Telegram Web Link
#በእንተ #ልደት #ክፍል #አንድ
ወልድ ቅድመ ዓለም ያለ እናት ከአብ ከሰው የማሰብ አቅም በላይ በሆነ መንገድ ከአብ ተወለደ። አብ ኖሮ ወልድ ያልነበረበት ዘመን የለም። ስለዚህ በቀዳማዊ ልደቱ አባት ከልጅ ለቅጽበት ያህል እንኳን አይቀድምም። በዚህ ጊዜ የመወለድ ትርጉምም መውጣት ነው። ይህንንም በምሳሌ ለመረዳት የፀሐይ ብርሃን ከፀሐይ ክበብ እንደሚወጣው ያለ ነው። በዚህ ጊዜ ክበቡ ይቀድማል ብርሃኑ ይከተላል አንልም። የፀሐይ ክበብ ከፀሐይ ብርሃን ተለይቶ አያውቅምና። በዚህ አምሳል አብ ወልድን ስለወለደው ከወልድ በፊት ነበረ አንለውም። በዘመን አንድ ናቸውና። ሊቅ አሐቲ ቅድምናሆሙ ለሥላሴ ወዕሩያን እሙንቱ በቅድምና እንዲል። የወልድ ከአብ መወለድ ዘኢየኀልቅ ልደት ይባላል። ይህም ማለት ሁልጊዜ ሲወለድ ይኖራል ማለት አይደለም። ሁልጊዜም ለዘለዓለሙ ወልድ ወልድ ሲባል ይኖራል ማለት ነው። ዘኢየኀልቅ መባሉ ከአብ በመወለዱ ተመትሮ ስለሌለበት ነው። በእኛ ልማድ ሕፃን ከእናቱ ሲወለድ ከእናቱም በህልውና ይለያል። ወልድ ከአብ ሲወለድ ግን በህልውና ከአብ ሳይለይ ነው። ይህንን ለመግለጽ ዘኢየኀልቅ ልደቱ እየተባለ ይነገራል።

ቅድመ ዓለም የነበረ ወልድ ሰውን ለማዳን ከሰው ተወለደ። ይህኛው ልደት ደኃራዊ ልደት ይባላል። ደኃራዊነቱ ለቀዳማዊው ልደት ነው። አንዳንድ ሰዎች ድንግል ማርያም ፈጣሪን ከወለደችው እርሷን መጀመሪያ ማን ፈጠራት እያሉ ሊጠይቁ ይችላሉ። ድንግል የወለደችው ፈጣሪዋን ነው። ድንግል ወለደቶ ለገባሪሃ ወውእቱኒ ፈጠረ ወላዲቶ እንዲል ማር ኤፍሬም። ከድንግል ማርያም የተወለደው እርሷን ቀድሞ የፈጠረ አምላክ ነው። ከእርሷ ሲወለድ አምላክነቱን እና የአምላክነቱን ሥራ ሳይለቅ ነው። ቀድሞ ከአብ ያለ እናት የተወለደ ወልድ በኋላ ያለ አባት ከድንግል ማርያም ተወለደ። የወልድ ህልውና ከማርያም ወዲህ አይደለም። ፎጢኖስ የተባለ ሰው ለፌ እማርያም ክዋኔሁ ለወልድ ብሎ የክሕደት ትምህርትን አስተምሮ ነበር። ነገር ግን ጌታ ሲያስተምር አብርሃም ሳይወለድ እኔ ነበርኩ ብሎ ስለተናገረ የፎጢኖስ ሐሳብ ልብ ወለድ መሆኑ ታወቀ።

ስለዚህ የወልደ እግዚአብሔር ልደታት ሁለት ናቸው። እነዚህም ቀዳማዊ ልደቱ ከአብ ያለ እናት፣ ደኃራዊ ልደቱ ከድንግል ማርያም ያለ አባት በድንግልና ነው።
#በእንተ #ልደት #ክፍል #ሁለት
የጌታ ልደት መላእክትንና ሰዎችን አንድ ላይ እንዲያመሰግኑ ያደረገ ልዩ ቀን ነው። ሰይጣን በባርነት ሥር አድርጎ ወደ ሲዖል ያግዘን ነበር። አሁን ከዚያ ግዞት ነጻ የሚያወጣ ንጉሠ ነገሥት እግዚአብሔር በሥጋ ተወለደልን። ግዕዛነ ሥጋን ግዕዛነ ነፍስን አገኘን። ሰው ሲፀነስ ሰይጣን የወንዱን ዘር ምክንያት አድርጎ ይቆራኘውና ሰው ከተወለደ ጀምሮ ክፉ ሥራን እንዲሠራ ያስደርገው ነበር። ጌታ ግን መንገድ ለወጦበታል ያለ ወንድ ዘር ተወልዶ ይህንን የሰይጣንን ክፉ ሥራ አራቀልን። ሊቁ ተወልደ በአምሳሊከ ከመ ይለድከ በአምሳሊሁ ብሎ እንደተናገረው። እኛን የሰው ልጆችን በጸጋ የእግዚአብሔር ልጅ ያደርገን ዘንድ እርሱ ከሰው ተወለደ። እርሱን መስለን እንወለድ ዘንድ እኛን መሰሎ ተወለደ።

የነቢያት ትንቢት በክርስቶስ መወለድ ተረጋገጠ። ይሁንና ዓለም መድኃኒቷን የተቀበለችው በከብቶች በረት ነው። ድንግል ማርያም ጌታን ከወለደችው በኋላም በድንግልና ጸንታ ኑራለች። ከወለደችው በኋላ አውራ ጣቱን አሰረችው። እንዲህም ማድረጓ የወለደችው ክርስቶስ ምትሐት አለመሆኑን ለማስረዳት ነው። በተጨማሪም ዮሴፍ ኒቆዲሞስ በዕለተ ዐርብ እንዲህ ይገንዙሀል ስትል ነው።
#በእንተ #ልደት #ክፍል #ሦስት
__ዓለመ ዓለመ ዓለም___
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዘመነ ማቴዎስ፣ ታኅሣሥ 29፣ ማክሰኞ ቀን፣ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ተወለደ። በዘመነ ማቴዎስ ተወለደ እንዳንልማ ማቴዎስ፣ ዮሐንስ፣ ሉቃስ፣ ማርቆስ በኋላ የተነሡ ሰዎች አይደሉምን? የሚል ጥያቄ ሊነሣ ይችላል። መነሣቱ መልካም ነው። ይህን የመሰለ ዓለም መጋቢት 29 ቀን በዕለተ እሑድ በዘመነ ዮሐንስ ተፈጠረች እየተባለ ይነገራል። ይህ አቆጣጠር አሁን ያለውን አቆጣጠር ይዘን ወደኋላ በመቁጠር የደረስንበት መሆኑን ልብ ማድረግ ይገባል።

ቅዱሳን መላእክት እግዚአብሔርን አይተውት ስለማያውቁ የእርሱን በሥጋ መወለድ እኛ ብቻ ሳንሆን መላእክትም በናፍቆት ይጠባበቁት ነበር። በጠባብ ደረት ተወስኖ በቤተልሔም ሲወለድም እረኞች አዩት መላእክትም አይተው አመሰገኑት። ርእይዎ ኖሎት አእኮትዎ መላእክት እንዳለ ሊቁ። የተወለደው ጌታ በድንግል ማኅፀን ተወስኖ በዓለም መልቶ የነበረና ያለ ነው። ዓለምን የያዘ ጌታ በድንግል ማኅፀን ዓለምነት ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ተቀመጠ። የዓለማት ዓለማቸው በድንግል ማኅፀን ዓለምነት ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ተቀመጠ። ስለዚህም ድንግል ማርያምን ዓለመ ዓለመ ዓለም እንላታለን።
#በእንተ #ልደት #ክፍል #አራት
ቤዛ ኵሉ ዓለም ዮም ተወልደ።
የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ዛሬ ተወለደ። የጌታ መወለድ ለዓለም ሁሉ የምሥራች ነው። ጌታ ጥቂት ቡድኖችን፣ ጥቂት ሀገሮችን፣ ጥቂት ሰዎችን ለማዳን አልመጣም። ዓለምን ሁሉ ለማዳን መጥቷል እንጂ። ስለዚህም መድኃኔዓለም ተብሏል። ዮም ተወልደ መድኃኔ ዓለም። ሰው አእምሮው ሰፊ ሆኖ ከሰፈር አስተሳሰብ ወጥቶ ለዓለም ሲያስብ ጌታን ይመስለዋል። በጌታ መወለድ አጋንንት እና ባለጊዜ የነበሩት እነሄሮድስ ተከፍተዋል። ጌታን የሚያጠፉ መስሏች 144000 ሕፃናተ ሳሌምን አስገድለዋል። ውሸታቸውን በአደባባይ የሚገልጽ ንጉሠ ነገሥት ክርስቶስ ተወለደ። እውነት ክርስቶስ እነሆ ተወለደልን።

ለዚህች ልዩ ቀን ያደረሰን እግዚአብሔር ይመስገን።
        ሥርዓተ ማኅሌት ዘልደት

የልደት
#ሥርዓተ_ማኅሌት ከሊቃውንቱ ጋራ አብረን ለማመስገን ይረዳን ዘንድ እንደሚከተለው ተዘጋጅቷል።

የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ (ሥርዓተ ነግሥ)
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፤በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፤በአሐቲ ቃል።

መልክአ
ሰላም ለአጻብኢክሙ እለ እምአጽፋር ኢይትሌለዩ፤ለቤትክሙ ሥላሴ ዘኢየኃልቅ ንዋዩ፤አመ አብዓልክሙ ሰብአ ድኅረ አንደዩ ጌጋዩ፤ዘኢርእዩ እምቅድመ ዮም መላእክተ ሰማይ ርእዩ፤ወአግብርተ ሰብእ መላእክት ተሰምዩ።

ዚቅ
ርዎኖሎት አእኮትዎ መላእክት፤ለዘተወልደ እማርያም እምቅድስት ድንግል፤ዮም ሰማያዊ በጎል ሰከበ።

ወረብ
'ርእይዎ ኖሎት'/፪/ አእኮትዎ መላእክት/፪/
ዮም ሰማያዊ በጎል ሰከበ ለዘተወልደ እምቅድስት ድንግል/፪/

ዘጣዕሙ፦
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤መሠረተ ህይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።

ዚቅ
መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን፤ወብእሲ ተወልደ በውስቴታ።

ነግሥ
ሰላም ለልደትከ ኦ አማኑኤል፤ዘቀዳሚ ወዘደኃሪ ብሉየ መዋዕል፤ኢየሱስ ክርስቶስ ዘአብ ቃል፤እፎ እፎ አግመረተከ ድንግል፤ወእፎ እንዘ አምላክ ሰከብከ በጎል።

ዚቅ
በጎል ሰከበ በአጽርቅት ተጠብለለ፤ውስተ ማኅጸነ ድንግል ኃደረ፤እፎ ተሴሰየ ሀሊበ ከመ ሕፃናት።

ወረብ
በጎል ሰከበ በአጽርቅት ተጠብለለ ኃደረ ማኅጸነ ድንግል/፪/
እፎ 'ተሴሰየ'/፪/ ሀሊበ ከመ ሕፃናት ተሴሰየ/፪/

መልክአ ኢየሱስ
ሰላም ለዝክረ ስምከ ስመ መሐላ ዘኢይሔሱ፤ዘአንበረ ቅድመ እግዚአብሔር በአትሮንሱ፤ኢየሱስ ክርስቶስ ለዳዊት ባሕርየ ከርሱ፤አክሊለ ስምከ እንዘ ይትቄጸል በርእሱ፤አህጉረ ፀር ወረሰ ኢያሱ።

ዚቅ
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ንሰብከ ወልደ እምዘርዓ ዳዊት ዘመጽአ፤ወተወልደ በሥጋ ሰብእ፤እንዘ ኢየዓርቅ እመንበረ ስብሐቲሁ፤ውስተ ማኅፀነ ድንግል ኀደረ ሥጋ ኮነ ወተወልደ፤ትጉኃን የአምኑ ልደቶ፤ወሱራፌል ይቀውሙ ዓውዶ፤መጽአ ይቤዝወነ ውስተ ዓለም የሀበነ ሰላመ፤ጋዳ ያበውዑ ቁርባነ።

ምልጣን
መጽአ ከመ ይቤዙ ዓለመ የሀበነ ሰላመ፤ጋዳ ያበውዑ ቁርባነ።

ምልጣኑ በዚቅ አይባልም በሰላም ሲሆን ነው የሚባለው

ወረብ ፩
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ንሰብከ ወልደ እምዘርዓ ዳዊት/፪/
ወተወልደ በሥጋ ሰብእ/፪/

ወረብ ፪
'ውስተ ማኅጸነ ድንግል ኃደረ'/፪/ ሥጋ ኮነ/፪/
ወተወልደ በሥጋ ሰብእ ሥጋ ሰብእ በሥጋ ሰብእ/፪/

ዘበአታ፦
ወልድ ተወልደ መድኃኒነ፤ጥዩቀ እምዘርዓ ዳዊት፤በቤተልሔም ዘይሁዳ

ወረብ፦
ወልድ ተወልደ መድኃኒነ ጥዩቀ ወልድ ተወልደ/፪/
እምዘርዓ ዳዊት ቤተልሔም በቤተልሔም/፪/

መልክአ ኢየሱስ
ሰላም ለአጽፋረ እዴከ ዘኅበሪሆን ፀዓዳ፤በምግባር ወግእዝ እለ ይትዋሐዳ፤ኢየሱስ ክርስቶስ ምስፍና አባሉ ለይሁዳ፤ለመንግሥትከ ሰፋኒት እንዘ ይትመሐለሉ ዓውዳ፤ሰብአ ሰገል አወፈዩ ጋዳ።

ዚቅ
አንፈርዓጹ ሰብአ ሰገል፤አምኃሆሙ አምጽኡ መድምመ፤ረኪቦሙ ሕፃነ ዘተወልደ ለነ።

አመላለስ
አንፈርዓጹ ሰብአ ሰገል/፪/
አምኃሁ አምጽኡ መድምመ/፬/

መልክአ ኢየሱስ
እምኲሉ ይኄይስ በሥላሴከ ተአምኖ፤ወበወላዲትከ ተማኅፅኖ፤ኢየሱስ ክርስቶስ እምቤተ መንግሥት ወተክህኖ፤ተሰብኦትከ እመቦ ዘያስተሐቅር መኒኖ፤ያንኮርኲር ታሕት ደይን ግዱፈ ከዊኖ።

ዚቅ
ወካዕበ ተማኅፀነ በማርያም እምከ፤እንተ ይእቲ እግዝእትነ፤ወትምክሕተ ዘመድነ በወሊዶተ ዚአከ።

ወረብ
'ትምክሕተ ዘመድነ'/፪/ በወሊዶተ ዚአከ/፪/
ይእቲ 'እግዝእትነ'/፪/ ማርያም ድንግል/፪/

ማኅሌተ ጽጌ
ኦ ዝ መንክር በዘዚአኪ አምሳል፤ኮከበ ትንቢት ዘቦቱ መልክአ ሕፃን ሥዑል፤ሠረቀ ያርኢ ተአምረኪ ድንግል፤ወመርሖሙ ለሰብአ ሰገል እምርሑቅ ደወል፤ጽጌኪ ኀበ ሀሎ ይሰክብ በጎል።

ዚቅ
ወኖሎት በቤተ ልሔም፤አንከሩ እምዘርእዩ ወሰምዑ፤ሰብአ ሰገል ርእዮሙ ኮከበ፤መጽኡ እምርኁቅ ብሔር፤ከመ ይስግዱ ለወልድኪ ወይግነዩ ለኪ።

ወረብ
በኮከብ መጽኡ ሰብአ ሰገል/፪/
ይስግዱ ለአማኑኤል ይስግዱ/፪/

አንገርጋሪ
ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደቱ ለክርስቶስ፤እምቅድስት ድንግል፤ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ፤ዘሎቱ ሰብአ ሰገል ሰገዱ ሎቱ፤አማን፤መንክር ስብሐተ ልደቱ።

ምልጣን ዘዜማ ወዘአቋቋም
ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ፤ዘሎቱ ሰብአ ሰገል ሰገዱ ሎቱ፤ አማን፤መንክር ስብሐተ ልደቱ።

አመላለስ
'አማን በአማን'/፪/ መንክር 'አማን በአማን'/፪//፪/
መንክር ስብሐተ ልደቱ/፬/

ወረብ ዘአንገርጋሪ
ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደቱ ለክርስቶስ/፪/
እምቅድስት 'ድንግል'/፪/ ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ/፪/

እስመ ለዓለም
ተወልደ ኢየሱስ በቤተ ልሔም ዘይሁዳ፤አዋልደ ጢሮስ አሜሃ ይሰግዳ፤ሰብአ ሰገል አምጽኡ ሎቱ ጋዳ፤ወይትኃሠያ አዋልደ ይሁዳ።

አመላለስ፦
ሰብአ ሰገል አምጽኡ ሎቱ ጋዳ[፪]
ወይትኃሠያ አዋልደ ይሁዳ[፬]


ወረብ ዘእስመ ለዓለም
ተወልደ ኢየሱስ 'በቤተ ልሔም'/፪/ ዘይሁዳ በቤተ ልሔም/፪/
አዋልደ ጢሮስ 'አሜሃ ይሰግዳ'/፪/ በቤተ ልሔም/፪/

@Mezigebehayimanot
@Mezigebehayimanot
@Mezigebehayimanot
እንኳን አደረሳችኁ !
#ልደቱ_ለእግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ
#ጌና_እና_ልደት
ጌና እና ልደት ዋዜማና ክብረ በዓል /የተለያዩ ቀናት/ ቢኾኑም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን ጌና ልደትን እየተካ እንጠቀምበታለን፤ ነገር ግን ይህ ሊስተካከል ይገባዋል፡፡ ልዩነት ስላለውም የኢትዮጵያ ብርሃን የተባለው አፈ ጳዝዮን አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ለጌናና ለልደት ለ2ቱም በዓላት ለየብቻቸው በመጽሐፈ ምሥጢር ድርሰት ደርሶላቸዋል፡፡
#ጌና፤ የልደት በዓል ዋዜማ ቀን ሲኾን በዚህ ቀን ‹‹በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ›› የተባለለትን ‹‹የገና ጨዋታ›› እንጫወታለን፤ የምንጫወትበት የኳሱ ስያሜ ‹‹ሩር›› ሲባል ስያሜውን ያገኘው፤ ሰብዓ ሰገል እልፍ እልፍ ሠራዊት አስከትለው የተወለደውን አይሁድ ንጉሥ ፍለጋ ወደ ንጉሡ ሔሮድስ ደርሰው ነበርና፤ ሔሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ፈልጎና በውስጡ ሸሽጎ ለሰብዓ ሰገል ሂዱ ሕፃኑን ፈልጉ ስታገኙትም ንገሩኝ ብሎ ሰድዷቸዋል፤ ነገር ግን በዚያው ሳይነግሩኝ እንዳይሄዱ በማለት እነርሱ ሳያውቁ ‹‹ሩር›› የተባለ ሰላይ በመሃላቸው አስገብቶ ነበርና ሰብዓ ሰገልን ይመራቸው የነበረው ኰከብ ተሠውሮባቸዋል፤ ሰብዓ ሰገል ሠራዊታቸውን ቢያጣሩ ከመሃከላቸው የተቀላቀለ ሩር የተባለ የሔሮድስን ሰላይ አገኙ ይህንንም ሰላይ የሰብዓ ሰገል ሠራዊት አንገቱን በሰይፍ ቀልተውታልና ያን ለማስታወስ ዛሬ በገና ጨዋታ ላይ ሩር የተባለው ኳስ የሔሮድስ ሰላይን ‹‹ሩር›› እንዲያስታውስ አባቶች ሥርዐትን ሠሩ፡፡
#ልደቱ_ለእግዚእነ_ኢየሱስ_ክርስቶስ
#‹‹ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ::›› /#ቅዱስ_ያሬድ/
ጌታችን ለሰው ልጆች ብሎ፤ የሰው ልጆች ፍቅር አገብሮት ንጽሕትና ቅድስት ከኾነች ከእመቤታችን ያለ ወንድ ዘር በመጋቢት 29 ተጸንሶ ታኅሣሥ 29 በ1ዓ.ም. (ዓለም ከተፈጠረ፥ ዘመን ከተቈጠረ በ5,500 ዓመት) በበረት ተወልደ፡፡ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን በረት ቻለው፤ ወሰነውም በሌሊት መንጋቸውን የሚጠብቁ እረኞች ነበሩ፡፡ መልአኩ መጥቶ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹እነሆ! ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኀኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና፡፡ ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ›› አላቸው፡፡ ሉቃ2፡10-12፡፡ ከመለአኩም ጋራ ሠራዊተ መላእክት መጥተው ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ለዕጓለ እመሕያው /ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ/›› አሉ፡፡ ቅዱሳን መላእክትም ከእነርሱ ተለይተው ወደ ሰማይ በወጡ ጊዜ እረኞቹ እርስ በርሳቸው ‹‹እንግዲህ እስከ ቤተ ልሔም ድረስ እንሂድ፣ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን የሆነውን ነገር እንይ›› ተባባሉና ፈጥነው መጡ፡፡ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በግርግም ተኝቶ አገኙ፡፡ አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ፤ የሰሙትን ሁሉ እረኞቹ በነገሯቸው ነገር አደነቁ፤ የብርሃን እናቱ እመ አምላክ ግን ይህን ነገር ሁሉ በልብዋ እያሰበች ትጠብቀው ነበር፡፡ ሉቃ 2፡13-19፡፡
መላእክትም ሰማይ መንበሩ ምድር የእግሩ መረገጫ የሆኑለት አምላክ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ በጎል ተኝቶ በጨርቅ ተጠቅልሎ አይተውት ደስ ብሏቸው ወደ ሰማይ ቢያርጉ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በዕሪና ከመንበሩ አይተውት ‹‹ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት›› ብለው አመስግነውት በጣዕም ላይ ጣዕም፤ በጸጋ ላይ ጸጋ ተጨምሮላቸው ደስ ብሏቸዋል፡፡ ልደቱን ይሹታልና፤ መላእክትም ብቻ አይደሉም እንስሳትም አራዊትም ደስ ብሏቸዋል፡፡ #ይህም_ሊታወቅ_አንድ_ባሕታዊ_በቋራ_/_ኋላ_ማኅበረ_ሥላሴ_ገዳም/_ቋርፍ_ሲምስ_ቶራ_ሚዳቋ_ዮም_ተወልደ_ መድኀኔ_ዓለም_ዮም_ተወልደ_ቤዛ_ኵሉ_ዓለም_ዮም_ተወልደ_ከሣቴ_ብርሃን፡፡ እያለች ስትዘል አይቷል። በጌታችን በልደቱ የባሕር ውኃ ወተትና ማር ተራሮች እንጀራ እንጨቶችም የበረከት ፍሬ ሆነዋል፡፡ ልደቱንም በኮከብ ተረድተው ሰብአ ሰገል (የጥበብ ሰዎች) ስማቸውም ማንቱሲማር፣ ሜልኩ በዲዳስፋ የተባሉ የፋርስ ነገሥታት ከገነት የተገኘ ወርቅ፣ ዕጣን ከርቤ አምጥተው ገብረውለታል፡፡ /ዘኅ 20፡17፡፡
‹‹ሰው ሆይ! ፈጽመህ ደስ ይበልህ፣ እግዚአብሔር ዓለሙን ወዶታልና አንድ ልጁንም የሚያምንበት ሁሉ እስከ ዘለዓለም ፈጽሞ ይድን ዘንድ አሳልፎ ሰጥቷልና ልዑል ክንዱን ሰደደልን፡፡››
‹‹በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው፤ በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሆኗልና ኑ ይህን ድንቅ እዩ፤ ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ፤ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፣ ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት፡፡ የማይታወቅ ተገለጠ፣ የማይታይ ታየ፣ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በእርግጥ ሰው ሆነ፡፡››
‹‹ከቅድስት ሥለሴ አንዱ ወልድ መዋረዳችንን አይቶ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ባሕርዩን ዝቅ አደረገና መጥቶ በድንግል ማኅፀን አደረ፤ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀርም እንደ እኛ ሰው ሆነ፡፡ ነቢያት ትንቢት እንደተናገሩለት በቤተልሔም ተወለደ፤ ፈጽሞ አዳነን፣ ወገኖቹም አደረገን፡፡››
ይህችም ዕለት፤  ነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ ብሎ ትንቢት የተናገረላት ናት፡- ‹‹እነሆ ድንግል ፀንሳ ወንድ ልጅ ትወልዳለች፣ ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች፣ ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡ /ት.ኢሳ. 7፥14/
**ነቢይ ሕዝቅኤል ‹‹እግዚአብሔርም አለኝ ‹ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች፣ አትከፈትም፣ የሚገባበትም የለም የእስራኤል ፈጣሪ እግዚአብሔር እንደተዘጋች ይገባባታልና ተዘግታ ትኑር››› አለ፡፡
**ነቢዩ ዳንኤልም ‹‹ሌሊት በራእይ አየሁ ‹እነሆ ታላቁ እንደ ሰው ልጅ በሰማይ ደመና መጣ፤ ዘመኑን ወደሚያስረጅ ደረሰ፣ ከፊቱም አቀረቡት፣ የዘላለም አገዛዝ፣ ጌትነት፣ መንግሥት ተሰጠው፡፡ ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል፤ አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው፤ መንግሥቱም የማያልፍ የማይጠፋ ነው››› አለ፡፡
**ዳግመኛም ኢሳይያስ ‹‹እግዚአብሔር እንደ እኔ የሥጋ መጋረጃ በመጋረድ ተገለጠልኝ›› አለ፡፡ አሁንም ደግሞ ‹‹አዲስ ሰማይ አዲስ ምድር እሠራ ዘንድ አለኝ›› አለ፡፡ ሁለተኛም ‹‹በእሴይ ሥር በትር ትወጣለች፣ ከእርሷም ጽጌ አበባ ይወጣል›› አለ፡፡ ዳግመኛም ‹‹ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና ይኸውም ሥልጣን በጫንቃው የሆነ ክርስቶስ ነው፣ ስሙም ድንቅ መካር፣ ኃያል አምላክ፣ የዘላለም አባት፣ የሰላም አለቃ ይባላል›› አለ፡፡
**ነቢዩ ኤርምያስም ስለ እግዚአብሔር ‹‹በዚያን ወራት ለዳዊት ብርሃንን አወጣለሁ፣ በምድርም የቀና ፍርድን ያደርጋል፣ እግዚአብሔርም ያመኑትን ያድናቸዋል›› አለ፡፡
**ኤልሳም ‹‹እግዚአብሔር ከሰማይ ይወርዳል፣ በእስራኤል ልጆች አደባባይም በመመላለስ ለሕዝቡ ዕውነትን ያስተምራቸዋል፡፡ ከአብርሃም ልጅነት ልዩ ከሆኑ ወገኖች በቀር አሕዛብ ሁሉ ይታዘዙለታል›› አለ፡፡
**ናሆምም ‹‹እግዚአብሔር በእኔ አርአያ ይመጣል፣ ልብሱም እንደልብሴ ነው›› አለ፡፡
ሥርዓተ ማኅሌት አመ ፩ ለጥር እስጢፋኖስ



የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ (ሥርዓተ ነግሥ)
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፤በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፤በአሐቲ ቃል።

መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለአቊያጺክሙ እለ ተኀብአ እምዓይን፤አናሚያኒሁ ሥላሴ ለሜላተ ሰማይ ብርሃን፤ልብሰ ሰማዕትና ይኩንኒ ምሕረተክሙ ክዳን፤ላዕሌየ እስመ ኢሀሎ ልብሰ እሰጢፋኖስ ዕብን፤ወሥርጋዌሁ እሳት ለቂርቆስ ሕፃን።

ዚቅ
ሃሌ ሉያ ለአብ፤ሃሌ ሉያ ለወልድ፤ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ፤እስጢፋኖስ በጽጌ ሃይማኖት ተሠርገወ በፍቅረ አምላኩ መዊተ ፈተወ ለወልደ አብ ልደቶ ዜነወ በእንተ ጽድቅ ወሕይወት ደሞ ከዓወ።

ዘጣዕሙ
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኰት
ስሙ።

ዚቅ
መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን፤ወብእሲ ተወልደ በውስቴታ።

ወረብ
መሠረታቲሃ/፪/ውስተ አድባር/፪/
ወብእሲ ተወልደ በውስቴታ ተወልደ/፪/

መልክአ እስጢፋኖስ
ሰላም ለዝክረ ስምከ እንተ ጸሐፎ በአክናፉ፤እግዚአ መናፍስት ሕያው ዘኢይመውት ለዝላፉ፤ስሙዓ ዜና እስጢፋኖስ ለዓለም እስከ አጽናፉ፤ምስለ ማኅበረ በኲር አኃዊከ እለ በሃይማኖት አዕረፉ፤ስመ ዚአየ አዘክር መላእክት ይጽሐፉ፡፡

ዚቅ
ኢየሩሳሌም ትቤ ተወልደ ንጉሥየ ወአምላኪየ፤ኢየሩሳሌም ትቤ በቤተልሔም ተወልደ በተድላ መለኮት፤ኢየሩሳሌም ትቤ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት፤ኢየሩሳሌም ትቤ ዘይሴብሕዎ ሐራ ሰማይ በማኅበረ ቅዱሳን ኢየሩሳሌም ትቤ።

ወረብ
አምላኪየ/፪/ተወልደ ንጉሥየ በቤተልሔም/፪/
ዘይሴብሕዎ ኵሎሙ ሐራ ሰማይ ማኅበረ ቅዱሳን
ደብረ___/፪/

መልክአ እስጢፋኖስ
ሰላም ለልሳንከ በኦሪተ ሙሴ ዘአዝመረ፤ጽሒፈ ወንጌል አሜሃ እስመ ማቴዎስ አድኀረ፤አእምሮትከ እስጢፋኖስ በላዕሌየ ተነክረ፤አልቦ ዘኮነ በቅድሜከ ለሰማዕታት በኵረ፤እንበለ ሕጻናት አርእስቲሆሙ ዘሄሮድስ አምተረ፡፡

ወረብ
አእምሮትከ እስጢፋኖስ በላዕሌየ ተነክረ/፪/
አልቦ በቅድሜከ ለሰማዕታት በኵረ ዘኮነ/፪/በቅድሜከ/፪/

ዚቅ
ቀትለ ሕጻናት ንጉሠ ገሊላ ሶበ ኀሠሠ በዘባነ እሙ
ድንግል ክርስቶስ ተግኅሰ እስጢፋኖስ ሰማዕት እንዘ
ይጸውር ንጉሠ ሐራ ሄሮድስ ዐላዊ ተለውዎ ርእሰ።

መልክአ እስጢፋኖስ
ሰላም ለሕፅንከ እንተ ኮነት ማኅፈዳ፤ለጥበብ ኅሪት ንጉሠ እስራኤል ዘንእዳ፤ነቢያተ አበዊሃ ወሐዋርያተ ውሉዳ፤ከመ ቀተለት እስጢፋኖስ ኢየሩሳሌም ሳይዳ፤እፎ ቀተለተከ ዳግመ በዓውዳ፡፡

ዚቅ
ኢየሩሳሌም/፪/ እንተ ትቀትሎሙ ለነቢያቲሃ
ወትዌግሮሙ ለሐዋርያቲሃ ሚ መጠን ዘተክዕወ
ዲቤሃ እምደመ አቤል ጻድቅ እስከ ደመ እስጢፋኖስ
ቀዳሜ ሰማዕት።

ወረብ
ሚ መጠን ዘተክዕወ ዲቤሃ ደመ እስጢፋኖስ/፪
ኢየሩሳሌም/፪/እንተ ትቀትሎሙ ለነቢያት/፪

መልክአ እስጢፋኖስ
ሰላም ለጸአተ ነፍስከ በሠርቀ ወርኀ ጥር ወርኀ ሱላሜ፤እንተ ይእቲ ትትበሀል ዓውደ ዓመቶሙ ለሰብአ ሮሜ፤ሶበ ጸለይከ እስጢፋኖስ ለስምዓ ገድልከ ጊዜ ፍጻሜ፤ከመ ተመጠወ መድኃኒነ ነፍሰ ዚአከ አበሜ፤ተመጠው ነፍስየ ዘአልቦ ቅያሜ፡፡

ዚቅ
ወወጽአት መንፈሱ ሶቤሃ፤ወተቀበልዎ መላእክት በስብሐት ወበማኅሌት፤እንዘ ይብሉ ሃሌ ሉያ፤ወአብዕዎ ኢየሩሳሌም ሰማያዊተ።

ወረብ
እንዘ ይብሉ መላእክት ሃሌ ሉያ ወተቀበልዎ ለእስጢፋኖስ/፪/
ወአብዕዎ ኢየሩሳሌም ሰማያዊተ ደብረ_/፪/

መልክአ እስጢፋኖስ
ሰላም ለበድነ ሥጋከ እም እግዚአብሔር ዘተሠልጠነ፤ከመ ይፈውስ ዱያነ ወከመ ያንሥእ ሙታነ፤በእንተ ዝንቱ እስጢፋኖስ ክብረ ሞትከ አእመርነ፤በመትል ወበዓል ዘእግዚእከ አመ በዓልከ ኮነ፤እምቅኔ ግብርናት አዕረፍነ ኵልነ፡፡

ዚቅ
ዓቢይ ወክቡር አንተ እስጢፋኖስ ዘበመትል ወበዓለ እግዚእከ ኮነ በዓልከ እስመ ለኵሉ ነባሪ ወቀናዪ እረፍተ ኮነ በዓልከ።

ወረብ
ዓቢይ ወክቡር አንተ እስጢፋኖስ/፪/
እስመ ለኵሉ ነባሪ ወቀናዪ እረፍተ ኮነ በዓልከ/፪/

መልክአ እስጢፋኖስ
ሰላም ለግንዘተ ሥጋከ ምስለ ግብረ ማኅሌት ወይባቤ፤በመዓዛ ዕፍረት ጽዑጥ ወጼና ሕውስ ከርቤ፤ተሰጥዎሙ እስጢፋኖስ ተራድኦሙ በጊዜ ምንዳቤ፤ማኅበረ ቅዱሳን ፍፁማን ከመ ቃለ መጽሐፍ ይቤ፤ኪያከ ይጼውዑ አርከ ኪያከ አበ ኪያከ ረዳኤ ወኪያከ መጋቤ፡፡

ዚቅ
ተጋብኡ በቅጽበት ለግንዘተ ሥጋሁ ቅዱስ ብጹዓን ሐዋርያት ቦኡ ኀቤሁ በሰላም አምኁ ኪያሁ በስብሐት ገነዙ ሥጋሁ።

ወረብ
ብጹዓን ሐዋርያት በሰላም ተጋብኡ/፪/
ለግንዘተ ሥጋ ሥጋሁ ቅዱስ/፫/ እስጢፋኖስ/፪/

ምልጣን
አክሊሎሙ ለሰማዕት ሠያሚሆሙ ለካህናት ሰበክዎ ነቢያት አዕኰትዎ መላእክት ወልድ ተወልደ ብኁተ ልደት አንጐድጐደ እምሰማያት ወረደ።

አመላለስ
አንጐድጐደ አንጐድጐደ/፪/
ወረደ/፬/ እምሰማያት/፬/

ቅንዋት
ተሰደ ሰይጣን(ጽልመት) ወተቀደሰ ዓለም በእንተ ልደቱ ለወልድ እግዚአብሔር ነቢያት ኮንዎ ሰማዕቶ ከመ ይትወለድ ክርስቶስ እምድንግል አክሊሎሙ ለሰማዕት ወረደ ዲበ ዕፅ ተሰቅለ።
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
Audio
ወደእኛ ተመልከት 
                                                  
Size:- 26.2MB
Length:-1:15:20
       
     በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
Forwarded from Quality move bot
ተዋህዶ ሀይማኖቴ ነው ስለ ሀይማኖቴ ማወቅ መረዳት መጻህፍትን ማንበብ እፈልጋለው የየእለቱን ስንክሳር ማንበብ እፈልጋለው ያለ ሁሉ ሊቀላቀላቀላቸው ሚገባ ድንቅ ኦርቶዶክሳዊ ቻናል 3 ቻናሎች
👇 ከታች Join በሉ
ሥርዐተ ማሕሌት ዘሥላሴ ጥር ፯

ስምዐኒ እግዚኦ ጸሎትየ፥ ሀሌ ሉያ ሀሌ ሉያ፥ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፥ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፥ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፥ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፥ ሀሌ ሉያ ሀሌ ሉያ፥ አመ ዕለተ እጼውዐከ ፍጡነ ስምዓኒ፥ ሀሌ ሉያ ሀሌ ሉያ፥ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፥ ሀሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፥ ንወድሶ ለዘሀሎ እግዚአብሔር ልዑል፥ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኵሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።

ነግሥ
ሰላም ለአብ ዘእም ቅድመ ዓለም ነጋሢ፤ ለወልድ ሰላም ሥጋ ማርያም ለባሲ፤ ለመንፈስ ቅዱስ ሰላም ኀጢአተ ዓለም ደምሳሲ፤ ኀይልየ ሥላሴ ወጸወንየ ሥላሴ፤ በስመ ሥላሴ እቀጠቅጥ ከይሴ።

ዚቅ
ዘለብሰ ስብሐተ፤ ሀሎ ሰማያተ፤ እምድንግል ቃል ሥጋ ኮነ፤ በቤተ ልሔም ተወልደ።

ወረብ፦
ዘለብሰ ስብሐተ ዘለብሰ ስብሐተ ሀሎ ሰማያተ፤
እም ድንግል ቃል ሥጋ ኮነእምድንግል ቃል።

መልክዐ ሚካኤል
ሰላም ለአጽፋረ እግርከ ፍናዋተ ረድኤት በተኃልፎ፤ ዘኢተዳደቆን እብነ አዕቅፎ፤ ሚካኤል ቀዳሲ ትሥልስተ አካላት በኢያዕርፎ፤ ኢትኅድገኒ በዓለም እስመ ኪያከ እሴፎ፤ አልቦ ብእሲ ዘየኀድግ ሱታፎ።

ዚቅ
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር፤ ዘበተዋሕዶ ይሤለስ፤ እም ኀበ ትጉሃን ይትቄደስ፤ እሳተ ሕይወት ዘኢይትገሠሥ፤ ወዘኢይጤየቅ ለዓይን ረቂቅ መንፈስ፤ ንሰግድ ለትሥልስቱ አሐተ ስግደተ፤ ወሎቱ ናቄርብ ስብሐታተ።

ማኅሌተ ጽጌ
ተፈሥሒ ማርያም እንተ ኢተአምሪ ብእሴ፤ ዘጸገይኪ ለነ አሐደ እምነ ሥላሴ፤ እንዘ ትዘብጥ ከበሮ ቅድመ አዕላፈ ኤፍሬም ወምናሴ፤ ለተአምርኪ ትነግር ውዳሴ፤ ማርያም እኅቱ ለሙሴ።

ዚቅ
በፈቃደ አቡሁ ወረደ ኀበ ማርያም ተአንገደ፤ በድንግልናሃ ንጹሕ እግዚአብሔር ተወልደ።

ወረብ፦
በፈቃደ አቡሁ ወረደ  ተአንገደ በደብረ ብርሀን ፤
በድንግልናሃ ንጹሕ በድንግልናሃ ንጹሕ እግዚአብሔር ተወልደ።

መልክዐ ሥላሴ
ሰላም ለህላዌክሙ ዘይመውእ ህላዌያተ፤ ለረኪበ ስሙ ኅቡዕ አመ ወጠንኩ ተምኔተ፤ እም ግብርክሙ ሥላሴ ሶበ ረከብኩ አስማተ፤ መለኮተ ለለአሐዱ ዘዚኣክሙ ገጻተ፤ እንበለ ትድምርት እሰሚ ወእሁብ ትድምርተ።

ዚቅ
ነአምን በአብ ወነአምን በወልድ፤ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ፤ ነአምን ዘንተ ሥላሴ ፩ ውእቱ አምላክ ፍጹም፤ ዘእምኔሁ ለአብ ወልድ ተወልደ፤ በአምሳለ ዚኣሁ፤ ኅቡር ኅላዌሁ፤ ነአምን ንሕነ ነአምን።

ወረብ
ነአምን በአብ ወነአምን በወልድ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ/፪/
፩ ውእቱ አምላክ ፍጹም ፩ ውእቱ/፪/

መልክዐ ሥላሴ
ሰላም ለአጻብኢክሙ እለ እም አጽፋር ኢይትሌለዩ፤ ለቤትክሙ ሥላሴ ዘኢየኀልቅ ንዋዩ፤ አመ አብዐልክሙ ሰብአ ድኅረ አንደዮ ጌጋዩ፤ ዘኢርእዩ እም ቅድመ ዮም መላእክተ ሰማይ ርእዩ፤ ወአግብርተ ሰብእ መላእክት ተሰምዩ።

ዚቅ
ርእይዎ ኖሎት አእኮትዎ መላእክት፤ ለዘተወልደ እማርያም እም ቅድስት ድንግል፤ ዮም ሰማያዊ በጎል ሰከበ።

ወረብ
ርእይዎ 'ኖሎት'/፪/ ርእይዎ አእኮትዎ/፪/
ለዘተወልደ እማርያም እምቅድስት ድንግል/፪/

መልክዐ ሥላሴ
ለዘበነጊድ አቅረብኩ መካልየ ልሳን ስብሐታተ፤ መጠነ ራብዕ ዐሥር እንዘ አተሉ ሰብዓተ፤ ህየንተ አሐዱ ሥላሴ እለ ትፈድዩ ምዕተ፤ ጸግዉኒ እም ገጽክሙ ንዋየ ገጽ ትፍሥሕተ፤ ወዲበ ዐሠርቱ አህጉር ሀቡኒ ሢመተ።

ወረብ
ጸግዉኒ አጋዕዝትየ እም ገጽክሙ ንዋየ ገጽ/፪/
ወዲበ ዐሠርቱ አህጉር ሀቡኒ ሢመተ/፪/

ዚቅ
ስብሐት ለከ ስብሐት ለዘወለደከ፤ ስብሐት ለዘሠረፀ እም አቡከ፤ ዘዕሩይ ምስሌሁ ወምስሌከ፤ በከዊነ ዘሀሎ ወይሄሉ፤ ለዓለመ ዓለም።

ወረብ
ስብሐት ለከ ስብሐት ለዘወለደከ ስብሐት ለዘሠረፀ እም አቡከ/፪/
ዘሀሎ ወይሄሉ ዘዕሩይ ምስሌሁ/፪/

አንገርጋሪ
ኵሉ ይሰግድ ለሥላሴ፤ ወይትቀነይ ኵሉ ለመንግሥተ ሥላሴ፤ እስመ ኮነ ዘይነብር ዲበ ኪሩቤል፤ ወበዐይኑ ይኔጽር ቀላያተ።

አመላለስ
እስመ ኮነ ዘይነብር ዲበ ኪሩቤል እስመ ኮነ/፪/
ወበዐይኑ 'ይኔጽር'/፪/ ቀላያተ/፪/

ወረብ
ኵሉ ይሰግድ 'ለሥላሴ'/፪/ ኵሉ ይሰግድ/፪/
ወይትቀነይ ኵሉ ለመንግሥተ 'ሥላሴ'/፪/ ኵሉ ይሰግድ/፪/

እስመ ለዓለም
እገኒ ለከ እግዚኦ አምላኪየ ዘዲበ ሠረገላ ኪሩቤል ትነብር፤ ኢየሐፅፅ ወልድ እም ህላዌሁ ለአብ፤ እንዘ ሀሎ ምድረ ኀቤነ ነገረነ ዜናከ፤ ማርያምሰ ተንከተመ እግዚአብሔር ኮነት ለነ፤ ዛቲ ይእቲ ትምክሕትነ ስምዐ ግዕዛንነ፤ ወተወልደ መድኀኒነ ፍሥሓነ ወክብርነ፤ ወልዶ ዘያፈቅር ፈነወ ለነ።

አመላለስ፦
ወተወልደ መድኀኒነ ፍሥሐነ ወክብርነ[፪]
ወልዶ ዘያፈቅር ፈነወ ለነ። [፬]

ወረብ
እገኒ ለከ አምላኪየ ዘዲበ ሠረገላ ኪሩቤል ትነብር/፪/
ኢየሐፅፅ ወልድ እም ህላዌሁ ለአብ ህላዌሁ/፪/
2024/09/21 19:37:13
Back to Top
HTML Embed Code: