Telegram Web Link
Audio
ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወረቅ እንዳሰተማረው

የህጻናት ልጆች አስተዳደግ

እናትን እናት የሚያሰብላት ⤴️
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን

ወድ እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን ዋላቹ የክርስቶስ ሰላም ጸጋ ይብዛላቹ

አጭር ጥያቄ እውነት ሀሰት በማለት መልሱ


1️⃣✍🏽 ያዕቆብ የአብርሃም የልጅ ልጅ ነው

2️⃣✍🏽 እናቱ በጣም ትወደው ከነበሩ በኦሪት ከተጸፈው አንዱ ያዕቆብ ነው

3️⃣✍🏽 የወንድሞን ብኩረና በምግብ የገዛው ያዕቆብ ነው

4️⃣✍🏽 ከአባቶ በረከት ቀድሞ ሰለ ወሰደበት ወንድሞን ልገለው በተነሳ ጊዜ ወደ አጎቶቹ የተሰደደው ያዕቆብ አይደለም

5️⃣✍🏽የሚወዳት ለሚያፈቅራት ሴት 14 አመት ተገዝቶላት ሌላዋ ቢሰጡት የምወዳት ሴት ሌላ አልፈልጌም ብሎ እንደገና ሰባት አመት በአጠቃላይ 21አመት ለሚወዳት ሴት የተገዛው ያዕቆብ ነው


አዛምዶ ከግእዝ ወደ አማርኛ
"""ሀ"" ሀምድብ ግእዝ ""ለ""ለምድብ አማረኛ ምርጫው ነው

"""ሀ""""

1= ኮነ……
2= ሎሀ….
3=ሰገደ….
4= ጥዕየ….
5= ለቅሐ…..
6= ሐገገ……
7= ሠምረ….


===ለ==

ሀ=ሆነ
ለ=ጻፈ
ሐ=ሰገደ
መ=ዳነ
ሠ=አበደረ
ረ=ሕግ ሠራ
ሸ=ወደደ


ሁላችሁም ተሳተፉ በጠም ቀላል ጥያቄ ነው

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለ ወላዲቱ ድንግል ወለ ክብር መሰቀሉ ይቆየን አሜን
!...
የእግዚአብሔርን እንግዳ ሲጠብቅ እግዚአብሔር እንግዳ ሆነለት!

መምህር ሃይማኖት አስከብር

ሐምሌ ፯ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም

ወድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ? እንኳን ለቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! እንደሚታወቀው ሐምሌ ፯ የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ በዓል ነው፤ የበዓሉን ታሪክ በአጭሩ አቅርበንላችኋል፡፡

ከላይ በርእሱ እንደገለጸው የእግዚአብሔርን እንግዳን ሲጠብቅ እግዚአብሔር እንግዳ የሆነለት ታላቁ አባትን አብርሃምን እናነሣለን፡፡ በዚህ ዕለትም ታላቁ አባት አብርሃም ሥላሴን በቤቱ ያስተናገደበት ዕለት ነው፡፡ ውድ አንባብያን! እግዚአብሔርን በቤታችን እንዴት ማስተናገድ ይቻላል?እንዴትስ ወደ ቤታችን መቀበል እንችላለን? እግዚአብሔርን በቤታችን ማስተናገድ ከአባታችን አብርሃም እንማራለን፡፡

በቅዱሳን መጽሐፍት እንደተጻፈው አብርሃም በተመሳቀለ ጎዳና ድንኳኑን ተክሎ በአራቱም አቅጣጫ የሚመጣውን እንግዳ ይቀበል ነበር፡፡ የደከመውን እግሩን አጥቦ፣ የተራበውን አብልቶና አጠጥቶ የሚልክ እንግዳ የሚወድ ታላቅ አባት ነው፡፡ ሥራው መልካም ሥራ በመሆኑና ሰይጣን በአብርሃም ላይ ቀናበት፤ መልካም ሲሠራ ሰይጣን ደስ ስለማይሰኝ የሚደንቀውም በመልካም ሥራ ሰይጣን የሚደሰት ቢሆን ነበር፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን የደከማቸው ሰዎች ወደ እንግዳ ተቀባዩ አብርሃም ቤት ሲገሰግሱ ሰይጣን ጎዳና ላይ ተቀምጦ እንግዶችን ‹‹ወዴት ትሄዳላችሁ እያለ ይጠይቅ›› ጀመር፡፡ እነርሱም ‹‹ስንደክም የምናርፍበት፣ ሲርበን፣ ሲጠማን የምንበላበትና የምንጠጣበት ወደ ደጉ እንግዳ ተቀባዩ ወደ አብርሃም ቤት እንሄዳለን እንጂ›› አሉት፤ ሰይጣንም ‹‹የድሮው አብርሃም መሰላችሁ! እኔም እንደ እናንተ ደክሞኝና እርቦኝ ተቀብሎ ያስተናግደኛል ብዬ ብሄድ በድንጋይ እራሴን ፈንክቶ፣ ደሜን፣ አፍስሶ፣ ልብሴን ቀምቶና ገፎ ላከኝ እንጂ፡፡›› እንዲህ እያለ ለሦስት ቀን እንግዳ እንዳይሄድ ከለከለበት፤ አብርሃምም ‹‹ማዕደ እግዚአብሔርን ያለ እንግዳ ምስክርነት አልቆርስም›› ብሎ ለሦስት ቀን ይጠብቅ ነበር፡፡ ታዲያ የአብርሃምን ደግነት የተመለከተ እግዚአብሔር ሰይጣን ሊያስቀረው የማይችል እንግዳ ራሱ እግዚአብሔር እንግዳ ሆኖ በአብርሃም ቤት ተገኘ፤ አብርሃምም የእግዚአብሔርን እንግዳ ሲጠብቅ እግዚአብሔር እንግዳ ሆነለት፡፡ (ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ አንድምታ 4$#2) እግዚአብሔርም በአብርሃም ቤት በአንድነት በሦስትነት ተገለጠለት፡፡

በኦሪት ዘፍጥረት ላይ ተጽፎ እንደምናገኘው እግዚአብሔር ለአብርሃም በአንድነቱና በሦስትነቱ እንደተገለጠለትና በቤቱ እንደተስተናገደ ሲገልጽ ቅዱሱ መጽሐፍ እንዲህ ይለናል፡፡ ‹‹በቀትር ጊዜ አብርሃም በድንኳኑ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በመምሬ ዛፍ ሥር ተገለጠለት፤ ዐይኑንም ባነሳ ጊዜ ሦስቱ ሰዎች በፊቱ ቁመው አየ፤ ሊቀበላቸውም ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ወደ እነርሱ ሮጠ፤ ወደ እነርሱም ሰገደ፤ አቤቱ በፊትህ ሞገስን አግኝቼ ከሆነ ባርያህን አትለፈው፡፡›› (ዘፍ. 08$1)

ሦስት ቀን ያለ እንግዳ እና ያለ ምግብ የቆየ ሰው በዚያ ላይ እግዚአብሔርን ሲያይ ከደስታው ብዛት የተነሣ ‹‹አብርሃም ወደ ሥላሴ ሮጦ ሰገደ፡፡›› አብርሃም እየጠበቀ የነበረው ሰውን ነበርና፡፡ ሰውን ሰይጣን ቢያስቀርበት ሰውን የፈጠረ እግዚአብሔር በአብርሃም ቤት ተገኘ፤ መባረክ እንዲህ ነው! በትንሹ ሲጠበቅ በብዙ መባረክ እንደዚህም ነው፤ በቅዱስ መጽሐፍ እንግዳ መቀበልን ማዘውተርና ብዙዎች እንግዳዎችን በመቀበል ፈንታ መላእክትን እንደተቀበሉ ተጽፏል፡፡ ሎጥም መላእክትን የተቀበላቸው በእንግዳ አምሳል ነበር፡፡ (ዘፍ.09$3)

ብዙ አባቶች በእንግዳ አምሳል ጻድቃንን፣ መላእክትን እግዚአብሔርን በቤታቸው ያስተናገዱት ለዚህም ነው፤ እንግዳ መቀበል እግዚአብሔርን መቀበል ነውና፡፡ አብርሃምም ‹‹ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ፤ እግራችሁን ታጠቡ፤ ከዚህ ዛፍ በታች እረፉ፤ ቁራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፤ ልባችሁን ደግፉ፤ ወደ ባሪያችሁ መጥታችኋል›› አላቸው፡፡ እነርሱም ‹‹እንደወደድክ አድርግ›› አሉት። በዚያን ጊዜ ጽንዓ ፍቅሩን ለማጠየቅ ‹‹አዝለህ አስገባን›› አሉት፡፡ እርሱም ከሦስቱ አካል አንዱ ሲያስገባ ሁለቱም ቤት አገኛቸው፤ ይህም አንድነቱን ሦስትነቱን ይገልጻል፡፡ ሊቁ ቅዱስ ጎርጎርዮስም ‹‹አንሰ እቤ እግዚአብሔር በእንተ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፤ እኔ እግዚአብሔር ስል ስለ አብ ስለ ወልድ ስለ መንፈስ ቅዱስ ነው›› በማለት ተናግሯል፡፡ ‹‹እግዚአብሔርም ተገለጠለት›› ካለ በኋላ ‹‹ሦስት ሰዎች አየ›› ማለቱ ነው ነው፡፡ እግዚአብሔር የባሕርይ አንድነቱ የሦስቱም ስም ነው፡፡ አንድነቱ በባሕርይ በሥልጣን፣ በአገዛዝ፣ በመለኮቱና በመንግሥቱ ነው፡፡

በሦስትነቱ በአካል በስም በግብር ነው፡፡ ለዚህም ለአብርሃም በአንድነቱም በሦስትነቱም እግዚአብሔር ተገለጠለት፡፡ አብርሃም ወደ ሣራ ዘንድ በመሄድ ‹‹ሦስት መስፈሪያ ዱቄት ለውሰሽ አንድ እንጎቻ አድርገሽ አዘጋጂ›› አላት፡፡ ሦሰት ማለቱ የሦስትነቱ፣ አንድ አድርጊው ማለቱ የአንድነቱ ምሳሌ ነው፡፡ ወደ ላሞቹ ሄዶ ከላሞቹ መካከል ያማረውን የተዋበውን ንጹሑን ወይፈን አቀረበ፤ እግዚአብሔር ንጹሐ ባሕርይ ነውና ንጹሐ ነገር ይወዳል፡፡ አብርሃም ያዘጋጀውን ተመገቡ፤ ሥላሴ ምግብ የሚበሉ ሆነው አይደለም፤ ‹ተመገቡ› ብሎ መናገሩ በሰው አምሳል ስለተገለጡለት ለአብርሃምም የበሉ መስሎት ስለታዩት እንጂ ለሥላሴስ መብልና መጠጥ አይስማማቸውም፡፡ ‹‹ሥላሴ ምግብ በሉ›› ማለት ‹‹እሳት ቅቤን በላው›› እንደማለት ነው፡፡ ቅቤውም ከእሳት ገብቶ አልቀለጠም ማለት ነው፤ መብልና መጠጥ የሥጋ ፈቃድ ነው፡፡ ይህም ይታወቅ ዘንድ የታረደው ወይፈንም ተነሥቶ ‹‹ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ›› ብሎ አመስግኗል፡፡ አንዳንዶች ይህንን ሲሰሙ ላያምኑ ሞኝነት ይችላሉ፤ በመጽሐፍ ቅዱስ ግን እግዚአብሔር የበለዓምን አህያ እና የቢታንያም ድንጋዮችን አናግሯል፤ ስለዚህ በሰው ዘንድ ነው እንጂ በእግዚአብሔር ዘንድ ይቻላል የማይቻል የለም፡፡

እግዚአብሔርም አብርሃምን ጠርቶ ‹‹ሚስትህ ሣራ ወዴት ናት›› አለው፡፡ እግዚአብሔር ስለ ሣራ አብርሃምን መጠየቁ ያለችበት ጠፍቶት አልነበረም፤ ልጅ እንደምትወልድ ሊነግረው ነው እንጂ፤ አብርሃምም ‹‹በድንኳን ውስጥ አለች›› አለ፡፡ ‹‹ወይቤሎ ሶበ ገባእኩ እመጽዕ ኀቤከ አመ ከመ ዮም ትረክብ ሣራ ወልደ፤ የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ እመለሳለሁ፤ ሚስትህ ሣራ ልጅ ትወልዳለች›› ብሎ ለአብርሃም ነገረው፡፡ (ዘፍ 08$0) ሣራም በአብርሃም በኋላ ቁማ ነበርና ሰማች፤ አብርሃምና ሣራ ፺፱ ሣራ ፹፱ ዓመታቸው ስለነበር አርጅተዋልና መውለድ አይችሉም፡፡ ሣራ ብቻዋን ሳቀች፤ ይህም ሣራ አርጅቻለሁ የሴቶች ልማድም አቁማለች እንዴት ሰው ካረጀ በኋላ ልጅ ይወልዳል፡፡ ‹‹ሲያረጁ በአምባር ይዋጁ›› እንዲሉ እስከ ‹‹ዛሬ ድረስ ገና ቆንጆ ነኝ›› ብላ ተጠራጠረች፤ ‹‹ትወልጃለሽ›› መባሏ አሳቃት፤ ‹‹ወይቤሎ እግዚአብሔር ለአብርሃም ምንት አስሐቃ ለሣራ እግዚአብሔር፤ አብርሃምን ሣራን ምን አሳቃት›› አለው፤ ሣራም ‹‹አልሳቅሁም›› አለች፤ እግዚአብሔር መሳቋን እንዳወቀም ከነገራት በኋላ ‹‹በድጋሚ በዓመት እንደ ዛሬው እመጣለሁ›› አለው፤ ወንድ ልጅም እንደምትወልድም አበሠራት፤ ‹‹ጌታዬም አርጅቷል እኔስ ገና ነኝ?›› ብላም ሣራ ጠየቀች፤ ‹‹ቦኑ ነገር ዘይሰአኖ ለእግዚአብሔር፤ በእውነት ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለ?›› እግዚአብሔርም አለ ‹‹እኔ የማደርገውን
ከአብርሃም እሰውራለሁ፤ አብርሃም በምድር ላይ ትልቅ ብርቱ ሕዝብ ይሆናል፡፡›› መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታቸንን ለማብሠር በመጣ ጊዜ ‹‹ልጅ ትወልጃለሽ›› ባላት ጊዜ ‹‹ወንድ ሳላውቅ እንደምን ይሆናል›› በማለት ስትጠይቀው መልአኩ ያስረዳት ዘንድም ከእርሷ በፊት ስለ ፀነሱችውን ኤልሳቤትን ነገራት፤ ለእግዚአብሔር የሚሣነው ነገር እንደሌለም አስረዳት፡፡ (ሉቃ. 1$@6-#7) ይህም እግዚአብሔር በዘመን ብዛት የማይለወጥ መሆኑን ያስረዳል፡፡ በአብርሃም ድንኳን እግዚአብሔር ተገኝቶ ለአብርሃምና ለሣራ የምሥራች ነገሯቸው፡፡ በአማናዊት ድንኳን እመቤታችን ተገኝቶ የምሥራችን ነገራት፤ ከዚህ አያይዞ ለአብርሃም እንዲህ ብሎት ነበር፤ ‹‹በዘርህ አሕዛብ ይባረካሉ፡፡›› ከአብርሃም ዘር ከተገኘችው እመቤታችን የረከሰው ዓለም ሁሉ እንዲባረክ ሆነ፤ ምክንያቱም ከእመቤታችን የተገኘው መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ስለሆነ፡፡

በአብርሃም ድንኳን ሥላሴ ተስተናግደውበታል፤ ይህች ድንኳን በእመቤታችን ትመሰላለች፤ በአብርሃም ድንኳን ‹‹አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ›› እንደገቡ ሁሉ አምስት ሽህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም በእመቤታችን እግዚአብሔር አብ ለአጽንዖ እግዘአብሔር መንፈስ ቅዱስ፣ ለአንጽሖ አግዚአብሔር ወልድ፣ በተለየ አካሉ ሥጋን ለመልበስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም አድረዋልና እመቤታችን በአብርሃም ድንኳን መመሰልዋ እንዲህ ስለሆነ ‹‹አብና መንፈስ ቅዱስ ተዋሐዱ አይባልም ወልድ በተለየ አካሉ እንጂ፤

በአጠቃላይ በዚህ ዕለት በአብርሃም ቤት እግዚአብሔር የተስተናገደበት፣ አንድነቱና ሦስትነቱ የተገለጠበት፣ አብርሃም እና ሣራ ካረጁ በኋላ ልጅ እንደሚወልዱ የተበሠረበት፣ ይሰሐቅንም እንደሚወልድ የተነገረበት እንዲሁም አብርሃም በእግዚአብሔር ፊት ቆሞ ስለ ገሞራ ሰዎች የማለደበት ዕለት ነው፡፡

ለአብርሃም ምሥጢሩን የገለጠ እግዘአብሔር ለሁላችን ይግለጥልን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
Audio
ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወረቅ እንዳሰተማረው

የህጻናት ልጆች አስተዳደግ

እናትን እናት የሚያሰብላት ⤴️

ቀጣይ ርዕስ
ልጆች ወላጆች ያተርፋባቸው ዘንድ የተሰጡ መክሊቶቾ
Audio
ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወረቅ እንዳሰተማረው

የህጻናት ልጆች አስተዳደግ


ልጆች ወላጆች ያተርፋባቸው ዘንድ የተሰጡ መክሊቶቾ⤴️
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ክርስቲናያን መንፈሳዊ ትምህርቶች እና ጽሁፎች ቻናል⛪️
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን ወድ እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን ዋላቹ የክርስቶስ ሰላም ጸጋ ይብዛላቹ አጭር ጥያቄ እውነት ሀሰት በማለት መልሱ 1️⃣✍🏽 ያዕቆብ የአብርሃም የልጅ ልጅ ነው 2️⃣✍🏽 እናቱ በጣም ትወደው ከነበሩ በኦሪት ከተጸፈው አንዱ ያዕቆብ ነው 3️⃣✍🏽 የወንድሞን ብኩረና በምግብ የገዛው ያዕቆብ ነው 4️⃣✍🏽 ከአባቶ በረከት ቀድሞ ሰለ ወሰደበት…
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን

*ወድ እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አመሽቹ የክርስቶስ ሰላም ጸጋ ይብዛላቹ*

ጥያቄ ማጠቃለያ መልሰሰ🌻እውነት ሀሰት


1️⃣✍🏽 ያዕቆብ የአብርሃም የልጅ ልጅ ነው

✍🏽እውነት

2️⃣✍🏽 እናቱ በጣም ትወደው ከነበሩ በኦሪት ከተጸፈው አንዱ ያዕቆብ ነው

✍🏽እውነት
3️⃣✍🏽 የወንድሞን ብኩረና በምግብ የገዛው ያዕቆብ ነው

✍🏽እውነት
4️⃣✍🏽 ከአባቶ በረከት ቀድሞ ሰለ ወሰደበት ወንድሞን ልገለው በተነሳ ጊዜ ወደ አጎቶቹ የተሰደደው ያዕቆብ አይደለም

✍🏽ሀሰት ያዕቆብ ነው
5️⃣✍🏽የሚወዳት ለሚያፈቅራት ሴት 14 አመት ተገዝቶላት ሌላዋ ቢሰጡት የምወዳት ሴት ሌላ አልፈልጌም ብሎ እንደገና ሰባት አመት በአጠቃላይ 21አመት ለሚወዳት ሴት የተገዛው ያዕቆብ ነው

✍🏽እውነት

አዛምዶ ከግእዝ ወደ አማርኛ
"""ሀ"" ሀምድብ ግእዝ ""ለ""ለምድብ አማረኛ ምርጫው ነው መልስ🌻

"""ሀ""""

1= ኮነ……✍🏽
2= ሎሀ….✍🏽
3=ሰገደ….✍🏽
4= ጥዕየ….✍🏽
5= ለቅሐ…..✍🏽
6= ሐገገ……✍🏽
7= ሠምረ….✍🏽


===ለ==

ሀ=ሆነ
ለ=ጻፈ
ሐ=ሰገደ
መ=ዳነ
ሠ=አበደረ
ረ=ሕግ ሠራ
ሸ=ወደደ


ሁላችሁም በእውነት ቃለ ህይወት ያሰማልን እግዚአብሔር የአገልግሎት ዘመናቹ ይበረክልን ጸጋው ያብዛላቹ አሜን🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለ ወላዲቱ ድንግል ወለ ክብር መሰቀሉ ይቆየን አሜን
Audio
ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወረቅ እንዳሰተማረው

የህጻናት ልጆች አስተዳደግ


ልጆች ወላጆች ያተርፋባቸው ዘንድ የተሰጡ መክሊቶቾ⤴️
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ክርስቲናያን መንፈሳዊ ትምህርቶች እና ጽሁፎች ቻናል⛪️
Photo
#ይህን ያለው ሻለቃ ኃይለ ገብረ ሥላሴ አይደለም ። እንዲ ያለው የደማስቆው ሯጭ ቅዱስ ጳውሎስ ነው ። “በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።” #1ኛ ቆሮ 9፥24 ክርስቲያኖች የዚህች ዓለም ዙር እስኪያልቅ ድረስ በትጋት እና በውድድር መንፈስ መሮጥ አለባቸው ። ያሸነፉ ሁሉ እንጂ የሮጡ ሁሉ ጥሩ ዋጋን አይሸለሙም። “ እላችኋለሁና ጽድቃችሁ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን ጽድቅ ካልበለጠ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም።” #ማቴ 5፥20 በእርግጥ የኑሮ ሩጫ ለየ ቅል ነው እግዚአብሔር ወንዱን ከሴቱ ሕጻኑን ከአዋቂው ደምሮ በአንድ መስፈርት አያወዳድርም ለሁሉም እንደስራው መደብ በጽድቅ ይፈርድለታል እንጂ። ጻድቁ ወደፊት ይጽደቅ ቅዱሱም ወደፊት ይቀደስ ጠማማውም ወደ ፊት ይጥመም "እነሆ በቶሎ እመጣለሁ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍለው ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ዘንድ አለ እንዳለ ራእይ .ዮሐ22÷12

#ቅዱስ_ጳውሎስ ምርጥ ዕቃዬ ከመባሉ በፊት ሳዉል ይባል ነበር። ሁል ጊዜ ለኦሪት ሕግ የሚቀና ስለነበር ክርስቶስን እንከተላለን የሚሉ ክርስቲያኖች ሲመጡ ከኦሪቷ ሕግ ያፈነገጡ ስለመሰለው እነርሱን ያጠፉ ዘንድ ሌሊትና ቀን ሳይታክት ተሯሩጧል ። #ሐዋ 8፥3

ክርስቲያኖችን ለማሰር ብዙ ጊዜ ሮጧል፤ ክርስቲያኖችን ለማስደብደብ ብዙ ጊዜ ጥሯል፤ ክርስቲያኖችን ለማሳደድ ብዙ ጊዜ ሽምጥ ጋልቧል፤ክርስቲያኖችም በድንጋይ ተወግረው ሲሞቱ የገዳዮችን ልብሶች በደስታ ጠብቆል። ሳውል በዚህ ነገር ሁሉ ሮጧል ግን በምድርም ሆነ በሰማይ ኒሻን የሚሸልመው አልነበረም።

#በመጨረሻ ግን ክርስቲያኖችን ጨርሶ ይፈጅ ዘንድም የፍቃድ ደብዳቤ ሊያጽፍ ወደ ደማስቆ ሽምጥ ጋለበ በአጥፊነት መንፈስም ሮጠ #ሐዋ 9÷15

ወደ ከተማዋ ሲገባ ግን በታላቅ ብርሃን ተመታ ከፈረሱም ወድቆ ከብርሃኑ ጸዳል የተነሳ ዐይኑ ታውሮ ማየት ተሳነው ወዲያውም ሳውል ሳውል ስለምን ታሳድደኛለህ የሚል ቃል ሰማ።

#የማሳድድህ_አንተ ማነህ ? ብሎ ጠየቀ የምታሳድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ የመውጊያውን ብረት ብትረግጥ ላንተ ይብስብሃል አለው ሳውልም ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ አለው ወደ ደማስቆም ግባ ሐናንያ የሚባል የእግዚአብሔር ሰው ታገኛለህ እርሱ ይፈውስሃል አለው ።

ሳዉልም ከምድር ተነሳ ዐይኖቹም እንደታወሩ ነበሩ እየመሩም ወደ ከተማዋ አገቡት ለሐናንያም የጠርሴስ ሰው ሳውል ወደ እርሱ እንደሚመጣ በራዕይ ተነገረው ።

#ሐናንያ_ግን ስለ ሳውል ክፋት ብዙ ይሰማ ነበርና እንዴት እፈውሰው ዘንድ ይገባልን አለው ። ጌታም ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእስራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና አለው። #ሐዋ 9÷ 13-15

#እግዚአብሔር እንዲህ ነው እያሳደድከውም ይወድሃል እየገደልከው ያኖርሃል እያሰርከው ይፈታሃል እየሸሸህው በፍቅር ይከተልሃል ሰዎች እንደ ሸክም ሲቆጥሩህ ሁሉን ቻይ ትከሻህ ያለው ይሆናል ብሎ ይመሰክርልሃል ሰው ኃጢያተኛ እያለህ እርሱ ግን ምርጤ ይልሃል። #እግዚአብሔር እንዲህ ነው!
ሐናንያም ሄዶ ወደ ቤቱ ገባ፥ እጁንም ጭኖበት፦ ወንድሜ ሳውል ሆይ፥ ታይ ዘንድና መንፈስ ቅዱስ ይሞላብህ ዘንድ ላከኝ አለ። #ወዲያውም_እንደ_ቅርፊት_ያለ ከዓይኑ ወደቀ፥ ያን ጊዜም ደግሞ አየ፤ ተነሥቶም ተጠመቀ፥ በክፉት መንገድ ሮጦ ያተረፈው እውርነትን ተረዳ አሁን ግን በጽድቁም መንገድ መሮጥን መረጠ።“
#እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በመንገድ ላይ ቁሙ #ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ እነርሱ ግን ” ያለ ዐይን መመልከት፣ መሄድ እንዲሁም መሮጥ አይቻልም።
በሥጋ ለመሮጥ ዓይነ ሥጋ በመንፈሳዊ ሕይወት ለመሮጥ ዐይነ ልቡና ሊኖረን ይገባል ያለ ዐይን እንኳን መሮጥ በደህንነትና በምቶት መራመድ አይቻልም። ዐይን ለሰውነት ሁሉ ወሳኝ አካል ናት በእርግጥ ዐይን አይሮጥም የሚሮጠው እግር ነው ሆኖም መነሻውን መገስገሻውንና መዳረሻውን ዐይን ካላመለከተችሁ እግር ወስዶ ወስዶ ገደል ይከታል ። “ዕውርም ዕውርን ቢመራው ሁለቱም ወደ ጉድጓድ ይወድቃሉ አለ።” #ማቴ 15፥14
ስለሆነም በእግረ ሥጋ ለመሮጥ ዐይነ ሥጋ በእግረ ልቡና ለመሮጥ ዐይነ ልቡና የግድ ያስፈልገናል። #ታገኙ_ዘንድ_ሩጡ " ብሎ ስለ መንፈሳዊ ሩጫ የመከረን ቅዱስ ጳውሎስ ከሥጋው ዐይንና ከልቦናው ዐይን ላይ ጋርዶት የነበረው ቅርፊት ከወደቀለት በኋላ ነው።
#አሁን የሚያሯሩጠው ሳውል ተብሎ አይጠራም ፤ አሁን የሚያሳድደው ሳውል መባሉ ቀርቷል፤አሁን ደብዳቢ መሆኑ አብቅቷል። አሁን ስለ ስሙ ከቦታ ቦታ የሚሯሯጥ ምርጥ ዕቃ ጳውሎስ ሆኗልና አሁን ስለስሙ ከሀገር ወደ ሀገር የሚንከራተት ስደተኛው ሆኗልና ። 2ቆሮ 11÷23-27
ዋጋ ለማግኘት መሮጥ እንዳናይ የጋረደንን ግርዶሽ ከመጣል ይጀምራል ። ከሳውል ዐይን ቅርፊት መሳይ ነገር ወደቀ ሲል ከአስተሳሰቡና ከልቦናውም ዐይን ጭምር ቅርፊቱ እንደወደቀለት ማስተዋል ያስፈልጋል። ክርስቶስን ወዶ እናቱን ማሳደድ ክርስቶስን ወዶ ክርስቲያኖችን መጥላት ይህ የልቡና ግርዶሽ ፣ ይህ የልቡና ሽፋን፣ ይህ የዕሊና ቅርፊትም ነውና። #እግዚአብሔር እንደ ሳውል ነቅሎ ይጣልላቸው አጥርተው ያዮ ዘንድም የተንሸዋረረ ዐይነ ልቦናቸውን ሐናንያ በመሰሉ የቅዱሳኑ ጸሎትና ምልጃ ያብራላቸው።

#ሃይማኖት የሌላችሁ ወደ ሃይማኖት ሩጡ
#ሃይማኖት ያላችሁ ወደ ምግባር ገስግሱ
#ምግባር ያላችሁ ወደ ትሩፉት ፍጠኑ ወደ ገነት በር ትደርሳላችሁ ተከፍቶም ታገኙታላችሁ ከየት ናችሁ የሚላችሁም አይኖርም። ያን ጊዜ የደማስቆውን ሯጭ ታኙታላችሁ አብራችሁትም “ መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤” ትላላችሁ ። #2ኛ ጢሞ 4፥7


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፳፮/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
Audio
ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወረቅ እንዳሰተማረው

የህጻናት ልጆች አስተዳደግ


ልጆች ወላጆች ያተርፋባቸው ዘንድ የተሰጡ መክሊቶቾ⤴️
Audio
ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወረቅ እንዳሰተማረው

የህጻናት ልጆች አስተዳደግ


ልጆች ልናወርሳቸው ሰለ ሚገባ ሀብት ⤴️
2024/10/02 22:37:31
Back to Top
HTML Embed Code: