Telegram Web Link
#ቤተሰብና_ምጽዋት

ኦርቶዶክሳውያን ባልና ሚስት ለጸሎት የሚኾን ቤት ከማዘጋጀት በተጨማሪ፥ ምጽዋት ከመስጠት አንጻርም ሊበረቱ ይገባቸዋል፡፡ ቢቻል ቢቻል ድኾችን በየጊዜው የሚመግቡባት አንዲት ቤት ብትኖራቸው መልካም ነው፡፡ ይህቺን ቤትም “የክርስቶስ በዓት” ብለው ሊሰይሟት ይችላሉ፡፡ ምክንያቱም በድኾቹ አድሮ በዚያች ቤት ውስጥ መጥቶ የሚመገበው ራሱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና፡፡ ከዚሁ በተጨማሪ በቤተ ክርስቲያን ሙዳየ ምጽዋት ሳጥን እንዳለች ኹሉ ክርስቲያኖችም በየቀኑ ምጽዋት የሚያስቀምጡባትና አጠራቅመውም ድኾችን የሚረዱባት ትንሽ “ሙዳየ ምጽዋት” ማዘጋጀት ይገባቸዋል፡፡ ምጽዋት ባለበት ዲያብሎስ የለምና፡፡ በየቀኑ ጸሎት ከመጀመራቸው በፊትም በሙዳየ ምጽዋቷ ውስጥ የዓቅማቸውን ምጽዋት በማስቀመጥ መጀመር አለባቸው፡፡   

ከድኾች በተጨማሪ የኦርቶዶክሳውያን ባልና ሚስት ቤት ዘወትር ለመነኰሳት ክፍት መኾን አለበት፡፡ ቅዱሳኑ ምድራውያን መላእክት ወደዚያ ቤት ሲገቡ፥ እኩያት አጋንንትም በአንጻሩ እንደ ጢስ ተነው እንደ ትቢያ በነው ይጠፋሉና፡፡

(ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው፣ ገጽ 63-64 ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
"እውነተኛ ሐሴት ትፈልጋላችሁን? እንግዲያውስ ለድሆች መጽውቱ፤ ክርስቶስን ወደ ቤታችሁ ጥሩት፡፡ ይህን ስታደርጉ ማዕዱ ቢነሣም ሐሴቱ አይነሣም፤ ይቀጥላል እንጂ፡፡ በተለይ ደግሞ በዚህ በወርሐ ጦም ይህን አብዝታችሁ አድርጉት።"

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
#አትርሳ!

አንድ ሰው ወደ ቤተ መንግሥት አንዲት ሴተኛ አዳሪን ይዞ መጥቶ በንጉሡ ፊትም ሩካቤ ቢፈጽም፣ ወይም ቢሰክር፣ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ ተግባር ቢፈጽም የቅጣት ቅጣት ይደርስበታል፡፡

አሁን ራሳችንን ጥያቄ እንጠይቅ፡፡ እግዚአብሔር የሰማይም የምድርን ንጉሥ ነው ወይስ አይደለም? ነው! የምናደርገውን ማንኛውም ድርጊት ይመለከታል ወይስ አይመለከትም? ኧረ ይመለከታል!
ታዲያ በምድራዊ ንጉሥ ፊት ከላይ የጠቀስናቸውን ነውሮች ደፍሮ የፈጸመ ሰው ጽኑ ቅጣት የሚቀጣ ከኾነ እንደዚህ ያሉ ተግባራትን በእግዚአብሔር ፊት ለማከናወን የምንደፍረው ለምንድን ነው? ምድራዊው ንጉሥ ቢቀጣ ምድራዊ ቅጣትን ነው፡፡ ሰማያዊው ንጉሥ ሲቀጣ ግን ሰማያዊ ቅጣት እንደ ኾነ አናውቅምን? ...

ሰው ሆይ! እያንዳንዷን ድርጊትህ የሚመለከት የሰማይም የምድርም ንጉሥ እንዳለ በፍጹም አትርሳ፡፡

(#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ- አምስቱ የንስሐ መንገዶች እና ሌሎች - ገጽ 119)
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
"እጅግ የምወዳችሁ ምእመናን ሆይ የጾም ጥቅሟ ምን ያህል የበዛ እንደሆነ ነፍሳችን ከዚህ ብዙ ጥቅምን እንደምታገኝ ከጌታችንና እና ከአገልጋዮቹ ተምረናል፡፡ ስለሆነም የጾም ወራት ሲቃረብ ግድ የለሽነትንና ሞራለ ቢስነትን ከእኛ አስወግደን ንዑድ ክቡር የሚሆን ጻውሎስ፡- የውጭው ሰውነታችን ይበልጥ ሲጠፋ የውስጡ ሰውነታችን ይበልጥ ይታደሳል’’ ብሎ እንዳስተማረን እጅግ ደስ ተሰኝተን ልንቀበለው ይገባናል ብዬ እማልዳችኃለሁ፡፡ /2ኛ ቆሮ 4፡16/

ጾም የነፍስ ምግብ ሥጋ ሰውነታችን እንዲወፍር እንደሚያደርግ ሁሉ ጾምም ነፍስን ያበረታል ፈጣንና መንፈሳዊ ክንፍን ይሰጣል፤ ወደ ሰማያዊ ምስጢር ገብታ በፅሞና እንድትያዝ ያደርጋታል የዚህን ዓለም  ተድላና ደስታ እንድትንቅ ያስችላታል፡፡

ቀላል ጭነትን የተሸከሙ መርከቦች ፈጥነው ባህሩን እንደሚሻገሩ እጅግ ብዙ ጭነትን የተሸከሙት ግን ባህሩንና ወጀቡን ቶሎ ማለፍ እንደሚያቅታቸው ሁሉ ልክ እንደዚሁ ጾምም ውስጣዊ ምስጢር እንድንገባ በዚያም ስላሉ አይነገሬ በረከቶችን እንድናስብ በዚህ ዓለም ላይ ያሉት ሁሉም ነገሮች እንደ ጠዋት ጤዛ ፈጥነው የሚያልፉ እንደሆኑ እንድንገነዘብ ታደርጋለች፡፡

ከዚሁ በተቃራኒ አብዝቶ መብላትና ራስን አለመግዛት ደግሞ አእምሯችን የጠፋ ሥጋችን የወፈረ ውስጣችን በእግረ ብረት የተጠፈረ በዚህ ሁሉ ተከበን እጅግ በከፉ ምግባራት የተያዝን የዘለዓለማዊ ሕይወታችን ጠላቶች ሆነን እንድንጓዝ ያደርጉናል፡፡

ስለዚህ ተወዳጆች ሆይ! መብልንና ራስን አለመግዛት ተከትለው የሚመጡትን ኃጣውእ በማወቅ ከድኅነታችን ጋር  በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ቸልተኞች አንሁን፡፡"

( ኦሪት ዘፍጥረት - በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
___ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፮___
አንቀጽ ፮ ስለ ቀሳውስት ይናገራል።
፩) ቅስና ነውር ነቀፋ የሌለበት አንዲት ሴት ያገባ ሰው ይሾም። ቂመኛ አይሁን። አብዝቶ የሚጠጣ አይሁን። እንግዳ መቀበልን የሚወድ ይሁን። ደግ ሰው፣ ቸር ይሁን።
_
፪) ነገረ ሃይማኖትን የሚያስተምር ይሁን። እውነተኛ ትምህርትን በማስተማር ሰውን ማረጋጋት የሚችል ይሁን። ምን የበቃ ቢሆን ቄስ ፴ ዓመት ሳይሞላው አይሾም። የመጻሕፍትን ነገር የማያውቅ ቅስና አይሾም። ይልቁንም አራቱን ወንጌል ያልተረጎመ አይሾም።
_
፫) አምስት ሰዎች ያልመሰከሩለት ቅስና አይሾም። ቄስ በኤጲስ ቆጶሱ በአንብሮተ እድ ይሾማል። ቀሳውስት ቁመው ይጸልዩለት። ቄስ መምህር እንደመሆኑ ያስተምር።
_
፬) የቄስ ሥልጣን ማስተማር፣ ማጥመቅ፣ ቀድሶ ማቁረብ እና ሕዝቡን መባረክ ነው። ቄስ ማንንም አይሹም። ቀሳውስት በመንበሩ ዙሪያ ከኤጲስ ቆጶስ ፊት ሊሄዱ አይገባም።
_
፭) ቄስ ሁለት እህትማማች ካገባ ሰው ሠርግ አይሂድ። ይህን ያደረገ ሰው ንስሓ የሚገባው ነውና። ቄስ ከሐዋርያት የወጣ ሥርዓት በሕዝቡ ምንም ምን አያጽናባቸው።
_
፮) የሚታከም ቢሆን ነው እንጂ ቄስ በማንም በማን ፊት አይራቆት። ቀሳውስት ከኤጶስ ቆጶሳቸው በዓመት ሦስት ጊዜ ይሰብሰቡ።
_
፯) በጉቦ፣ በማስፈራራት፣ በማድላት፣ በተንኮል የተሾመ ቄስ ይሻር። ሁለት ሴት ያገባ ቄስ ይሻር። ሕዝቡን ከማስተማር ቸል የሚል ቄስ ይሻር።
_
፰) ሐሰት በመመስከር ሰውንም በማጣላት የታወቀ፣ የሚታበይ፣ ሥርዓትን አውቆ የማይሠራት፣ ዘወትር የሚሰክር፣ አራጣ የሚቀበል፣ ከሴሰኛ ሴት የደረሰ፣ በጠንቋዮች ነገር የሚያምን፣ ኮከብ በመቁጠር የሚታመን፣ ሥር የሚምሱትን ቅጠል የሚበጥሱትን ነገር የሚያምን፣ ከከሓድያን የተጠመቀ ቁርባናቸውን የተቀበለ፣ አብሯቸው የሚጸልይ ከክህነቱ ይሻር።
_
፱) አባለዘሩን የሰለበ፣ ሲሰርቅና በሐሰት ሲምል የተገኘ፣ የጋብቻ ሥርዓትና ሥጋ መብላት እንዲሁም ወይን መጠጣት አይገባም የሚል፣ በገበያ መካከል የሚበላ፣ ከመሸታ ቤት ገብቶ የሚጠጣ፣ ሙቶ የተገኘውን የአውሬ ትራፊ የሆነውን የሚበላ፣ ከደዌ ለመዳን ከዓላውያን ቤተክርስቲያን የገባ፣ የአይሁድን ጾም የሚጾም በዓላቸውን የሚያከብር፣ ወደ ዓላውያን ቤተክርስቲያን እጅ መንሻ የሚወስድ፣ ተወግዞ ከተለየው ጋር የተነጋገረ አብሮት የሚጸልይ፣ የኤጲስ ቆጶሱን ደብዳቤ ሳይዝ ሩቅ ሀገር የሚሄድ ከክህነቱ ይሻር።
_
፲) አገለግላለሁ ብሎ ወይም እመነኩሳለሁ በማለት ሚስቱን የፈታ ቄስ ይሻር። በታወቀ ምክንያት የተሻረ ቄስ ወይም ዲያቆን ቢኖርና ከተሻረ በኋላ የክህነት ሥራ ቢሠራ ከምዕመናን ፈጽሞ ይለይ። መሻሩን እያወቀ ከእርሱ ጋር አንድ የሚሆንም ይለይ።
_
፲፩) ምእመናንን ከቁርባን የሚከለክል ቄስ ከሹመቱ ይሻር። ቄስ ከተሾመ በኋላ ሳይሾም የሠራት ኃጢአት ብትታወቅበት ከምእመናን ይለይ። ቀሳውስት ሐሜተኞች አይሁኑ።
_
፲፪) ለሴት በደሟ ወራት ሥጋውን ደሙን ያቀበለ ከሹመቱ ይሻር። ቀሳውስት ዲያቆናት ከሚያገለግሉባት ቤተክርስቲያን ወጥተው ወደ ሌላ ቢሄዱ ምእመናን ሊቀበሏቸው አይገባም።
_
፲፫) ቄስ ሚስቱ ብትወልድ ከአገልግሎት አይከልከል።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።
ክፍል ፯ ይቀጥላል።
መ/ር በትረማርያም አበባው።
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
__ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፯__
አንቀጽ ፯ ስለ ዲያቆናት ይናገራል።
፩) ዲያቆናት ጸጥ ያሉ፣ የሚታዘዙ ይሁኑ። ዲያቆናት ሁለት ሦስት ሰዎች መስክረውላቸው ይሾሙ። በአገልግሎት ሁሉ ይፈተኑ። ለሰው የሚያዝኑ የሚራሩ ይሁኑ። በቀለኞች ሳይሆን በቀልን የሚተው ይሁኑ። ቁጡ ብስጩ አይሁኑ።
_
፪) ዲያቆናት ባለጸጎችን ደስ የሚያሰኙ ነዳያንን የሚያሳዝኑ አይሁኑ። አንድነትን ሦስትነትን (ምስጢረ ሥላሴን) ለመማር ለማስተማር ይትጉ። ምዕመናንን በፍጹም ክብር ያክብሩ። ሰውን በማፈር እግዚአብሔርን በመፍራት ይኑሩ። ዲያቆን በአንብሮተ እድ ይሾማል። ቀሳውስት ዲያቆናትም ቆመው ይጸልዩለት።
_
፫) ሰው ተምሮ ከተገኘ ዲቁና በ7 ዓመት፣ በ12 ዓመት መሾም ይችላል። ሀገሪቱ ሰፊ ካልሆነች ሰባት ዲያቆናት ሊሾሙ ይገባል። ሀገሪቱ ሰፊ ከሆነች ኤጲስ ቆጶሱ እንደወደደ ይሹሙ። ዲያቆናት ከቤተክርስቲያን ገንዘብ ይመገቡ። ዲያቆናትን ያክብሯቸው። ዲያቆን ቀሳውስትን ያገልግላቸው። ከሕዝቡ ወገን ጠያቂ የሌላቸውን ድውያንንም በመጠየቅ ያገልግላቸው። ለኤጲስ ቆጶሱም ችግራቸውን ይንገረው።
_
፬) ዲያቆኑ በቤተክርስቲያን ሕዝቡ እንዳይተኙ እንዳይስቁ እንዳይዘባበቱ ይጎብኛቸው። ዲያቆን ደሙን በቄሱ ትእዛዝ ለምእመናን ያቀብል። በመዓርግ ከእርሱ ለሚበልጥ ደሙን አያቀብል። ኤጲስ ቆጶስ ቄስ ባይኖር በምሳ ጊዜ አቡነ ዘበሰማያት ደግሞ ባርኮ ይስጥ። ዲያቆን ያስተምት ያጠምቅ፣ ሥጋውን ደሙን ያቀብል ዘንድ፣ ሕዝብን ይባርክ ዘንድ አይገባውም። ዲያቆን ዓውዱን አይያዝ።
_
፭) ሊቀ ዲያቆን በጸሎተ ቅዳሴ ጊዜ ከኤጲስ ቆጶስ ቀጥሎ ይቁም። ከኤጲስ ቆጶሱ ብቻ በቀር ሌላ በበላዩ አይፍረድ አይቀመጥ። እስመ ውእቱ ሊቀ ካህናት። የካህናት አለቃ ነውና።
_
፮) ዲያቆናት ሆይ የተቸገሩትን ልትጎበኟቸውና የተቸገሩበትንም ነገር ለኤጲስ ቆጶሳችሁ መንገር ይገባችኋል።
_
__አንቀጽ ፰___
ስለ ንፍቀ ዲያቆን፣ አናጉንስጢስ፣ አፃዌ ኆኅት፣ መዘምር (ዳዊት ደጋሚ) እና ዲያቆናዊት ይናገራል። ሁሉም በቃል እንጂ በአንብሮተ እድ አይሾሙም።
፩) አናጉንስጢስ (አንባቢ) በንባብ ከፈተኑት በኋላ ይሾም። ነገር የማያበዛ ይሁን። ዋዛ ፈዛዛ አይናገር። አከናውኖ የሚያናብ ይሁን። የሚያነበውን ለመሥራት የሚተጋ ይሁን። ሚስት የሌለው ይሾም። አናጉንስጢስ ቢሰርቅ ለዓመት ከአገልግሎት ይከልከል። ከዓመት በኋላ ያንብብ። እስከ ዕለተ ሞቱም በአናጉንስጢስነት መዓርግ ይኑር።
_
፪) ዲያቆናዊትነትን የምትሾም ሴት 60 ዓመት የሆናት ትሁን። በአንድ ወንድ ጸንታ የኖረች ትሁን። በበጎ ሥራ ጸንታ እንደኖረች የመሰከሩላት ትሁን። ልጆቿን በሥርዓት ያሳደገች፣ እንግዳ የምትቀበል ትሁን። ዲያቆናዊት የምትሾም ሴቶችን እንድታገለግል ነው። ተጠማቂ ሴትን ከአንገቷ በላይ ቄሱ ሜሮን ይቀባታል። የቀረውን የአካል ክፍል ዲያቆናይቱ የቄሱን እጅ ይዛ ትቀባታለች። ዲያቆናዊት ሴቶችን ትገሥፃቸው።
_
፫) ንፍቀ ዲያቆናት ረዳቶች ናቸው። በዲያቆን ቦታ ሆነው ማገልገል አይገባቸውም። ንዋየ ቅድሳትን እንዲነኩ አልተፈቀደም። ልብሰ ተክህኖ መልበስ አልተፈቀደላቸውም።
_
፬) መዘምራን ዳዊት ደጋሚ እንደመሆናቸው ዳዊት. ይድገሙ። መዘምራን እና አናጉንስጢሳውያን ሚስታቸው ሞታ ሁለተኛ እናግባ ቢሉ ማግባት ይችላሉ።
_
፭) በር ጠባቂዎች (ዐጸውተ ኀዋኅው) ወንዶች በሚገቡበት በር ቁመው ይጠብቁ። በር ጠባቆች አንድ ሰዓት እንኳ ከበር መለየት የለባቸውም።
_
፮) ከሴቶች ወገን ቅስና ዲቁና መሾም አይገባም። በቤተክርስቲያንም ጸሎት መጀመር አይገባቸውም። ቃላቸውን ከፍ አድርገው አይጸልዩ።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።
ክፍል ፰ ይቀጥላል።
መ/ር በትረማርያም አበባው።
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
__ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፰___
አንቀጽ ፱ የካህናትን ሁሉ ነገር ይናገራል። ካህናት የሚላቸው የሚከተሉት ናቸው።
፩) ሊቀ ጳጳሳት (ፓትርያርክ)
፪) ጳጳስ (መጥሮጶሊስ)
፫) ኤጲስ ቆጶስ
፬) ቆሞስ (ኮሬ ኤጲስ ቆጶስ)
፭) ቀሳውስት
፮) ዲያቆናት
፯) ንፍቀ ዲያቆናት
፰) አናጉንስጢስ
፱) መዘምራን
፲) አፃዌ ኆኅት. ናቸው።
፩) ከተጠመቀ በኋላ የገዘሩትን (የገረዙትን)፣ በግድ ሰዎች የሰለቡትን፣ ባለመድኃኒት በደዌ ምክንያት አባለ ዘሩን መድኃኒት አድርገት የተቆረጠውን ለክህነት በቅተው ከተገኙ ይሾሙ። በፈቃዱ ራሱን የሰለበ ግን አይሾም።
_
፪) ባሮች ጌቶቻቸው ሳይፈቅዱላቸው ከክህነት ሥራ ወገን በማናቸውም አይሾሙ። ጌታው ነጻ ያወጣው ቢሆንና በራሱ ፈቃድ ያድር ዘንድ ነጻ ቢያወጣው ለክህነት የበቃ ቢሆን ይሾም።
_
፫) ምእመን በክርስቶስ ስም አምኖ መከራ ቢቀበል ዲቁና ቅስና ተሹሞ ለማገልገል በአንብሮተ እድ አይሹሙት። አምኖ በሰማዕትነት በተቀበለው መከራ መንፈስቅዱስ አክብሮታልና። መንፈስቅዱስ ሹሞታልና። የክርስቶስን ስም አልክድም ብሎ አምኖ ወደ ዓላውያን ነገሥታት ገብቶ መከራ ባይቀበል፣ እጁን በሰንሰለት እግሩን በእግር ብረት ታሥሮ መከራ ያልተቀበለ ቢሆን ከሰው የተለየ መከራ ባያገኘው ግን በአንብሮተ እድ ይሹሙት። ኤጲስ ቆጶስነት የሚሾም ቢሆን ግን በአንብሮተ እድ ይሹሙት።
_
፬) ሰው በአካሉ ነውር ስለተገኘበት ከሹመት አይከልከል። አንካሳም ቢሆን፣ አንድ ዓይናም ቢሆን፣ ግራኝም ቢሆን በቅቶ ከተገኘ መቀደስ የሚችል ከሆነ ይሾም።
_
፭) ቤተክርስቲያን ሁላችንንም በጥምቀተ ክርስትና ወልዳናለች።
_
፮) ሁለተኛ ያገባ፣ ሚስት ካገባ በኋላ ገልጦ ወይም ሰውሮ ዕቁባት ያኖረ፣ አግብታ የተፈታችውን ያገባ፣ ዘማዊትን ያገባ፣ ወደዘፈን ቤት የምትሄደውን ያገባ ክህነት አይሾም።
_
፯) አዲስ አማኝ የሃይማኖቱ መረዳት ንጽሕናው እስኪመረመር ድረስ ክህነት አይሾም።
_
፰) አንዱስ እንኳ ለክህነት ይበቃል ብለው ሳይመሰክሩለት አይሾም። ካህናት ከመሾማቸው በፊት ሊቀ ዲያቆኑ አስቀድሞ በንባብ ይፈትናቸው።
_
፱) ለጸሎት ለአገልግሎት እንዳያንሱ በቤተክርስቲያን የሚኖሩ ካህናት ጥቂቶች አይሁኑ። ዳግመኛም ቤተክርስቲያን የምትሰጠው ምግብ እንዳታጣ ካህናት አይብዙ። ምግብ ልብስ መስጠት በሚቻላት መጠን ትሹም እንጂ።
_
፲) ኤጲስ ቆጶስ ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሾመ ነፍስን ሥጋን ከጥፋት ይጠብቅ ዘንድ ነው። ክህነት በክብር ከመንግሥት ትበልጣለች።
_
፲፩) በብሉይ ኪዳን ደቂቀ ሜርያርይ ንዋየ ቅድሳትን ይሸከሙ ነበር፣ ደቂቀ ጌድሶር አዕማደ ደብተራ ኦሪትን ይሸከሙ ነበር፣ ደቂቀ ቀዓት ታቦተ ጽዮንን ይሸከሙ ነበር፣ አልዓዛር ኢታምር መሥዋዕተ ሠክር መሥዋዕተ ነግህ ይሠው ነበር፣ ናዳብ አብዩድ አርደው አወራርደው ያቀርቡ ነበር፣ አሮን ከዓመት አንድ ጊዜ ቅድስተ ቅዱሳን ገብቶ ይሠዋ ነበር፣ ሙሴ አሮንን ከሾመ በኋላ የክህነት ሥራን አልሠራም።
_
፲፪) ወደ ቤት ስትገቡ "ሰላም ይኵን ለሰብአ ዝንቱ ቤት" በሉ። በረከት የሚገባው ሰው ከዚያ ቢኖር በረከታችሁ ይደርበት። በረከት የሚገባው ሰው ባይገኝ ግን በረከታችሁ ወደእናንተ ይመለስ።
_
፲፫) በከንቱ የሚራገም ሰው ራሱን ብቻ ረገመ። በማይገባ የሚሆን መርገም በማንም በማን አይደርስም። [ቁጥር ፪፻፺፫]።
_
፲፬) (ሐተታ) እየጸለይን ሳለ አንዱ ሊያነጋግረን ቢመጣ አረማዊ ከሆነ ውዳሴ ማርያም እየደገምን ከሆነ የዕለቱን ጨርሰን፣ ዳዊት እየደገም ከሆነ አሥሩን መዝሙር ጨርሰን በአቡነ ዘበሰማያት አሥረን እናነጋግረው። ክርስቲያን ከሆነ የያዝነውን አንቀጽ ጨርሰን በአቡነ ዘበሰማያት አስረን እናነጋግረው። ከዚያ ካረፍንበት መቀጠል ነው። አቋርጠን ከተነጋገርን ግን እንደገና ጀምረን መጸለይ ይገባናል።
_
፲፭) መዓርጋቸውን እንዳያስነቅፉ ካህናት ምጽዋት መቀበል አይገባቸውም። ከቤታቸው ይስጧቸው እንጂ ከአደባባይ ወድቀው አይለምኑ።
_
፲፮) ካህናት ከሠርግ አዳራሽ ሄደው ዘፈን መስማት አይገባቸውም። የሚፈክሩት የሚዘፍኑት ሳይመጡ በልተው ጠጥተው መርቀው ይመለሱ እንጂ።
_
፲፯) ካህን ከሰው ወገን ለአንዱስንኳ አይገዛ። ካህናት የሰው ተገዦች ሊሆኑ አይገባም። ክፉ ሥራ በመሥራት ለሰው አብነት አይሁኑ። ካህን ከሥጋዊ ሹማምንት ለአንዱስንኳ ሹም አይሁን። [ቁጥር ፫፻፯]
_
፲፰) ካህናት ፈጽመው አይነግዱ። እደ ጥበብ ይማሩ እንጂ። ጽፈው ደጉሰው ራሳቸውን ያኖሩ ዘንድ።
_
፲፱) በካህናት የሚፈረደውን ፍርድ ወደ መኳንንት አይውሰዱት። የዚህ ዓለም ነገሥታት መኳንንት በካህናት ላይ አይፈርዱምና። እያንዳንዱ ካህናት በመኳንንት ይፈርዳሉ እንጂ።
_
፳) በኤጲስ ቆጶስ ክፉ ቃል የሚናገር ሰው እነሆ እግዚአብሔርን በደለ።
_
፳፩) ልጄ ሆይ ቃለ እግዚአብሔር ወንጌልን ያስተማረህን ልጅነትን ለማግኘት ምክንያት የሆነኽን እንደ እግዚአብሔር አክብረው።
_
፳፪) ካህናት በጨዋ ዳኛ መዋስ አይገባቸውም። ራሱን የሰለበ ካህን ከሹመቱ ይሻር።
_
፳፫) ገበጣ የሚጫወት ካህንን ተው ይበሉት። ባይተው ከክህነቱ ይሻር። ሕዝባውያንም ካሉ ከምእመናን ይለዩ።
_
፳፬) በአንድ ዓይና፣ በአንካሳ፣ በዕውር የዘበተ ካህን ቢኖር ከምእመናን ይለይ።
_
፳፭) በሐሰት የማለ ካህን ከሹመቱ ይሻር። ሥጋዊ በሽታ ሳይከለክለው ዐቢይ ጾምንና ረቡዕ እና ዓርብን የማይጾም ካህን ከሹመቱ ይሻር።
_
፳፮) የቅስና መዓርግ ከተቀበለ በኋላ ሚስት ያገባ ለሹመቱ ይሻር።
_
፳፯) ቄስ ጠጥቶ ቢሰክር፣ ቢራቆት ከሰው ተለይቶ ሰባት ሱባዔ ይጹም። ከቅስና በታች ባለ መዓርግ በዲቁና እያገለገለ አንድ ዓመት ይኑር። ዲያቆን ቢሆን አምስት ሱባዔ ይጹም። በንፍቀ ዲያቆናት አራት ወር ያኑር።
_
፳፰) ጨዋው ጨዋውን ቢሰድብ እንደ ሕፃን ተቆጥተው ይተውት። ካህን ካህኑን ቢሰድብ ይለይ። ቀኖናውን እስኪፈጸም ድረስ ከምእመናን ይለይ።
_
፳፱) ነገር እያሠራ ዘወትር የሚያጣላ ሰው ቢኖር አንድ ጊዜ ሁልጊዜ ይተው። ዘወትር ነገር መሥራቱን ባይተው ከሹመቱ ይሻር።
_
፴) የወታደር ልብስ የለበሰ ቄስ ቢኖር አራት ወር ከቤተመቅደስ በአፍአ ይቁም። ዲያቆን ቢሆን በአፍኣ ሁለት ወር ይቁም። @EotcLibilery @EotcLibilery @EotcLibilery
_
፴፩) ቄሱ ዲያቆኑን ቢጣላው፣ ዲያቆኑም ቄሱን ቢጣላው ቅጣታቸው በኤጲስ ቆጶሱ ሰባት ሱባዔ ይሁን። አንባቢ ቄሱን ቢጣላው ቄሱ ይቅጣው።
_
፴፪) ካህን ከካህን ጋር ቢጣላ ታርቀው እስኪመለሱ ድረስ ሁለቱም ከአገልግሎት ይለዩ።
_
፴፫) ደዌ ሥጋ የታመመ ሰው እና ለምጻም ሰው ቤተመቅደስ ገብቶ ማገልገል አይገባውም። ነውር ሆኖ አይደለም። ካህናትን እንዳያሰድብ ነው እንጂ።
_
፴፬) ካህን ኤጲስ ቆጶሱ የሰጠውን የክህነት ወረቀት ሩቅ ሀገር ሲሄድ ካልያዘው የዚያ ሀገር ሰዎች ወረቀቱን ሳያዩ አይቀበሉት።
_
፴፭) ከተወገዘ ሰው ጋር አብሮ የጸለየ ከምእመናን ይለይ።
_
፴፮) {ቁጥር ፫፻፴፱} ካህን በአነዋወሩ ደግ ቢሆን ተስማምተው ሊያከብሩትና ሊታዘዙት ይገባል። በአኗኗሩ ክፉ ቢሆን ግን፣ በደሉ ቢታወቅ፣ በበደሉ ጸንቶ ቢኖር ሊቃውንት መጽሐፍ እንዳዘዘው ሊፈርዱበት ይገባል። በደሉ ባይታወቅ ግን፣ በበደሉ ጸንቶ ባይኖር ሊሽሩት አይገባም።
_
፴፯) ክህነት የአምላክ ገንዘብ ናት። በኃጥኡ ቄስና በጻድቁ ቄስ በተናዘዙ ሰዎች መካከል ሀብት ሥርየት ልጅነት በሚያገኙበት ሥልጣነ ክህነት መለያየት የለባቸውም። ኃጥእ ቄስ ራሱን ይጎዳል እንጂ ለሌላው ሀብት ልጅነት ሥርየት ይሰጣልና። [ቁጥር ፫፻፵፬ ሐተታ]።
_
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
ክፍል ፱ ይቀጥላል
መ/ር በትረማርያም አበባው። @EotcLibilery @EotcLibilery @EotcLibilery
Forwarded from የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አስተምህሮ ("የአምር አቡክሙ ሰማያዊ ዘትፈቅዱ ዘእንበለ ትስአልዎ።" ማቴ. ፮፡፰)
Share በማድረግዎ የጠፋችዉን ነፍስ ምናልባት ያተርፉ እንደሆን ማን ያውቃል?
Forwarded from የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አስተምህሮ ("የአምር አቡክሙ ሰማያዊ ዘትፈቅዱ ዘእንበለ ትስአልዎ።" ማቴ. ፮፡፰)
➦ቅኔ እም ኀበ መምህር ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ
መወድስ
°ቃለ ሕገ ወንጌል እግዚእ ብዕለ ጥበብከ ዘኵሎ ፈጠረ እም ኀበ አልቦ ኀበ ቦ፥
°ዲበ ወኢምንት ርቱዐ ከመ ያስተርኢ ጥበቦ፥
°ለሰማይ ኒቆዲሞስ ዲበ ምድር ትእዛዘ ኦሪት አቅዲሙ ረበቦ፥
°አንተሰ እግዚአ ኵሉ ለዘእም ሀብትከ ርህበ እም ሀብተ ጸጋከ ታጸግቦ፥
°ኢይሴወርሂ ቅድመ ዐይንከ መንፈቀ ሌሊት ቀሪቦ፥
°ኒቆዲሞስ ዘተሐብአ ጽልመተ ተገልቢቦ፥
°እመኒ ይሴወር መዝገበ በረከት ዘጊቦ፥
°ለለ አሐዱ ከመ ምግባሩ እስመ ፍትሐ እዴከ ትረክቦ።

ዋይ ዜማ
°ኒቆዲሞስ ወርሐ ሰማይ ዘአኰነኖ ሌሊተ እግዚአ ኵሉ ወንጌል፥
°ኀተወ መንፈቀ ሌሊት በብሩህ ፀዳል፥
°ወእስከነ አድማስ በጽሐ ፀዳለ ብርሃኑ ቀሊል፥
°እስመ ለኒቆዲሞስ ወርሕ ግብረ እደ ሐይል፥
°ተፈጥሮቱ በጽኑዕ ቃል። (ዮሐ. ፫፡፩-፲፩)

ግእዝ ክብር ይእቲ
°ወልደ ሐቌ ገሃነም ሲኦል ዘእደ ዐማኑኤል ይዳደቆ፥
°አብደኑ ጥዩቀ እስመ የሐውር ዕራቆ፥
°ወአመ ሠርቀ ወርሕ ኮነ ለእመ ቆመ ርሒቆ፥
°ሕማሙ እኩይ ኀበ ጸድፈ መስቀል ያወድቆ።

ግእዝ ዕጣነ ሞገር
°አመ ምስለ ሐይላት ዐርገ ናቡከደነፆር ንጉሥ ኒቆዲሞስ ዘአኮ እጓለ ማውታ፥
°ለኢየሩሳሌም ወንጌል ካልእተ ኦሪት ቴምናታ፥
°ምስለ እሊኣሃ ሐይላት ለዓለመ ዓለም ይንሥታ፥
°ለወንጌል ኢየሩሳሌም በሌሊት ዐገታ፥ (፪ ነገ. ፳፭፡፩-፯)

ዐሠረ ነጋሢ
°እለ እም ርሑቅ ቆምክሙ በአፍኣ ንዑ ወንሕትታ፥
°ለደብረ ምሕረት ድንግል ዘዓዲ ንጽሐ መላእክት ትርሲታ፥
°እግዚእ አምጣነ ሐደረ በውስቴታ።

➤መጋቢት ፳፬/፳፻፲፭ ዓ.ም
➤ርእሰ አድባራት ወገዳማት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል - ድሬዳዋ

https://www.facebook.com/Yared.ZeraBuruk?mibextid=ZbWKwL
Audio
በዚህ ዘመን ማንን እንከተል?
                         
Size 25.8MB
Length 1:14:01

  በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
#የጌታ_ስቅለት_በአበው

"አደምን የፈጠሩ እጆቹ በመስቀል ቀኖች ተቸነከሩ ወዮ በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ቀኖች ተቸነከሩ ወዮ የማይሞተው ሞተ ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ ሙታንን ያድናቸው ዘንድ ሞተ የምትወዱት ሰዎች ፈጽሞ አልቅሱለት፡፡" #ቅዳሴ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

“እጆቹን እግሮቹን በተቸነከረባቸው ችንካሮች መወጋቱንም እናምናለን፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ እርሱ ደዌያችንን ወሰደ ሕማማችንንም ተሸከመ፤ እኛን ለማዳን ኃጢአታችንንም ለማሥተሥረይ መከራ ተቀበለ እንዳለ፣ በባሕርዩ ሕማም የሌለበት ሲሆን በሥጋ የታመመ ነው፤ በእርሱ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ድነናል አለ፡፡ በተገረፈና በተቸነከረም ጊዜ በመከራው ሁሉ መለኮትን ሕማም ተሰማው የሚል ሰው ቢኖር የተለየ የተወገዘ ይሁን፡፡” #ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ሊቀ_ጳጳስ

‹‹የሚሠዋ በግ እርሱ ነው፤ የሚሠዋ ካህን እርሱ ነው፡፡ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም መሥዋዕት የሚቀበል እርሱ ነው፡፡ በፈቃዱ መከራን በሥጋው የተቀበለ መከራንም ሁሉ የታገሠ እርሱ ነው፡፡ እንደ በግ ሊሠዋ መጣ፤ በግ በሚሸልተው ሰው ፊት እንዳይናገር አልተናገረም፤ በአንደበቱ ሐሰት አልተገኘበትም፡፡›› #ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ

‹‹ታመመ ሞትን ከተቀበለበት ከሥጋ ጋር ተዋሕዶ በመስቀል ላይ በፈቃዱ ለሥጋውያን ሞተ፤ ባሕርየ መለኮት ሥጋን ተዋሕዶ በማኅፀን ካደረ ጀምሮ ሥጋ ገንዘቡ እንደመሆኑ በሥጋ ይኸንን ሥርዐት ፈጸመ፡፡ ለማይመረመር ለመለኮቱ ባሕርይ እንደሚገባ ደግሞ እርሱ ኅብስት አበርክቶ ሁሉን ያጠግባል፤ አይራብም፤ አይጠማም፤ አይደክምም፤ አያንቀላፋም፤ አይታመምም፤ አይሞትም፤ ሕይወትን ለሁሉ ይሰጣል፡፡ ዳግመኛ በዛ በሲኦል ተገዝተው ያሉ ነፍሳትን ያድን ዘንድ በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ወረደ በመለኮቱም ሲኦልን በዘበዘ›› #ቅዱስ_ቄርሎስ_ዘእስክንድርያ

‹‹ሙሴም ሞትን ያጠፋ ዘንድ አልቻለም፤ እርሱንም ይዞ ገዛው እንጂ፤ ከእርሱም በኋላ የተነሡ ነቢያትንም ሁሉ ሞት ገዛቸው እንጂ፡፡ ክርስቶስ ግን በቸርነቱ ለሁሉ ሕይወትን ሰጠ›› #ቅዱስ_አቡሊዲስ_ዘሮም

‹‹ምትሐት ያይደለ በእውነት ተራበ፣ ተጠማ እንጂ፡፡ ዳግመኛም ከኃጥአን ከመጸብሐን ጋር በላ ጠጣ፤ ያቀረቡለትንም በላ፡፡ ራሱን አሳልፎ ለመስቀል ሰጠ፤ እጁን እግሩን ተቸነከረ፤ ጎኑን በጦር ተወጋ፤ ከእርሱም ቅዱስ ምሥጢር የተገለጠበት ደምና ውኃ ፈሰሰ /ወጣ/፡፡›› #ቅዱስ_ባስልዮስ_ዘቂሳሪያ

@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
"ሁሉን የያዘውን ያዙት፤ ሁሉን የሚገዛውን አሠሩት፤ የህያውን አምላክ ልጅ አሠሩት፤ በቁጣ ጎተቱት፤ በፍቅር ተከተላቸው። በሚሸልተው ፊት እንደማይናገር እንደ የዋህ በግ በኋላቸው እየተከተለ ወሰዱት፤ ሊቃነ መላእክት በመፍራት እና በመንቀጥቀጥ ከፊቱ የሚቆሙለትን በአደባባይ አቆሙት፤

ኃጢአትን ይቅር የሚለውን ኃጥእ አሉት፥ በመኳንንት የሚፈርደውንም በእርሱ ፈረዱበት፤ ለሱራፌል ዘውድ የሚያቀዳጃቸውን የሾህ ዘውድ አቀዳጁት፤ ለኪሩቤል የገርማ ልብስ የሚያለብሳቸውን ለመዘበት ቀይ ግምጃ አለበሱት፤ ኪሩቤል በእሳት ክንፍ ተሸፍነው በፊቱ የሚሰወሩለትን እርሱን ክፉ ባሪያ አሥሮ ፊቱን ጸፋው፤ የመላእክት ሠራዊት በፍጹም መደንገጥ የሚሰግዱለት እየዘበቱበት በፊቱ ተንበረከኩ፡፡

ይህን ያህል ትህትና እንደምን ያለ ትህትና ነው? ይህን ያህል ትእግስት እንደምን ያለ ትእግስት ነው? ይህን ያህል ዝምታ እንደምን ያለ ዝምታ ነው? ይህን ያህል ቸርነት እንደምን ያለ ቸርነት ነው? ኃያል ወልድን ፍቅር ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው በደል የሌለበትን እንደበደለኛ ሰቀሉት፡፡ ህይወትን የሠራውን ከበደለኞች ጋር ቆጠሩት፤ አዳምን የሠሩ እጆች በመስቀል ቀኖዎት ተቸነከሩ፤ ወዮ በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ተቸነከሩ፡፡

ወዮ በአዳም ፊት የህይወት እስትንፋስን እፍ ያለ አፍ ከሃሞት ጋር የተቀላቀለ የኮመጠጠ መፃፃን ጠጣ፤... ወዮ የወልድን መከራውን የሚናገር ምን አፍ ነው? ምን ከንፈር ነው? ምንስ አንደበት ነው? የፍቁሩ የጌታ ህማማት በተነገረ ጊዜ ልብ ይለያል፤ ህሊናም ይመታል፤ ነፍስም ትንቀጠቀጣለች፤ ሥጋም ይደክማል የማይሞተው ሞተ፤ ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ፤ ሙታንን ያድናቸው ዘንድ ሞተ። የምትወዱት ሰዎች ፈጽሞ አልቅሱለት፡፡"

/ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
2024/09/24 10:25:26
Back to Top
HTML Embed Code: