Telegram Web Link
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል
ዲያቆን ተስፋዬ ቻይ
ኅዳር 12 ቀን ፳፻፲፭ ዓመተ ምሕረት
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? እየበረታችሁ ነውን? የሩብ ዓመት የምዘና ፈተናስ እንዴት ነው? መቼም ትምህርቱን በትኩረት ከተከታተላችሁ የምዘና ጥያቄዎችን እንደምትሠሩት ጥርጥር የለውም! በተለይ ልጆች መምህራን የሚነግሯችሁን በትኩረት በማዳመጥ፣ መጻሕፍትን በማንበብና ያልገባችሁን በመጠየቅ ጥሩ ውጤት ማስመዝገብ አለባችሁ፡፡ መልካም! ውድ የእግአብሔር ልጆች ለዛሬ ምንማረው ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት መካከል አንዱ ስለሆነው ስለ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! አምላካችን እግዚአብሔር በዕለተ እሑድ ቅዱሳን መላእክትን ፈጥሯቸዋል፤ እነርሱም እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑና እኛንም የሚጠብቁ ናቸው፤ ነቢዩ ንጉሥ ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹የእግዚአብሔር መላእክት በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራሉ፤ ያድናቸውማል››  በማለት እንደ ገለጸልን  ቅዱሳን መላእክት እኛን ከክፉ ነገር ይጠብቁናል፡፡ (መዝ.፴፬፥፯)
ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ታዲያ እኛ የእነርሱን ጥበቃና ርዳታ ስንፈልግ እግዚአብሔርን  እንድንፈጽመው ያዘዘንን ትእዛዝ ስንፈጽምና  ጥሩ ሥነ ምግባራት ሲኖረን ነው፡፡ ልጆች! መላእክት በተፈጥሮ ብዙ ቢሆኑም የመላእክት አለቃ የሚባሉ ግን ሰባት ናቸው፤ ከእነዚህም የመላእክት ሁሉ አለቃ አንዱ ቅዱስ ሚካኤል ነው፤ ሚካኤል ማለት ‹‹ማን እንደ እግዚአብሔር›› ማለት ሲሆን ከእግዚአብሔር ተልኮ ሰዎችን በችግራቸው የሚረዳና ፈጣሪውንም የሚያመሰግን መልአክ ነው፡፡
ውድ የእግአብሔር ልጆች ! ቅዱስ ሚካኤል በመጽሐፍ ቅዱስ እንዲሁም በድርሳነ ቅዱስ ሚካኤል እንደተጻፈልን ለችግራቸው ደርሶ የልባቸውን የፈጸመላቸው፣ ከመከራ ያዳናቸው፣ ከሰይጣን ተንኮል የታደጋቸው ብዙ ሰዎች ናቸው፡፡ ሁል ጊዜ በየወሩ በ፲፪ (ዐሥራ ሁለት) ቀን መታሰቢያ በዓሉን እንዘክራለን፤ በዓመት ውስጥ ኅዳርና ሰኔ ወር ላይ ደግሞ ዓመታዊ ክብረ በዓሉ ይዘከራል፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ታሪኩ ብዙ ቢሆንም በኅዳር ፲፪ ቀን የሚከበርበትን በመጠኑ እንነገራችኋለንና አጽንዖት (ትኩረት) ሰጥታችሁ ተከታተሉን፡፡ መልካም! ኅዳር ፲፪ ቀን ቅዱስ ሚካኤል የመላእክት ሁሉ አለቃ አድርጎ እግዚአብሔር የሾመበት ቀን ነው፤ ሌላው ደግሞ ልጆች እስራኤላውያንን ከፈርኦን ሠራዊት የታደገበት በዓል ነው፤ እስራኤላውያን ከግብጽ አገር በስደት (በመከራ) ከነበሩበት እግዚአብሔር ሲያወጣቸው ሊቀ ነቢያት ሙሴን መርጦት ሕዝቡን እየመራ ከግብጽ ወደ ከነዓን ወደ ተባለች አገራቸው ይመራቸው ጀመር፡፡ ይገርማችኋል ልጆች! ፈርዖን የተባለው የግብጽ ንጉሥ ሕዝቡን ሊይዛቸው ብዙ ሠራዊት (ወታደር) አስከትሎ ከኋላቸው ሲከተላቸው እስራኤላውያን ለማምለጥ ወደ ፊት ሲሄዱ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ከፊታቸው እየመራ መልካሙን መንገድ ያሳያቸው ነበር፡፡ እንደገናም መንገዱ በረሃ ነበርና ፀሐይ እንዳይነካቸው በደመና እየጋረደ ማታ ደግሞ ሲሆን እንዲታያቸው ብርሃን (ፋና) እያበራላቸው ይጓዙ ነበር፡፡
አያችሁ ልጆች! ለዚህ እኮ ነው ነቢዩ ዳዊት ‹‹ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና››  ያለው መልካም ከሆንንና የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ከጠበቅን ክፉ ነገር እንዳይነካንና መንገዳችን እንዲቀና እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክቱን ይልክልናል፡፡ (መዝ.፺፥፲፩) ታዲያ አንድ ጊዜ እስራኤላውያንን ያሳድድ የነበረው ፈርኦን ከኋላ ሲከተላቸው እነርሱም ወደ ፊት ሲሄዱ በጣም ትልቅ ባሕር አጋጠመቸው፡፡ ልጆች! ሕዝቡ ከኋላቸው ፈርኦን ነበር፤ ከፊታቸው ደግሞ ትልቅ ባሕር ነበር፡፡ የዚህን ጊዜ በጣም ተጨነቁ፤ ፈሩም፤ ወዴት እንደሚሄዱ አማራጭ አጡ፡፡
ከዚያም ይመራቸው የነበረው ሊቀ ነቢያት ሙሴ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ እግዚአብሔርም እንዲረዳቸው ቅዱስ ሚካኤልን ላከላቸው፡፡ ከዚያም ነቢዩ ሙሴ በበትሩ ባሕሩን ሲነካው ያ ትልቁ ባሕር ሁለት ቦታ ክፍል አለ፡፡ ይገርማችኋል ልጆች! ውኃው እንደ ግድግዳ ቀጥ ብሎ ቆመ፤ ከዚያም ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው ለሁለት በተከፈለው ባሕር መካከል ሕዝቡ ተሻገሩ፡፡
ልጆች! እግዚአብሔር ሁሉን ማድረግ የሚቻለው አምላካችንና ፈጣሪያችን ነው፡፡ ባሕሩን በቅዱስ ሚካኤል አማካኝነት ደረቅ አደረገላቸውና በውስጡ አልፈው ሄዱ፤ ይገርማችኋል! ያሳድዳቸው የነበረው ፈርኦን ተከትላቸው፤ ለሁለት ተከፍሎ እንደግድግዳ (ግንብ) በቆመው ባሕር ውስጥ ሠራዊቱን (ወታደሩን) አስከትሎ  ገባ፡፡ ከዚያም ሕዝቡ ሁሉ ባሕሩን አቋርጠው እንደጨረሱ የፈርኦን ሠራዊቶች ከመካከል ሲገቡ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ባሕሩን በበትሩ ነካው፤ በዚያን ጊዜ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ያንን ባሕር ወደ ቦታው እንዲመለስ ሲያደርገው እንደ ግንብ የነበረው ውኃ ፈሰሰ፤ ከዚያም ፈርኦንና ሠራዊቱ በባሕር ውስጥ ሰጠሙ፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! በመጀመሪያ እግዚአብሔር ፈርኦንን ሊያስተምረው ብዙ ተአምራትን እያደረገ አሳይቶት ነበር፡፡ ፈርኦን ግን ሳያምን ስለቀረና በትእቢቱ የተነሣ እምቢ በማለቱ በመጨረሻም በኤርትራ ባሕር ሰጠመ፡፡ ሕዝቡም ጠላቶቻቸውን ለቀጣላቸውና እነርሱንም ከመከራ ላዳናቸው አግዚአብሔር ‹‹እግዚአብሔርን እናመስግነው፤ምስጉን ነው የተመሰገነ…›› እያሉ ዘመሩ፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እግዚአብሔርን የታመነ መከራ ቢገጥመውም ቅዱሳን መላእክቱን ልኮ ያድነዋል፤ እስራኤላውያን በእግዚአብሔር ታምነው ስለነበር በችግራቸው ጊዜ ቅዱስ ሚካኤልን ላከላቸው፡፡ መልአኩ በመንገዳቸው እየመራና የሚያስፈለጋቸውን እያደረገ ጠላቶቻቸውን በመቅጣት ጭንቀታቸውን አራቀላቸው፤ ከመከራ ታደጋቸው፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ከእስራኤላውያን ታሪክ ምን እንማራለን እግዚአብሔርን የሚያምን በመከራው ጊዜ ቅዱሳን መላእክት እንደሚላኩላት፣ ሕጉንና ትእዛዙን ማክበር እንዳለብን፣ ቅዱሳን መላእክትን በችግራችን ጊዜ ስንጠራቸው ፈጥነው እንደሚያድኑን ተምረናል፡፡ ሌላው ደግሞ ልጆች! የሚነገረውን የማይሰማና ከጥፋቱ የማይመለስ መጨረሻው መጥፋ እንደሆነ አይተናል፡፡  ፈርኦን የተባለው ጨካኝ ንጉሥ የእግዚአብሔርን ልጆች መከራ ሲያሳያቸው እግዚአብሔር ተአምራት አድርጎ ከጥፋቱ እንዲመለስ ነገረው፤ እርሱ ግን አልመለስም አለ፤ በመጨረሻም በባሕር ውስጥ ሰጠመ፡፡
ልጆች! አመጸኛና ተው የሚሉትን የማይሰማ መጨረሻው ጥፋት ነው፡፡ ታላላቆቻችንን የሚነግሩንን መስማትና ከጥፋት እንድንመለስ ሲመክሩን መመለስ አለብን፡፡ ፈርኦን ተው ሲባል እምቢ አለ፤ ግን በመጨረሻ ተቀጣ።
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት መካከል አንዱ ስለ ሆነው ስለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ካደረጋቸው ብዙ ድንቅ ተአምራቶቹ በኅዳር ፲፪ ቀን የሚታሰበውን ብቻ በጥቂቱ ነግረናችኋል፡፡ በቀጣይ ደግሞ የሌሎቹን ሊቃነ መላእክት ታሪክ እንነግራችኋለን፤ ይቆየን! ደኅና ሁኑ ልጆች!
ስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን!!!
Audio
መሠረተ እምነት  በአንዲት ሀይማኖት

ምስጢረ ሜሮን ለምን ከጥምቀት ቀጥሎ እንዲፈጸም ይደረጋል

ሜሮን አቀባብ እንዴት ነው

ኃጢአት ለንስሐ አባት መናዘዝ ለምን አሰፈለገ

አዘጋጅና አሳታሚ :-ኢንጂነር ወንዴ ጫኔ
Audio
መሠረተ እምነት  በአንዲት ሀይማኖት

ከንስሐ በፊት

በንስሐ ጊዜ

አዘጋጅና አሳታሚ :-ኢንጂነር ወንዴ ጫኔ
Audio
"" የሰማይ ወፎችን ተመልከቱ ""

(ማቴ. ፮:፳፮)

በመምህርዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ

(ኅዳር 14 - 2015)
Audio
ወፍም ቤትን አገኘች
                   
  በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
Audio
መሠረተ እምነት  በአንዲት ሀይማኖት

ከንስሐ በሃላ



አዘጋጅና አሳታሚ :-ኢንጂነር ወንዴ ጫኔ
Audio
መሠረተ እምነት  በአንዲት ሀይማኖት


ክህነት ምንድነው


የምሥጢር ክህነት አመሠራረ ኪዳን

የምስጢር ክህነት አመሠራረት በሐዲስ ኪዳን

አዘጋጅና አሳታሚ :-ኢንጂነር ወንዴ ጫኔ
Audio
መሠረተ እምነት  በአንዲት ሀይማኖት


የክህነት ዓላማና ጥቅም ምንድነው

ሥልጣና ክህነት ለማን ይስጣል

አዘጋጅና አሳታሚ :-ኢንጂነር ወንዴ ጫኔ
Audio
መሠረተ እምነት  በአንዲት ሀይማኖት

ስርዓት ተክሊል ምንድነው

ጋቢቻ መቼ እና ማን መሰረተው

አዘጋጅና አሳታሚ :-ኢንጂነር ወንዴ ጫኔ
Audio
መሠረተ እምነት  በአንዲት ሀይማኖት

ጋቢቻ ቅድም

ጋቢቻ በሃላ

አዘጋጅና አሳታሚ :-ኢንጂነር ወንዴ ጫኔ
Audio
መሠረተ እምነት  በአንዲት ሀይማኖት

ፋቺ የሚፈቅድባቸው ምክንያቶችስ

ምሥጢረ ቀንዲል

አዘጋጅና አሳታሚ :-ኢንጂነር ወንዴ ጫኔ
ከወደቁ አይቀር .....#ለጽዮን
____

አንዳንድ ውድቀቶች ካለ አስፍላጊ አቋቋሞች በእጅጉ የተሻሉ ናቸው ። ለምሳሌ ከሐውልቱ እንደምናየው ለጽዮን መውደቅ በእውነቱ ዋጋ ያለውና የተሻለ አወዳደቅ ነው::

#ይህ በመጠኑና በውበቱ ከፍ ያለው ሃውልት አሁን ሳይወድቅ ቆሞ ካለውና በቅርቡ ከሮም ከመጣው ዕድሜ ይሁን በሰው ሀገር ያለ ቦታው መቆሙ የሞራል መላሸቅ ያስከተለበት የሚመስለሁ እንደ አዛውንት ጎብጦ በመደገፊያ በግድ ከቆመው ሐውልት በተለየ መልኩ በፊት ለፊቱ ወድቆ ይታያል::

ይህ የአክሱም ሐውልት ከመሐመድ ግራኝ ወራራ በኋላ የተነሳችው ሴቷ ግራኝ ዮዲት ጉዲት ካስከተለችው ጥፋቶች መካከል የጥፉቷን ግንባር ቀደም ገፈት ቀማሽ የሆነ ታሪካዊ የሀገር ቅርስ ነው :: ዮዲት በክርስቲያንኖችና በቤተክርስቲያን ላይ ባደረባት የተሳሳት ጥላቻ ኃያሌ የጭካኔ ተግባራትን በክርስቲያኖችና በቤተክርስቲያን ላይ ያስከተለች የታሪክ ጠባሳ ነች ::

#ከበዙ ጥፉቶች በኃላ ወደ እዚህ ወደ አክሱም ሐውልት መቆሚያ አካባቢ ስትደርስም ጭፍሮቿ እንደለመዱት የእክሱምን ሐውልቶች ይጥሏቸውና ይሰባብሯቸው ዘንድ ተራኮቱ ዮዲትም ሁሉንም ሐውልቶች አትጣሏቸው አንዱንና ትልቁን ለዐይንም የሚማርከውን ሐውልት ብቻ ጣሉት ሌሎቹን ግን እንዳትነኩ ስትል ትዕዛዝ አስተላለፈች ጭፍሮቿም ለምን? ሲሉ ጠየቁ


በሌሎች ቦታዎች እዳደረግን ሁሉንም ብንሰባብርና ብናወድማቸው መጪው ትውልድ ሲያቸው አንድ ጊዜ ተበሳጭቶ ብስጭቱን ይተወዋል የሚያምረውን ና ተለቅ የሚለውን ሃውልት ብቻ ብንጥለውና ሌላው ብንተውለት ግን ባየውና በሰማው ቁጥር ይህ ትልቁኮ ባይወድቅ ከነዚኞቹ በላይ ውብ የሀገር ቅርስ ሆኖ ይታይ ነበር እያለ ዘላለም ዓለሙን እየተቃጠለ ሲብሰለሰል ይኖራል ገባችሁ ስትልም አምቧረቀችባቸው::


#ሐውልቱ ግን ለትውልዱ ቁጭት ሳይሆን ትምህር ይሆን ዘንድ ወደ ጽዮን ወደቀ ተንበርከኮም ሰገደላት ። የጌታዬ እናት በፊትሽ እቆም ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል? እያለም ተሳለማት ሉቃ1÷43። ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ ልብ ያለውም ልብ ያድርግ "በፈሊጥ ካልገባው በፍልጥ " እንዲሉ ። ሰው ሁለት ጊዜ ይማራል ይላሉ ሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን አንድ በሣር " ሀ " ብሎ ካልሆነም በአሳር " ዋ "ብሎ ። ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ብራና ዳምጠው ቀለም በጥብጠው በሣር ስግደት እንደሚገባት ሲያስተምሩን ካልገባን በአሳር ጎንበስ ማለታችን አይቀርምና ከአሳሩ በፊት በሳሩ ተማሩ እንላለን።

#የአስጨናቂዎችሽም_ልጆች_አንገታቸውን_ደፍተው_ወደ_አንቺ_ይመጣሉ ፥ የናቁሽም ሁሉ #ወደ_እግርሽ_ጫማ ይሰግዳሉ፤ #የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል #ቅዱስ_የሆንሽ_ጽዮን ይሉሻል።”
#ኢሳ 60፥14


አ.አ ኢትዮጵያ
ተርቢኖስ ዘተክለ ኤል
እርሱ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲገለጥና እርሱ እንዳይታይ ተናግሮ ነበር ከዚሆ በተጨማሪም እንዲህ በማለት ተናግሯል ሙሽራይቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው ቆሞ የማሰማው ሚዜው ግን በሙሽራው ድምፅ እጅግ ደስ ይለዋል እንግዲህ ይህ ደስታዬ ተፈጸመ እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያሰፈልጋል ዮሐንስ 3÷29-30

አቡነ ሺኖዳ ሣልሣዊ እንደ ተረጎሞት
ተክለሐይማኖት ባህታዊ

ተክለ ሐይማኖት ባህታዊ
ምድራዊ ሲሉህ ሰማያዊ
በአደባባዩ ተተክለሃል
ተክልዬ መልካሙን ፍሬ አፍርተሃል

ቃልኪዳን አለህ የገነነ
ምህረት የሚያሰጥ የታመነ
በስምህ ውሃ አጠጥተን
ዋጋችን በዝቷል አባታችን
      #አዝ
እኛም ሆነናል ልጆችህ
ማርኮ አስቀርቶን ምግባርህ
በምልጃህ ጸሎት ትሩፋት
ቤታችን መላ በረከት
       #አዝ
ምህረት ይዘንማል ከሰማይ
በአንድ እግርህ ቆመህ ስትጸልይ
ብዙ ተጋድለህ አትርፈሀል
ያገለገልከው አክብሮሃል
        #አዝ
ተሰባበሩ ጣዖታቱ
አምነው ሰገዱ መኳንንቱ
የበረታው ቃል ከአፍህ ወጥቶ
የአምላክ አድርጓል ሁሉን ገዝቶ

         ዘማሪት
     ጸዳለ ጎበዜ
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE
#24ቱ_ካህናተ_ሰማይ_25 ሆኑ !
___

አስቀድመው ቅዱሳን ሐዋርያት 12 ብቻ ነበሩ ከመካከላቸውም ይሁዳ ገንዘብ ወዶ ዘመድ ለምዶ አገልግሎቱን ትቶ ሄደ ሐዋርያትም ወንጌል በዓለም ሳይሰበክ ቢቀር አገልግሎታችን ተስተጎግሎ መቅረቱ  አይደለ ብለው እግዚአብሔር ባወቀ ይሁዳ በተዋት አገልግሎት ፈንታ ሌላ ሰው እንዲሿምላቸው በርናባስንና ማትያስን አቀረቡ መንፈስ ቅዱስም ማቲያስን መርጦ ሰጣቸው:: የሚገርመው ነገር የእግዚአብሔር ድንቅ ስጦታ ነው በአንዱ ይሁዳ ፈንታ ሁለት ምትኮችን ሰጣቸው አንዱ ማቲያስ ሲሆን ሌላው እራሱ በቃሉ ሐዲስ ሐዋርያ ብሎ የሾመው ተክለ ሃይማኖት ነው ቅዱስ ጳውሎስን ከአሳዳጅነት ቅዱስ ጴጥሮስን ከዓሳ አጥማጅነት እደጠራቸው  ሐዋርያትን በጠራበት አጠራሩ አባታችን ተክለ ሃይማኖትን እንሰሳ ከሚያድኑበት ("ድ")ጠብቆ ይነበብ) ጫካ ጠርቶ በወንጌል መረብነት ሰው የሚድኑ ("ድ")ላልቶ ይነበብ አዳኝ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጉ  ሾማቸው የሐዋርያት ቁጥረም 12 ቢሆንም  በሐዲሱ ኢትዮጵያዊ ሐዋርያ አማካኝነት  ያለ ወትሮ 13 ሆነ ምነው መጻሕፍት 12ቱ ሐዋርያት አይደል የሚለው ቢሉ መጻሕፍት በቀረበው የመጥራትም ፀባይ አላቸው 12ቱን ሐዋርያት አስሩም አያለ እንደጠራቸው ማለት ነው ስለዚህ 12ሐዋርያት ስላለ 13ተኛ አይጨመርም አያሰኝም

#አባታችን ተክለ ሃይማኖት ቁጥራቸው ከሐዋርያት ወገን ብቻ ሳይሁን ከስማዕታትም ጋር ጭምር ነው ምነው ሰማዕታት ስለ ክርስቶስ ሲሉ ሥጋቸውን የቆረሱ ደማቸውን ለምስክርነት ያፈሰሱ እንደነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ያሉ ሰዎች አይደሉም  እንዴ ቢሉ አባታችን ተክለ ሃይማኖት መከራን አብዝቶ በመቀሎል ከሰማዕቱ በምን ተለዮ?በዳሞቱ ንጉስ እጃቸው በሰይፍ ተቆረጠች እግዚአብሔር እንደ ቀድሞ ጤነኛ አደረገላቸውጉልያድን በሚያካክሉ በሞተሎሚ  በወታደሮች በሽምግልና አቅማቸው ደም በአፍና በአፍንጫቸው እስኪተፉ ተደብድበዋል በንብ ቀፎ ተደርገው ወደ ገደል ተጥለዋል ከዚህ ሁሉ ስቃይና ደም መፍሰስ በኃላ እራሱ አልበቃ ብሏቸው ወደ አደባባይ ወጥቼ ስለ ስምህ መስክሬ እንደሰማዕታት ደሜን አፍስሼ ልሞት እፈልጋለው አሉ:: እግዚአብሔር ግን ከዚህ በላይ ሰማዕትነት አንደሌለ ሲነግረን እኔ ከአንተ ሰውነት በእመምህ ምክንያት የሚወጣውን ፈሳሽ እኔ እንደ ሰማዕታት ደም አቆጥርልሃለው ብሎ ዕረፍታቸውን በሰማዕታት ዕረፍት ቆጠረው ::
    #አንዳንድ ሞኝ ሰዎች ይህን በማንበብ እንዴት የተክለ ሃይማኖት በእመም ከሰውነታቸው የወጣ ፈሳሽ(ተቅማጥ)እንዴት ከሰማዕታት ደም ጋር እኩል ይሆናል? ሲሉ ይሰማሉ ጌታችን መዳኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌሉ" ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል"ሲል ተደምጧል #ማቴ 25 ÷40 ታዲያ ለሰው ማድረግ ለእርሱ እንደማድረግ ተደርጎ ከተቆጠረ ወይም የአባታችን የሰውነት ( ፈሳሽ ተቅማጥ) እንዴት አንደ ሰማዕታት ደም መቆጠሩ ስህተት አይደለም እንደውም ይህ ነገር ስህተት ነው ከማለት ይልቅ የጌታችን ምሳሌ ስህተት ይመስላል ሰው ሲራብ ማብላት ሰው ሲጠማ ማጠጣት ሰው ሲታሰር ሄዶ መጠነቅ የማይራበው እግዚአብሔር ተርቦ እንደ ማብላት የማይጠማውን እግዚአብሔርን ተጠምቶ እንደ ማጠጣት የመይታሰረው እግዚአብሔርን ታስሮ እንደተጠየቀ አድርጉ መቁጠር  አንዴት ይቻላል? ሌላውና ወሳኙ ነጥብ በህመም ከሰውነት የሚወጣ ፈሳሽ(ተቅማጥ) እና ደም  ከሚያስከትሉት ችግር አንጻር ምንም ልዮነት የላቸውም በሳይንሱም ዓለም አገልግሎቱን ያልጨረሰ ፈሳሽ ከሰውነት ከወጣ በቶላ በሌላ ፈሳሽ ምግቦች እንዲተካ ይደረጋል ለምሳሌ" ሀተት "የተሰኘውን የጠቅማጥ በሽታ ብንወስድ ለሁለት ሳምንት እና ከዛ በላይ ለሆኑ ቀኞች  ተተኪ ፈሳሽ ምግብ ሳንወስድ ዝም ብንለው  ወደ ሞት ያደርሰናል ይህ ማለት ደም ሥር ተቆርጦ ብዙ ደም ከፈሰሰ በኃላ ምንም ተተኪ ፈሳሽ ሳይወስዱ እንደመቀመጥ እና እነደሚያስከትለው ችግር ሊቆጠር ይችላል:: ስለዚህ ሰማዕታት ደማቸውን አፈሰሱ ሲባል ለመኖር የሚያስችላቸውን ወሳኝ ነገር(ደም)ከሰውነታቸው ወጣ ማለት ነው አባታችን ተክለ ሃይማኖትም ልክ እንደ ደም ጥቅምነቱን ሳይሰጥ ከሰውነታቸው በመውጣቱ ደሙ ሳይፈስ ቀርቶ ቢሆን ኖሮ ሰማዕታት የክብርን አክሊል ወደ ሚቀዳጅባት ሞት እንደማይቀርቡ ሁሉ አባታችንም ለሞት ባልቀረቡ ነበር::

አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ቁጥራቸው ከሐዋርያት ወይም ከሰማዕታት ወገን ናቸው ተብሎ ብቻ አይታለፍም ከካህናተ ሰማይ ከሡራፌል ጋርም ይመደባሉ ለወትሮ ካህናተ ሰማይ ሡራፌል ቁጥራቸው 24ብቻ ነበሩ ኢትዮጵያዊው አባት ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት የኢትዮጵያ ሲሳይ ሐዲስ ሐዋርያ ሰማእት ወነብይ ወካህን በተወለዱ እና ባደጉ ጊዜ ግን 25ለመሆን ተገደዋል ::ኃዳር 24ቀን 24ቱ ካህናተ ሰማይ ሡራፌል እንደለመዱት ሥሉስ ቅዱስ ብለው መንበሩን አያጠኑ ሳለ ድንገት ቅዱስ ሚካኤል ከሰዎች ወገን የሆነ ሰው ሲሆን እንደ መላእክት  ስድስት የፀጋ ክንፎች የተሰጡት ብርሃን ዘኢትዮጵያ የሆነውን አባታችን ተክለ ሃይማኖትን ይዞ አመጣው  የወርቅ ማዕጥንትም ተሰጠው ከዙፋኑም ወዳጄ ተክለ ሃይማኖት ቁጥርህ ከንግዲህ ወዲህ ከ24ቱ ሰማያተ ካህናት ጋር ይሁን  አለው:: 25ተኛ ካህንም ሆኖ የሥላሴን መንበር ሥሉስ ቅዱስ እያለ በወርቅ ማዕጥንት አጠነ: : ራዕ ዮሐ 4÷4 ገድለተክለ ሃይማኖት
*ይቆየን*
#የባታችን እረድኤትና ምልጃው አይየን ለዘላለሙ አሜን!!!

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
2024/09/30 19:22:48
Back to Top
HTML Embed Code: