያለ እውነት ወደ ላይ ሊወነጨፍ አይችልም የስምምነት ቀንበራቸው አንድ ነው።"
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
መልካሙ አምላካችን እግዚአብሔር የሰዎችን መልካም ሥራ ሁሉ አይዘነጋም ጥቂት ብትሆንም እንኳ።

እርሱ በመልካም ምድር ላይ ከወደቀች በኋላ ሠለሳ ስድሳና መቶ እጥፍ ፍሬ ስለምታፈራው መልካም ፍሬ አስተምሯል። አምላካችን እዚህ ላይ ሠላሳ ፍሬ ያፈራችውን ዘር ከመልካም ዘር ነው የቆጠራት። እርሱ ሠርክ አሥራ አንድ ሰዓት ላይ መጥተው የተቀጠሩትን ሠራተኞች ተቀብሏል። (ማቴ 20፥9) ከእርሱ በስተቀኝ የተሰቀለውን ወንበዴ የተቀበለው በሕይወቱ የመጨረሻ ሰዓት ውስጥ ነበር። (ሉቃ 23፥43) እርሱ ታናናሾች ለተባሉት ሰዎች በደቀ መዝሙሩ ስም ቀዝቃዛ ውኃ ወይም ጽዋ ያጠጣ ዋጋውን እንደማያጣ እውነት እላችኋለሁ ብሎ በማሳሰብ ተናግሯል። (ማቴ 10፥42) የእርሱ መልካምነት ሦስት ዓመት ተመላልሶ ምንም ፍሬ ላላገኘባትን በለስ ሊያስቆርጣት ባዘዘ ጊዜ ጠባቂዋ በመካከል በአስታራቂነት ገብቶ "......ጌታ ሆይ ዙሪያዋን እስክኮተኩትላት ፋንድያ ስካፈስላት ድረስ በዚች ዓመት ደግሞ ተዋት ወደ ፊትም ብታፈራ ደኀና ነው ያለዚያ ግን ትቆርጣታለህ። (ሉቃ 13፥8-9) በማለት እንዲናገር ፈቅዶለታል።

አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ!
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
"እንግዲህ ከሀሜት፣ ከሀሰት ጓደኝነት፣ የጌታን ሥም በግብዝነት ከሚጠሩ፣ ምንም የማያውቁትን ከሚያታልሉ በመራቅ ለጥሩ ነገር እንቅና። ማንም ኢየሱስ በሥጋ እንደመጣ የማያምን ፀረ ክርስቶስ ነው። ማንኛውም በመስቀል ላይ መከራ መቀበሉን የማያምን ዲያብሎስ ነው። ማንም የክርስቶስን ትምህርት ለራሱ እንደሚመቸው የሚያጣምም እና ትንሳኤና የመጨረሻ ፍርድ የለም የሚል ይህም የሰይጣን የበኩር ልጅ ነው።"

ቅዱስ ፖሊካርፐስ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
እግዚአብሔር ሰዎችን ኹሉ ሲፈጥራቸው በመንፈሳዊ ማንነታቸው እኩል አድርጎ ነው፡፡ እንዲህም ስለ ኾነ እያንዳንዱ ሰው በጎም ኾነ ክፉ ግብር ለመሥራት እኩል ዝንባሌ አለው፡፡ እግዚአብሔርን ለመታዘዝም ኾነ ላለመታዘዝ እኩል የመምረጥ ዕድል አለው፡፡ ከዚህ ውጪ በኾነ ነገር ግን ሰው ኹሉ እኩል አይደለም፡፡ አንዳንዱ እጅግ አስተዋይ ነው፤ ሌላው ደግሞ ደከም ያለ ነው፡፡ አንዳንዱ በሰውነቱ ብርቱና ጤናማ ነው፤ ሌላው ደግሞ ደካማና ሕመም የሚበዛበት ነው፡፡ አንዳንዱ ሰው መልከ መልካምና ማራኪ ነው፤ ሌላው ደግሞ አይደለም፡፡

ይህ ኹሉ ቢኾንም ግን በኾነ ነገር ስጦታው ያለው ሰው ስጦታው የሌለውን ሌላውን ሰው ሊንቀው አይገባም፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ ለእያንዳንዳችን የተለያየ ስጦታን የሰጠን አንዳችን አንዳችንን እንድንጠቅም ነውና፡፡ እግዚአብሔር እያንዳንዳችን ከሌላው ወንድማችን የምንፈልገው ጥቅም እንዲኖር ያደረገው በመካከላችን መጠላላትና መለያየት እንዳይኖር ነው፤ እንድንፋቀርና አንድ እንድንኾን አስቦ ነውና፡፡

ስለዚህ ወዳጄ ሆይ! ወንድምህ ከአንተ ይልቅ አስተዋይና ዐዋቂ፥ ብርቱም ቢኾን በዚህ ቅር አይበልህ፡፡ ከዚህ ይልቅ እግዚአብሔርን አመስግን፤ ከወንድምህ አስተዋይነትና ዐዋቂነት ብርታትም ትጠቀማለህና፡፡ በዚህ ብቻ ሳታቆምም ራስህን፡- “ስጦታዬ ምንድን ነው? ወንድሜን እኅቴን በምን ልጠቅም እችላለሁ?” ብለህ ጠይቅ፡፡ ይህን ጥያቄ በትክክል ስትመልስ፥ እንደ መለስከው ምላሽም ስትተገብር በአንድ መልኩ በሚበልጥህ ሰው ቅር መሰኘትህን፥ በሌላ መልኩ ደግሞ የምትበልጠውን ሌላውን ወንድምህን መናቅህን ታቆማለህ፡፡

(#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ)
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
"ዲያብሎስ ልጅነታችንን እናቆሽሽ ዘንድ በእኛ ላይ የሚተናኰለው ተንኰል በጣም ተደጋጋሚና ኃይለኛ ነው፡፡ ስለዚህ ይህን መንቻካ የዲያብሎስን ደባ ድል እንነሣ ዘንድ ዘወትር ንቁዎችና ጠንቃቆች ልንኾን ይገባናል፡፡ እኛ ይህን ማድረግ ሳንችል ቀርተን እጅግ ጥቂት መግቢያ ቀዳዳ የምንተውለት ከኾነ ግን እርሱ ጥቂቷን ቀዳዳ ሰፊ በር ያደርጋታል፡፡ እንዲህ አድርጎም ኃይሉን ኹሉ ተጠቅሞ ወደ እኛ ይገባል፡፡

ስለዚህ ስለ ድኅነታችን የሚገደን ከኾነ እንደዚህ ጥቂትና ቀልድ በሚመስሉ ነገሮች እንኳን አንዘናጋ፤ እርሱ የሚንቀውና ጥቂት የሚለው ኃጢአት የለምና፡፡ እኛ ጥቃቅን የምንላቸውን ነገሮች መነሻ አድርጎ ልጅነታችንን የምናቆሽሽበትን ታላላቅ ኃጢአቶችን እንድንሠራ አድርጎ እጅግ ይተጋልና፡፡"

(#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ)
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ሥርዓተ ዋዜማ ዘዓውደ ዓመት
🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊

በ፩ ሃሌታ ብጹዕ አንተ ዮሐንስ፤ ዘሀለወከ ታእምር፤ ወተሐውር ቅድመ እግዚአብሔር፤ ጸሊ በእንቲአነ፤ ውስተ ርእሰ ዓውደ ዓመት ተጽሕፈ ተዝካርከ፤ ባርከኒ፤ እንሣእ በረከተከ።

ምልጣን፦ውስተ ርእሰ ዓውደ ዓመት ተጽሕፈ ተዝካርከ፤ ባርከኒ፤ እንሣእ በረከተከ።

አመላለስ፦
ባርከኒ ባርከኒ/፪/
እንሣእ በረከተከ እንሣእ በረከተከ /፬/

በ፭ ለእግዚአብሔር ምድር በምልዓ
ይቤ ዮሐንስ ለልየ ርኢኩ፤ ወአነ ሰማዕቱ፤ አንሰ ኢየአምሮ፤ ዳዕሙ ከመ ያእምርዎ ፳ኤል አንሰ መጻእኩ።

እግዚአብሔር ነግሠ
ጸርሐ ዮሐንስ ወይቤ ድኅረ እምነቢያት እምቅድመ ምጽአተ ወልድ ቤዛ ኃጢአቶሙ አጥምቅ በማይ አንሰ ተፈኖኩ።

ምልጣን
ጸርሐ ዮሐንስ ወይቤ፤ ድኅረ እምነቢያት እምቅድመ ምጽአተ ወልድ ቤዛ ኃጢአቶሙ አጥምቅ በማይ፤ አንሰ ተፈኖኩ።

በ፭ እግዚኦ ጸራሕኩ ኀቤከ
እምከርሠ እሙ አእመረ ፤ እምከርሠ እሙ አእመረ ሰገደ ወአንፈርዓፀ።

ምልጣን
እምከርሠ እሙ አእመረ ሰገደ ወአንፈርዓፀ፤ ሰገደ ወአንፈርዓፀ፤ እምከርሠ እሙ አእመረ፤ ሰገደ ወአንፈርዓፀ።

ይትባረክ
ጸርሐት ቤተ ክርስቲያን ኀበ ዮሐንስ ወትቤሎ አንተኑ ክርስቶስ ወይቤላ አንሰ ኢኮንኩ ኪያሁ ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር ዘየዓትት ኃጢአተ ዓለም።

ምልጣን፦ነዋ በግዑ  ኃጢአተ ዓለም ዘየዓትት ነዋ በግዑ  ኃጢአተ ዓለም ዘየዓትት።

ሰላም
በ፬: ዘመጠነዝ ትርሢተ ክብር፤ ፈሪሃ ልዑል ትሕትና ወፍቅር፤ ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ ዘመላእክት ይሰግዱ ሎቱ፤ ኃይለ ልዑላን ኪያሁ ይሴብሑ፤ ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ ዘምስለ እግዚኡ ኪዳነ ዘአቀመ ወብዙኃነ አሕዛበ አእመነ፤ ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ ውስተ ሐቌሁ ቅናቱ ዘአዲም፤ ንብረቱ ገዳም ወኲሉ ነገሩ በሰላም፤ ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ እግዚኡ ዘከመ ከለሎ፤ ዮም በምድር ተዝካሩ በሰማያት በላዕሉ፤ ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ ይቤሎ መድኃኒነ ለዮሐንስ፤ ዕውራን ይሬእዩ ወጽሙማን ይሰምዑ፤ እለ ለምጽ ይነጽሑ፤ እለ መጽኡ ኀቤየ።

ምልጣን፦ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ እግዚኡ ዘከመ ከለሎ ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ ዘመላእክት ይሰግዱ ሎቱ ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ ውስተ ሐቌሁ ቅናቱ ዓዲም ንብረቱ ገዳም ወነገሩኒ ሰላም።

አመላለስ፦
ውስተ ሐቌሁ ቅናቱ ዓዲም/፪/
ንብረቱ ገዳም ወነገሩኒ ሰላም/፬/
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ሥርዓተ ማኅሌት ዘዓውደ ዓመት
🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊
ስርዓተ ነግሥ
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል

መልክዐ ሥላሴ
ሰላም ለገበዋቲክሙ እለ ዕሩቃን እምልብሰ ወርቅ፤ ሥሉስ ቅዱስ ሥርግዋነ መፍርህ መብረቅ፤ መንገለ(ኀበ) ፍኖቱ ምጽዋት ለቆርነሌዎስ ጻድቅ፤ ይምርሐኒ ወንጌልክሙ እግዚአ ፍኖት ረቂቅ፤ ዘጸያሔሁ ዮሐንስ መጥምቅ።

ዚቅ
ወአንተኒ ሕፃን ነቢየ ልዑል ትሰመይ፤ እስመ ተሐውር ቅድመ እግዚአብሔር ከመ ትጺሕ ፍኖቶ።

ዓዲ
ወንጌል ቅዱስ ዘሰበከ ዮሐንስ፤ ቃለ ወልደ እግዚአብሔር።

ዘጣዕሙ
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።

ዚቅ
ምንተ እንከ እብል በእንተ ማርያም መሠረተ ጽድቅ ኃደረ ላዕሌሃ፤ ወአዘዘ ደመና በላዕሉ።

ነግሥ
ምስለ ራጉኤል ስዑል በነበልባል ወዮሐንስ ድንግል፤ ወበርተሎሜዎስ ሐዋርያ ሰባኬ ወንጌል፤ ወኢዮብ ዓዲ ተወካፌ ቊስል፤ ዓውደ ዓመት ለባርኮ እምጽርሐ አርያም ጌልጌል፤ ማርያም ንዒ ለምሕረት ወሣህል።

ወረብ
ዓውደ ዓመት ለባርኮ ባርኮ ዓውደ ዓመት/፪/
ንዒ ማርያም ለምሕረት ወሣህል/፪/

ዚቅ
ንዒ ኀቤየ ኦ ድንግል ምስለ ወልድኪ ፍቁርኪ ዮሐንስ ከመ ትባርኪ ላዕሌነ።

ዓዲ
በምድረ ጽዮን ኢይኩን ሐከክ፤ ወበገራኅታ ኢይብቊል ሦክ፤ ጸሊ ኀበ አምላክ ራጉኤል መልአከ፤ ዓውደ ዓመት ከመ ይትባረክ።

መልክዐ ዮሐንስ
በስመ እግዚአብሔር እሳት በሐቅለ ኅሊና ነዳዲ፤ ወበስመ ማርያም ድንግል መጥበቢተ ዓለም አባዲ፤ ማኅቶተ ጸዳል ዮሐንስ ጽልመተ አበሳ ሰዳዲ፤ ከመ እዜኑ ኂሩተከ እደ ኃጣውእየ ይፍዲ፤ በአየረ ሰማይ ይጸርሕ ቃልከ ዓዋዲ።

ዚቅ
እገኒ ለከ እግዚኦ በኲሉ ልብየ፤ ወእዜኑ ኂሩተ ዚአከ፤ እትፌሣሕ ወእትሐሠይ በአድኅኖትከ።

ወረብ
እገኒ ለከ እግዚኦ በኲሉ ልብየ/፪/
እትፌሣሕ ወእትሐሠይ በአድኅኖትከ/፪/

ዓዲ
ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ ማኅቶተ ጥበብ ውስተ አልባቢነ አኅቱ፤ ኀበ አዘዝከነ ኑፈር ወን

መልክዐ ዮሐንስ
ሰላም ለሥዕረተ ርእስከ እንተ ደለዎ እኳቴ፤ ወለርእስከ ሰላም ዘተመትረ ከመ ናቡቴ፤ ርእሰ ዓውደ ዓመት ዮሐንስ ወላዴ መጥቅዕ ወአበቅቴ፤ መብልዕ ዜና ፍቅርከ ወነገረ ጽድቅከ ስቴ፤ ያስተፌሥሕ መላእክተ ወሰብአ መዋቴ።

ወረብ
"ርእሰ ዓውደ ዓመት ዮሐንስ"/፪/ ወላዴ መጥቅዕ/፪/
ወላዴ መጥቅዕ ወአበቅቴ ወላዴ መጥቅዕ/፪/

ዚቅ
ውስተ ርእሰ ዓውደ ዓመት ተጽሕፈ ተዝካርከ፤ ባርከኒ እንሣእ በረከተከ።

መልክዐ ዮሐንስ
ሰላም ለአዕይንቲከ እለ ሠኑየ ይትኌለቁ፤ ወለአእዛኒከ ሰላም እለ ይትላጸቁ፤ ዮሐንስ ከማከ ሶበ ፈተዉ ወጽሕቁ፤ እሳተ ነዳዴ ኢተክህሎሙ ያጥምቁ፤ ራጉኤል በትጋሁ ወኢዮብ በጽድቁ።

ወረብ
"እሳተ ነዳዴ" ኢተክህሎሙ ያጥምቁ/፪/
ዮሐንስ ከማከ ሶበ ፈተዉ ወጽሕቁ/፪/

ዚቅ
ሰላማዊ ብእሲሁ፤ ቅዱሳት እደዊሁ  እለ አጥመቃሁ፤ ለመድኃኔዓለም።

መልክዐ ዮሐንስ
ሰላም ለአማዑቲከ እግዚአብሔር ዘገብሮ፤ ወለንዋየ ውስጥከ ሰላም መንጦላዕተ ሥጋከ እንተ ሰወሮ፤ ዮሐንስ ልብው መዝገበ ጥበብ ወአእምሮ፤ እፎ ኢያጽራከ ለሀቅለ ገዳማት ፃዕሮ፤ ፍጹመ መኒነከ አብያተ ዘውቅሮ።

ወረብ
"አብያተ ዘውቅሮ"/፪/ መኒነከ/፪/
ፍጹመ መኒነከ ዮሐንስ ልብው/፪/

ዚቅ
አብያተ ዘውቅሮ መኒነከ፤ በተዘከሮ ማኅደር ዘበሰማያት፤ ፀጒረ ገመል ረሰይከ ዓራዘከ።

መልክዐ ዮሐንስ
አምኃ ስብሐት አቅረብኩ ለመልክዕከ በጽዋዔ፤ እንዘ አስተዋድድ ቃለ መጠነ ራብዕ ሱባኤ፤ ተወክፈኒ ዮሐንስ ምስለ በርተሎሜዎስ ቀርነ ጉባኤ፤ ከመ ተወክፈ እግዚእከ ቅድመ ወንጌላዊት ትንሣኤ፤ እምደ አሐቲ ብእሲት ጸራይቀ ክልዔ።

ዚቅ
ዮሐንስ እዴከ መጥወኒ፤ ወበርተሎሜዎስ አቡየ ለባርኮ ቅረበኒ።

ወረብ
ዮሐንስ እዴከ መጥወኒ/፪/
ወበርተሎሜዎስ አቡየ ለባርኮ ቅረበኒ/፪/

አንገርጋሪ
ወአንተኒ ሕፃን ነቢየ ልዑል ትሰመይ፤ ዓርኩ ለመርዓዊ ትሰመይ፤ ወአዝማዱ በሥጋ ትሰመይ፤ ተፈኖከ ታርኁ አናቅጸ ጽድቅ።

አመላለስ፦
ተፈኖከ ታርኁ/፪/
ታርኁ አናቅጸ ጽድቅ/፬/

ወረብ
ወአንተኒ ሕፃን ነቢየ ልዑል ትሰመይ ነቢየ ልዑል/፪/
ዓርኩ ለመርዓዊ ትሰመይ ነቢየ ልዑል/፪/

እስመ ለዓለም፦
በመንፈስ የሐውር ወበኃይለ ኤልያስ፤ አልቦ፤ዘየዓብዮ ለዮሐንስ

አመላለስ፦
አልቦ ዘየዓብዮ/፪/
አልቦ ዘየዓብዮ ለዮሐንስ/፬/
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
ከገቢረ ኀጢአት ሳይወጡ አዲስ ዓመት ሲመጣ መደሰት፣ ብዙ መብልና መጠጥ ማዘጋጀት፣ አዲስ ልብስም መልበስ ጥቅም የለውም፡፡ ነፍሳችን በኀጢአት እየተጨነቀች፣ ነፍሳችን ተርባና ተጠምታ ሳለ፣ የተዳደፈ የኀጢአት ልብስም ተጆቡና ሳለ አዲስ ዓመት ማክበር ለእኛ ምን ጥቅም ይሰጠናል? እንዲህ ከገቢረ ኀጢአት ሳይወጡ አዲስ ዓመትን ማክበር ማለት ለእኔ እንደ ልጆች የዕቃ ዕቃ ጨዋታ ነው፡፡

ክርስቶስ ከዚሁ ሥራ አውጥቶናል፡፡ ከሕፃንነት አዕምሮ ወደ ማወቅ አሸጋግሮናል፡፡ ከምድራውያን ለይቶ ከሰማያውያን ጋር ደባልቆናል፡፡ ስለዚህ “መልካሙን ሥራችሁን ዐይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ” እንደ ተባለ አፍአዊ ሳይኾን መንፈሳዊውን ብርሃን ልናበራ ይገባናል (ማቴ.5፡16)፤ በአዲሱ ዓመት፡፡ ይህም ብርሃን ተስፋ መንግሥተ ሰማያትን የሚያስገኝ ነው፡፡

ወዳጄ ሆይ! ቤቱ ቆሽሾ ሳለ ውጫዊ በሩን ብቻ ለማሽቀርቀር ለምን ትጨነቃለህ? ነፍስህ በኀጢአት ተዳድፋ ሳለ ሥጋህን ብቻ ለማስደሰት ለምን ትሮጣለህ? አስቀድመህ ቤቱን (ነፍስህን) ለማስዋብ አትሽቀዳደምምን? አስቀድመህ ለነፍስህ የምታስብ ከኾነ ከሰው እጅ ሳይኾን ከክርስቶስ እጅ ሹመት ሽልማት ትቀበላለህ፡፡ ኹል ጊዜ “የማደርገው ነገር እግዚአብሔር ይከብርበታልን?” ብለህ አስብ እንጂ እንዲሁ በዘልማድ የምትመላለስ አትኹን ብዬ እመክርኻለሁ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሲመክረን፡- “እንግዲህ የምትበሉ ወይም የምትጠጡ ብትኾኑ ወይም ማናቸውም ነገር ብታደርጉ ኹሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት” ያለንም ስለዚሁ ነውና በአዲሱ ዓመት በድርጊቶቻችን ኹሉ እግዚአብሔርን ለማክበር እንዘጋጅ (1ኛ ቆሮ.10፡31)፤ አዲስ ዓመት ማክበር ማለት ይኼ ነውና፡፡

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
(ሰማዕትነት አያምልጣችሁ መጽሐፍ - #ገብረ_እግዚአብሔር_ኪደ)
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
Audio
እንደዚህ ያሉትን እወቋቸው 
                                                  
Size:- 27.8MB
Length:-1:19:49
       
     በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@EotcrLibilery
@EotcrLibilery
@EotcrLibilery
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ሥርዓተ ዋዜማ ዘዓውደ ዓመት
🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊

በ፩ ሃሌታ ብጹዕ አንተ ዮሐንስ፤ ዘሀለወከ ታእምር፤ ወተሐውር ቅድመ እግዚአብሔር፤ ጸሊ በእንቲአነ፤ ውስተ ርእሰ ዓውደ ዓመት ተጽሕፈ ተዝካርከ፤ ባርከኒ፤ እንሣእ በረከተከ።

ምልጣን፦ውስተ ርእሰ ዓውደ ዓመት ተጽሕፈ ተዝካርከ፤ ባርከኒ፤ እንሣእ በረከተከ።

አመላለስ፦
ባርከኒ ባርከኒ/፪/
እንሣእ በረከተከ እንሣእ በረከተከ /፬/

በ፭ ለእግዚአብሔር ምድር በምልዓ
ይቤ ዮሐንስ ለልየ ርኢኩ፤ ወአነ ሰማዕቱ፤ አንሰ ኢየአምሮ፤ ዳዕሙ ከመ ያእምርዎ ፳ኤል አንሰ መጻእኩ።

እግዚአብሔር ነግሠ
ጸርሐ ዮሐንስ ወይቤ ድኅረ እምነቢያት እምቅድመ ምጽአተ ወልድ ቤዛ ኃጢአቶሙ አጥምቅ በማይ አንሰ ተፈኖኩ።

ምልጣን
ጸርሐ ዮሐንስ ወይቤ፤ ድኅረ እምነቢያት እምቅድመ ምጽአተ ወልድ ቤዛ ኃጢአቶሙ አጥምቅ በማይ፤ አንሰ ተፈኖኩ።

በ፭ እግዚኦ ጸራሕኩ ኀቤከ
እምከርሠ እሙ አእመረ ፤ እምከርሠ እሙ አእመረ ሰገደ ወአንፈርዓፀ።

ምልጣን
እምከርሠ እሙ አእመረ ሰገደ ወአንፈርዓፀ፤ ሰገደ ወአንፈርዓፀ፤ እምከርሠ እሙ አእመረ፤ ሰገደ ወአንፈርዓፀ።

ይትባረክ
ጸርሐት ቤተ ክርስቲያን ኀበ ዮሐንስ ወትቤሎ አንተኑ ክርስቶስ ወይቤላ አንሰ ኢኮንኩ ኪያሁ ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር ዘየዓትት ኃጢአተ ዓለም።

ምልጣን፦ነዋ በግዑ  ኃጢአተ ዓለም ዘየዓትት ነዋ በግዑ  ኃጢአተ ዓለም ዘየዓትት።

ሰላም
በ፬: ዘመጠነዝ ትርሢተ ክብር፤ ፈሪሃ ልዑል ትሕትና ወፍቅር፤ ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ ዘመላእክት ይሰግዱ ሎቱ፤ ኃይለ ልዑላን ኪያሁ ይሴብሑ፤ ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ ዘምስለ እግዚኡ ኪዳነ ዘአቀመ ወብዙኃነ አሕዛበ አእመነ፤ ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ ውስተ ሐቌሁ ቅናቱ ዘአዲም፤ ንብረቱ ገዳም ወኲሉ ነገሩ በሰላም፤ ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ እግዚኡ ዘከመ ከለሎ፤ ዮም በምድር ተዝካሩ በሰማያት በላዕሉ፤ ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ ይቤሎ መድኃኒነ ለዮሐንስ፤ ዕውራን ይሬእዩ ወጽሙማን ይሰምዑ፤ እለ ለምጽ ይነጽሑ፤ እለ መጽኡ ኀቤየ።

ምልጣን፦ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ እግዚኡ ዘከመ ከለሎ ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ ዘመላእክት ይሰግዱ ሎቱ ርእዩ ዕበዮ ለዮሐንስ ውስተ ሐቌሁ ቅናቱ ዓዲም ንብረቱ ገዳም ወነገሩኒ ሰላም።

አመላለስ፦
ውስተ ሐቌሁ ቅናቱ ዓዲም/፪/
ንብረቱ ገዳም ወነገሩኒ ሰላም/፬/
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ሥርዓተ ማኅሌት ዘዓውደ ዓመት
🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊🕊
ስርዓተ ነግሥ
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል

መልክዐ ሥላሴ
ሰላም ለገበዋቲክሙ እለ ዕሩቃን እምልብሰ ወርቅ፤ ሥሉስ ቅዱስ ሥርግዋነ መፍርህ መብረቅ፤ መንገለ(ኀበ) ፍኖቱ ምጽዋት ለቆርነሌዎስ ጻድቅ፤ ይምርሐኒ ወንጌልክሙ እግዚአ ፍኖት ረቂቅ፤ ዘጸያሔሁ ዮሐንስ መጥምቅ።

ዚቅ
ወአንተኒ ሕፃን ነቢየ ልዑል ትሰመይ፤ እስመ ተሐውር ቅድመ እግዚአብሔር ከመ ትጺሕ ፍኖቶ።

ዓዲ
ወንጌል ቅዱስ ዘሰበከ ዮሐንስ፤ ቃለ ወልደ እግዚአብሔር።

ዘጣዕሙ
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።

ዚቅ
ምንተ እንከ እብል በእንተ ማርያም መሠረተ ጽድቅ ኃደረ ላዕሌሃ፤ ወአዘዘ ደመና በላዕሉ።

ነግሥ
ምስለ ራጉኤል ስዑል በነበልባል ወዮሐንስ ድንግል፤ ወበርተሎሜዎስ ሐዋርያ ሰባኬ ወንጌል፤ ወኢዮብ ዓዲ ተወካፌ ቊስል፤ ዓውደ ዓመት ለባርኮ እምጽርሐ አርያም ጌልጌል፤ ማርያም ንዒ ለምሕረት ወሣህል።

ወረብ
ዓውደ ዓመት ለባርኮ ባርኮ ዓውደ ዓመት/፪/
ንዒ ማርያም ለምሕረት ወሣህል/፪/

ዚቅ
ንዒ ኀቤየ ኦ ድንግል ምስለ ወልድኪ ፍቁርኪ ዮሐንስ ከመ ትባርኪ ላዕሌነ።

ዓዲ
በምድረ ጽዮን ኢይኩን ሐከክ፤ ወበገራኅታ ኢይብቊል ሦክ፤ ጸሊ ኀበ አምላክ ራጉኤል መልአከ፤ ዓውደ ዓመት ከመ ይትባረክ።

መልክዐ ዮሐንስ
በስመ እግዚአብሔር እሳት በሐቅለ ኅሊና ነዳዲ፤ ወበስመ ማርያም ድንግል መጥበቢተ ዓለም አባዲ፤ ማኅቶተ ጸዳል ዮሐንስ ጽልመተ አበሳ ሰዳዲ፤ ከመ እዜኑ ኂሩተከ እደ ኃጣውእየ ይፍዲ፤ በአየረ ሰማይ ይጸርሕ ቃልከ ዓዋዲ።

ዚቅ
እገኒ ለከ እግዚኦ በኲሉ ልብየ፤ ወእዜኑ ኂሩተ ዚአከ፤ እትፌሣሕ ወእትሐሠይ በአድኅኖትከ።

ወረብ
እገኒ ለከ እግዚኦ በኲሉ ልብየ/፪/
እትፌሣሕ ወእትሐሠይ በአድኅኖትከ/፪/

ዓዲ
ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ ማኅቶተ ጥበብ ውስተ አልባቢነ አኅቱ፤ ኀበ አዘዝከነ ኑፈር ወን

መልክዐ ዮሐንስ
ሰላም ለሥዕረተ ርእስከ እንተ ደለዎ እኳቴ፤ ወለርእስከ ሰላም ዘተመትረ ከመ ናቡቴ፤ ርእሰ ዓውደ ዓመት ዮሐንስ ወላዴ መጥቅዕ ወአበቅቴ፤ መብልዕ ዜና ፍቅርከ ወነገረ ጽድቅከ ስቴ፤ ያስተፌሥሕ መላእክተ ወሰብአ መዋቴ።

ወረብ
"ርእሰ ዓውደ ዓመት ዮሐንስ"/፪/ ወላዴ መጥቅዕ/፪/
ወላዴ መጥቅዕ ወአበቅቴ ወላዴ መጥቅዕ/፪/

ዚቅ
ውስተ ርእሰ ዓውደ ዓመት ተጽሕፈ ተዝካርከ፤ ባርከኒ እንሣእ በረከተከ።

መልክዐ ዮሐንስ
ሰላም ለአዕይንቲከ እለ ሠኑየ ይትኌለቁ፤ ወለአእዛኒከ ሰላም እለ ይትላጸቁ፤ ዮሐንስ ከማከ ሶበ ፈተዉ ወጽሕቁ፤ እሳተ ነዳዴ ኢተክህሎሙ ያጥምቁ፤ ራጉኤል በትጋሁ ወኢዮብ በጽድቁ።

ወረብ
"እሳተ ነዳዴ" ኢተክህሎሙ ያጥምቁ/፪/
ዮሐንስ ከማከ ሶበ ፈተዉ ወጽሕቁ/፪/

ዚቅ
ሰላማዊ ብእሲሁ፤ ቅዱሳት እደዊሁ  እለ አጥመቃሁ፤ ለመድኃኔዓለም።

መልክዐ ዮሐንስ
ሰላም ለአማዑቲከ እግዚአብሔር ዘገብሮ፤ ወለንዋየ ውስጥከ ሰላም መንጦላዕተ ሥጋከ እንተ ሰወሮ፤ ዮሐንስ ልብው መዝገበ ጥበብ ወአእምሮ፤ እፎ ኢያጽራከ ለሀቅለ ገዳማት ፃዕሮ፤ ፍጹመ መኒነከ አብያተ ዘውቅሮ።

ወረብ
"አብያተ ዘውቅሮ"/፪/ መኒነከ/፪/
ፍጹመ መኒነከ ዮሐንስ ልብው/፪/

ዚቅ
አብያተ ዘውቅሮ መኒነከ፤ በተዘከሮ ማኅደር ዘበሰማያት፤ ፀጒረ ገመል ረሰይከ ዓራዘከ።

መልክዐ ዮሐንስ
አምኃ ስብሐት አቅረብኩ ለመልክዕከ በጽዋዔ፤ እንዘ አስተዋድድ ቃለ መጠነ ራብዕ ሱባኤ፤ ተወክፈኒ ዮሐንስ ምስለ በርተሎሜዎስ ቀርነ ጉባኤ፤ ከመ ተወክፈ እግዚእከ ቅድመ ወንጌላዊት ትንሣኤ፤ እምደ አሐቲ ብእሲት ጸራይቀ ክልዔ።

ዚቅ
ዮሐንስ እዴከ መጥወኒ፤ ወበርተሎሜዎስ አቡየ ለባርኮ ቅረበኒ።

ወረብ
ዮሐንስ እዴከ መጥወኒ/፪/
ወበርተሎሜዎስ አቡየ ለባርኮ ቅረበኒ/፪/

አንገርጋሪ
ወአንተኒ ሕፃን ነቢየ ልዑል ትሰመይ፤ ዓርኩ ለመርዓዊ ትሰመይ፤ ወአዝማዱ በሥጋ ትሰመይ፤ ተፈኖከ ታርኁ አናቅጸ ጽድቅ።

አመላለስ፦
ተፈኖከ ታርኁ/፪/
ታርኁ አናቅጸ ጽድቅ/፬/

ወረብ
ወአንተኒ ሕፃን ነቢየ ልዑል ትሰመይ ነቢየ ልዑል/፪/
ዓርኩ ለመርዓዊ ትሰመይ ነቢየ ልዑል/፪/

እስመ ለዓለም፦
በመንፈስ የሐውር ወበኃይለ ኤልያስ፤ አልቦ፤ዘየዓብዮ ለዮሐንስ

አመላለስ፦
አልቦ ዘየዓብዮ/፪/
አልቦ ዘየዓብዮ ለዮሐንስ/፬/
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
እንኳን አደረሳችሁ፡፡ አደረሰን፡፡

✿ለሁላችንም የሰላም ፡ የተፋቅሮ ፡ የበረከት እና የንስሃ ዘመንን አምላከ ቅዱሳን ይስጠን፡፡

✿ለዓለም ሰላምን ፡ ለአብያተ ክርስቲያናት ደህንነትን ፡ ለሃገራችንም በጎውን ዘመን ይስጥልን፡፡

✿እንደ ሰው አስበን ፡ እንደ ክርስቲያን መኖሩን ያድለን፡፡

✿ድሃ ተበደለ ፡ ፍርድ ተጓደለ የሚል መሪን አይንሳን፡፡

✿የአባቶቻችንን ዘመን ይመልስልን፡፡

✿የከርሞ ሰውም ይበለን ፡፡

✿ቸሩ እግዚአብሔር አይተወን፡፡ አይጣለንም፡፡

✿"የአንድ ገብስ እሸት፡፡
የአንድ ላምም ወተት፡፡"
ከተባለለት የተባረከው ዘመን ያድርሰን፡፡

✿የታመሙትን ፈውሶ፡፡
✿የወጡትን በሰላም መልሶ፡፡
✿ያለቀሱትን እንባቸውን አብሶ፡፡
✿የወደቁትን አንስቶ፡፡
✿በግፍ የታሰሩትን ፈትቶ፡፡
✿የሞቱትንም ነፍሳቸውን ይማርልን፡፡

ቸሩን ዘመን ይስጠን፡፡

✞ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም በረድኤት አትለየን፡፡ ✞

አሜን፡፡


@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
“የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለ ልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት በጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና።”

(1ኛ ጴጥሮስ 4፥3)
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
2024/09/25 10:26:49
Back to Top
HTML Embed Code: