Telegram Web Link
🎤ሱባኤ-ማለት-ምን-ማለት-ነው ?

🌿 ሱባኤ ቃሉ የግዕዝ ቃለ ሲሆን ትርጉሙ ሰባት 7 ማለት ነው። ሱባኤ ፍጹም ዕለታትንና ቦታን ወስኖ ለተወሰኑ ቀናት መቆየት ማለት ነው። አንድ ሱባኤ 7 ሁሉት ሱባኤ 14 እያለ ይቀጥላል።
🌿🎤 የሱባኤ ጥቅሞች
1️⃣ለመለመን
ስንለምን ግን ይሚጠቅመንን ለይተን መሆን አለበት።
አንዳንድ ጊዜ ለመናችንን አናወቅም የዘብዴዎስ ልጆች
ያዕቆብና ዮሐንስ የለመኑት አለ ማር 10 ጌታም ምን ልፈጽምላችሁ
ትወዳላችሁ አላቸው እነሱም አምላክን ምድራዊ ንጉስ አደረጉትና
በዘፋንህ ግራና ቀኝ አድርገን
አሉት!እርሱም የምትለምኑትን አታወቁም አላቸው።
የምንለምነው ብዙ ነው እግዚአብሔር የሚመልስልን ግን የሚጠቅመንን ነው።
ሱባኤ ስንገባ የገባንበት አላማ ካለን በሱባኤው መጨረሻ መልስ እናገኛለን።
2️⃣ከእግዚአብሔር ጋር ለመነጋገር ነው።
ሙሴ አርባ ቀንና አርባ ለሊት ከፆመና ከፀለየ በኋላ ከአምላኩ
ጋር ተነጋግሯል ።
3️⃣ከቅዱሳን በረከትን ለመሳተፍ
የእመቤታችን ፆም ሱባኤ ስንገባ ከእመቤታችን በረከትን ለማግኘት
4️⃣ምስጢር እንዲ ገለጽልን
ብዙ ጊዜ ለሰው የማንናገረው ድፍን ያለ ነገር ይገጥመናል
በዚህን ጊዜ ሱባዔ እኔገባለን።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በ3️⃣ኛው ነው
ለቅዱስ ገብርኤል መልስ የመለሰችለት።እመቤታችን ውሃውን
አስቀምጣ ወደ ቤተመቅደስ ነው የገባችው ዘግታ ሱባኤዋን
ጀመረች።ቅዱስ ገብርኤል እዛም አልቀረም እቤተመቅደስ ገባ
አናገረችውም
ሐዋርያትም የእመቤታችንን እርገት ለማየት ነው 1️⃣6️⃣ ቀን
ሱባኤ የገቡት እሱም ድጋሚ ገለጸላቸው
እኔ ዳንኤል ሶስት ሳምንት እንጀራ አልበላሁም ማለፊያ ውሃም
አልጠጣሁም ።ዳን 1️⃣0️⃣÷2️⃣
5️⃣መንፈሳዊ ስራን ለመስራት
ክህነት ምልኩስና ጋብቻ ወዘት የመሳሰሉትን ለመፈጸም
ሱባኤ ያስፈልጋል ።ሐዋርያት ዓለምን ዞረው ለማስተማር
ሱባኤ ገብተዋል።
🌿የሱባኤ አይነቶች
የሱባኤ አይነቶች ሦስት ናቸው።
1️⃣የግሌ ሱባኤ
2️⃣የማህበር ሱባኤ
3️⃣የአዋጅ ሱባኤ
4️⃣የግሉ ሱባኤ በሁለት ይከፈሊል።
1ዝግ ሱባኤ
2የንስሀ ሱባኤ
ንስሀ ከገባን በኋላ ንስሀ አባቴ ቀጣኝ እንላለን
ንስሀ ቅጣት ሳይሆን ህክምና መዳህኒት ነው።
እነዚህን ሁሉት ሱባኤዎችን ስንፈጽም የክህነት አባቶች ያስፈልጋሉ።
የማህበር ሱባኤ
በማህበር ስለማህበር ስለ ሀገር የሚጸለይበት ሱባኤ ነው
የአዋጅ ሱባኤ
ማንም በሀገር ደረጃ አያውጀውም በሲኖዶስ የሚታወጅ ነው።
🌿የሱባኤ ቅድመ ዝግጅቶች
1️⃣መጠናቀቅ በመጀመሪያ አንድ ሰው ሱባኤ ከመጀመሩ
በፊት መጠናቀቅ አለበት።
በቅዴሴ ሰዓት ስልክ ይዘን እየረበሽን እግዚአብሔር
ከእኛ ጋር በሚነጋገርበት ጊዜ እኛ ለብቻችን እናወራለን
ይሄ ተገቢ አይደለም።
ቅዳሴ ከሁሉ በላይ የከበረ ነው ከቅዳሴ በላይ ምን አለ?
የክርስቶስ ስጋና ደም የሚፈተትበት መልአክት እንደ ሽ የሚነጠፍበት።
2️⃣ምክረ ካህን ከአባቶቻችን ምክር ማግኘት አለብን
ከሱባኤ በፊት
ስትጸልዩ እንደ ግብዞች አትሁኑ ማቴ 6÷5
3️⃣የሚፈለገውን ነገር መሟላት
4️⃣አቅምን ማወቅ ይህ በጣም ከባድ ነው የለ አቅም
ብንጀምረው አንፈጽመውም።
ፆመን ፆመን ሲያቅተን እግዚአብሔርን እናማርራለን ይሄ ተገባ አይደለም ።
5️⃣ቦታ መምረጥ ቦታ መምረጥ ማለት ለፈተና የማያጋልጡ መሆን አለበት።
በሱባኤ ወቅት የምንጠብቃቸው ስርዓቶች
1አንደበትን መጠበቅ
አንደበት እሳት ነው ከአንድ ምላስ መርገምና ምርቃት
ይወጣሉ ያዕቆ 3:6-10
ለአፌ ጠባቂን አኑር "መዝ 14:3"
2በሱባኤ ወቅት አብዝቶ መጸለይ
በፊት ከምናደርገው ጸሎት የበለጠ መፀለይ አለብን።
3በመጠን መመገብ
በሱባኤ ወቅት አብዝተን ከመመመገብ መቆጠብ አለብን።
4በሱባኤ ወቅት አብዝተን መማር አለብን።
ዝግ ሱባኤ ካልሆነ ደጋግመን መማር አለብን፤
5በሱባኤ ወቅት አለባበስን ማስተካከል
ማቅ ባንለብስ አመድ ባንነሰንስም ቢቻለን ገላን የሚያሳዩ ልብሶችን
መልበስ የለብንም ያለበለዛ ሱባዔው ከንቱ ነው።
በሱባኤያችን ምንም አናገኝም።

ወስብሐት ለ እግዚብሔር
ወለወላዲቱ_ድንግል
#ወለመስቀሉ_ክብር_አሜን
Facebook 304267218643491
ቪዲዮ ካልከፈተላችሁ ይህን ተጠቀሙ

✞እንኳን አደረሰን !

"በመከራው ከመሰልነው፤ በክብሩም እንመስለዋለን!"

☞በዓለ ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት፤ (ልደቱ ወቅዳሴ ቤቱ)
ወበዓለ ቅዱሳን፦
•ሄኖክ ነቢይ
•ቴክላ ሐዋርያዊት
•አበከረዙን ሰማዕት
•ዱማድዮስ ሶርያዊ
•ሕጻን ሞዐ ዘደብረ ሊባኖስ
•ይስሐቅ ሰማዕት
•እንዲኒና ዘባና
•ኢላርያ ዘድምድል
•ቴክላ ወሙጊ ዘቀራቁስ
•ታቦት ወኖኅ ዘሮሜ
*ለነፍሴ ነፍሷ ነሽ*

ለነፍሴ ነፍሷ ነሽ ለመንገዴ ፋና
እንዳልጠፋ አምናለው ያንቺ ልጅ ነኝና/2/
አዝ..........
የጻድቃን እናቶች እጅብ ብዙ ናቸው
ከብሉይ ከሃዲስ ብንዘረዝራቸው
አንቺ ግን አንዲት ነሽ የለሽም ጭማሬ
ትኖሪያለሽ እንጂ ትውልድ ስታስምሪ
አዝ..........
ያንቺን ስም ተማጽኖ ያንቺን ስም ቀድሶ
አንቺን አመስግኖ አንቺን አወድሶ
የተጠቀመ እንጂ በረከት አግኝቶ
አልታየም እስከ አሁን የተጎዳ ከቶ
አዝ..........
ጎርጎርዮስና ሊቁ ዮሐንስ
አትናቴዮስ እና ሊቁ ባስልዮስ
አባ ኤፍሬም እና አባ ጊዮርጊስ
ተጠቅመዋል ባንቺ በስጋም በነፍስ
አዝ..........
አባትህን ጠይቅ ስለሚለን ቃሉ
ብንጠይቃቸው ቅዱሳኑን ሁሉ
ስላንቺ ነገሩን ክብር ተዓምራትሽን
ለሰው ዘር በሙሉ አማላጅ መሆንሽን
አዝ..........
ገብርኤል ከሰማይ ኤልሳቤጥ ከምድር
በአንድ መሰከሩ ስለ ድንግል ክብር
ሰዓኒ ለነ ብሎ ተማጽኖ በአንቺ ስም
የተጠቀመ እንጂ የተጎዳ የለም

ለነፍሴ ነፍሷ ነሽ ለመንገዴ ፋና እንዳልጠፋ አምናለው ያንቺ ልጅ ነኝና/2/
2024/09/29 21:27:39
Back to Top
HTML Embed Code: