Telegram Web Link
ሥርዓተ ማኀሌት ዘኅዳር ፲፪ ፤ በዓለ ቅዱስ ሚካኤል
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
+ የአያቶች ቀን +

እናትነት ጸጋ ነው:: አባትነትም ደስታ ነው:: ከሁለቱ በላይ ደግሞ አያት መሆን ይበልጣል:: ልጅን ከማየት የበለጠ የልጅ ልጅን የማየት ደስታ እጅግ ትልቅ ነው:: እናት ለልጅዋ ከምታሳየው ፍቅር የአያት ፍቅር የሚበልጠው በአያት እጅ ያደጉ ልጆች ስስትና እንክብካቤ የሚበዛባቸው ለዚህ ነው:: ወላጆች የሚቆጡት ልጅ አያት ሥር የሚደበቀው ለዚህ ነው::

የአባቶችና የእናቶች ቀን እንደሚታሰበው ሁሉ አብልጦ ሊታሰብ የሚገባው የአያቶች ቀን ነው:: ዕድሜ ቢጫናቸው እንኳን ለልጅ ልጆቻቸው ፈገግታቸው የማይደበዝዝ በዕድሜያቸው ፀሐይ መጥለቂያ ሳይደክማቸው ፍቅር የሚሠጡ የፍቅር ጥግ ማሳያዎች አያቶች ናቸው::

ዛሬ በቤተ ክርስቲያን የአያቶች ቀን በታላቅ ድምቀት እየተከበረ ነው:: በምድር ካሉ አያቶች ሁሉ የሚበልጡት አያቶች ቅድስት ሃና እና ቅዱስ ኢያቄም የሚታሰቡበትክብረ በዓል ነው:: ድንግል ማርያም ከእናቶች ሁሉ እንደምትበልጥ ወላጆችዋም ከአያቶች ሁሉ ይበልጣሉ:: እርስዋን የአምላክ እናት ብለን እንደምናከብር እነርሱንም የአምላክ አያቶች ብለን እናከብራቸዋለን::
በመለኮቱ አባት እንጂ አያት ለሌለው ለመድኃኔ ዓለም ክርስቶስ አያቶቹ የሆኑ ሃና እና ኢያቄም እጅ ክቡራን ናቸው::

ሃና ሰማይን ወለደች ልጅዋ ፀሐይን ወለደች:: ሃና ምንጭን ወለደች ልጅዋ የሕይወትን ውኃ ወለደች:: በጌታ የዘር ሐረግ ውስጥ የተቆጠሩ ሁሉ ክቡራን ናቸው የመጨረሻዎቹ አያቶቹ ደግሞ የመጨረሻው ክብር ይገባቸዋል::

ሃና እና ኢያቄም የልጅ ልጄ የሚሉት ፈጣሪያቸውን ነው:: እርግጥ ነው በሕይወት ቆይተው ቀድሞ በሕልም አይተው ያልተረዱትን የልጃቸውን ልጅ ክርስቶስን አቅፈው ለመሳም አልታደሉም:: ሆኖም ድል አድራጊው የልጅ ልጃቸው የሲኦልን መዝጊያ ሰብሮ ነፍሳትን ሲያወጣ አያቶቹንም አውጥቶአቸዋልና ልጃቸው የወለደችውን ፀሐይ በሲኦል ሲያበራ አይተው ሕልማቸው ተፈትቶአል::

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ኅዳር 11 የቅድስት ሀና በዓል
ድሬዳዋ ኢትዮጵያ

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ! በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)

@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
ሥርዓተ ማኀሌት ዘኅዳር ፲፪ ፤ በዓለ ቅዱስ ሚካኤል
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
ሥርዓተ ማህሌት አመ ፲ወ፪ ለኅዳር ሚካኤል


የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ (ሥርዓተ ነግሥ)
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፤በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፤ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፤ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፤ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፤በአሐቲ ቃል።


መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለጒርዔክሙ ስቴ አንብአ ሰብእ ዘኀሠሠ፤ብዑላነ ሞገስ ሥላሴ ኢታንድዩኒ ሞገሰ፤ከመ ትትኃየዩኒሰ ወኢትኅድጉኒ ጽኑሰ፤ሚካኤልኑ ለአውጽኦ ስጋየ ጌሠ፤ወእመ አኮ ገብርኤል ወሀበኒ ነፍሰ።


ዚቅ
አመ ይፈጥራ እግዚአብሔር ለምድር፤ኢዜነዎ ለሰማይ፤ወኢተማከረ ምስለ መላእክቲሁ፤ወተከለ ፫ተ ዕፀ ህይወት በዲበ ምድር።


ነግሥ
ጐሥዐ ልብየ ጥበበ ወልቡና፤ለውዳሴከ ጥዑመ ዜና፤ቅዱስ ሚካኤል ልማድከ ግብረ ትሕትና፤አንተኑ ዘመራኅኮሙ ፍና፤ወአንተኑ ለ፳ኤል ዘአውረድከ መና።


ወረብ
አንተኑ ሚካኤል መና መና ዘአውረድከ/፪/
ወአንተኑ ለ፳ኤል መና ዘአውረድከ/፪/

ዚቅ
አዝነመ ሎሙ መና ይብልዑ፤ፀዓዳ ከመ በረድ፤ወርእየቱ ከመ ተቅዳ፤ኅብስተ እምሰማይ ወሀቦሙ፤አውኃዘ ሎሙ ማየ ህይወት፤ዘትረ ኴክኅ ፈልፈለ ነቅዕ ዘኢይነቅዝ፤ኅብስተ እምሰማይ ወሀቦሙ።


መልክአ ሚካኤል
ሰላም ለዝክረ ስምከ ምስለ ስመ ልዑል ዘተሳተፈ፤ወልደ ያሬድ ሄኖክ በከመ ጸሐፈ፤ሶበ እጼውዕ ስመከ ከሢትየ አፈ፤ረዳኤ ምንዱባን ሚካኤል በከመ ታለምድ ዘልፈ፤ለረዲኦትየ ነዓ ሰፊሐከ ክንፈ።

ወረብ
ረዳኤ ምንዱባን ሚካኤል ረዳኤ ምንዱባን/፪/
በከመ ከመ ታለምድ ዘልፈ/፪/

ዚቅ

ውእቱ ሚካኤል መልአከ ኃይል፤ልዑል ውእቱ ልዑለ መንበር፤ይስአል ለነ፤ረዳኤ ይኲነነ አመ ምንዳቤነ፤ሰፊሆ ክነፊሁ ይጸልል ዲቤነ።

@EotcLibilery

ወረብ፦
ውእቱ ሚካኤል መልአከ ኃይል ልዑል ውእቱ ልዑለ መንበር/፪/
ይስአል ለነ አመ ምንዳቤነ ይስአል ሰፊሆ ክነፊሁ/፪/


መልክአ ሚካኤል
ሰላም ለልሳንከ በነቢበ ጽርፈት ዘኢተኃበለ፤በእንተ ሥጋሁ ለሙሴ አመ ምስለ ሰይጣን ተበኃለ፤ሚካኤል ክብርከ እምክብረ መላእክት ተልዕለ፤ቀዊምየ ቅድመ ስዕልከ ሶበ አወትር ስዒለ፤በብሂለ ኦሆ ፍጡነ አስምዓኒ ቃለ።

ወረብ
ቀዊምየ ቅድመ ስዕልከ ሶበ አወትር ስዒለ/፪/
"በብሂለ ኦሆ"/፪/ ፍጡነ አስምዓኒ ቃለ/፪/

ዚቅ
ረሰዮ እግዚኡ ለውእቱ ሚካኤል፤እምኲሎሙ መላእክት ይትለዓል መንበሩ፤ስዩም በኀበ እግዚኡ ምእመን።


ወረብ
እግዚኡ ረሰዮ ለውእቱ ሚካኤል/፪/
እምኲሎሙ መላእክት መላእክት ይትለዓል መንበሩ/፪/

መልክአ ሚካኤል
ሰላም ለሕንብርትከ ሕንብርተ መንፈስ ረቂቅ፤ዘቱሣሔሁ መብረቅ፤ነግሀ ነግህ አንተ በአዝንሞ መና ምውቅ፤በገዳም ዘሴሰይኮሙ ለነገደ ኅሬ ደቂቅ፤ሴስየኒ ሚካኤል ሕገከ በጽድቅ።


ወረብ
"በገዳም"/፫/ ዘሴሰይኮሙ/፪/
ለነገደ ለነገደ ኅሬ ደቂቅ/፪/


ዚቅ
ባሕረ ግርምተ ገብረ ዓረፍተ፤ወበውስቴታ አርዓየ ፍኖተ፤በእደ መልአኩ አቀቦሙ በገዳም ለሕዝቡ አርብዓ ዓመተ፤ወሴሰዮሙ መና ኅብስተ፤ኪነ ጥበቡ ዘአልቦ መስፈርተ።


ወረብ
በእደ መልአኩ አቀቦሙ መልአክ ለ፳ኤል/፪/
ወሴሰዮሙ መና በገዳም በገዳም አርብዓ ዓመተ/፪/

ወረብ
ባሕረ ግርምተ ዓረፍተ ገብረ አርአየ ፍኖተ እግዚአብሔር/፪/
በእደ መልአኩ አቀቦሙ ለ፳ኤል አርብዓ ዓመተ ለሕዝቡ በገዳም/፪/


መልክአ ሚካኤል
አምኃ ሰላም አቅረብኩ ለመልክእከ ኲሉ፤ለለ፩ዱ ፩ዱ ዘበበክፍሉ፤ሚካኤል ክቡር ለልዑል መልአከ ኃይሉ፤ተወኪፈከ አምኃየ እምኑኀ ሰማያት ዘላዕሉ፤ዕሴተ ጸሎትየ ፈኑ ወአስብየ ድሉ።

ዚቅ
ተወከፍ ጸሎተነ ውስተ ኑኃ ሰማይ፤ወስዕለተነ ከመ መዓዛ ሠናይ፤ተወከፍ ጸሎተነ ውስተ ኑኃ ሰማይ።


ወረብ
ተወከፍ "ጸሎተነ ውስተ ኑኃ ሰማይ"/፪//፪/
ወስእለተነ ከመ መዓዛ ሠናይ ሊቀ መላእክት/፪/


አንገርጋሪ
ውእቱ ሚካኤል መልአከ ኃይል፤ልዑል ውእቱ ልዑለ መንበር፤ይስአል ለነ፤ረዳኤ ይኲነነ አመ ምንዳቤነ፤ሰፊሆ ክነፊሁ ይጸልል ዲቤነ።


ምልጣን
ይስአል ለነ፤ረዳኤ ይኲነነ አመ ምንዳቤነ፤ሰፊሆ ክነፊሁ ይጸልል ዲቤነ።


አመላለስ፦
ሰፊሆ ክነፊሁ/፪/
ክነፊሁ ይጸልል ዲቤነ/፬/


ወረብ ዘአንገርጋሪ
ውእቱ ሚካኤል መልአከ ኃይል ልዑል ውእቱ ልዑለ መንበር/፪/
ይስአል ለነ ረዳኤ ይኲነነ ይስአል አመ ምንዳቤነ/፪/


እስመ ለዓለም
ሚካኤል እመላእክት መኑ ከማከ ልዑል፤አስተምሕር ለነ ሰአልናከ፤በ፲ቱ ወ፵ቱ ትንብልናከ፤ሚካኤል እመላእክት መኑ ከማከ ልዑል፤ዓይኑ ዘርግብ፤ልብሱ ዘመብረቅ ሐመልማለ ወርቅ፤ሚካኤል እመላእክት መኑ ከማከ ልዑል፤ይሰግድ በብረኪሁ፤እስከ ይመጽእ ሥርየት ለኃጥአን፤ሚካኤል እመላእክት መኑ ከማከ ልዑል፤መኑ ከማከ ክቡር።

ወረብ ዘእስመ ለዓለም ፩
ሚካኤል መልአክ እመላእክት መኑ ከማከ ልዑል/፪/
አስተምሕር ለነ ሰአልናከ በ፲ቱ ወ፵ቱ ትንብልናከ/፪/

@EotcLibilery

ወረብ ዘእስመ ለዓለም ፪
ሚካኤል እመላእክት መኑ ከማከ ልዑል/፪/
ሐመልማለ ወርቅ ልብሱ ዘመብረቅ ዓይኑ ዘርግብ ሊቀ መላእክት/፪/


ወረብ ዘእስመ ለዓለም ፫
ሚካኤል እመላእክት መኑ ከማከ ልዑል/፪/
ይሰግድ በብረኪሁ እስከ ይመጽእ ሥርየት ለኃጥአን/፪/

እመሒ ስሕተኩ አንትሙ እለ በመንፈስ አርትዕ(የተሳሳትኩት ቢኖር እናንተ በመንፈስ ያላችሁ አቃኑት)🙏🙏🙏
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
 
በሕይወት ውስጥ መጀመሪያ ከፊት የሚመጡት ሰዎች "ሔዋንህ" ወይም "አዳምሽ" ላይሆኑ ይችላሉ። ልክ አዳም ከተፈጠረ በኋላ መጀመሪያ በእርሱ ፊት እንስሳትን እንዳገኘ እና ለእነርሱም የሚገባቸውን ስም እየሰጠ እንዳሰናበታቸው፣ አንተም አንዳንዴ በኑሮህ ቀድመህ የምታገኛቸው አካላት "ጎረቤት፣ የሥራ ባልደረባ፣ ጓደኛ" እያልክ ስም የምታወጣላቸው ብቻ ይሆናሉ። ለምን? "እንደ አንተ ያሉ (የሚመቹ) ረዳቶች" አይደሉማ። አዳም ለእንስሳት፣ ለሰማይ ወፎችና ለምድር አራዊት ሁሉ ስም ካወጣላቸው በኋላ መጽሐፉ "ለአዳም እንደ እርሱ ያለ ረዳት አልተገኘለትም ነበር" ይላል።(ዘፍ 2፥20)

አዳም እንደ እርሱ ያለ ረዳት ከእንስሳቱ መካከል ፈልጎ በማጣቱ "በቃ የምን መኩራት ነው? ያሉት እነዚህ ስለሆኑ እኔን ባትመስል እንኳ ትንሽ ለእኔ የቀረበችውን ብመርጥ ይሻላል" አላለም። ከሌሎች ይልቅ በአካላዊ ቁመና ለእርሱ የምትቀርበውን ትልቅ ጦጣ (Chimpanzee) መርጦም ወደ ፈጣሪው በመውሰድ "እባክህ ጌታዬ፣ ለአንተ የሚሳንህ የለምና ትንሽ ጸጉሯን ብትቀንስ፣ ጅሯቷን ብታጠፋ እና ፊቷ አካባቢ ማስተካከያ ብታደርግላት እንደ እኔ ያለ ረዳት ትሆናለች" ብሎ ሲማጸን አናገኝም። ይህን ቢያደርግ ኖሮ አሁን የአዳምን ታሪክ የምናነብ ሰዎች ሁሉ በችኮላው እየተገረምን እንስቅበት ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔር ከጥቂት ቀን በኋላ አጥንቷ ከአጥንቱ፣ ሥጋዋ ከሥጋው የተፈጠረ ሔዋን የተባለች እጅግ ውብ ሚስት እንደሰጠው ስለምናውቅ።

ከአንተ ጋር በሃይማኖት፣ በአመለካከትና ይህን በመሳሰሉት ነገሮች ጨርሳ ልትገጥም የማትችል የማትመችህን ረዳት "ለአንተ ምን ይሳንሃል? አስተካክልልኝ" እያልክ ለምን ትታገላለህ። በፍጹም ስለማይሆንሽ ሰው ለምን የmodification ጥያቄ ታቀርቢያለሽ? ጥቂት ጊዜ ከታገስህ እግዚአብሔር ለአንተ የምትመችህን (compatible) ረዳት ያመጣልሃል። አሁን ግን ፊት ለፊት ያገኘሃት ጥሩ የሥራ ባልደረባ ወይም ጓደኛ እንጂ የምትመች ረዳትህ አይደለችም።

በሕይወት ውስጥ ቀድሞ የመጣ ሁሉ ባል ወይም ሚስት አይሆንም። መጽሐፍ ቅዱስም "ቢቻላችሁስ... ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ" ይላል እንጂ "ከሁሉ ጋር ተጋቡ" አላለንም።(ሮሜ 12፥18)

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
“ፆም የፀሎት ምክንያት ናት፤ የፀጋ ዕንብ መገኛ ናት አርምሞን የምታስተምር ናት፤ ለበጎ ስራ ሁሉ ታነቃቃለች፤ የፀዋሚ ስጋው ምንጣፉን አንጥፎ ሌሊቱን ሁሉ ተኝቶ ማደር አይቻለውም በምን ጎኑ ይተኛዋል? ሰው አብዝቶ በፆመ ያህል በዚህ መጠን በትህትና ሁኖ እያለቀሰ ይፀልያል፤ ፀሎታት ከልቡናው ይታሰባሉ አንድም ፀሎተ ልብ ይሰጠዋል፤ በፊቱ የትእግስት ምልክት ይታያል በሃጢአቱ ያዝናል ክፉ ህሊና ይርቅለታል የበጎ ነገር መገኛ መከማቻ በምትሆን በፆም ይኖራልና፤ ፆምን የናቀ ያቃለለ ሰው በጎውን ነገር ሁሉ ከራሱ አራቀ፡፡”

ማር ይስሃቅ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
ጾም ሙሽሪትን ትመስላለች፤ ሙሽሪትን በሠርግ አዳራሽ ኾነው የሚቀበሏት ሰዎች ቤቱን ያስጌጡታል፤ ይሸልሙታል፡፡ ወደ ሠርጉ አዳራሽ የሚገባውን ሰው የሠርግ ልብስ ለብሶ እንደኾነ፣ የቆሸሸ እንዳልኾነ አይተው ያስገቡታል፡፡ እኛም እንዲኽ ልንኾን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ልቡናችንን በማንጻት፣ ልል ዘሊል ከመኾን በመራቅ፣ የክፋት እርሾን በማስወገድ፣ ከጾም ጋር አብረው የሚመጡትን የሚያጅቧትን መልካም ምግባራትንም ለመቀበል የልቡናችንን ውሳጤ በመክፈት የምግባር እናት፣ የማስተዋል እንዲኹሉም ለሌሎች ምግባራት ኹሉ ንግሥት የምትኾን ጾምን ልንቀበላት ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ይኽን ያደረግን እንደኾነ ታላቅ ሐሴት እናደርጋለን፤ ርሷም ቁስለ ነፍሳችንን ትፈውስልናለች፡፡

በሌላ አገላለጽ ብነግራችኹ ሐኪሞች በአንድ ታማሚ ሰውነት ውስጥ ያለውን ቆሻሻ፣ መርዘኛ ፈሳሽን ማስገድ ሲፈልጉ መጀመሪያ የሚያደርጉት ነገር ቢኖር ታማሚው ምግብ ከመውሰድ እንዲቈጠብ ነው፡፡ ታማሚው ለጊዜው ምግብን ከመብላት ካልተከለከለ ሓኪሞቹ የሚሰጡት መድኃኒት እንደተፈለገው ውጤት አይሰጥም፡፡

እኛም ቁስለ ነፍስ ቁስለ ሥጋ የምትፈውሰውን ጾም ስንቀበላት ከዚኽ በላይ ልንኾን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ድኅነተ ሥጋ ድኅነተ ነፍስን የምንሻ ከኾነ ልቡናችንን ንጹሕና ንቁ በማድረግ ልንወስዳት ይገባናል፡፡ እንዲኽ ካልኾነ ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ያመዝናል፡፡

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
Audio
በእግዚአብሔር ዘንድ የተከበሩ 3 ነገሮች 
                                                  
Size:- 26.5MB
Length:-1:53:25
       
     በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
“እግዚአብሔር ባይፈቅድ ነው”

| ጃንደረባው ሚድያ | ኅዳር 2016 ዓ.ም.|

✍🏽 ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ እንደጻፉት

ካለፉት ቀናት መካከል አንደኛው ቀን የትምህርት ቤት ወንድሜን ለመጠየቅ የሄድሁበት ቀን ነበር። ከተገናኘን ብዙ ቀን ሆኖን ስለነበር ለእግርህ ውኃ ላሙቅልህ፣ ምግብ ይቅረብልህ አላለኝም። እንዲሁ ያለፈውን ዘመናችንን በዛሬ ዐይናችን እያየን በዛሬ ሚዛን እየመዘንን በሚያስቀው ስንስቅ በሚያስጸጽተው ስንጸጸት ቆይተን ለእንግድነቴ የሚገባው ግብዣ ከተደረገልኝ በኋላ ዛሬአችንን ወደ መገምገም ተመለስን።

የቆሎ ተማሪ አፈር ላይ ተኝቶ ይማራል እንጅ “አፈር ፈጭተን ውኃ ተራጭተን” ይሉት ጨዋታ አያውቅምና ያ አፈር ላይ ተኝቶ አብሮኝ ይማር የነበረው ጓደኛዬ ዛሬ የአንድ ድርጅት ባለቤት ሆኗል። የሚኖሩበት ቤት ፀሐይ ሳትወጣ ብትዘገይ የሚያሞቅ፣ የተመኙትን ነፋስ የሚያነፍስ መሣሪያ የተገጠመለት ዘመናዊ ድንኳን ነው። በመጨረሻ የጠየቅሁት ጥያቄና የመለሰልኝ መልስ ነው ዛሬ ለምጽፍላችሁ ደብዳቤ መነሻ የሆነኝ። “ዜማ ቤት እያለን ማኅሌት በጣም ትወድ እንደነበር አውቃለሁ እንዲያውም ትዝ ካለህ ከማኅሌት ስትመለስ የመጀመሪያ ሥራህ የነበረው ተኝተው ያደሩ ተማሪዎች ላይ ውኃ መድፋት ነበር ዛሬስ እንዴት ነህ?” አልሁት ትንሽ እንደማፈር ሲል አየሁት።

ትንሽ እንደማሰብ አደረገና “እኔማ አገልግሎት ምን ያኽል እንደምወድ አንተም ታውቃለህ ነገር ግን የምወደውን አገልግሎት ሰዎች አስጠሉኝና ተውሁት። ለጥቂት ቀናት እንዳልሄድ አለመፈለጋቸውን እያወቅሁ ተጋፍቸ ሄድሁ፤ አንድ ቀን መኪናዬን ያልተገባ ነገር አደረጉብኝ ሌላም ልነግርህ የማልፈልገውን አደረጉብኝ፤ ሲሰለቸኝ መቼስ ሰው ይደለሁ? በቃ ማገልገሌን እግዚአብሔር ባይፈቅድልኝ ነው ብየ እርግፍ አድርጌ ተውሁት ይሄው አራት ዓመቴ ማኅሌቱን ከተውሁት አለኝ”።

እንዲህ አይነት መወሰኛ ቃል እየተጠቀምን ነገሮችን ሁሉ በጅምር የምናስቀር ብዙ ሰዎች መኖራችንን ባሰብሁ ጊዜ እንድጽፍ ተገደድሁ። ብዙ ሰዎች ብትጠይቋቸው ያላገቡት እግዚአብሔር ስላልፈቀደ ነው። ያልቆረቡት እግዚአብሔር ስላልፈቀደ ነው። ሥራቸው ስኬት ያላመጣላቸው እግዚአብሔር ስላልፈቀደ ነው። የጀመሩትን ነገር ሁሉ ያልጨረሱት እግዚአብሔር ስላልፈቀደ ነው። ሩቅ አስበው ከቅርብ የተመለሱት እግዚአብሔር ስላልፈቀደ ነው። እንዲህ እያሉ ይቀጥላሉ። ሁሉንም ነገር እግዚአብሔር ስላልፈቀደ ብለው ነው የሚተዉት።

ለአንዳንዶቹ የሚመስላቸው እግዚአብሔር ከፈቀደ ያለምንም ትግል ነገሮች ሁሉ የሚከናወኑ ይመስላቸዋል። እግዚአብሔር ከፈቀደ ነገሮች ሁሉ “ለይኩን” በሚል ትዕዛዝ እንዲፈጸሙላቸው ይፈልጋሉ። እግዚአብሔር የፈቀደልንን ሕይወት ለመኖር ሲባል እኮ ነው ይሄ ሁሉ ተጋድሎ፤ የሰማዕታት ተጋድሏቸው፣ የጻድቃን ምናኔአቸ፣ የደናግል የመነኮሳት ትዕግሥታቸው፣ የሰብአ ዓለም ሕግ መጠበቃቸው፣ የካህናት ትጋታቸው የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማስቀየር የሚደረግ ይመስላችኋል? ይሄ ሁሉ ሩጫ እግዚአብሔር የፈቀደልንን ሕይወት እንዳናጣ ለመሆን ነው።

ሐዋርያትን “ሑሩ ወመሀሩ” ብሎ ያዘዘ ማነው? ቅዱስ ጳውሎስን “ንዋየ ኅሩየ ረሰይኩከ” ብሎ ያከበረ ማነው? ኃጥአንን ለንስሐ የጠራ ማነው? ነገር ግን በፈቀደላቸው መንገድ ሲጓዙ የሚገጥማቸውን ተጋድሎ ተመልከቱ። ዓለም ሳይፈጠር ጀምሮ መንግሥተ ሰማያት ለሰው የተዘጋጀች ስጦታ ናት ቢሆንም ዓለም ሳይፈጠር የተዘጋጀልንን ስጦታ ዓለምን ካላሸነፍን አናገኘውም ማቴ 25፥34፣ 1ዮሐ 5፥5
የእስራኤል ከግብጽ መውጣት ከእግዚአብሔር ዘንድ የተቆረጠ ነገር ነበር። “በግብፅ ያለውን የሕዝቤን መከራ በእውነት አየሁ፥ ከአስገባሪዎቻቸውም የተነሣ ጩኸታቸውን ሰማሁ፤ ስቃያቸውንም አውቄአለሁ፤ ከግብፃውያንም እጅ አድናቸው ዘንድ፥ ከዚያችም አገር ወተትና ማር ወደምታፈሰው ወደ መልካሚቱና ወደ ሰፊይቱ አገር ወደ ከነአናውያንም ወደ ኬጢያውያንም ወደ አሞራውያንም ወደ ፌርዜወናውያንም ወደ ኤዊያውያንም ወደ ኢያቡሳውያንም ስፍራ አወጣቸው ዘንድ ወረድሁ” ዘፀ 3፥7 ብሎ መውጣታቸው ፈቃዱ መሆኑን ገልጿል።

ዳሩ ግን እስራኤል የእግዚአብሔር ፈቃድ ስለሆነ ያለምንም ሰልፍ ግብጽን ለቀው መውጣት አልቻሉም። እግዚአብሔር ለእስራኤል መውጣትን እንደፈቀደ ሁሉ የፈርዖንን ልብ እንደሚያጸናም “እኔም የፈርዖንን ልብ አጸናለሁ” ዘጸ 4፥21። ብሏል። ምን አይነት ነገር ነው? በአንድ በኩል ፈቅጃለሁ እስራኤል ይውጡ ይላል በሌላ በኩል የፈርዖንን ልብ አጸናለሁ ይላል።

ተመልከተው! የእግዚአብሔር ፈቃድ ታግለህ እንድታሸንፍ ነው እንጅ ለይኩን ተብሎ በቃል በተፈጠረ ዓለም ውስጥ በቃል እንደማዘዝ ቀላል በሆነ መንገድ እንድትጓዝ አይደለም። እግዚአብሔር ከፈቀደልህም በኋላ አስማተኞች ይፈታተኑሃል፤ ፈርዖን ፍርድ ያጠብቅብሃል፤ አስገባሪዎች ግብር ይጭኑብሃል፤ አንዳንዴም ለጸሎት ለዝማሬ ወደ ቤተ እግዚአብሔር ስታቀና ባዩ ጊዜ እንደ ሥራ ፈት ይቆጥሩህና ለማሰናከያ የሚሆን ሽልማት ያለው ሥራ ለምስጋና በተመደበው ጊዜ ያዘጋጁልሃል። እና አንዳንዴ እንዲያውም በቃ የጀመርሁት ጸሎት፣ ሱባኤ፣ ቅዳሴ፣ ቁርባን፣ ኪዳን የበለጠ ፈተናዬን ስላበዛብኝ ከሰይጣን ጋር እልህ ከምጋባ አርፌ ብቀመጥ ይሻለኛል እንድትል ያደርግሃል። እስራኤልም ያሉት እንዲሁ ነበር “በፈርዖንና በሠራዊቱ ፊት ሽታችንን አግምታችኋል፥ ይገድሉንም ዘንድ ሰይፍ በእጃቸው ሰጥታችኋልና እግዚአብሔር ይመልከታችሁ ይፍረድባችሁም” ዘጸ 5፤21 ብለው ሊያድኗቸው ከተላኩ አገልጋዮቻቸው ጋር መጣላት ጀመሩ። የተፈቀደልህ ቦታ እስከምትደርስ ድረስ ላንተ ነጻ መውጣት ከተላኩ ካህናት መነኮሳት ጋር ሳይቀር የሚያጋጭ ፈተና ያጋጥምሃል።

በአንድ በኩል እግዚአብሔር የላካቸው ሰዎች “እኔ እግዚአብሔር ነኝ ከባርነት ነጻ አወጣችኋለሁ፤ ከተገዥነትም አድናችኋለሁ በተዘረጋ ክንድ በታላቅ ፍርድም እታደጋችኋለሁ ለእኔም ሕዝብ እንድትሆኑ እቀበላችኋለሁ” ዘጸ 6፥6 ብሏል ብለው ይነግሩናል። ግን እግዚአብሔር በሕይወታችን ውስጥ ወዴት አለ? በሥራችን የረዳን፣ መከራችን ያቀለልን፣ ባርነታችንን ያስቀረልን መቼ ነው? እንላለን አይደል? አወ ይቀላል ስንል መከራው እየበዛ ሲሄድ፤ በምንረግጠው ጭቃ ውስጥ የልጆቻችን ደም ተቀላቅሎ ስናይ፤ በከተማው የሚሰማ የገራፊዎች ጅራፍ ድምጽ ብቻ ሲሆን፤ እስራኤል በደሙ ጭቃ አቡክቶ በሚገነባው ፒራሚድ ግብጻዊ ሲያጌጥበት ስናይ ከዚህ ሌላ ስሜት ሊኖረን እንደማይችል ይታወቃል።

ነገር ግን እውነቱን ከመጽሐፍ ቅዱስ ተረዱት። እግዚአብሔር “ኃይሌን ባንተ አሳይ ዘንድ ስሜም በምድር ሁሉ ይነገር ዘንድ ለዚህ አሰነሣሁህ” ሮሜ 9፥17 ብሎ የኃይ መገለጫ አድርጎታል። እኛ በፈርዖን ላይ የሚገለጠውን ኃይሉን እንጠባበቃለን እንጅ እግዚአብሔር እኛን ለማዳን አልፈቀደም ብለን አናንጎራጉርም።

የጌታ ፈቃድ እስኪሆን እስኪደረግ ድረስ በብርቱ ትግል ውስጥ እናልፋለን። ከዚህ አስጨናቂ ሕይወት መውጣታችንን ቢወድም ኃይሉን በጠላቶቻችን ላይ እንዲያሳይ የኛ ትዕግሥት ያስፈልጋል። የእግዚአብሔርን ማዳን ገና በሰፊው ስትደረግልን በሕይወታችን ውስጥ እናያለን። ከተፈቀደልን ሕይወት የምንደርሰው በትዕግሥት ነው።

ከማንጎራጎር ወጥተን በእኛ ላይ የወደደውን ለማድረግ ሥልጣን ያለውን ጌታ የሚያደርገውን ሁሉ በማስተዋል መመልከት ነው። ሸክላ ሠሪ የወደደውን ሊሠራበት በእጁ ያለውን ጭቃ ሥልጣን የለውምን? እግዚአብሒርም በእኛ ላይ የወደደውን የሚያደርግበት ሥልጣን አለው።
በትግል የምትኖሩ ሁሉ እግዚአብሔር በትግል ውስጥ ለምን እንዳኖራችሁ ትግላችሁ ውስጥ እግዚአብሔር እየሠራ ያለውን መልካም ነገር መርምሩና ድረሱበት። ምናልባትም በእናንተ ትግል ውስጥ ፈታኞቻችሁን እየቀጣላችሁ ይሆናል። የእስራኤል መቆየት ለግብጽ ቅጣት ነበር እንጅ ጥቅም አልነበረም።

ግብጽ በውኃ ፋንታ ደም የቀዳችው፣ ምድሯ በቅማልና በጓጉንቸር የተሞላው፣ ለሦስት ቀናት ብርሃን ከማየት የተከለከለችው፣ ከንጉሡ ቤት ጀምሮ በሁሉም ግብጻውያን ቤት ውስጥ በማለዳ ሬሳ የተገኘው በእስራኤል መቆየት ነው። እስራኤልን መልቀቅ ጥቅሙ ለእስራኤል ብቻ ሳይሆን ለግብጻውያንም ነበር። ፈርዖን ግን ይህንን አላወቀም።

ሰላም የነሡን ሰዎች ሰላም ቢሰጡን ዕዳ ቆልለው የሚያስጨንቁን ሰዎች ባያስጨንቁን ዕረፍቱ ለሁላችንም ከእግዚአብሑእር ዘንድ ይሆንልን ነበር ግን አስገባሪዎቻችን ይህ አይገባቸውም። እኛማ እግዚአብሔር የፈቀደው ቀን ሲደርስ ከዚህ መውጣታችን አይቀርም። ምክንያቱም በትግል ውስጥ እንድናልፍ ፈቃዱ ቢሆንም በዚያው ውስጥ ሳለን እጃችንን ለሞት እንደንሰጥ ግን አያደርገንም።

ዳዊት ከተቀባ በኋላ በሳዖል መሳደዱ ዱር ለዱር መንከራተቱ አያስደንቅም? በእግዚአብሔር ፈቃድ ለንጉሥነት የተመረጠው ዳዊት ከዕለታት አንድ ቀን የሚበላው አጥቶ ያልተፈቀደለትን እንጀራ እስከ መብላት ደርሷል። ይህ ሁሉ መሆኑ የዳዊት መንግሥት የጌታ ፈቃድ ባይሆን ነውን? አይደለም! ጨለማውም የሚመጣው በጌታ ፈቃድ ነው። ብርሃንም የሚሆነው በጌታ ፈቃድ ነው። “ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉም” ዮሐ 15፥5 ማለቱን አስተውሉ!

ማስታወሻ:- ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ የአራቱ ጉባኤያት መምህርና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የሊቃውንት ጉባኤ ሰብሳቢ ሲሆን የመጻሕፍት ደራሲም ናቸው:: ሊቅ ሊቃውንት የጃንደረባው ሚዲያ ዐምደኛ ሲሆኑ ጽሑፎቻቸው ዘወትር ሰኞ የሚነበቡ ይሆናል::
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
2024/09/28 05:25:43
Back to Top
HTML Embed Code: