Telegram Web Link
​​መናፍቃን ማንኛውንም ጥያቄ ሲጠይቅወት መልሱ ይኸው ሼር አድርጉት መረጃው ለሁሉም ይድረስ
፨፨፨ለመናፍቃን የማያዳግም መልስ፨፨፨
የመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃ

1: ሥለ ሥላሴ

የእግዚአብሔር አንድነትና ሶስትነት:-
✞ዘፍ 1:26 ዘፍ 3:22
✞ዘፍ 11:18 ዘፍ 18:1-2
✞ኢሳ 48:26 ማቴ 3:16-17
✞ማቴ 28:19 ሉቃ 1:35
✞ዮሐ 7:28-29 ዮሐ 14:25-26
✞የሐ.ስራ 3:14 1ኛ ቆሮ 12:4-7
✞2ኛ ቆሮ 13:14 ኤፌ 4:4-7

2: የእመቤታችን ቅድስናዋ ፣ ክብሯ ፣ ድንግልናዋንና
አማላጅነቷ:-

✞መዝ 9:11 መዝ 13:10
✞መዝ 44:9 መዝ 86:5
✞መዝ 131:13 መዝ 44:2
✞መኃ 4:12 ኢሳ 7:14
✞ኢሳ 49:23 ኢሳ 60:14
✞ማቴ 1:23 ሉቃ 1:28
✞ሉቃ 1:42 ዮሐ 2:1-11
✞ዮሐ 19:16 ሮሜ 11:26-27
✞2ኛ ቆሮ 11:2 ራዕ 12:16

3: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፈራጅ እንጅ አማላጅ
አይደለም፡-

✞ዘፍ 3:22 1ኛ ሳሙ 16:1
✞ኢሳ 9:6 ዳን 7:14
✞ሆሴ 13:4 ዘካ 9:9-10
✞ሚክ 5:2 ሉቃ 1:32-33
✞ዮሐ 10:30 ሉቃ 2:12
✞ዮሐ 14:7 ሮሜ 9:5
✞ቆላ 2:9-10 ቲቶ 2:11-13
✞ዕብ 1:3-4 ዕብ 1:10-11
✞1ኛ ጴጥ 3:23 1ኛ ዮሐ 2:23
✞ራእ 3:22 ራእ 22:12-13

4: ስለታቦት እና ፅላት

✞ዘፃ 24:12 ዘፃ 25:10
✞ዘፃ 25:21 ዘፃ 26:34
✞ዘፃ 31:18 ዘፃ 32:15
✞ዘፃ 34:1 ዘፃ 34:28
✞ዘፃ 37:1 ዘፃ 40:20
✞መኃ 7:89 ኢያ 3:3
ኢያ 7:6 2ኛ ቆሮ 6:16

5: ሥለ ፆም የመጽሐፍ ቅዱስ ማሥረጃ:-

✞ዘፃ 34:28 ዘፃ 9:9
✞ሳሙ 20:26 1ሳሙ 7:6
✞1ሳሙ 31:13 2ኛ ሳሙ 1:12
✞2ኛ ሳሙ12:16 ዕዝ 8:21
✞ዕዝ 68:10 ዕዝ 108:24
✞ኢሳ 48:3 ኤር 36:9
✞ዳን 9:3 ዳን 20:2-3
✞ኢዩኤ 2:14 ኢዩኤ 2:12
✞ዩና 3:5 ማቴ 4:2
✞ማቴ 6:16:18 ማቴ 9:14-15
✞ማቴ 17:21 ማር 2:18
✞ማር 9:29 ሉቃ 2:37
✞ሉቃ 18:12 የሐ.ስራ 13:3 ✞የሐ.ስራ 14:23 2ኛ ቆሮ
11:17

6: መስቀል በመጽሐፍ ቅዲስ:-

✞ማቴ 10:38 ማቴ 16:20
✞ማር 8:34 የሐ.ስራ 5:30
✞1ኛ ቆሮ 1:18 ገላ 3:13
✞ገላ 6:13 ፊል 2:8
✞ፊል 3:18

7: ጥምቀትን በተመለከተ:-

✞ሕዝ 36:25 ማቴ 3:5-6
✞ማቴ 26:19-20 ማር 1:4-5
✞ማር 16:16 ሉቃ 3:21
✞ዮሐ 3:5 ዮሐ 3:22
✞ኤፌ 4:5 ገላ 3:26-27
✞የሐዋ 19:4 የሐዋ 18:8
✞የሐዋ 13:24 የሐዋ 10:47
✞የሐዋ 9:18  1ኛ ቆሮ 1:16
✞1ኛ ቆሮ 10 :2 1ኛ ቆሮ 12:13

8:ስዕለትን በተመለከተ:-

✞ዘኁ 28:20 ዘኁ 21:2
✞ዘፃ 23:21 መሳ 11:30
✞መዝ 49:14 መዝ 75:11
✞1ኛ ሳሙ 1:11 መክ 5:4-5
✞ዮና 2:10 ናሆ 1:15
✞የሐዋ 18:18

9: ፃድቃን ሠማዕታት ያማልዳሉ:-

✞ዘፍ 18:17-18 ዘፍ 18:23:24
✞ዘፍ 20:7 ዘፍ 33:3
✞ዘፍ 42:6 1ኛ ሳሙ 28 :14
✞2ኛ ሳሙ 1:2 2ኛ ነገ 1:13
✞2ኛ ነገ 2:15 2ኛ ነገ 4:9
✞2ኛ ነገ 4:32-35 መዝ 88:34
✞ማቴ 18:18 ዮሐ 20:23
✞የሐዋ 10:25 የሐዋ 16 :29
✞1ቆሮ 6:1-2 ፊሊ 4:6
✞1ኛጢሞ 5:17 ያዕ 5:14
✞ራዕ 14:13

10: መላዕክት ዘወትር በእግዚአብሔር ፊት ይቆማሉ:-

✞መዝ 148:2 ኢሳ 6:3
✞ማቴ 4:12 ማቴ 18:10
✞ማቴ 25:31 ማር 8:38
✞ራእ 1:11 ሉቃ 1:19

11: መላዕክት ፀሎታችን ወደ እግዚአብሔር ያደርሳሉ:-

✞ጦቢ 12:15 ሉቃ 15:10
✞የሐዋ 10:4 እዩብ 25:3
✞ኤር 33:22 ዳን 7:10
✞ሄኖ 10:1 ራዕ 5:11

12:ለመላዕክት የአክብሮት ስግደት ይገባል:-

✞ዘፍ 19:1 ማኅ 22:31
✞ኢያ 5:14 ዳን 8:16-17
13:መላዕክት አብሣሪያን ናቸው:-
✞ዘፍ 16:11 ሉቃ 1:13
✞ሉቃ 1:19 ሉቃ 1:30-31
✞ሉቃ 2:10-11

14:መላዕክት በአደጋ ጊዜ ፈጥነው ይደረሣሉ:-

✞ዘፍ 22:11-12 መዝ 90:11-12
✞ዳን 6:22 ዳን 10:13
✞ማቴ 2:13 የሐዋ 5:19-20
✞የሐዋ 12:7

15: ፀበል መርጨት ያስፈልጋል:-
✞ዘኁ 19:20

በተጨማሪም ሁላችንም እያንዳንዱን የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍል ደጋግመን እናንብበው እግዚአብሔር አምላክ ማስተዋልና ጥበቡን ይስጠን
አሜን

@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
የቁባቱን በድን የቆራጠው ካህን! (መሳ. 19-20)


በእስራኤል ልጆች ታሪክ ውስጥ አያሌ አስከፊ ተግባራት ተከናውነዋል፤ ዛሬ የምናየው ይህ አንዱ ነው፤ “በዚያም ዘመን በእስራኤል ዘንድ ንጉሥ በሌለበት ጊዜ በተራራማው በኤፍሬም አገር ማዶ የተቀመጠ ሌዋዊ ነበረ፤” (መሳ. 19፥1) ይላል፣ በመሳፍንት መጽሐፍ ውስጥ ከተቀመጡት የብንያም ሰዎችን የሥነ ምግባር ብልሹነትና በምላጭ ጫፍ ላይ መቆማቸውን ከሚያሳዩት ታሪኮች አንዱን ለመተረክ ሲነሳ።

በርግጥ ሌዋዊው ካህን ቁባቱን ፍለጋ ከኤፍሬም ወደ ቤተልሔም መሄዱ፣ ከአንድ ሚስት በላይ ማግባቱን ያሳያል፤ ይህ በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት ያለው ተግባር አልነበረም፤ በተጨማሪም፣ እግዚአብሔር ለእስራኤል ልጆች መሳፍንትን የሰጠው፣ ርሱ ብቻውን በነርሱ ላይ ሊነግሥ ነበር። ነገር ግን ለጌታ ከመታዘዝ ይልቅ፣ የሃይማኖት መሪዎቿ ድካምና ኃጢአት እያየለባቸውና እየባሰባቸው ሲሄድ በተደጋጋሚ እንመለከታለን።


ካህኑ ቁባቱን አጊኝቶአት ይዞ፣ ከቤተልሔም ወደ ኤፍሬም በሚመለስበት ጊዜ እግረ መንገዱን ጊብዓ በምትባል በብንያማውያን ከተማ መሸበትና አደረ።

የከተማዪቱ ሰዎች ግን ልክ እንደ ሰዶምና ገሞራ ሰዎች፥ እጅግ አስጸያፊ ተግባር የሚፈጸሙ ነበሩ። በእንግድነት ወደ ነርሱ የመጡትን ካህንና ቁባቱን ከማስተናገድ ይልቅ፣ በካህኑ ላይ የሰዶማዊነት ነውር ሊፈጽሙበት ፈልገው አሳዳሪውን ሽማግሌ፣ እደ ሰዶም ሰዎች ግድ አሉት። ሽማግሌው፦ “ወንድሞቼ ሆይ፥ ይህን ክፉ ነገር፥ እባካችሁ፥ አታድርጉ፤ ይህ ሰው ወደ ቤቴ ገብቶአልና እንደዚህ ያለ ኃጢአት አትሥሩ። ድንግል ልጄና የእርሱም ቁባት፥ እነሆ፥ አሉ፥ አሁንም አወጣቸዋለሁ፤ አዋርዱአቸው፤ እንደ ወደዳችሁም አድርጉባቸው፤ ነገር ግን በዚህ ሰው ላይ እንደዚህ ያለ ኃጢአት አታድርጉ” (19፥23-24) ብሎ ቢለምናቸውም፣ ሰዎቹ ግን ሊሰሙ ፈጽሞ አልወደዱም። በመጨረሻም ግን ሽማግሌው የገዛ ሴት ልጁንና የሌዋዊውን ቁባት አውጥቶ ሰጣቸው።

ሰዎቹ፣ የሌዋዊው ቁባት እስክትሞት ድረስ በመፈራረቅ ሌሊቱን ሙሉ አመነዘሩባት። ሽማግሌው እንደ ሎጥ፣ ራሱን ከማኅበረ ሰቡ ርኩሰት የጠበቀና ያገለለ መኾኑ እጅግ ያስደንቃል፤ ተግባራቸውንም “ክፉ ነገር” ብሎ መጥራቱ ይኸንኑ ያሳያል፤ ሌዋዊው ግን ያሳየው ግዴለሽነትና ደንታ ቢስነት ያሳዝናል።

ሌዋዊው የቁባቱን ሬሳ 12 ቦታ ቆራረጠና ለእያንዳንዱ የእስራኤል ነገድ አንዳንዱን ቁራጭ ላከ። ይህም ነገር የ12ቱን ነገዶች ቁጣ ቀሰቀሰና ምን እንደ ተፈጸመ ለማየት መጡ። ታሪኩን በሰሙ ጊዜ፥ ይህን ኃጢአት የፈጸሙትን ሰዎች አሳልፈው እንዲሰጧቸው ብንያማውያንን ጠየቁ። ብንያማውያን ተቃወሙ፥ የርስ በርስ ጦርነት ተነሣ። በጦርነቱም 40000 እስራኤላውያንና 25100 ብንያማውያን ሞቱ። የብንያማውያን ሴቶችና ልጆች በሙሉ ተገደሉ። ከብንያም ነገድ በሙሉ የተረፉት 600 ሰዎች ብቻ ነበሩ።

ሌሎች እስራኤላውያን፥ ከእስራኤል ነገዶች አንዱ የኾነው የብንያም ነገድ ሊጠፉ እንደ ኾነ ተገነዘቡ፤ ስለዚህ ለእነዚህ 600 ብንያማውያን 600 ሚስቶች የሚገኙበትን ዘዴ ፈጠሩ። በዚህም የብንያምን ነገድ ጨርሶ ከመጥፋት አዳኑት።

ሰዎች ራሳቸው የሚፈልጉትን ነገር ብቻ ሲያደርጉ፥ ኃጢአታቸው አድጎ በርካታ ሰዎችን እንደሚነካና እንደሚያጠፋ አይገነዘቡም። ኀጢአትና ኀጢአተኝነት የመዛመትና ሌላውን የመውረስ ጠባይ አለው፤ የጊብዓ ሰዎች ኃጢአት በሺህ የሚቆጠሩ የበርካታ እስራኤላውያንን ሞትና የብንያም ነገድን ወደ ውድመት የሚያደርስ ጥፋት አስከትሎ ነበር። የአንድ ካህን ሕገ እግዚአብሔር መጣስና የብንያም ነገድ ሰዶማዊነት መኾን፣ ፍጻሜውን መራራ አድርጎታል። ኀጢአት በማናቸውም መንገድ የፍጻሜ መንገዱ ጣፋጭ አይኾንም!

እንግዶችን በማስተናገድ አንዳንዶች ራሱ እግዚአብሔርን ሌሎች ደግሞ መላእክትን ተቀብለው ነበር፤ የብንያም ሰዎች ግን እንግዶቻቸውን ለነውር ተግባር ፈለጉ፡፡ ወንዶቹ ኀፍረተ ቢስና ፍትሕ አልባ ነበሩ፡፡ ምናልባት ታሪኩ ሊረሳ እንጂ ሊተረክ የሚገባው አይመስልም፤ ግን እንድንተርከው ታዝዘናል፡፡ የሴቲቱ ታሪክ አሳዛኝና ልብ ሰባሪ ነው፤ የሚቆምላትና የሚከላከልላት አልነበረም፡፡ ሌዋዊው ሊንከባከብ ከአባትዋ ቤት ቢያወጣትም፣ ነገር ግን ለርኩሳንና ለማይራሩ ሰዎች አሳልፎ ሰጣት፡፡ በዚያ ሙሉ ሌሊት የተፈጸመባትን ርኩሰት ማስተዋልና ርኅራኄ ሊያሳያት ሲገባ ግን አላደረገም፤ ብሎም የቀብር ክብርዋን በመንፈግ ሰውነቷን ቆራረጠው!

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንዲህ ያሉ ታሪኮች መቀመጣቸው፣ ሰው ከእግዚአብሔር ፊትና ከአገዛዙ ሲለይ፤ በራሱም መንገድ መልካም መስሎ የታየውን የሚያደርግ ከኾነ ፍጻሜው ይኸው መኾኑን ያሳያል፡፡ ወዳጆቼ! ዛሬም በምድራችን ላይ የምንሰማቸው አያሌ ክፉ ተግባራት፣ ከዚህ እውነታ እምብዛም የራቁ አይደሉም! ከኀጢአታችን ለመታቀብና ለመተው፤ ብሎም ንስሐ ገብቶ ለመመለስ ፈቃደኞች ባልኾንን መጠን፣ የኀጢአት ፍሬና መከር መብላታችንና ማጨዳችን አይቀሬ ነው! “ኑ፥ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ፤ እርሱ ሰብሮናልና፥ እርሱም ይፈውሰናል፤ እርሱ መትቶናል፥ እርሱም ይጠግነናል።” (ሆሴ. 6፥1) የሚለው የጌታ ቃል ዛሬም ሕያው ነውና እንመለስ!

@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
Audio
ሥር ሰዳችሁ እደጉ 
                                                  
Size:- 68.3MB
Length:-1:13:47
       
     በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
ሰው አዝርእትን አትክልትን ይመስላል። አዝርእት ተዘርተው፣ አብቅለው፣ አብበው፣ አፍርተው ከጎተራ ይቀመጣሉ። ሰውም ተጸንሶ፣ ተወልዶ፣ በመልካም ሥራ አብቦ፣ ፍሬ ትሩፋትን አፍርቶ ከመንግሥተ ሰማያት ይገባል።

ፍጥረታትን በጽሙና ሆነን ብንመረምራቸው ፍቅርን፣ ትሕትናን፣ ትዕግሥትንና የመሳሰሉትን እንማርባቸዋለን። ጊዜያችንን በሚጠቅም ነገር እናውለው። ሞት መኖሩን አስበን እንኑር። ከትላንት ዛሬ፣ ከዛሬ ነገ በሥነ ምግባር ልንሻሻል ይገባናል።

ሠናይ ጊዜ
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5
Forwarded from ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ (🌼 £itsum 🌼)
+ ስለቅዱሳንና ቅድስና ጥቂት +

በዘመነ ሐዲስ ቅዱሳን ሲባል፡- ሐዋርያት፣ ነቢያት፣ ሰማዕታት፣ ሊቃውንት፣ መናንያን /ገዳማውያን/፣ ደጋግ ሰብአ ዓለም ይጠቀሳሉ፡፡ ቅዱሳን ዜግነትና ተቋማዊ አጥር ባይኖርባቸውም በልማድ እንደየሚከበሩበት ቦታ ስፋትና ጥበት አካባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ እየተባሉ ይለያሉ፡፡ የቅድስና አሰጣጡ አስቀድሞ በጉባኤ ደረጃ አልነበረም፡፡ ሰማዕታት የሆኑ እንደሆነ ምስክርነቱ የአደባባይ ነውና በቶሎ ቅድስና ያገኛሉ፡፡ አንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅና ቅዱስ ባስልዮስ ያሉ በአፍም በመጻፍም የገነኑ አበው ግብርና ቅድስናቸው ከመጉላቱ የተነሣ ከቤተ ክህነቱ ቀድሞ ምዕመኑ በቅድስና ጠርቷቸዋል፡፡ ቅድስናው በገቢረ ተአምርና በራእይ የሚገለጥም አለ፡፡

በዚህ ዘመን ግን ከሞላ ጎደል በሁሉም ሐዋርያዊ ትውፊትን በሚከተሉ አብያተ ክርስቲያናት ቅድስና በቃለ ሲኖዶስ ይሰጣል፡፡ የእኛም አካሄድ ተመሳሳይ ነው፡፡ አንድ አባት ቅዱስ ከተባለ በኋላ ስለሚደረገው ልዩ ልዩ ተግባር በ #ወልታ_ጽድቅ ወይም በዲያቆን ሰሎሞን #የኢትዮጵያ_ቤተ_ክርስቲያን_ወርቃማ_ዘመናት ወይም ደግሞ በዶ/ር ሐዲስ የሻነው የትምህርተ ሃይማኖት መጻሕፍት ማንበብ ይቻላል፡፡ ቅድስና በየጊዜው የሚጨመር ነው፤ አይቆምም፡፡ በሌላ በኩል በበጎ የሚነሣው አባት ላይ ከጊዜ በኋላ የሃይማኖት ህፀፅ የተገኘ እንደሆነ የሚታረምበት ዕድል ስለመኖሩ የአርጌንስ ታሪክና የእኛ ሲኖዶስ የግብፆችን የስንክሳር ስርዋጽ ያረመበት ድርጊት ይጠቁመናል፡፡

በ1960ዎቹ ተጀምሮ ሲካሄድ ቆይቶ እንደ መቀዛቀዝ ባለው የኦሪየንታል-ምሥራቃውያን ኢመደበኛ ንግግር የቅድስና አሰጣጥን፣ ማንና እንዴት ቅዱስ ይባል ማለትን ለነገረ መለኮትና ለታሪክ ምሁራን በመተው በግራ ቀኝ ወገኖች የተላለፈው ግዝት እንዲነሣ ሐሳብ ቀርቦ ነበረ፡፡ ሐሳቡ እስካሁን ዳር አልደረሰም ብቻ ሳይሆን በቤተ ክርስቲያናችን በ1988 ዓ.ም. በቅዱስ ሲኖዶስ በተቋቋመ የጳጳሳትና የሊቃውንት ኮሚቴ የተዘጋቸው የእምነት፣ ሥርዓትና የውጭ ግንኙነት መጽሐፍ በኬልቄዶናውያን ላይ የተላለፈው ግዝት እንደማይነሣ፣ በእነርሱ ስር ያሉ አበውንም በቅድስና መቀበል እንደማይችል በአጽንዖት ገልጧል፡፡ ቀድመው በስንክሳራችን በገቡት የሃይማኖት ጀርባቸው ከወደ ኬልቄዶን በሚመዘዝ አበው ላይ ግን ያሳረፈው ውሳኔ የለም፡፡
---

( ደብተራ በአማን ነጸረ )

#ኦርቶዶክሳዊ_አእምሮ
2024/09/24 06:30:10
Back to Top
HTML Embed Code: